en
Feedback
Shien ekawuch

Shien ekawuch

Open in Telegram
869
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1230 days
Posts Archive
#ሲንጋፖር "ከ19 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደንዛዥ ዕፅ ክስ አንዲት ሴትን በሞት ልትቀጣ ነው!!! @ሲንጋፖር ከ19 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት ልጅ በሞት ልትቀጣ መሆኑን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ገልፀዋል። የ45 ዓመቷ የሲንጋፖር ዜግነት ያላት ሳሪዴዊ ድጃማኒ በ2018 ዓመት 30 ግራም ሄሮይን የተሰኘ አደንዛዥ እፅ በማዘዋወሩ ጥፋተኛ ሆና ተገኝታለችልቻ። @ከሲንጋፖርዊው ሞህድ አዚዝ ቢን ሁሴን በኋላ በሦስት ቀናት ውስጥ በሞት የምትቀጣ ሁለተኛዋ የአደንዛዥ ዕፅ ወንጀለኛ ስትሆን ከመጋቢት 2022 ጀምሮ የሞት ቅጣት ተግባራዊ ከተደረገባቸው ደግሞ 15ኛዋ ትሆናለች። @ሲንጋፖር ህብረተሰቡን ለመጠበቅ አስፈላጊ ነው ስትል በአደንዛዥ እፅ ላይ ጠንካራ ህጎች ትከተላለች። አዚዝ 50 ግራም ሄሮይን በማዘዋወር ወንጀል የተከሰሰ ሲሆን በሲንጋፖር ህግ መሰረት ከ 15 ግራም በላይ ሄሮይን እና ከ 500 ግራም በላይ ካናቢስ ይዘው የተገኙ ሰዎች ላይ የሞት ቅጣት ሊተገበር ይችላል ይላል። @በዚህም መሰረት የ56 አመቱ መሀመድ አዚዝ ሁሴን በሲንጋፖር ቻንጊ እስር ቤት ውስጥ በትላንትናው እለት በሞት ተቀጥቷል። የ45 ዓመቷ ሳሪዴዊ ድጃማኒ የሞት ትጣቷ በነገው እለት አርብ እንደሚተገበር የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገልፀዋል። @የመጨረሻው ሴት በሲንጋፖር ውስጥ በሞት የተቀጣችውን የ36 ዓመቷ ፀጉር አስተካካይ ዬን ሜይ ዋይን የምትባል ሲሆን እ.ኤ.አ በ2004 በአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪነት ክስ እንደነበር የሮይተርስ ዘገባ አመላክቷል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የቀድሞው "የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ "ኢኒጂነር ስመኘው በቀለ ህይወታቸው ካለፈ አምስተኛ ዓመቱን ደፈነ!!! @የቀድሞው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢኒጂነር ስመኘው በቀለ ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓ.ም በአዲስ አበባ፣ በመስቀል አደባባይ ሕይወታቸው አልፎ ከተገኘ ዛሬ ሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም አምስተኛ ዓመቱን ደፍኗል፡፡ @የመሃንዲሱ ግድያን በተመለከተ ፖሊስ በወቅቱ በሰጠው መግለጫ ራሳቸውን አጥፈተው ስለመሆኑ መግለፁ ይታወሳል፡፡ @ይህ የሞታቸው ዜና እንደተሰማም የወቅቱ የኢፌዴሪ ፕሬዘደንት የነበሩት ሙላቱ ተሾመ የህዳሴ ግድቡን ወደ ሚፈለገው ደረጃ ለማድረስ በከፍተኛ የሀገር ፍቅር ስሜት የሰሩ መሆናቸውን በመግለፅ ለሌሎችም ምሳሌ ሁነው ይኖራሉ ሲሉ ባወጡት የሀዘን መግለጫ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ነበር፡፡ @በዚህ የኢንጂነሩ አሟሟት ዙሪያ በርካታ የሴራ ትንተናዎች ትናንትም፣ ዛሬም መሰጠታቸውን እንደቀጠሉ ናቸው፡፡ በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ከቀድሞው መሪ ሀይለማርያም ደሳለኝ ከተረከቡ በአምስተኛው ወር ገደማ የመሃንዲሱ ህልፈት መሰማቱ ግራ ገብ ሆኖ ነበር፡፡ @ከዚህ የሞት ዜና አስቀድሞ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ ኢትዮጵያ በተለይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ በኩል የተለያዩ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ስታከናውን ቆይታለች፡፡ ከእነዚህ አንደኛው ዐብይ አህመድ ወደግብፅ ካይሮ ያደረጉት ጉዞ መሆኑ ይጠቀሳል፡፡ @የቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስዩም መስፍን ከትግራይ ቲቪ- ኢትዮ ፎረም ዝግጅት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከካይሮ ጉዟቸው መልስ ከመሃንዲሱ ጋር መገናኘታቸውን ነበር፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+1

#በሱዳን" ዋና ከተማ ኻርቱም አጎራባች አካባቢዎች በአየር እና በመድፍ ጥቃት ቢያንስ "16 ሰዎች መገደላቸውን በአቅራቢያው የሚገኙ እማኞች ገለጹ!!! @በሰሜን ምዕራብ ኻርቱም ኦምባዳ አካባቢ በተፈጸ
+1
#በሱዳን" ዋና ከተማ ኻርቱም አጎራባች አካባቢዎች በአየር እና በመድፍ ጥቃት ቢያንስ "16 ሰዎች መገደላቸውን በአቅራቢያው የሚገኙ እማኞች ገለጹ!!! @በሰሜን ምዕራብ ኻርቱም ኦምባዳ አካባቢ በተፈጸመው የመድፍ ጥቃት ስድስት ዜጎች ትናንት መገደላቸውን የአካባቢው እማኞች ለፈረንሳይ የዜና ወኪል አዣንስ ፍራንስ ፕረስ ተናግረዋል። @የአካባቢው ነዋሪ የሆኑት መሐመድ መንሱር ለዜና ምንጩ እንደገለጹት እርሳቸው ብቻ በጥቃት ከፈራረሱ ቤቶች የስምንት ሰዎችን አስከሬን በማውጣት እረድተዋል። ከአጎራባች ቤቶችም እንዲሁ ሁለት ሕጻናትን ጨምሮ አራት ሰዎች መገደላቸውን ሌላው የዓይን እማኝ ሃጋር ዩሱፍም ገልጸዋል። @እንዲያም ሆኖ ትናንትን ጨምሮ ባለፉት ቀናት በደረሰው ጥቃት የተገደሉትም ሆነ የተጎዱት ብዛት ገና ይፋ እንዳልተነገረ ነው የተገለጸው። ሱዳን ውስጥ በከፍተኛዎቹ ጀነራሎች መካከል ውጊያ ከተጀመረ አንድ መቶ ቀናት አልፈዋል፤ በዚህ ጊዜ ውስጥም የተገደሉት ሰዎች ቁጥር 3,900 ገደማ እንደሚደርስ መረጃዎች ያመለክታሉ። @አብዛኛው ውጊያ ሲቪሎች በብዛት በሚኖሩባቸው አካባቢዎች እንደሚደረግም ነው የሚገለጸው። በዚህ ምክንያትም ከመኖሪያ አካባቢው የተፈናቀለው ሕዝብ ከሦስት ሚሊየን አልፏል። DW *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የኤርትራው ፕሬዝደንት "ኢሳያስስ አፈወርቂ ወደ ሩሲያ አቀኑ!!! @የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቱን የቀረላቸውን የጉብኝት ጥሪ ተቀብለው ዛሬ ማለዳ ሩሲያ
#የኤርትራው ፕሬዝደንት "ኢሳያስስ አፈወርቂ ወደ ሩሲያ አቀኑ!!! @የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቱን የቀረላቸውን የጉብኝት ጥሪ ተቀብለው ዛሬ ማለዳ ሩሲያ አቅንተዋል፡፡ @ኢሳያስ ወደ ሞስኮ ያቀኑት በሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ሲሆን፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ኦስማን ሳላህ ጋር ነው በጉባኤ ላይ የሚሳተፉት፡፡ @በነገው ዕለት የሚካሄደው የሩሲያ አፍሪካ አገራት ጉባኤ የሚካሄደው ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን፣ በርካታ የአፍሪካ አገራት መሪዎች ይሳተፉበታል፡፡ @የሩሲያ-አፍሪ ጉባኤ አሜሪካ የአፍሪካ አገራትን በጥብቅ ድፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከጎኗ ለማሰለፍ የተነሰሰችውን የኤሜሪካ-አፍሪካ ጉባኤ የሚገዳደር አቻ የድፕሎማሲ ሰበት መድረክ ነው፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#EBC"የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ ከወርሃዊ ኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ቢል ጋር ተዳምሮ እንዲዘጋጅ መደረጉ ተነገረ!!! @ከሰኔ ወር ጀምሮ የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ በየወሩ 10 ብር ከወርሃዊ ኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ቢል ጋር ተዳምሮ እንዲዘጋጅ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። @ይህ የሚመለከታቸው ከ50 ኪሎ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል የሚጠቀሙ ደንበኞችን ብቻ መሆኑን ተገልጿል። @በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቲቪ) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዋጅ ቁጥር 1278/2015 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ዓመታዊ የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፍጆታ ሂሳብ ክፍያ ቢል ጋር እንዲሰበስብ መወሰኑን ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+1

#በህንድ "ፍቅረኛዋን በድብቅ ለማግኘት ስትል የመንደሩን "የኤሌክትሪክ ኃይል ስታጠፋ የነበረችው "ወጣት ተያዘች!!! @በህንድ ቢሃር ግዛት የምትኖር አንዲት ወጣት ከፍቅረኛዋ ጋር ማንም ሳያያቸው ለመገናኘት በሚል የመንደሩን የኤሌክትሪክ ኃይል ስታጠፋ መቆየቷ ተደርሶባተል። ፍቅረኛዋ ከሌላ ሰፈር የሚመጣ ሲሆን የሰፈሯ ልጆች ይህንን ካዩ ፀብ ይቀሰቀሳል በሚልና በሁለቱ መንደሮች መካከል ዘለግ ላሉ ዓመታት ግጭት ስለነበር ይህንኑ መንገድ መርጣለች። @በቢሃር ግዛት ምዕራብ ሻምፓራን አውራጃ ውስጥ በምትገኝ የቤቲያህ መንደር በየምሽቱ በሚባል ደረጃ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ከአንድ ሳምንት በላይ አስቆጥሯል። ድቅድቅ ጨለማው ለሌቦች አመቺ ሆኖ ስርቆት እንዲበራከት ምክንያት ሆኗል። @ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያስተካክል ጥሪ ባቀርቡም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ኃይል ተወካዮቹ ግን ምንም አይነት የመሠረተ ልማት ችግር እንደሌለ ተናግረዋል። አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች በመንደሩ ውስጥ ነቅተው ሲመለከቱ ታዲያ ጨለማውን ተገን አድርገው ተሸፍነው የሚገናኙ ጥንዶችን ያስተውላሉ። @የአካባቢው ተወላጅ የሆነችው ፕሪቲ ኩማሪ ከተቀናቃኝ መንደር ከሚኖረው ፍቅረኛዋ ራጅ ኩማር ጋር በፍቅር ወድቃ ነበር እና ግንኙነቱን ሚስጥራዊ ለማድረግ በየጊዜው የመንደሩን የኤሌክትሪክ መስመር ስትቆርጥ እንደቆየች ተደርሶባታል። @ፕሪቲ መብራት ታጠፋ በነበረበት ቀናቶች በመንደሩ ውስጥ በርካታ ስርቆቶች ይፈጸሙ ነበር። በህንድ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተለቀቀ ምስል ጥንዶቹ ሲያዙና ፕሪቲ ፍቅረኛዋን ከመንደሩ ወጣቶች