en
Feedback
Shien ekawuch

Shien ekawuch

Open in Telegram
869
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1230 days
Posts Archive
#በአልጄሪያ በተቀሰቀሰው ሰደድ እሳት "የ34 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ!!! @በመላው አልጄሪያ በተቀሰቀሰው ሰደድ እሳት ቢያንስ 34 ሰዎች ህይወታቸውን ሲያጡ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ደግሞ ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን የአልጄሪያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በ16 አውራጃዎች 97 ሰደድ እሳት በደን፣ በሰብል እና በእርሻ መሬት ላይ በትላንትናው እለት ጉዳት አድርሷል። @ወደ 8,000 የሚጠጉ የእሳት አደጋ ተከላካዮች እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰሩ መሆናቸውን ባለስልጣናቱ ተናግረዋል። @በተጨማሪም 26 ሰዎች የቆሰሉ ሲሆን 1,500 ያህል ሰዎች በፌናያ፣ ቤጃያ፣ ዝባርባር እና ቡዪራ ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል። በቤጃያ በተነሳው የእሳት ቃጠሎ 10 ወታደሮች መሞታቸውን የአልጄሪያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። @ከአልጀርስ በስተምስራቅ ተራራማ ካቢሊ ክልል ውስጥ እጅግ በጣም ሰፊ የሆነ ሰደድ እሣት በከፍተኛ ንፋስ እየተገፋ በቤጃያ እና ጂጄል የባህር ዳርቻ ከተሞች ወደሚገኙ የመኖሪያ አካባቢዎች እየተሰራጨ ይገኛል።የቃጠሎው መንስዔ ላይ የፍትህ አካላት ምርመራ መጀመራዠውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል። @በሰሜናዊ አልጄሪያ በቅርብ ቀናት ውስጥ ከፍተኛ ሙቀት እየተመዘገበ ሲሆን የሙቀት መጠኑ 48 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ደርሷል።በሰሜን አፍሪካ ውስጥ በተለያዩ ክልሎች ያለው የሙቀት መጠን ከመደበኛው እስከ 7 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ከፍ ብሏል። @የአልጄሪያ የሚቲዎሮሎጂ ጽህፈት ቤት በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል ከ48 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በላይ የሙቀት መጠኑ እስከ ወሩ መጨረሻ ሊቀጥል እንደሚችል አስጠንቅቋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#በጃፓን በመኪናው ስር "ካሜራ በመትከል አጭር ቀሚስ ያደረጉ ሴቶችን ፎቶ ሲያነሳ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዎሉን "የሀገሪቱ ፓሊስ አስታወቀ!!! @የ44 አመቱ ጃፓናዊ ሳቶሺ ኒሺሙራ የተባለው
#በጃፓን በመኪናው ስር "ካሜራ በመትከል አጭር ቀሚስ ያደረጉ ሴቶችን ፎቶ ሲያነሳ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዎሉን "የሀገሪቱ ፓሊስ አስታወቀ!!! @የ44 አመቱ ጃፓናዊ ሳቶሺ ኒሺሙራ የተባለው ግለሰብ አጭር ቀሚስ የለበሱ ወጣት ልጃገረዶች ፎቶ ለማንሳት በሚል በሚያሽከረክረው መኪና ስር በርካታ ካሜራዎችን በመትከል ፎቶ ሲያነሳ በመያዙ ጨዋነት በጎደለው ድርጊቱ በቁጥጥር ስር ውሏል።