en
Feedback
Shien ekawuch

Shien ekawuch

Open in Telegram
869
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1230 days
Posts Archive
#የ2 ልጆቹን "እናት በመጥረቢያ የገደለው ግለሰብ "በዕድሜ ልክ እስራት ተቀጣ!!! @በሌላ ወንድ እጠረጥርሻለሁ በሚል ምክንያት ሚስቱን በመጥረቢያ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ተከሳሽ የእድ
#የ2 ልጆቹን "እናት በመጥረቢያ የገደለው ግለሰብ "በዕድሜ ልክ እስራት ተቀጣ!!! @በሌላ ወንድ እጠረጥርሻለሁ በሚል ምክንያት ሚስቱን በመጥረቢያ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ተከሳሽ የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ውሳኔ ተላልፎበታል፡፡ @ፍቃዱ ሽፈራው የተባለው ተከሳሹ ወንጀሉን የፈፀመው ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዓ/ም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ልዩ ቦታው አርሴማ አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡ @ከሌላ ወንድ ጋር እጠረጥርሻለሁ በሚል ምክንያት ከጠዋቱ 3፡30 ሰአት ገደማ @የ2 ልጆቹ እናት የሆነችውን የትዳር አጋሩን የተለያየ የሰውነት ክፍሏን በመጥረቢያ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል፡፡ @የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተከሳሽ ፍቃዱ ሽፈራው ላይ ከእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ቅጣት በተጨማሪ ከህዝባዊ መብቶቹ ለዘወትር እንዲሻር ውሳኔ አስተላልፎበታል ። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የሽምግልና ሙከራ ያልተሳካለት "የሱዳን ጦርነት "100ኛ ቀኑን መያዙ ተነገረ!!! @ተፋላሚ ወገኖች ሀገሪቱን ወደ ዲሞክራሲ ለማሸጋገር የተያያዘ እቅድ ላይ ተለያይተዋል::ጦርነቱ የቀጠለበት የሱዳን ግጭት 100ኛ ቀኑን እሁድ ሲደፍን፤ በአንዳንድ ክፍሎች ግጭት ተቀስቅሷል። @የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ፤ ከአረብ ሚሊሻ እስከ የጦር ሰራዊቱን የመዋጋት ጉዙ የቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ኃይሎች የሽምግልና ሙከራዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ለመጣው ግጭት መውጫ መንገድ ማግኘት አልቻሉም።ሚያዚያ 15 በሱዳን ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች በስልጣን ሽኩቻ ጦርነቱ ፈንድቷል። @ከ700 ሽህ በላይ ሰዎች ወደ ጎረቤት ሀገሮች መሰደድን ጨምሮ ከሦስት ሚሊዮን በላይ ተፈናቅለዋል። ጤና ጥበቃ ሚንስቴር በጦርነቱ አንድ ሽህ 136 ሰዎች ተገድለዋል ብሏል። ምንም እንኳን ባለስልጣናት ቁጥሩ ከዚህ ከፍ ያለ ነው ብለው ቢያምኑም። @ጦር ሰራዊቱም ሆነ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ድል መቀናጀት ባይችሉም፤ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በዋና ከተማይቱ ካርቱም የበላይ ነው ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። @ጦርነቱ ወደ ምዕራብ በተለይም በግጭት ሲናጥ ዓመታትን ወዳሳለፈው የዳርፉር ክልል በመስፋፋቱ በዋና ከተማው ውስጥ ያሉ መሰረተ ልማቶች እና አስተዳደሮች ፈርሰዋል። @በሳምንቱ መጨረሻ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ከካርቱም በስተደቡብ በሚገኙ አካባቢዎች