ድብደባ ለመከላከል ስትሞክር ያሳያል። ራጅኩማር በፍቅረኛው መንደር የደረሰበትን ድብደባ ከራሱ ሰፈር ጓደኞች ጋር በመምጣት አጥቂዎቹን ተበቅሏል። @ይህው ፀቡ በሁለቱ መንደሮች ከዚህ በላይ እንዳይጋጋል ጥንዶቹ ጋብቻ እንዲመሰርቱ በአካባቢው ነዋሪዎችን ይሁንታን አግኝተዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#ሁለት" የእንጀራ ልጆቿን "በአሰቃቂ ሁኔታ ገድላ ያቃጠለችው ግለሰብ በሞት እንድትቀጣ ተፈረደ!!! @በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ ከታ ወረዳ፤ ኹለት የእንጀራ ልጆቿን በአሰቃቂ ኹኔታ ገድላ ያቃጠለችው ግለሰብ በሞት ፍርድ እንደተፈረደባት ኦቢኤን ዘግቧል፡፡ @የሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት የኹለት ዓመትና የአስራ ኹለት ዓመት የእንጀራ ልጆቿን ሆን ብላና ጨለማን ተገን አድርጋ በቀን 27/08/2015 ከለሊቱ 5:00 ላይ በመጥረቢያ ቆራርጣ ገድላ ያቃጠለችው ነጋሴ ከበደ በሞት ፍርድ እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል። @ተከሳሿ ወንጀሉን ፈጽማ ከሸሸችበት ዕለት አንስቶ በፓሊስ ስትፈለግ ከቆየች በኋላ፤ ፓሊስ ባካሄደው ከፍተኛ ጥረት ግንቦት 1/2015 በቁጥጥር ሥር ውላ የፍርድ ሂደቷን ስትከታተል መቆየቷን ችሎቱ አስረድቷል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+5

#በመካነ ሰላም" ከተማ በወጣቶችና ከመከላከያ ሠራዊት መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ኹለት ሰዎች መገደላቸው ተነገረ!!! @በአማራ ክልል "በደቡብ ወሎ ዞን መካነሰላም ከተማ እሁድ ሐምሌ 16/2015 የከተማው ወጣት ከመከላከያ ሠራዊት አባላት ጋር በተፈጠረ ግጭት ኹለት ሰዎች መገደላቸውን፤ የመካነ ሰላም ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ገልጿል፡፡ @የመካነ ሰላም ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት የሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ አረጋ አህመድ፤ “እሁድ ሐምሌ 16/2015 ከቀኑ አምስት ሰዓት ላይ በከተማው የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የቤተክርስቲያን የጥበቃ ሠራተኛ የነበረን አንድ ሰው “የፋኖ አባል ነው” በማለት በቁጥጥር ሥር ለማዋል ሙከራ ማድረጋቸውን ተከትሎ፤ በከተማው ከሚገኙ ወጣቶች ጋር ግጭት ተፈጥሮ ነበር፡፡” ብለዋል፡፡ @አክለውም፤ መከላከያ ሠራዊት አባላት “የፋኖ አባል ነው” ብለው የጠረጠሩትን ግለሰብ በከተማው አቅራቢያ ወደሚገኝ የመከላከያ ካምፕ በሚወሰዱበት ወቅት፤ የከተማዋ ወጣቶች ከመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ ደንጋይ መወርወራቸውን ገልጸው፣ የቆሰሉ የሠራዊቱ አባላት መኖራቸውንም ተናግረዋል። @ይህን ተከትሎም የመከላከያ ሠራዊት አባላቱ በተኮሱት ጥይት ኹለት ሰዎች መገደላቸውን ጠቅሰው፤ ከስድስት በላይ ወጣቶች ቆስለው አራቱ ወደ ባህርዳር ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸውን ገልጸዋል፡፡ @በአሁኑ ወቅት የፋኖ ታጣቂዎች በቦረና ሳይት ብሔራዊ ፓርክ መሽገው እንደሚገኙና በነዋሪዎች ዘንድ ሌላ ግጭት ሊፈጠር ይችላል የሚል ስጋት መኖሩን ያነሱት ቡድን መሪው፤ አሁን ላይ ግን አንጻራዊ ሰላም መኖሩን ጠቁመዋል። @በተመሳሳይ ባለፈው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን በወገዲ ወረዳ በመከላከያ ሠራዊት አባላትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ተኩስ ተከፈቶ እንደነበር ገልጸው፤ በዚያም አንዳንድ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ተዘግተው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ @እንዲሁም በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ አግሪት ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ሰኞ ሐምሌ 17/2015 ምሽት አንድ ሰዓት አካባቢ በመከላከያ ሠራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ወጊያ ሲካሄድ ማደሩንና ስድስት የሚሊሻ አባላት መገደላቸውን ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል፡፡ @ሆኖም ከተደረገው ውጊያ በኋላ በወረዳው እና አካባቢው በርካታ የመከላከያ ሠራዊት አባላት መግባታቸው ተጠቁሟል። @በአማራ ክልል “መንግሥት በኃይል ለማውረድ የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ኃይሎች አሉ” በሚል፤ የፌደራል መንግሥቱ እና የክልሉ አስተዳደር ለወራት የዘለቀ የሕግ ማስከበር ዘመቻ እያካሄዱ ይገኛል። አዲስ ማለዳ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#የሆሮ ጉዱሩ ሀገረስብከት ምእመናን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ውሳኔን እንደማይቀበሉ ገለፁ!!! @ምእመናን በሲኖዶሱ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ አሰምተዋል። @እኛ የምናውቀው በኦ
+1
#የሆሮ ጉዱሩ ሀገረስብከት ምእመናን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ውሳኔን እንደማይቀበሉ ገለፁ!!! @ምእመናን በሲኖዶሱ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ አሰምተዋል። @እኛ የምናውቀው በኦሮሚያና በብሄሮች ብሄረሰቦች የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ የተሾሙትን አቡነ ሚናስ ነው ያሉት ምእመናኑ፣ የኢትዮጵያ ሲኖዶስ የምእመናንን ጥያቄና ፊላጎት ማክበር እንዳለበት አሳስበዋል። @የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስና ጠቅላይ ቤተክህነት ከምእመናን፣ ከሀገረስከቶችና ከኦሮሚያ አህጉረስብከት ጋር በትብብር ካልሰሩና አሁን በያዙት በእኔ አውቅልሃለሁ መንገድ ከቀጠሉ አንዳች ውሳኔያቸው በኦሮሚያ ውስጥ ተፈፃሚ ሊሆን እንደማይችል ሊረዱ ይገባል ብሏል። @ከምእመናንና ከኦሮሚያ አህጉረስብከት ጋር እልህ መጋባት ነባሩን ሲኖዶስና ጠቅላይ ቤተክህነቱን ነው ዋጋ የሚያስከፍለው ሲሉ አሳስበዋል። @ይህ በእንዲህ እንዳለ የሆሮ ጉዱሩ ሀገረስብከት ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ ሲኖዶስ የህዝቡን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ወደ ጎን መተውን ነው የገለፀው። @የህዝቡን ጥያቄ በተፃረረ መልኩ ነበሩ ሲኖዶስ የሚያስተላልፈውን ውሳኔ አጥብቆ እንደሚቃወም አስታውቋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ "ለትኩረት" ሲባል አራት ኮሌጆችን ሊዘጋ ነው መባሉን መምህራን ተቃወሙ!!! @ትምህርት ሚንስቴር