ይህው ተግባር ቪኦዩሪዝም ወይም የአጭር ቀሚስ ፎቶግራፍ ተብሎ ይጠራል። @ቃሉ ያለፍቃድ በሴቶች ቀሚስ ስር ፎቶግራፍ ለማንሳት አግባብ ባልሆነ መንገድ የሚሞክሩትን ወንዶች ይገልፃል። ይህው ሰው ታዲያ በቀላል ማመላለሻ መኪናው ስር ቢያንስ አራት ካሜራዎችን በመትከል በዝግታ ቀሚስ በለበሱ፣ አንዳንዶቹ ገና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ በሆኑ ልጃገረዶች ላይ ፎቶ ሲያነሳ ቆይቷል። @በጭነት መኪናው ስር ካሜራዎች ከተገኙ በኋላ ፖሊስ በግለሰቡ ላይ ባደረገው ማጣራት እስከ 1,000 የሚደርሱ አጭር ቀሚስ ያደረጉ ልጃገረዶችን ቪዲዮ ሲያነሳ እንደነበር አስታውቋል። @ጃፓን አጭር ቀሚስ የሚያደርጉ ሰዎችን እያሰሱ ፎቶ የሚነሱ ግለሰቦች በሶስት ዓመታት እስር ወይም 21ሺ የአሜሪካ ዶላር ቅጣት ትጥላለች። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ ከአሜሪካዋ ዴንቨር ከተማ "ከንቲባ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸው ተነገረ!!! @የትግራይ ክልል ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በአሜሪካ "ከዴንቨር ከንቲባ ማይክ ጆንስተን ባካሄዱ
+1
#ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ ከአሜሪካዋ ዴንቨር ከተማ "ከንቲባ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸው ተነገረ!!! @የትግራይ ክልል ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በአሜሪካ "ከዴንቨር ከንቲባ ማይክ ጆንስተን ባካሄዱት የሁለትዮሽ ውይይት በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ ዙርያ ማብራርያ የተሰጣቸው ሲሆን የትግራይ እና ዴንቨር ግንኙነትም ለማጠናከር በውይይቱ መስማመታቸውን ተገልፃል። @28 አመታት ያስቆጠረው በአክሱም እና ዴንቨር የእህተማማች ከተሞች ግንኙነት ያተኮረ ውይይት ማካሄዳቸውን የተገለፀ ሲሆን አሁን ላይ ትግራይ የምትገኝበት ከባድ ሁኔታ ለመውጣት በምታደርገው ጥረት የዴንቨር ማህበረሰብ ሊያበረክተው በሚችለው ድጋፍ ዙርያም መነጋገራቸው ለማወቅ ተችሏል። @የትግራይ ኮሚኒቲ በዴንቨር መድረኩ እንዲዘጋጅ እንዲሁም እንዲካሄድ ለባረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋና ተችሮዋቸዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ኢትዮጲያ በ2015 ዓመት "ከአህያ ስጋ የወጪ ንግድ 3 መቶ ሺህ የአሜሪካን ዶላር ገቢ አገኘው አለች!!! @በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ የአህያ ስጋን ወደ ሆንግኮንግ በመላክ 3 መቶ ሺህ የአሜሪካን ዶላር የውጪ ምንዛሬ ገቢ ማግኘቷን የእንስሳት ልማት ኢንስትቲዩት አስታውቋል፡፡ @በኢንስትቲዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ሳህሉ ሙሉ በተለይ ከብስራት ሬድዮና ቲቪ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት፣ ከአህያ ስጋ ውጪ የአህያ ቆዳን እንደ ቻይና ያሉ ሃገራት ለመድሃኒትነት በስፋት ሲጠቀሙበት የሚስተዋል በመሆኑ የስጋ ምርቱን ወደ ሆንግኮንግ እንዲላክ ተደርጓል ብለዋል፡፡ @ገቢው የተገኘውም በተጠናቀቀው በጀት አመት 140 ቶን የአህያ ስጋ ምርትን ወደ ውጪ ገበያ በመላክ እንደሆነ ጨምረው ገልጸዋል፡፡በበጀት አመቱ 6 መቶ ቶን የአህያ ስጋን ወደ ውጪ ለመላክ አስቀድሞ ታቅዶ እንደነበር ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡ @በአህያ ስጋ የወጪ ንግድ ዙሪያ የቄራ ድርጅቶች የማጓጓዣ ኮንቴይነር እጥረት የነበረባቸው በመሆኑ ምርቱ ከአመቱ አጋማሽ በኃላ ለአለም አቀፍ ገበያ እንዲቀርብ አሉታዊ ተጽእኖ እንዲኖረው አስገዷል፡፡ @ይኸው ችግር በዘንድሮው አመት በታቀደው ልክ ገቢ እንዳይገኝ ያደረገ ዋነኛ መንስኤ እንደሆነ ተመላክቷል፡፡ @ይሁን እንጂ በዘርፏ ከተስተዋለው የማጓጓዣ ኮንቴይነር እጥረት አኳያ በዘንድሮ በጀት አመት የተሻለ አፈጻጸም ተገኝቷል የተባለ ሲሆን ባለፈው በተመሳሳይ ወቅት ከአህያ ስጋ የውጪ ንግድ ሽያጭ 2 መቶ ሺህ ገደማ የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኝቶ እንደነበር ዶክተር ሳህሉ ሙሉ አስታውሰዋል፡፡ @በተጠናቀቀው የ2015 በጀት አመት ከአህያ ስጋ የወጪ ንግድ የተገኘው ገቢም ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ እንዳለው ያሳያል፡፡ @ከማጓጓዣ ኮንቴይነር እጥረት ጋር በተያያዘ ያለውን ችግር ለመፍታትም ከባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተለያዩ ስራዎች በመሰራታቸው እና ለቄራ ድርጅቶች አስፈላጊው ግብአት እንዲሟላላቸው በመደረጉ ከአህያ ስጋ የወጪ ንግድ የተሻለ ውጤትን ማግኘት ተችሏል፡፡ @በሚቀጥሉት ዓመታት ከዘርፏ የተሻለ ገቢን ለማግኘትና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለመደገፍ የሚያስችሉ ስራዎችን በተጠናከረ መልኩ ለመስራት ታቅዷል ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ሳህሉ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮና ቲቪ ተናግረዋል፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+2

#ሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ አግሪት አካባቢ በተከፈተ የተኩስ ልውውጥ ጉዳት መድረሱ ተነገረ!!! @ትናንት ምሽት በአማራ ክልል በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ልዩ ስሙ አግሪት በሚባል ቦታ የወረዳው ሚሊሻ
#ሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ አግሪት አካባቢ በተከፈተ የተኩስ ልውውጥ ጉዳት መድረሱ ተነገረ!!! @ትናንት ምሽት በአማራ ክልል በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ልዩ ስሙ አግሪት በሚባል ቦታ የወረዳው ሚሊሻ እና ፖሊስ አባላት በአካባቢው ከሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት ጋር የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ እንደነበር ተገልፀዋል። @በዚህ የተኩስ ልውውጥ ከፖሊስ እና ከሚሊሻ የሞቱ መኖራቸውን ገልፀዋል።ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ በመቄት ሸድሆ ሆስፒታል ይገኛሉ ተብሏል። ከፋኖ አባላቶቹ በኩል ስለደረሰው ጉዳት የተገለፀ ነገር የለም። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#በትግራይ ክልል "ከአንድ ሺሕ በላይ ሰዎች በረኀብ እንደሞቱ ተነገረ!!! @በትግራይ ክልል፣ ባለፉት ሦስት ወራት፣ የሰብአዊ ርዳታ ምግብ በመቋረጡ፣ ከአንድ ሺሕ በላይ ሰዎች በረኀብ እንደሞቱ፣ የክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። @በተለይ፣ ከአምስት ዓመት በታች የኾኑ ሕፃናት እና የዕድሜ ባለጸጋ አረጋውያን፣ ይበልጥ እየተጎዱ በመኾኑ፣ ከወራት በፊት የተቋረጠው ርዳታ ዳግም እንዲጀመር፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አሳስቧል፡፡ @ከዚኹ ጋራ በተያያዘ፣ ተፈናቃዮች እየደረሰባቸው ያለው ሰብአዊ ቀውስ፣ በከፍተኛ ሁኔታ እየተባባሰ እንደኾነም፣ ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ *ዝርዝሩን "ከቴሌግራም" ቻናላችን ላይ ያገኛሉ👇👇 *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+7

#በኦሮሚያ ክልል "50 ብር ጉቦ ካላመጣህ" በማለት የትራፊክ ፖሊሶች ሾፌር "መግደላቸው ተሰማ!!! @አስደንጋጩ የዶቼ ቨለ ዘገባ "በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የትራፊክ ፖሊስ አባላት የጠየቁትን የሃምሳ ብር ጉቦ አልሰጠም ያሉትን አንድ አሽከርካሪ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን የሟች ቤተሰቦች እና የሥራ ባልደረቦች ገለጹልኝ ሲል ጀምሯል ፡፡ @ዘገባው ሲቀጥል ባለፈው ዓርብ በትራፊክ ፖሊስ አባላቱ በጥይት ተገደለ የተባለውና ትናንት እሁድ የተቀበረው የ33 ዓመቱ ሳሙኤል መረተ ነዋሪነቱ በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡ @ጓደኞቹ እንደሚሉት ሳሙኤል ከረጅም ጊዜ አንስተቶ የአሽከርካሪነት ሥራውን ሲያከናውን የቆየው ከአዲስ አበባ ቡታጅራ በተዘረጋው መስመር ላይ ነበር ፡፡ @ሳሙኤል በመስመሩ በሰበብ አስባቡ ካልቀጣንህ የሚሉትን የትራፊክ ፖሊስ አባላት ለማባበል ዝርዝር የሃምሳ ብር ኖቶችን በእጃቸው እያስጨበጠ ማለፍ የሁልጊዜ ተግባሩ እንደነበር ጓደኞቹ ይናገራሉ ፡፡ @ይህ የሃምሳ ብር ጣጣ ታዲያ “ አንሷል ጨምር አልጨምርም “ በሚል ከትራፊክ ፖሊስ አባላት ጋር የገባበት እሰጥ አገባ ለህይወቱ መጥፋት ምክንያት መሆኑን ነው በሥፍራው ነበርን ያሉ ለዶቼ ቬለ DW የገለጹት ፡፡ @የሳሙኤል ረዳት ሆኜ ሥሠራ ነበር የሚለው አንዱዓለም ሁሴን መንገደኞችን አሳፍረው ከአዲስ አበባ ቡታጅራ በመጓዝ ላይ እንዳሉ በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ተሬ ወረዳ ላይ ሲደርሱ ሦስት ትራፊኮች እንዳስቆሟቸው ይናገራል፡፡ @ሟች ሳሙኤል የመውጫ ወረቀት እና ሃምሳ ብር ሲሰጥ ከትራፊኮቹ አንዱ ሀምሳውን ቀይረህ መቶ አድርግ ሲለው መስማቱን የጠቀሰው አንዱዓለም “ ሟቹም አሁን የለኝም አልተዘጋጀሁም ሲለው ትራፊኩም አለበለዚያ የተሸከርካሪውን ሠሌዳ እፈታለሁ በማለት ሟችን በቦክስ መታው ፡፡ @ይሄኔ በንዴት ተሽከርካሪውን አስነስተን ወደፊት መሄድ ስንጀምር ተከትለው መተኮስ ጀመሩ ፡፡ ጥቂት እንደተጓዝን ተሸከርካሪውን በማቆም እኔም ሆንኩ ሌሎች መንገደኞች ደንግጠን ወረደን መሮጥ ጀመርን ፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እሱን በጥይት መትተው ጣሉት “ ብሏል፡፡ @ከትራፊክ ፖሊስ አባላቱ ጋር አለመግባባቱ የተነሳው በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ተሬ ወረዳ ላይ ቢሆንም ግድያው የተፈጸመው ግን በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ሱተን ዙሪያ ቀበሌ ድረስ ተከታትለው በመምጣት አንደሆነ የተናገሩት የሟች ሳሙኤል አባት አቶ መረተ ለማ ” ይህን ለማን አቤት ልበል ? “ ሲሉም ጠይቀዋል ፡፡ @ዶቼ ቬለ DW በጉዳዩ ላይ በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የተሬ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ፈይሳ ደበላን ጠይቋል ፡፡ አዛዡ ግን ወንጀሉ የተፈጸመው እሳቸው ከሚመሩበት የተሬ ወረዳ አልፎ ጉራጌ ዞን ውስጥ መሆኑን በመጥቀስ “ በዚህ ላይ እኔ የምላችሁ ነገር የለም ፡፡ ባይሆን የደቡብ ክልል ፖሊስን ጠይቁ “ ብለዋል ፡፡ @የወንጀሉ አድራሾች በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኙ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ናቸው የሚሉት የጉራጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ጠጄ መሀመድ በበኩላቸው አሁን ላይ ድርጊቱን በመፈጸም የተጠረጠሩ ሦስት የትራፊክ ፖሊሶች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ @የተከሰተው ነገር አሳዛኝ ነው “ ያሉት ኮማንደር ጠጄ "የወንጀሉ ተጠርጣሪዎች ወዲያው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ጥሩ ነገር ነው፡፡ አሁን ምርመራውን ከኦሮሚያ ክልል የሥራ ሃላፊዎች ጋር አብረን እየሠራን እንገኛለን ፡፡ ወንጀሉ የተፈጸመው በጉራጌ ዞን ውስጥ በመሆኑ ምርመራውን ወደ ዞኑ ለማዛወር በሂደት ላይ ነው ተብሏል። DW *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+2