ተንቀሳቅሷል። በጦር ኃይሉ የአየር ጥቃት እንደተፈጸመባቸው እማኞች ገልጸዋል። @ከሀገሪቱ ትላልቅ ከተሞች አንዷ በሆነችው ኒያላ እና የደቡብ ዳርፉር ዋና ከተማ ከሀሙስ ጀምሮ በመኖሪያ አካባቢዎች ግጭቶች መቀጠላቸውን እማኞች ተናግረዋል። በአካባቢዎቹ ቢያንስ 20 ሰዎች መሞታቸውን የህክምና ምንጮች ገልጸዋል። @ለሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች በተደጋጋሚ የተኩስ አቁም ስምምነት ያስገኙ ንግግሮችን እንደገና ለመጀመር በጂዳ ልዑካን ልከዋል። @በፈረንጆቹ 2019 የቀድሞ ገዥ ኦማር አልበሽር ከስልጣን ከተወገዱ በኋላ፤ የሰራዊቱ መሪዎች እና ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ የጋራ ምክር ቤቱን መርተዋል። ሀገሪቱን ወደ ዲሞክራሲ ለማሸጋገር የተያያዘ እቅድ ላይ ተለያይተዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#የኢቲዮጵያ ጠ/ሚ አብይ አህመድ፦ ከስልጣን ሲወርድ የኢትዮጵያን ሀብት ዘርፎ በሻሻ የሚደበቅ አይነት መሪ አይደለም፤ የሚሰራው ስራ አንገቱን የማያስደፋው በመሆኑ ጎንደር ፣ ደሴ፣ አዳማ፣ ጅማ፣ ድሬዳ
#የኢቲዮጵያ ጠ/ሚ አብይ አህመድ፦ ከስልጣን ሲወርድ የኢትዮጵያን ሀብት ዘርፎ በሻሻ የሚደበቅ አይነት መሪ አይደለም፤ የሚሰራው ስራ አንገቱን የማያስደፋው በመሆኑ ጎንደር ፣ ደሴ፣ አዳማ፣ ጅማ፣ ድሬዳዋ ወይም አርባምንጭ ላይ እጁን በኪሱ ከቶ ወክ እያደረገ ልታገኘው የምትችለው አይነት ዘመናዊ መሪ ነው። @በየጎጣቸው ስር የተወሸቁ ፖለቲከኞች ሊጎትቱት ይሞክራሉ፤ የጀመረው ዘመናዊ ፖለቲካ ግን ጎጠኞችን ራቁት አስቀርቶ የኢትዮጵያን ታሪክ እስከወዲያኛው የሚቀይር ነው"። #ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ እንደተናገሩት *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ብራዚል "በሰማይ ላይ የሚበሩ ታክሲዎችን ልትሰራ መሆኑ ተነገረ!!! @የብራዚሉ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ በሳኦ ፖሎ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የሰማይ ላይ በራሪ ታክሲዎችን ሊሰራ መሆኑ ተገልጿል፡፡እነዚ
+4
#ብራዚል "በሰማይ ላይ የሚበሩ ታክሲዎችን ልትሰራ መሆኑ ተነገረ!!! @የብራዚሉ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ በሳኦ ፖሎ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የሰማይ ላይ በራሪ ታክሲዎችን ሊሰራ መሆኑ ተገልጿል፡፡እነዚህ የሰማይ ላይ ታክሲዎች እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2026 ተግባራዊ እንደሚደረጉ ተመልክቷል፡፡ @ስድስት ሰዎችን የመጫን አቅም የሚኖራቸው በራሪ ታክሲዎቹ ለአንድ ሰው ከ50 እስከ 100 ዶላር የሚያስከፍሉ ይሆናል ተብሏል፡፡ @ለጊዜው ኩባንያው ሶስት ሺ በራሪ ታክሲዎች የሚፈበርክ ሲሆን የመጀመሪያው በራሪ ታክሲ ለሙከራ በዚህ አመት ተገጣጥሞ ለእይታ እንደሚቀርብ ተጠቅሷል፡፡ @በራሪ ታክሲዎቹ በርቀት ለሚጓዙ ተሳፋሪዎች አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን የአየር እና የከተማ የድምጽ ብክለትን እንዲሁም የትራፊክ መጨናነቅን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የቀድሞው የኢቲዮጵያ ብሔራዊ ቡድን "አሰልጣኝ ውበቱ አባተ "በ416,000 ወርሃዊ ደመወዝ ለሶስት ዓመት "የፋሲል ከነማ ዋና አሰልጣኝ ሆኖ ተቀጠረ!!! @ዉበቱ አባተ እስከ 2018 መጨረሻ ድረስ ለ
#የቀድሞው የኢቲዮጵያ ብሔራዊ ቡድን "አሰልጣኝ ውበቱ አባተ "በ416,000 ወርሃዊ ደመወዝ ለሶስት ዓመት "የፋሲል ከነማ ዋና አሰልጣኝ ሆኖ ተቀጠረ!!! @ዉበቱ አባተ እስከ 2018 መጨረሻ ድረስ ለሶስት አመታት ክለቡን ያሰለጥናል። ፋሲል ከነማ በአጠቃላይ 15 ሚሊዮን ብር በወር የተጣራ 416ሺ ብር ለአሰልጣኙ የሚከፍል ይሆናል ሲል ትርታ ስፖርት ዘግቦታል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የፌዴራል መንግሥት፣ የትግራይና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታት "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ የሚያደርጉት ግልጽና ስውር እንቅስቃሴ ይቅርታ የማያሰጥ "ሀገር የማፍረስ ተልዕኮ ነው "አለ እናት ፓርቲ!!! *በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ፦ @ኢትዮጵያን አጽንተው ካቆዩና ካቆሙ ተቋማት ከመንግሥታዊ ሥርዓት ባልተናነሰ ሁኔታ የሃይማኖት ተቋማት በግንባር ቀደምነት የሚጠቀሱ ናቸው። ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለአገራችን ኢትዮጵያ በብዙ መልኩ ትልቅ ባለውለታ ናት። ይሁን እንጂ መንግሥት ሕዝባችንን ለመለያየት በተጠና መልኩ እየተገበረ ያለውን የጎሳ ፖለቲካ ትርክት በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ በማስረጽና በመጫን የፍቅር፣ የሰላምና የአንድነት ሰባኪ በሆነችው ቤተ ክርስቲያን ከፋፋዮችን ደግፎ በማሰማራትና ለእኩይ አላማቸው ማስፈጸሚያ አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ በእጅ አዙር ቤተ ክርስቲያኗ እንደ ተቋም ጸንታ እንዳትቆም ጉልህ የሆነ የማፍረስ ሥራ እየሠራ ይገኛል። @ከወራት በፊት "የብሔር ብሔረሰቦች ሲኖዶስ" በሚል በኦሮሚያ ክልል በትላንትናው ቀን ደግሞ "መንበረ ሰላማ" በሚል "የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ፈጸምን" የተባለበት ሁኔታ የዚሁ ቤተ ክርስቲያኒቱን የማፍረስ ሴራ መገለጫዎች ናቸው። በዚህ እኩይ ተግባር ቀደም ሲል የጠቀስናቸው የፌዴራል መንግሥቱ፣ የኦሮሚያ ክልልና የትግራይ ክልል መንግሥታት ከድርጊቱ ፊታውራሪዎች ባልተናነስ እኩል ተጠያቂነት አለባቸው። @እናት ፓርቲ እንደ ወግና ሥርዓት ጠባቂ የፓለቲካ ፓርቲ በእምነት ተቋማት ላይ የሚቃጣ ጥቃትና የሚደረግ ሴራ አገርን የማፍረስ ተልእኮ አካል እንደሆነ በጽኑ ያምናል፤ አጥብቆም ይኮንናል። የእንደዚህ ዓይነት እኩይ ተቋም አፍራሽና አገር አፍራሽ ተግባራትን ክፉ ፍሬና ውጤት መመልከቻው እሩቅ ሳይሆን በአጭር ጊዜ የሚታይ፣ ጥሎት የሚያልፈው ጠባሳ ታሪክ በክፉ የሚመዘግበውና የሚያወሳው ጉዳይ ይሆናል። @በትግራይ ባሉ አባቶች "መንበረ ሰላማ" ከመሰየም ጀምሮ ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ያፈነገጡ ድርጊቶች ሲፈጸሙ ቅዱስ ሲኖዶስ በተደጋጋሚ የሰላምና የውይይት ጥሪ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል። ቀደም ሲል "የብሔር ብሔረሰቦች ሲኖዶስ" በሚል በኦሮሚያ መንግስት ጣልቃ ገብነት ሲከናወን የነበረው ህገ-ወጥ ሲመት ለብዙ ምዕመናን ህይወት መቀጠፍ ምክንያት ነበር። መንግስት በጉዳዩ ላይ እንደሌለበት ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በአስታራቂነት ሲተውኑ ማየታችንም የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው። @አሁን ደግሞ የብፁአን አባቶችን "የአሸማግሉን" ጥሪ ጆሮ ዳባ ልበስ ያለው የብልጽግና ፓርቲ መራሹ መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የታላቋ ሀገረ ትግራይ ምስረታ ሰለባ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ በግልጽ እየተወጣ ይገኛል። *ስለሆነም፦ ፩. የፌዴራል