ዩኒቨርሲቲው "በትኩረትና ተልዕኮ" ልየታው መዝጋት "መብቱ" ነው ብሏል። @ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ቀጣይ የትኩረቴ አቅጣጫ አይደሉም ያላቸውን አራት ኮሌጆች ሊዘጋ ነው ሲሉ መምህራን አቤቱታ አቅርበዋል። @የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች እጣፋንታ ምን ይሆናል? የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 40 በመቶ ብቻ ማለፋቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ ዩኒቨርስቲው ሰኔ መጨረሻ ላይ በስብሰባ አሳውቆናል ያሉት መምህራን "በልየታ እና በልህቀት ማዕከል" ያልተካተቱ ናቸው ያላቸውን ማህበራዊ፣ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ፣ ህግና የስነ ትምህርት ኮላጆችን ሊዘጋ ነው ብለዋል። @መምህራኑ ዩኒቨርሲቲው ለዓመታት ያስተማራቸውንና ሀብቱን ያፈሰሰባቸውን አማርኛ ቋንቋን ጨምሮ ከባህል እና ከሀገር በቀል እውቀቶች ጋር የተያያዙ 18 ትምህርት ክፍሎችን ሊዘጋ ነው በማለት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። @ዩኒቨርሲቲው ሲከፈት የተጀመሩ ትምህርቶችና በሰው ኃይል የደረጁ የትምህርት ክፍሎች መዘጋታቸው አሳዝኖናል ብለዋል። @በእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል የስነ-ጽሁፍ መምህር የሆኑት መዘምር ግርማ፤ የዩንቨርስቲው "የልህቀት ማዕከል" ለመሆን አያስፈልጉም ያላቸውን፤ ነገር ግን 32 ፕሮግራም ያላቸውን የትምህርት ክፍሎች ለመዝጋት መወሰኑን "አምባገነን" ብለውታል። @ዩኒቨርሲቲው ባለፉት ሦስት ዓመታት በእነዚህ ትምህርት ክፍሎች ተማሪዎችን ላለመቀበል ውስጥ ውስጡን ሰርቷል ሲሉ የሚከሱት መምህሩ፤ የዩኒቨርሲቲው አሻራ እየጠፋ ነው ብለዋል። @ይዘጋሉ ከተባሉ ፕሮግራሞች አንዱ እስከ ሶስተኛ ዲግሪ (ፒ.ኤች.ዲ) ድረስ የሚያስተምረው የዘርዓ ያቆብ የመካከለኛው ዘመን ጥናት ማዕከል እንደሚገኝበት መዘምር ግርማ ለአል ዐይን ተናግረዋል። @ከዚህ በተጨማሪም በየዓመቱ ጉባኤ የሚያካሂደው ባህል ማዕከሉም ደጆቹ ከሚዘጉ የደብረ ብርሀን ዩኒቨርስቲ ተቋማት መሀል ሆኗል። @ዩኒቨርሲቲዎች ከሚቋቁሙበት ሦስት ዓላማ ውስጥ ጥናትና ምርምርና የማህበረሰብ ግልጋሎት የመስጠት ኃላፊነቱን ደብረ ብርሀን ዩኒቨርስቲ መዘንጋቱን ያሳያል ይላሉ። @ቢዚህ የሚስማሙትና ሌላው አል ዐይን ያነጋገራቸው የዩንቨርስቲው መምህር ዶ/ር አዲሱ ኃይሉ እርምጃው ዛሬ እንደቀላል ቢታይም ነገ ዋጋ የሚያስከፍል ነው ባይ ናቸው። @ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ የልህቀት ማዕከል መሆኑን እንደማይቃወሙ የሚገልጹት መምህሩ፤ ሆኖም አካሄድና አሰራሩ ግን ቆም ተብሎ መታየት እንደሚገባው ተንግረዋል። @"የልህቀት ማዕከል መሆን ማለት ሌላውን መዝጋት ሳይሆን ቅድሚያ መስጠት ማለት ነው። አካባቢዬን፤ አቅሜን አይቼ ያዋጣኛል የምለውን መንገድ ስሄድ ሌላውን መዝጋት ሳይሆን፤ ሌላውንም አቅፎ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ይኖራሉ ማለት ነው" በማለት ውሳኔውን “የማይዋጥ” ብለውታል። @ዩኒቨርሲቲው "በልየታ እና በልህቀት ማዕከል" የመረጣቸው ዘርፎች ቢዝነስ፣ ጤናና ግብርና መሆናቸው ተነግሯል። እነዚህ ዘርፎች አካባቢውን ያላጤኑና በዩኒቨርሲቲው አነስተኛ የሰው ኃይል ያላቸው ናቸው የሚሉት ዶ/ር አዲሱ፤ የዩኒቨርሲቲውን አቅምና ታሪካዊ ዳራ ከግምት ውስጥ ያላስገባ ነው ብለዋል። @በመቶዎች የሚቆጠሩ መምህራን እጣ ፈንታ ደጃቸውን ከሚዘጉ የትምህርት ክፍሎች ጋር የተሳሰረ ነው።