#ትዊተር" በሰማያዊ ወፍ ይወከል የነበረውን ሎጎውን ወደ በጥቁር መደብ ላይ ያለ የኤክስ (X) ምልክት መቀየሩን ይፋ አደረገ!!! @የዓለማችን ቁጥር አንድ ቱጃሩና አወዛጋቢው የትዊተር የማህበራዊ ትስስር መተግበሪያ ባለቤት ኤለን መስክ አሁን ደግሞ አዲስ መነጋገሪያ ነገር ይዞ ብቅ ብሏል። @አዲሱ ሎጎው የበርካታ ትዊተር ተጠቃሚዎችን ተቃውሞ ያስተናገደ ቢሆንም ባለቤቱ ኤለን መስክ የራሱንም የትዊተር ፕሮፋይል ፎቶ ወደ ኤክስ ምልክት በመቀየር ለውጡ የማይቀለበስ እንደሆነ አመላክቷል። @እኤአ 2006 ላይ በአሜሪካ የተመሰረተው የትዊተር ኩባንያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎችን ለማፍራት የቻለ የማህበራዊ ትስስር መተግሪያ አይነት ነው። @ስያሜው የመጣው ከአእዋፋት ዜማ ጋር የተገናኘ እንደሆነ ይገለፃል፤ “እገሌ ትዊት አደረገ” ሲባል በትዊተር አካውንቱ ላይ መልእክት ፃፈ/አስተላለፈ እንደማለት ነው። @ትዊተርን በዚህ ዓመት የገዛው ኤለን መስክ ከትላንት ሰኞ እለት ጀምሮ የትዊተርን ታዋቂ 'ሰማያዊ ወፍ' አርማ በ"X" ቀይሮታል። @መደቡ ጥቁር ሆኖ የ"X" ምልክት ያረፈበት አዲሱ ሎጎ፤ ካሊፎርኒያ በሚገኘው የኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ላይ እና በሰራተኞች መታወቂያ ላይም መቀመጡን ቢቢሲ ዘግቧል። @ለኮምፒተር ተጠቃሚዎች ሎጎው የተቀየረ ሲሆን የሞባይል መተግበሪያው ግን አሁንም የሰማያዊውን ወፍ ሎጎ እያሳየ ነው፤ ሲዘምን (አብዴት ሲደረግ) ግን ወደ አዲሱ ሎጎ ሊቀየር እንደሚችልም ተመላክቷል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+2

#የሳዉዲዉ አልሒላል ክለብ "ለፈረሳዊው ሙባፔ ያቀረበዉ ክፍያ "በኛ ሀገረ ገንዘብ ሲመነዘረ!!! 👉በአመት 700 ሚሊየን ፓዉንድ (56 ቢሊየን ብር) 👉በወር 58.3 ሚሊየን ፓዉንድ(4.6 ቢሊየን
#የሳዉዲዉ አልሒላል ክለብ "ለፈረሳዊው ሙባፔ ያቀረበዉ ክፍያ "በኛ ሀገረ ገንዘብ ሲመነዘረ!!! 👉በአመት 700 ሚሊየን ፓዉንድ (56 ቢሊየን ብር) 👉በወር 58.3 ሚሊየን ፓዉንድ(4.6 ቢሊየን ብር) 👉በቀን 1.9 ሚሊየን ፓዉንድ(153.4 ሚሊየን ብር) 💰 በሠአት 79908 ፓዉንድ(6.3 ሚሊየን ብር) 👉በደቂቃ 1331 ፓዉንድ(106480 ብር) 👉በሰከንድ 22 ፓዉንድ(1760 ብር) ነው። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#በኦሮሚያ "ሱተን ዙሪያ ቀበሌ ድረስ ተከታትለው በመምጣት ነው የገደሉት ይሄን ለማን አቤት ልበል!!!?"፦ ወላጅ አባት!!! @በኦሮሚያ ክልል፤ ምዕራብ ሸዋ ዞን የትራፊክ ፖሊስ አባላት የጠየቁትን ያህል ጉቦ አልሰጥም ያለን አንድ አሽከርካሪ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን የሟች ቤተሰቦችና የሥራ ባልደረቦች መግለፃቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል። @ድርጊቱ የተፈፀመው ባለፈው ዓርብ ዕለት ሲሆን በትራፊክ ፖሊስ አባላቱ በጥይት የተገደለው እና ትላንት ስርዓተ ቀብሩ ተፈፀመ የተባለው የ33 ዓመት እድሜ ያለው ሳሙኤል መረተ ነው።