መንግሥትና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ይህን በእነርሱው አይዞህ ባይነት እየተከናወነ ያለውን የጥፋት ጉዞ ወደ ትክክለኛ መንገድ በማምጣት ተገቢው የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ በማድረግ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፤ ፪. ቅዱስ ሲኖዶስ በኦሮሚያ ክልል በምእመናን ላይ የደረሰ ሞትና የአካል ጉዳት በማይደርስበት ኹኔታና ትዕግስት በተላበሰና አስተማሪ በሆነ መልኩ ችግሩ የሚፈታበትን ዘዴ በማበጀት የቤተክርስቲያኒቱን ልእልና እንዲያስከብር፤ ፫. የእምነቱ ተከታይ ምእመናንም ይህን ተከትሎ በተሰማቸው የሀዘን ስሜት አፍራሽ ወደ ሆነ አቅጣጫ ከማምራት እንዲቆጠቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን። *እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ! እናት ፓርቲ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ሐምሌ ፲፯ ቀን *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#በመላው ሀገሪቱ "የ12 ክፍል ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ዩንቨርስቲዎች በመግባት ላይ ናቸው!!! @በመላው ሀገሪቱ "የ2015 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች፤ ከትናንት እሁድ ሐምሌ 16/2015 ጀምሮ ወደ መፈተኛ ዩንቨርስቲዎች በመግባት ላይ ይገኛሉ። @የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ማጠናቀቂያ ፈተና በዩንቨርስቲዎች እንዲሰጥ ከባለፈው ዓመት ጀምሮ በትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ መተላለፋ ይታወቃል። @በዚህም መሰረት፤ ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ድረስ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጥ ሲሆን፤ የተለያዩ ዩንቨርስቲዎችም ተፈታኝ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛሉ፡፡ @ዩንቨርስቲዎቹ ከትናንት ጀምሮ በመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እየተቀበሉ ሲሆን፤ በቀጣይ በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት መስክ አገር አቀፍ ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎችን ይቀበላሉ፡፡ @ፈተናው በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የትምህርት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች እና የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች የጋራ ምክክር ማካሄዳቸው ተገልጿል፡፡ @በዚህም ከሐምሌ 19/2015 ጀምሮ በ102 የፈተና ጣቢያዎች የሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከሥርቆት በፀዳ መልኩ እንዲካሄድ ኹሉም ኃላፊነቱን ወስዶ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡ @በ2015 ትምህርት ዘመን መውለጃ ወራቸው የደረሰ ነፍሰ ጡር እና ጡት የሚያጠቡ ሴት ተፈታኞች፤ አንድ ሴት ሞግዚት ይዘው በመግባት እንዲፈተኑ ተገቢው ድጋፍ እንደሚደረግላቸው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+9

photo content

photo content
+1