የደብረ ብርሀን ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ተዘጉ የተባሉ ኮሌጆችን ተጠይቀው "ውሸት" ነው ብለዋል። @አራት ኮሌጅ ዘግተንም አናውቅም፤ አላሰብንም ውሸት ነው፤ አልሆነም” ሲሉ የመምህራኑን ቅሬታ አስተባብለዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#አሩሷደሮች መንግስት ማዳበሪያ በጊዜው አላቀረበም እህል መዝሪያ ጊዜው እያለፈብን ነው "ሚሰማን ካለ ብለው" መንገድ መዝጋታቸው ተነገረ!!! @በሶሮ ወረዳ የወሼባ ቀበሌ "አሩሷደሮች በአፈር ማዳበሪያ
#አሩሷደሮች መንግስት ማዳበሪያ በጊዜው አላቀረበም እህል መዝሪያ ጊዜው እያለፈብን ነው "ሚሰማን ካለ ብለው" መንገድ መዝጋታቸው ተነገረ!!! @በሶሮ ወረዳ የወሼባ ቀበሌ "አሩሷደሮች በአፈር ማዳበሪያ በጊዜ አለመድረስ በተቀሰቀሰ ቁጣ የመኪና መንገድ ዘግተው በሠላማዊ መንገድ የሚሰማን ካለ መጥቶ ሳያወያየን አንድንም ተሽከርካሪ አናሳልፍም ብለዋል። @ከጧዋት እስካሁን በሁለቱም አቅጣጫ የሚመጡ መኪናዎችና ተሳፋሪዎች በመንገድ መዘጋት ምክንያት ወደተነሱበትም ይሁን ወደምደርሱበት መመለስ አልቻሉም። @አሩሷደሮቹ" ማወያየትና መፍትሔ የሚሰጥ አካል አስቸኳይ መፍትሔ ልሰጥ ይገባል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ይህ ማዳበሪያ ለጠየቀ "አርሶ አደር ከመንግሥት የተሰጠ "የሀይል ምላሽ ነው!!! @በዛሬው እለት ማዳበሪያ ሳናገኝ የዘር ወቅት እያለፈብን ነው፣ መሬታችን ጦሙን ሊያድር ነው ብሎ አቤቱታ ለማቅረብ ወ
+1
#ይህ ማዳበሪያ ለጠየቀ "አርሶ አደር ከመንግሥት የተሰጠ "የሀይል ምላሽ ነው!!! @በዛሬው እለት ማዳበሪያ ሳናገኝ የዘር ወቅት እያለፈብን ነው፣ መሬታችን ጦሙን ሊያድር ነው ብሎ አቤቱታ ለማቅረብ ወደ ሀድያ ዞን አስተዳደር የመጡ አርሶ አደሮች "በፓሊስ" ተደብድበው በጥይት ከተበተኑ በኋላ የተወሰኑት "ማዳበሪያ የጠየቁት ገበሬወች" በፓሊስ መታሰራቸው ተሰምቷል። #ፍትህ_ለሀዲያ_ዞን_አርሶ_አደሮች! *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ሳይረፍድ መላ" ካልተበጀለት የአምሳ ብር ሱስ የአንድ ወንድማችን ነፍስ ብቻ ሳይሆን ሀገር ያጠፋል!!! @ከስር የምያዩት የ50 ብር እጥፋት በየመንገዱ ለትራፊክ ፖሊሶች የሚሰጥ ሲሆን ሹፌር ወይም የመኪናው ረዳት ጉዞ ከመጀመሩ በፊት ለትራፊክ ፖሊሶች የሚሰጡ ገንዘቦችን አንዲህ ማዘጋጀት ይጠበቅበታል። @በአካባቢው የትራንስፖርት አገልግሎት ከሚሰጡ አሽከርካሪዎች ባሰባሰብነው መረጃ አንድ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከአዲስ አበባ እስከ ወልቂጤ ወይም ከአዲስ አበባ እስከ ቡታጅራ ባለው መንገድ ብቻ በአማካይ እስከ 500 መቶ ብር በበዓል ወቅት ደግሞ ከ800 እስከ 1000 ብር ይሰጣል። @በዚህ መስመር ምን ያከል ተሽከርካሪ እንደሚመላለስ ሲታሰብ የሌብነቱ ተግባር እጅግ የገነገነ መሆኑን ያሳያል። @ሹፌሮች በሰጡት 50 ብር ትርፍ መጫን፣ ያለ ስምሪት ፍቃድ መንቀሳቀስ እና መሰል ህገ ወጥ ተግባራት በትራፊኮቹ እንዳላየ ይታለፋሉ። @በእርግጥ ሹፌሮች ህግ ባይተላለፋ እንኳን እቁብ መጣል ወይም ነገ ሲያጠፋ ይቅር እንዲባሉ እጅ መንሻ መስጠታቸው አይቀርም። @አስገራሚው ነገር ይህ ገንዘብ ሹፌሮች ከኪሳቸው የሚያወጡት ሳይሆን ከታሪፍ በላይ በተሳፋሪው ላይ የሚጣል እዳም ነው። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+1