ሳሙኤል መረት ነዋሪነቱ በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡ @ጓደኞቹ እንዳሉት ሳሙኤል ከረጅም ጊዜ አንስተቶ የአሽከርካሪነት ሥራውን ሲያከናውን የቆየው ከአዲስ አበባ ቡታጅራ በተዘረጋው መስመር ላይ ነበር። @በመስመሩ በሰበብ አስባቡ ካልቀጣንህ የሚሉትን የትራፊክ ፖሊስ አባላት ለማባበል ዝርዝር የ " ሃምሳ ብር " ኖቶችን በእጃቸው እያስጨበጠ ማለፍ የሁልጊዜ ተግባሩ እንደነበር ጓደኞቹ ይናገራሉ። @ይህ የሃምሳ ብር ጣጣ ታዲያ " አንሷል ጨምር አልጨምርም " በሚል ከትራፊክ ፖሊስ አባላት ጋር የገባበት እሰጥ አገባ ለህይወቱ መጥፋት ምክንያት መሆኑን ነው በሥፍራው ነበርን ያሉ ገልጸዋል። የሳሙኤል ረዳት ምን አለ ? የሳሙኤል መረተ ረዳት ሆኜ ሥሠራ ነበር የሚለው አንዱዓለም ሁሴን ፦ @መንገደኞችን አሳፍረን ከአዲስ አበባ ቡታጅራ በመጓዝ ላይ እያለን በኦሮሚያ ክልል ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ተሬ ወረዳ ላይ ስንደርስ ሦስት ትራፊኮች ያስቆሙናል። @ሳሙኤል የመውጫ ወረቀት እና ሃምሳ ብር ሲሰጥ ከትራፊኮቹ አንዱ ሀምሳውን ቀይረህ መቶ አድርግ ሲለው ሰምቻለሁ። @ሳሙኤል አሁን የለኝም አልተዘጋጀሁም ሲለው ትራፊኩ አለበለዚያ የተሸከርካሪውን ሠሌዳ እፈታለሁ በማለት በቦክስ መታው፡፡ @ይሄኔ በንዴት ተሽከርካሪውን አስነስተን ወደፊት መሄድ ስንጀምር ተከትለው መተኮስ ጀመሩ፡፡ @ጥቂት እንደተጓዝን ተሸከርካሪውን በማቆም እኔም ሆንኩ ሌሎች መንገደኞች ደንግጠን ወረደን መሮጥ ጀመርን፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እሱን በጥይት መትተው ጣሉት " ሲል ቃሉን ሰጥቷል። @የሟች ሳሙኤል አባት አቶ መረተ ለማ በበኩላቸው ፤ ከትራፊክ ፖሊስ አባላቱ ጋር አለመግባባቱ የተነሳው በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ተሬ ወረዳ ላይ ቢሆንም ግድያው የተፈጸመው ግን በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ሱተን ዙሪያ ቀበሌ ድረስ ተከታትለው በመምጣት አንደሆነ ገልጸዋል። " ይህን ለማን አቤት ልበል ? " ሲሉም ጠይቀዋል ፡፡ @በኦሮሚያ ክልል ደ/ምዕራብ ሸዋ ዞን የተሬ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ፈይሳ ደበላን ጉዳዩን በተመለከተ ከሬድዮ ጣቢያው ተጠይቀው ፤ ወንጀሉ የተፈጸመው እሳቸው ከሚመሩበት የተሬ ወረዳ አልፎ ጉራጌ ዞን ውስጥ መሆኑን በመጥቀስ " በዚህ ላይ እኔ የምለው ነገር የለም ፤ ባይሆን የደቡብ ክልል ፖሊስን ጠይቁ " ብለዋል። @የጉራጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ጠጄ መሀመድ ፤ የወንጀሉ አድራሾች በኦሮሚያ ክልል ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኙ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ናቸው ብለዋል። @አሁን ላይ ድርጊቱን በመፈጸም የተጠረጠሩ ሦስት የትራፊክ ፖሊሶች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል። @የተከሰተው ነገር አሳዛኝ ነው " ያሉት ኮማንደር ጠጄ " የወንጀሉ ተጠርጣሪዎች ወዲያው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ጥሩ ነገር ነው፡፡ አሁን ምርመራውን ከኦሮሚያ ክልል የሥራ ሃላፊዎች ጋር አብረን እየሠራን እንገኛለን ፡፡ *ቴሌገራም ቻናላችን፦https://t.me/Esattvnews

photo content
+2

#የፌዴራል መንግሥት፣ የትግራይና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታት "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ የሚያደርጉት ግልጽና ስውር እንቅስቃሴ ይቅርታ የማያሰጥ "ሀገር የማፍረስ ተልዕኮ ነው "አለ እናት ፓርቲ!!! *በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ፦ @ኢትዮጵያን አጽንተው ካቆዩና ካቆሙ ተቋማት ከመንግሥታዊ ሥርዓት ባልተናነሰ ሁኔታ የሃይማኖት ተቋማት በግንባር ቀደምነት የሚጠቀሱ ናቸው። ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለአገራችን ኢትዮጵያ በብዙ መልኩ ትልቅ ባለውለታ ናት። ይሁን እንጂ መንግሥት ሕዝባችንን ለመለያየት በተጠና መልኩ እየተገበረ ያለውን የጎሳ ፖለቲካ ትርክት በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ በማስረጽና በመጫን የፍቅር፣ የሰላምና የአንድነት ሰባኪ በሆነችው ቤተ ክርስቲያን ከፋፋዮችን ደግፎ በማሰማራትና ለእኩይ አላማቸው ማስፈጸሚያ አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ በእጅ አዙር ቤተ ክርስቲያኗ እንደ ተቋም ጸንታ እንዳትቆም ጉልህ የሆነ የማፍረስ ሥራ እየሠራ ይገኛል። @ከወራት በፊት "የብሔር ብሔረሰቦች ሲኖዶስ" በሚል በኦሮሚያ ክልል በትላንትናው ቀን ደግሞ "መንበረ ሰላማ" በሚል "የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ፈጸምን" የተባለበት ሁኔታ የዚሁ ቤተ ክርስቲያኒቱን የማፍረስ ሴራ መገለጫዎች ናቸው። በዚህ እኩይ ተግባር ቀደም ሲል የጠቀስናቸው የፌዴራል መንግሥቱ፣ የኦሮሚያ ክልልና የትግራይ ክልል መንግሥታት ከድርጊቱ ፊታውራሪዎች ባልተናነስ እኩል ተጠያቂነት አለባቸው። @እናት ፓርቲ እንደ ወግና ሥርዓት ጠባቂ የፓለቲካ ፓርቲ በእምነት ተቋማት ላይ የሚቃጣ ጥቃትና የሚደረግ ሴራ አገርን የማፍረስ ተልእኮ አካል እንደሆነ በጽኑ ያምናል፤ አጥብቆም ይኮንናል። የእንደዚህ ዓይነት እኩይ ተቋም አፍራሽና አገር አፍራሽ ተግባራትን ክፉ ፍሬና ውጤት መመልከቻው እሩቅ ሳይሆን በአጭር ጊዜ የሚታይ፣ ጥሎት የሚያልፈው ጠባሳ ታሪክ በክፉ የሚመዘግበውና የሚያወሳው ጉዳይ ይሆናል። @በትግራይ ባሉ አባቶች "መንበረ ሰላማ" ከመሰየም ጀምሮ ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ያፈነገጡ ድርጊቶች ሲፈጸሙ ቅዱስ ሲኖዶስ በተደጋጋሚ የሰላምና የውይይት ጥሪ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል። ቀደም ሲል "የብሔር ብሔረሰቦች ሲኖዶስ" በሚል በኦሮሚያ መንግስት ጣልቃ ገብነት ሲከናወን የነበረው ህገ-ወጥ ሲመት ለብዙ ምዕመናን ህይወት መቀጠፍ ምክንያት ነበር። መንግስት በጉዳዩ ላይ እንደሌለበት ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በአስታራቂነት ሲተውኑ ማየታችንም የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው። @አሁን ደግሞ የብፁአን አባቶችን "የአሸማግሉን" ጥሪ ጆሮ ዳባ ልበስ ያለው የብልጽግና ፓርቲ መራሹ መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የታላቋ ሀገረ ትግራይ ምስረታ ሰለባ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ በግልጽ እየተወጣ ይገኛል። *ስለሆነም፦ ፩. የፌዴራል መንግሥትና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ይህን በእነርሱው አይዞህ ባይነት እየተከናወነ ያለውን የጥፋት ጉዞ ወደ ትክክለኛ መንገድ በማምጣት ተገቢው የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ በማድረግ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፤ ፪. ቅዱስ ሲኖዶስ በኦሮሚያ ክልል በምእመናን ላይ የደረሰ ሞትና የአካል ጉዳት በማይደርስበት ኹኔታና ትዕግስት በተላበሰና አስተማሪ በሆነ መልኩ ችግሩ የሚፈታበትን ዘዴ በማበጀት የቤተክርስቲያኒቱን ልእልና እንዲያስከብር፤ ፫. የእምነቱ ተከታይ ምእመናንም ይህን ተከትሎ በተሰማቸው የሀዘን ስሜት አፍራሽ ወደ ሆነ አቅጣጫ ከማምራት እንዲቆጠቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን። *እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ! እናት ፓርቲ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ሐምሌ ፲፯ ቀን *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#የጋምቤላ ክልል የጸጥታ ኹኔታ የመንግሥትን ተጨማሪ ትኩረት የሚሻ ነው” ፦ ኢሰመኮ!!! @በጋምቤላ ክልል ያለው የጸጥታ ሁኔታ በነዋሪዎች ላይ ያደረሰው ከፍተኛ ጉዳት እና የሰብአዊ መብቶች ጥሰት፤ የመንግሥትን ተጨማሪ ትኩረት የሚሻ ነው ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ። @ኮሚሽኑ ከግንቦት ወር 2015 ጀምሮ በተለያዩ የጋምቤላ ክልል አካባቢዎች ሲከሰቱ የቆዩ የትጥቅ ግጭቶችን፣ የታጠቁ ቡድኖች ጥቃቶችንና አጠቃላይ የጸጥታ ችግሮችን እና በዚህ ሳቢያ የሚደርሱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን እየተከታተለ እንደሚገኝ አስታውቋል። @በተለይም ከግንቦት ወር 2015 ጀምሮ በክልሉ ላለው የጸጥታ ችግር መነሻ፣ በኢታንግ ልዩ ወረዳ በተወሰኑ ነዋሪዎች መካከል የተነሳ አለመግባባት መሆኑ ማረጋገጡን የገለጸ ሲሆን፤ ይሄው አለመግባባት በፍጥነት ወደ ብሔርን መሠረት ያደረገ ውጥረት እንደተሸጋገረ ነዋሪዎች ነግረውኛል ብሏል። @ይህንን ተከትሎም የተለያየ ብሔር ታጠቂ ቡድኖች በኢታንግ ልዩ ወረዳ፣ ጋምቤላ ወረዳ፣ ጎግ ወረዳ፣ በጋምቤላ ከተማ ብሔር ብሔረሰቦች ተብሎ በሚጠራው አካባቢ እና በከተማው በሚገኙ ሌሎች ሰፈሮች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ገልጿል፡፡ በዚህም ምክንያት በርካታ ሲቪል ሰዎች እንደተገደሉ፣ የአካል ጉዳት፣ መፈናቀል እና ንብረት ውድመት መድረሱን አስታውቋል። @በጸጥታው ችግር ምክንያት ገና ወደ አካባቢዎቹ በአካል ደርሶ ምርመራ ለማድረግ አለመቻሉን የገለጸው ኮሚሽኑ፤ ነገር ግን ነዋሪዎች በአንዳንድ አካባቢዎች ያሉ መንደሮች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መውደማቸውን ነዋሪዎች ገልጸውልኛል ብሏል። @በክልሉ በተደጋጋሚ ከጎረቤት አገር ደቡብ ሱዳን በሚመጡ ታጣቂ ቡድኖች በሚደርሱ ጥቃቶች እንዲሁም፤ አልፎ አልፎ በክልሉ በሚኖሩ ብሔሮች መካከል በሚከሰቱ ግጭቶች ሳቢያ ከፍተኛ ጉዳት የሚደርስ መሆኑም በመግለጽ፤ ክልሉ ወደ 350 ሺሕ የሚጠጉ የደቡብ ሱዳን ስደተኞችን በስምንት የተለያዩ ካምፖች እንደሚያስተናግድም አስታውሷል። @ከኹለት ወራት በላይ ለዘለቀው የጋምቤላ ክልል የጸጥታ ችግር እና በክልሉ ልዩ ልዩ አካባቢዎች በመድረስ ላይ ያሉ ግጭቶች ተሳታፊዎችን በተመለከተ ተጎጂዎችም ሆነ የክልሉ የጸጥታ እና የአስተዳደር ኃላፊዎች፤ የተለያዩ ብሔር ታጣቂ ቡድኖችን በኃላፊነት እንደሚጠቅሱም ኢሰመኮ ገልጿል። @በአንዳንድ አካባቢዎች የክልሉ ኑዌር ብሔረሰብ ታጣቂዎች፣ በሌላ አካባቢ የአኝዋ ብሔረሰብ ታጣቂዎች፣ እንዲሁም ከጎረቤት አገር ደቡብ ሱዳን የመጡ ታጣቂዎች እና በአንዳንድ የስደተኛ ካምፖች ውስጥ እንደሚኖሩ የተገለጸ ሰዎች ጭምር በግጭቶቹ ተሳታፊ መሆናቸውን ኮሚሽኑ አመላክቷል፡፡ @“እነዚህ ጥቃቶች እና ግጭቶች በአብዛኛው ብሔር ናቸው” ያለው ኮሚሽኑ፤ “በሌላ በኩል ግጭት የሚደርስባቸውን አካባቢዎች ያለ የብሔር ልዩነት ኹሉንም ነዋሪዎች አካባቢውን ሸሽቶ ለመፈናቀል፣ ለንብረት ውድመት እና ለሌሎች የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ያጋለጠ” መሆኑን ጠቁሟል። @የክልሉ መንግሥት ከሐምሌ 12/2015 ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት ተግባራዊ የሚሆን ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት እስከ ጠዋት 12፡00 ሰዓት የሚዘልቅ እና በኹሉም የክልሉ አካባቢዎች ተፈጻሚ የሚሆን የሰዓት እላፊ ገደብ፣ እንዲሁም ከተመደቡ የጸጥታ አካላት ውጪ መሣሪያ ይዞ የመንቀሳቀስ ገደብ መጣሉ ይታወሳል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+2