#እኛ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየጠበቅን ነው " - ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ!!! @የአማራ እና የትግራይ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን የወልቃይት፣ የጠለምትና የራያ አካባቢዎችን " ይገባኛል " ጥያቄን በተመለከተ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየተጠበቁ መሆናቸውን ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል አሳውቀዋል። @ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በአሁን ሰዓት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ምክትል አስተዳዳሪ እና የሰላምና የፀጥታ መምርያ ኃላፊ በመሆን እያገለገሉ ሲሆን በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ በቀረቡበት ወቅት " ሁለቱ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን አካባቢዎች በሕዝብ ውሳኔና በሕጋዊ መንገድ መፍታት አለባቸው " በሚል ስለሰጡት አስተያየት ተጠይቀው መልሰዋል። *ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ምን አሉ ? @በወልቃይት ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሳኔ እናደርጋለን ሲሉ በግልጽ አልሰማንም፡፡ @ነገር ግን በሕጋዊ መንገድ ቢፈታ ይሻላል የሚለውን ምክር አዘል ነገር ለፓርላማው ሲናገሩ ሰምተናል፡፡ @ግን በዚህኛው ቀጣና በዚህኛው ዞን ብለው ሲያነሱ እኔም በግል አልሰማሁም፣ እኛም የምናውቀው ነገርም የለም። ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ በየትኛው መንገድ ነው ሊፈታ የሚገባው የሚለውን ቀደም ሲል በተደጋጋሚ ተናግረናል፡፡ @ሊፈታ በሚገባው መንገድ እንዲፈታ ለመንግሥት አመልክተናል። @ራያም፣ ጠለምትም፣ ወልቃይትም ስላሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለየትኛው እንደተናገሩ ግልጽ አልሆነልኝም። በግምት መልስ ለመስጠት ያስቸግራል። @ብዙ ሰው መላምት ሊኖረው ይችላል ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ ሊፈታ የሚገባበትን መንገድ ጠቅሰን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ስላቀረብን ውሳኔውን እየጠበቅን ነው። @በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅትም ሆነ አሁን ከማኅበረሰቡ ጋር ነኝ ፤ የአገር መከላከያ ሠራዊት የወልቃይት አካባቢን እየተከላከለና እየጠበቀ እንዳለ ነው የምናውቀው። @በአካባቢው ከመከላከያ ጋር ምንም ዓይነት ጦርነት የለም፣ ተባብረን ነው እየሠራን ያለነው፡፡ አካባቢው ሰላማዊ በመሆኑ ፋኖ በሚል ምክንያት ምንም ዓይነት ግጭትም ሆነ ጦርነት የለም። " @የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳዳር በበኩሉ የክልሉ አስተዳደራዊ ወሰን ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ፣ በጦርነቱ ምክንያት ከምዕራብ ትግራይና ከሌሎች የአማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈናቀሉ የክልሉ ነዋሪዎቸ በአፋጣኝ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ በተደጋጋሚ ጥያቄ እያቀረበ ነው፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የመውጫ ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎች እስኪያልፉ መፈተን እንደሚችሉ "ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል!!! @ያላለፉ ተማሪዎች እጣ ፋንታስ ምንድን ነው ሲል አል ዐይን ላነሳላቸው ጥያቄ ዶ/ር ኤባ ሚጃና፤ እስኪያልፉ ድረስ “ያለገደብ” መፈተን ይችላሉ ብለዋል። @“በዓመት ሁለት ጊዜ ነው የምንሰጠው። በመጀመሪያው ያልተሳካለት በሁለተኛው መፈተን ይችላል። ከዚያ በሚቀጥለው ዓመትም ስዘጋጅ እፈተናለሁ ካለ መብቱ ነው። ስለዚህ ገደብ የለውም” ብለዋል። @ከዚህ ቀደም የመውጫ ፈተና የሚወስዱ የህግና የጤና ተማሪዎች ሁለት ፈተና እንዳልወሰዱ የጠቀሱት ስራ አስፈጻሚው፤ የፈቃድ ፈተና ግን ከሚመለከታቸው ተቋማት እንደሚወስዱ ገልጸዋል። @ኃላፊው ተማሪዎቻቸውን የማያበቁ የመንግስትም የግልም የትምህርት ተቋማት ከዚህ በኋላ አይቀጥሉም ብለዋል። ውጤቱ እውቅና ከመስጠት ጀምሮ ተማሪዎችን እስከመመደብ ድረስ እንደሚታይ ገልጸው፤ በሚቀጥሉት ዓመታት ጥብቅ አሰራርን በመዘርጋት የተሻለ ፈተና እንደሚሰጥም ተናግረዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+1

#የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት "አቶ ጌታቸው ረዳ በአሜሪካ ዴንቨር ያደረገው ንግግር!!! @የትግራይ ክልል ፕሬዝዳን አቶ ጌታቸው ረዳ "በአሜሪካ ዴንቨረ ከትግራይ ተወላጆችና ከደጋፊወቻቸው ጋር ሲወያዩ
+1
#የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት "አቶ ጌታቸው ረዳ በአሜሪካ ዴንቨር ያደረገው ንግግር!!! @የትግራይ ክልል ፕሬዝዳን አቶ ጌታቸው ረዳ "በአሜሪካ ዴንቨረ ከትግራይ ተወላጆችና ከደጋፊወቻቸው ጋር ሲወያዩ "ትግራይ ክልል "ላይ የተደረገው ጦርነት በ”design” የተደረገ ነው አማራና አፋር ከተደረገው አይወዳደርም ብለዎል:: @አቶ ጌታቸው ረዳ ለደጋፊወቻቸው እንደተናገሩት "መከላከያ በወልቃይትና ራያ የአማራ አስተዳደር መዋቅሮችን የማፍረስ ግዳጅ ተሰጥቶት እየሰራ ነው ስራውን ጀምሯል In principle ፌደራል መንግስት ግዛቶቹን ለመመለስ ተስማምቷል:: @ፕሬዝዳንቱ አክለውም "ምንም የፈረሰ ሰራዊት የለም "ያስረከብነው መሳሪያ የለም "በብዙ እስር ሽዎች የሚቆጠር ሰራዊት ገብተናል "ለቀጣይ ግዳጅ የተዘጋጀ ሰራዊት አለን ብሏል:: *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የአማራ ክልል የኢኮኖሚ ጭቆና "በመንግስት" እየተደረገበት ነው ተባለ!!! @የአማራ ክልል የምጣኔ ሀብት ጭቆና እየተደረገበት መሆኑን ከሐምሌ 12/2015 ጀምሮ ለሦስት ቀናት ስድስተኛ መደበኛ ጉባኤውን ሲያካሂድ የቆየው የክልሉ ምክር ቤት አባላት ገልጸዋል። @የምክር ቤት አባላት በክልሉ ከፍተኛ የሆነ የመንገድ፣ የመብራት፣ የውሃ፣ የኔትወርክ እና ሌሎች መሰረተ ልማት ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ "ነገር ግን የክልሉ መንግሥት ከወሬ በዘለለ እስካሁን ባለበት እየተጓዘ ነው።" ሲሉ ተደምጠዋል። @በዘንድሮው የምርት ዘመን ከፍተኛ የአፈር ማዳበሪያና የምርጥ ዘር እጥረት መኖሩም በቀጣይ ዓመት እስከ 50 በመቶ የሚደርስ የምርት መቀነስ ሊያስከትል እንደሚችልና ይህም የጎላ ቀውስ እንደሚያስከትል ጠቁመዋል። @እንዲሁም በክልሉ ይገነባሉ ተብሎ ከ20 ዓመት በፊት የታቀዱ ትላልቅ የመንገድ፣ የመስኖ፣ የማኑፋክቼሪንግ እና ሌሎች ፕሮጀክቶች መረሳታቸውን የጠቁሱት የምክር ቤት አባላቱ፣ እነዚህ ኹሉ ክልሉ የምጣኔ ሀብት ጫና እየተደረገበት መሆኑን ማሳያ ናቸው ብለዋል። @አዲስ አበባ ካሏት አምስት መግቢያና መውጫ በሮች የአማራ ሕዝብ የሚገባባቸው ኹለቱ ብቻ የሚዘጉ መሆኑም የክልሉ ሕዝብ እና ተወላጆች በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚደርስባቸውን ጫና የሚያሳይ ነው ተብሏል። @ስለሆነም የአማራ ሕዝብ የምጣኔ ሀብት፣ የማህበራዊ እና የፖለቲካ አገልግሎት እንዳያገኝ ጫና እየተደረገበት መሆኑ ነው በምክር ቤቱ የተጠቆመው። @በተጨማሪም የአማራን ሕዝብ አንገት ለማስደፋት በተግባር የሚገለጡ ቀን ከሌሊት የሚደረጉ ሩጫዎች መኖራቸው ተመላክቷል። @ስለሆነም ሕዝቡ ችግር የለበትም ያሉት የምክር ቤት አባላቱ፤ የክልሉን ችግር ለመፍታት ቅድሚያ መዋቅሩን እናስተካክል ሲሉ ተደምጠዋል። @በብዙ ቦታዎች ከመጠን ያለፈ የሰላም ችግር መኖሩን በማንሳትም፤ አሁን ላይ ያለውን የሰላም ችግር በውይይት መፍታት እንደሚገባ እና ክልሉም በጉዳዩ ላይ በደንብ መምከር እንዳለበት አሳስበዋል። @የክልሉ ርዕስ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ "ችግሩን በራስ የመፍታት አቅም መፍጠር አለብን" ሲሉ ገልጸው፤ "አማራ ክልል ላይ ያለው ጥያቄ ምንድን ነው? የሚለው መፈተሽ አለበት።" ብለዋል። @በክልሉ ያለውን ችግር ለመፍታትም በየዞኑ ከምክር ቤት አባላት አምስት አምስት ሰው ተምርጦ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽመግሌዎች፣ ምሁራንና ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የተሳተፉበት ውይይት ያለምንም ገደብ እንዲደረግ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ አዲስ ማለዳ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#የአሜሪካው የረድኤት ድርጅት ሳማሪታን ፐርስ ባልደረባ በአማራ ክልል "በወልዲያ መገደሉ ተሰማ!!! @የአሜሪካ የረድኤት ድርጅት የሆነው ሳማሪታን ፐርስ ኢንተርናሽናል ባልደረባ በአማራ ክልል ወልዲያ
#የአሜሪካው የረድኤት ድርጅት ሳማሪታን ፐርስ ባልደረባ በአማራ ክልል "በወልዲያ መገደሉ ተሰማ!!! @የአሜሪካ የረድኤት ድርጅት የሆነው ሳማሪታን ፐርስ ኢንተርናሽናል ባልደረባ በአማራ ክልል ወልዲያ ከተማ መገደሉን ከረድኤት ድርጅቱ ምንጮች ተሰምቷል። @የድርጅቱ የአቅርቦት ሠራተኛ የተገደለው በመንግስት ፀጥታ አካላት እና በፋኖ መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ መካከል በተተኮሰ ተባራሪ ጥይት መሆኑን ምንጮቻችን ገልፀዋል። @የሳማሪታን ፐርስ ኢንተርናሽናል ባልደረባው ሕይወት ያለፈው በጥይት ከተመታ በኋላ ለሕክምና ወደ ወልዲያ ሆስፒታል እየተወሰደ በነበረበት ወቅት ነው ተብሏል። @የረድኤት ሠራተኛውን ግድያ በተመለከተ የአሜሪካው ሳማሪታን ፐርስ ኢንተርናሽናልም ሆነ የኢትዮጵያ መንግሥት እስካሁን ያሉት ነገር የለም። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#በወልድያ "የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በርካቶች ቆስለው ሆስፒታል መግባታቸው ተነገረ!!! @በአማራ ክልል በወልድያ ከተማ ትላንት ማታ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ "በኢቲዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና "እራሳቸው
+1
#በወልድያ "የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በርካቶች ቆስለው ሆስፒታል መግባታቸው ተነገረ!!! @በአማራ ክልል በወልድያ ከተማ ትላንት ማታ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ "በኢቲዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና "እራሳቸው የአማራ "ነጻ" አውጪ ብለው በሚጠሩት "ፏኖች መካከል በነበረው የተኩስ ልውውጥ ብዙዎች ቆስለው ሆስፒታል መግባታቸው ተሰምቷል። @በነበረው ግጭትና አለመግባባት "እስካውን ባለው መረጃ "አንድ የሁለት ልጆች እናት "የጎዳና ተዳዳሪ በተባራሪ ጥይት ተመትታ ወዲያውኑ ህይወቷ ሲያልፍ ተጨማሪ አንድ የፖሊስ አባልና አንድ ሚሊሻም ህይወታቸው አልፏል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb