en
Feedback
Shien ekawuch

Shien ekawuch

Open in Telegram
869
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1230 days
Posts Archive
#አሳዛኝ ዜና!!! @ኢትዮጵያዊው ታዳጊ ለውድድር በሄደበት አገር ውሀ ገንዳ ውስጥ ሰጥሞ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። @በ1975 በተመሰረተው ጎቲያ ካፕ በመላው አለም የሚገኙ ከ35 ሺ በላይ ታዳጊዎች ይ
#አሳዛኝ ዜና!!! @ኢትዮጵያዊው ታዳጊ ለውድድር በሄደበት አገር ውሀ ገንዳ ውስጥ ሰጥሞ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። @በ1975 በተመሰረተው ጎቲያ ካፕ በመላው አለም የሚገኙ ከ35 ሺ በላይ ታዳጊዎች ይሳተፋሉ። በዚህ ስዊድን ጉተንበርግ ላይ በተደረገው ውድድር ላይ ከተጓዙት ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች መካከል አንዱ የ15 አመቱ ቅዱስ ነው። @በኡሌቪ ስቴዲየም መክፈቻው ስነስርአት ላይ ከቡድኑ ጋር ሰልፍ ላይ ነበር ። ዱባይ ውስጥ ነሀሴ ላይ በአንድ አካዳሚ የሙከራ እድልም አግኝቶ ለመጓዝ ዝግጅት ላይ ነበር ። @በትምህርቱ ጎበዝ እንደነበር እና የጠፈር ሳይንቲስት መሆን እንደሚፈልግ ይናገራል። ይሁን እንጅ ህልሙ ሳይሳካ በአጭር ተቀጨ። @ይህ ታዳጊ ባረፈበት ሆቴል ከጓደኞቹ ጋር ዋና እየዋየ እያለ ሰምጦ ህይወቱ አልፏል። ከመስመጡ በፊት በወቅቱ ማንም አላስተዋለውም ነበር። ዘግይቶ ግን አንዲት ሴት በሰጠችው ጥቆማ ነፍስ አድን ሰራተኞች ወደ ገንዳው ከነልብሳቸው ቢገቡም ህይወቱን ማትረፍ ሳይቻል ቀርቷል። @የኢትዮጵያ ቡድን ውድድሩን ሳያጠናቅቅ የቅዱስን አስከሬን ይዞ ተመልሷል ታናሽ ወንድሙ እስካሁን ከድንጋጤ አልነቃም ሆስፒታል ውስጥ ተኝቶ ይገኛል። ለቤተሰቦቹ መፅናናትን እንመኛለን። *ትርታ ስፖርት *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#በኒጀር መፈንቅለ መንግስት ደጋፊዎች “ረጅም እድሜ ለፑቲን” የሚሉ መፈክሮችን ማሰማታቸው ተነገረ!!! @ደጋፊዎቹ ሩሲያንና መሪዋን ሲያወድሱ የቀድሞ የኒጀር ቀኝ ገዢ ፈረንሳይ ውድመትን የሚመኙ መፈክሮች አሰምተዋል። @በኒጀር ባሳለፍነው ሳምንት የተፈፀመውን መፈንቅለ መንግስት የደገፉ የሀገሪቱ ዜጎች ባካሄዱት የድጋፍ ሰልፎች ላይ ሩሲያን የሚያወድሱ መፈክሮችን ሲያሰሙ ተስተውሏል። @በቅጽል ስሟ የዩራኒየም ምድር በመባል እምትታወቀው ምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ኒጀር ከሰሞኑ መፈንቅለ መንግሥት ተፈጽሞባታል።የፕሬዝዳንቱ ጠባቂዎች ፕሬዝዳንት መሀመድ ባዙም በቤተ መንግስታቸው እንዳሉ እንዳይንቀሳቀሱ ታግተዋል። @ጠባቂዎቹ ከእገታው በኋላ በፕሬዝዳንት ባዙም የሚመራው መንግሥት መፍረሱን እና ጀነራል ቲያኒ የሀገሪቱ ሙሪ መሆናቸውን በሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። @የዋግነሩ አዛዥ ፕሪጎዥን የኒጀርን መፈንቅለ መንግሥት አወደሱ የኒጀር ወታደሮች መፈንቅለ መንግስት ማካሄዳቸውን አወጁ ይህንን ተከትሎም በሀገሪቱ የተለያዩ የድጋፍ እና የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች እየተስተዋሉ ሲሆን፤ በትናትናው እለትም በሺዎች የሚቆጠሩ የመፈንቅለ መንግስቱ ደጋፊዎች ጫና እያደረገች ነው በሏት የቀድሞ የኒጀር ቅኝ ገዢ ፈረንሳይ ኤምባሲ ፊትለፊት ተሰብስበው ቁጣቸውን ገልጸዋል። @አንዳንድ ተቃዋሚዎች በኒጀር የፈረንሳይ ኤምባሲ ታፔላዎችን በመሰባበር ከረገጡ በኋላ በሩሲያ እና በኒጀር ባንዲራ በስፍራው ተክተዋል። @በሰልፈኞቹ መካከል “ረጅም እድሜ ለፑቲን፣ ሩሲያ ለዘላለም ትኑር” የሚሉ መፈክሮች የተሰሙ ሲሆን፤ ውድመት ለፈረንሳይ የሚሉ ድምጾችም ተሰምተዋል። የሩሲያው ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድን ዋግነር አዛዥ የሆኑት የቨግኒ ፕሪጎዚን መፈንቅለ መንግስቱን ተከትሎ የኒጀትን ወታደሮች ማድነቃቸው ይታወሳል። @የቨግኒ በድምጽ ባሰራጨው መግለጫ "የኒጀር ወታደሮች ያደረጉት ነገር ህዝብ በቅኝ ገዢዎች ላይ እያደረጉት ያለን ትግል ማገዝ ነው" ብለዋል። @ይሁን እንጂ የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ የተለያዩ የዓለም ሀገራ መንግስታት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት በኒጀር የተፈጸመውን መፈንቅለ መንግስት በመቃወም ላይ ይገኛሉ። @የአፍሪካ ህብረት የኒጀር ጁንታ በ15 ቀናት ውስጥ ፕሬዝዳንት ሞሀመድ ባዙምን ወደ ስልጣናቸው እንዲመልስ ያሳሰበ ሲሆን፤ ይህን ተፈጻሚ ካልሆነ ግን የመንግስት ግልበጣውን ባደረጉት ወታደራዊ መሪዎች ላይ “ጠንካራ ማዕቀብ” እንደሚጥል ነው ያስጠነቀቀው። @ለፕሬዝዳንት ባዙም ድጋፋቸውን የገለጹት አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረትም የመንግስት ግልበጣውን ባደረጉት ወታደራዊ መሪዎች ላይ ማዕቀብ ለመጣል መዘጋጀታቸውን ዩሮ ኒውስ አስነብቧል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#በትግራይ ክልል "ኤጲስ ቆጶሳት አቀባበል ስነ ስርአት "በዎና ከተማዎ "መቀለ መደረጉ ተነገረ!!! @የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክረስትያን መንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በመቐለ ህዝብ ደማቅ አቀ
+3
#በትግራይ ክልል "ኤጲስ ቆጶሳት አቀባበል ስነ ስርአት "በዎና ከተማዎ "መቀለ መደረጉ ተነገረ!!! @የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክረስትያን መንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በመቐለ ህዝብ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው ሲል የክልሉ ቴሌቪዢን ዘግቧል፡፡ @በትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክረስትያን መንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ኣዲስ ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት በመቐለ ከተማ ደብረ ገነት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስትያን ሲደርሱ በመቐለ ህዝብ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ብሏል፡፡ @የቅዱስ ፍሬሚናጦስ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ ብፁእ አቡነ ዮሃንስ እንዲሁም የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክረስትያን መንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ዋና ፀሓፊ አቡነ አረጋዊ እና ሌሎች የሀይማኖት አባቶች በአቀባበል ስነ ስርአቱ ላይ ተገኝተዋል "ሲል የክልሉ ቴሌቪዢን ዘግቧል፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#በፓኪስታን የፖለቲካ ሰልፍ ላይ በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት ቢያንስ "44 ሰዎች መገደላቸው ተነገረ!!! @በሰሜን ምዕራባዊ ፓኪስታን በነበረ የፖለቲካ ሰልፍ ላይ በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት ቢያንስ 44 ሰዎች ሲገደሉ 200 የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል ሲሉ የፓኪስታን መንግስት ባለስልጣናት ገልጸዋል። @ፍንዳታው የደረሰው በትላንትናው እለት ወግ አጥባቂው ጃሚያ ፓርቲ ፓኪስታንን ከአፍጋኒስታን ጋር በሚያዋስናት ድንበር አካባቢ በሚገንው ጃውር አውራጃ ላይ በነበረ የፖለቲካ ሰልፍ ነው። @ለጥቃቱ ወዲያው ኃላፊነቱን የወሰደ አካል የለም።የክልሉ ፖሊስ በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው አጥፍቶ ጠፊው በርካታ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች በተቀመጡበት መድረክ አካባቢ ያጠመደው ፈንጂ እንዳፈነዳው ገልጿል። @የመጀመርያ ምርመራዎች እንዳሳዩት ከሆና የአይኤስ ቡድን ከጥቃቱ ጀርባ ሊኖር እንደሚችል እና የፖሊስ መኮንኖች አሁንም ምርመራ ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል። @የታጠቀው ቡድን አይኤስ የፕሬዚዳንት አሽራፍ ጋኒ መንግስት ከወደቀ በኋላ በጎረቤት አፍጋኒስታን ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። የአፍጋኒስታን የታሊባን አስተዳደርን የሚቃወም ሲሆን ተራራማ ድንበር አቋርጠው በፔሻዋር አካባቢ በመደበቅ የሚታወቁ አባላት አሉት። @የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ የፓኪስታን መንግስት ባለስልጣናት እንደተናገሩት ጉዳት ከደረሰባቸው ሰዎች መካከል 15ቱ በአስጊ ሁኔታ ውስጥ ስለሚገኙ የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊጨምር እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። @ከጥቃቱ በስተጀርባ ያለው ዓላማ እስካሁን ግልጽ አይደለም.።የጸጥታ ሃይሎች አካባቢውን ከበው የፍንዳታው ምርመራ ማካሄዳቸውን ግን ቀጥለዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#የሐዘን መግለጫ!!! @የሞቱ ሰዎች ቁጥር 18 ደርሷል በምስራቅ መስቃን ወረዳ በተፈፀመ ጥቃት የደረሰው ጉዳት አስመልክቶ ከጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትህ ፓርቲ "የተሰጠ የሐዘን መግለጫ። @አንፃራዊ ሰላም አግኝቶ በነበረው የምስራቅ መስቃን‐ማረቆ አካባቢ ዳግመኛ ግጭት አገርሽቶ ባለፉት ጥቂት ቀናት ተከታታይ የህይወት፣ የአካል እና የንብረት ጉዳት ደርሷል። @ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በበቼ ቀበሌ 2 ተማሪዎች ጨምሮ 4 ሰዎች፤ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ.ም በእንሴኖ ኡስሜ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጋሮሬ ተብሎ በሚጠራ መንደር 2 ሰዎች፤ አርብ ሐምሌ 14 ቀን 2015 ዓ.ም. 1 ሰው፤ ሐምሌ 16 ቀን 2015 ዓ.ም 1 ሰው፣ እንዲሁም ቅዳሜ ሐምሌ 22 ቀን 2015 ዓ.ም በዲዳ ቀበሌ ገበያ በሚሄዱ ሰዎች ላይ በተከፈተ የተኩስ እሩምታ 8 ሰዎች ተገለዋል፡፡ @በነዚህ ጥቂት ቀናት ብቻ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 18 ደርሷል፡፡ በብዙ ሰዎች ላይ የአካል እና ንብረት ጉዳትም ደርሷል። @ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትህ ፓርቲ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው የሞት፣ የአካል እና ንብረት ጉዳት የተሰማው ጥልቅ ሐዘን ይገልፃል። አካባቢው ለአመታት በዘለቀ ግጭት ሲታመስ ቆይቶ በቅርቡ በተደረገ ዕርቅ የሰላም አየር መተንፈስ ጀምሮ የነበረ ሲሆን ከቅርብ ሳምንታት ጀምሮ በጦር መሳሪያ የታገዙ ግድያዎች እየተበራከቱ መጥተው አካባቢውን ወደለየለት ማህበረሰባዊ ግጭት እንዳያስገቡት ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። @ጉዳዩን የበለጠ አሳሳቢ የሚያደርገው ይህ ሁሉ ሲሆን የደቡብ ክልል አስተዳደር፣ የጉራጌ ዞንም ሆነ የሁለቱ ወረዳ አስተዳደሮች ስለ ጉዳዩ ምንም አለማለታቸው ነው። ክስተቱ ህዝባችን ምን ያህል ተጋላጭ እና መሪ አልባ እንደሆነ ያመላከተ ጉዳይ ነው ብለን እናምናለን። በመሆኑም: ‐ @በጉራጌ ዞን በተለይም በምስራቅ መስቃን ወረዳ እና አካባቢው እየተፈጠሩ ስላሉ ግጭቶች እና በዚህ ሳቢያ በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ እየደረሰ ስላለው ጉዳት፣ ስለ ግጭቱ መነሻ እና እየተወሰዱ ስላሉ የእርምት እርምጃዎች በየ ደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካላት ግልፅ ማብራሪያ እንዲሰጡ፤ @የህዝብን ደህንነት ማስጠበቅ የመንግስት ቀዳሚ ተግባር ሆኖ ሳለ ይህንን ኃላፊነታቸው መወጣት ተስኗቸው ለዜጎች ህይወት፣አካል እና ንብረት መጥፋት ምክንያት በሆኑ የፀጥታ እና የአስተዳደር አመራሮች ላይ አፋጣኝ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፣ @በግጭቱ ተዋናይ የሆኑ ወገኖች በአስቸኳይ በህግ ጥላ ስር ውለው አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድባቸው @ችግሩ ወደ ከፋ ደረጃ ከመድረሱ በፊት በአካባቢው በቂ ቁጥር ያለው እና ገለልተኛ የፀጥታ ኃይል እንዲሰፍር እንጠይቃለን። @በመጨረሻም በጉራጌ ዞን የተለያዩ ቦታዎች ግጭት ለመቀስቀስ የሚደረገው ጥረት ህዝቡን በፀጥታ ስጋት ውስጥ በመክተት የጉራጌን ህዝብ የክልል አደረጃጀት ጥያቄ ለመቀልበስ የሚደረግ ጥረት አካል እንደሆነ እንገነዘባለን። በመሆኑም ይህ ኃላፊነት የጎደለው ሴራ በአስቸኳይ እንዲቆም እና የጉራጌ ህዝብ የክልል አደረጃጀት ጥያቄ በአስቸኳይ ተፈፃሚ እንዲሆን አጥብቀን እንጠይቃለን። *ጎጎት ለጉራጌ! *ጎጎት ለኢትዮጵያ! *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+3

#በአማራ ክልል" አንድ የስራ ሀላፊ" ከስልጣናቸው መባረራቸው ተነገረ!!! @የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ እንግዳው ጠገናው “ኃላፊነትዎን በአግባቡ አልተወጡም” በ
+1
#በአማራ ክልል" አንድ የስራ ሀላፊ" ከስልጣናቸው መባረራቸው ተነገረ!!! @የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ እንግዳው ጠገናው “ኃላፊነትዎን በአግባቡ አልተወጡም” በሚል ከስልጣናቸው ተባረዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ከወልቂጤ "ጅማ መንገድ የታጠቁ ኃይሎች በአሽከርካሪዎች ላይ ተደጋጋሚ ዝርፊያና አፈና" እየፈጸሙ ነው ተባለ!!! @ከወልቂጤ ወደ ጅማ በሚወስደው መንገድ ጊቤ ሸለቆ ውስጥ የታጠቁ ኃይሎች በተሽከርካሪ
#ከወልቂጤ "ጅማ መንገድ የታጠቁ ኃይሎች በአሽከርካሪዎች ላይ ተደጋጋሚ ዝርፊያና አፈና" እየፈጸሙ ነው ተባለ!!! @ከወልቂጤ ወደ ጅማ በሚወስደው መንገድ ጊቤ ሸለቆ ውስጥ የታጠቁ ኃይሎች በተሽከርካሪዎች ላይ ተደጋጋሚ ዝርፊያ እየፈጸሙ መሆኑን አሽከርካሪዎች ገልጸዋል። @በዚህም በጊቤ ወንዝ አካባቢ የፖሊስ ልብስ ለብሰው የሚንቀሰቀሱ ኃይሎች፤ በተለይ በምሽት የሚያሽከረክሩ ሹፌሮችን በማሰቆም ገንዘብ አምጡ እንደሚሉና ገንዘብ አንሰጥም የሚሉ ሹፌሮችን የመኪናቸውን መስታወት እንደሚሰብሩ ነው የተናገሩት። አዲስ ማለዳ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የኢቲዮጵያ መንግስት ከሁለት ዓመታት በኋላ በጥራት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው በመንግስት በኩል "የኮንዶም" ምርትን ወደ ሀገር ውስጥ የማስገበት ሥራ ዳግም መጀመሩን አስታወቀ!!! @በጥራት ምክንያት በጤና ሚኒስቴር እና በኤችአይቪ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት መካከል የነበረው አለመግባባት ከአዲስ አቅራቢ ግዢ እንዲፈጸም በመስማማት በመፈታቱ ነው ግዢው የታዘዘው። @በዚህም፥ ከ55 ሚሊዮን በላይ ኮንዶም እየተጓጓዘ ሲሆን ሌሎች 33 ሚሊዮን የሚሆኑት የመጋዘን እና የትራንስፖርት ወጪን ሳይጨምር እያንዳንዳቸው በሶስት የአሜሪካን ሳንቲም ብቻ እየተገዙ ይገኛሉ። @በኢትዮጵያ በዓመት 248 ሚሊዮን ኮንዶም የሚያስፈልግ ሲሆን ነገር ግን ባለፈው ዓመት ወደ ሀገር የገባው የኮንዶም መጠን 80 ሚሊዮን ብቻ ነው። @ኮንዶም ወደ ኢትዮጵያ የሚገባው በሦስት መንገድ ሲሆን አንዱ መንግስት ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች በነጻ ለማከፋፈል የሚያስገባው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ እንደ ዲኬቲ ያሉ የለጋሽ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግላቸው የሚያስገቡበት መንገድ ሲሆን ሦስተኛው የግሉ ዘርፍ ለትርፍ የሚያስገባበት መንገድ ነው። @ከዚህ ውስጥ መንግስት 30 በመቶ የሚሆነውን አቅርቦት የሚሸፍን ሲሆን ቀሪው በሌሎቹ ይሸፈናል። ላለፉት ሁለት ዓመታት መንግስት ይህንን ሥርጭት ማቋረጡን ተከትሎና ሌሎች ምክንያቶች ተጨማምረው ሦስት ፍሬ ኮንዶም 30 ብር ይሸጥ ነበር። ይህም ከቅርብ ዓመታት በፊት 3 ብር በነበረ ኮንዶም ላይ የ 10% ጭማሪ በገቢያው ተስተውሏል። @በኢትዮጵያ የኮንዶም ፋብሪካ መትከል በመፍትሔነት ተቀምጧል! @የጤና ሚኒስቴር እና የኤችአይቪ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት በጋራ ኮንዶም ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባበትንና የሚከፋፈልበትን ሁኔታ ለመከታተል የሚያስችል አዲስ አሰራር ለመንደፍ አላማ አድርገው ጥናት አካሂደው ነበር። @በዚህም፥ ለጉዳዩ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት መንግስት እና የእርዳታ ድርጅቶች አጋሮችን በማፈላለግና በማስተባበር በኢትዮጵያ የኮንዶም ፋብሪካ ማቋቋም የሚል ድምዳሜ ተቀምጧል። @በኢትዮጵያ ኮንዶም ማምረት አዋጭ ነው? @የዲኬቲ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ዳይሬክተር መሀመድ ዳዋር በኢትዮጵያ ኮንዶም ማምረት አዋጭ መሆኑን የሚገልጹ ሲሆን ሆኖም የጥሬ እቃ አቅርቦቱ በሀገር ውስጥ በስፋት መኖሩ መታወቅ አለበት ይላሉ። @አክለውም፥ የወሊድ መከላከያ ምርቶች አቅራቢ የሆነው DKT በየዓመቱ ከ30-40 ሚሊዮን ኮንዶም ለኢትዮጵያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ፋብሪካው በኢትዮጵያ ቢቋቋም የለጋሾችን ገንዘብ ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመጠቀም እንደሚያስችልም ነው ሀሳባቸውን የሰጡት። (ዘገባው የሪፖርተር ነው) *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+2

#አሳዛኝ "የመኪና አደጋ ለፈተና ሲሄዱ በነበሩ የ12ተኛ ክፍል ተማሪወች ላይ ደረሰ!!! @በአደጋው 6 ተማሪዎች ከባድ ጉዳት፤ ከ9 ያላነሱ ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል " ፦ ፖሊስ!!። @የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከደብረ ወርቅ ወደ ደብረ ማርቆስ ዩንቨርስቲ ሲጓዙ በደረሰባቸው አደጋ ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። @አደጋው የደረሠው ዛሬ ሐምሌ 23/2015 ዓ/ም ከጥዋቱ 4:30 በምስራቅ ጎጃም ዞን አነደድ ወረዳ አምበር ዙሪያ ቀበሌ ልዩ ቦታው " ዚባ " አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ላይ ነው። @አደጋ የደረሰበት ከደብረ ወርቅ ከተማ ተነስቶ ወደ ደብረ ማርቆስ ሲጓዝ የነበረ " አባዱላ ሚኒባስ ኮድ 3-አማ 14062 " ሲሆን ወንዙ ውስጥ በመግባቱ ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሷል። @እንደ አነደድ ፖሊስ መረጃ ስድስት ሠዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል ተልከዋል። @ሌሎች ከዘጠኝ ያላነሱ የደረሰባቸው ጉዳት ቀላል በመሆኑ አምበር ጤና ጣቢያ ተረድተው ወደፈተና ቦታው ሄደዋል። @የደረሰውን አደጋ በተመለከተ በፍጥነት አደጋ መርማሪ ፓሊሶች ከቦታው ደርሰው የአደጋውን መንስኤ እያጣሩ መሆኑ የአነደድ ወረዳ ፓሊስ አሳውቋል። *መረጃው ፦ ከአነደድ ወረዳ ፖሊስ የተገኘ ነው። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+3

#የአማራ ፋኖ በጎጃም ጥምረት ፈጥረናል አሉ!!! @በዛሬው ዕለት 23/11/15 ዓ.ም በደጋ ዳሞት መናገሻ ከተማ ፈረስ ቤት ፋኖ በጎጃም ጥምረት ፈጥረናል ብለዎል። @ጥምረቱን የፈጠሩት፦ 1. የአማራ
+3
#የአማራ ፋኖ በጎጃም ጥምረት ፈጥረናል አሉ!!! @በዛሬው ዕለት 23/11/15 ዓ.ም በደጋ ዳሞት መናገሻ ከተማ ፈረስ ቤት ፋኖ በጎጃም ጥምረት ፈጥረናል ብለዎል። @ጥምረቱን የፈጠሩት፦ 1. የአማራ (ፋኖ) በደጋ ዳሞት! 2.የአማራ (ፋኖ) በደምበጫ! 3. የአማራ (ፋኖ) በማቻከል 4. የአማራ (ፋኖ) በጅጋ 5. የአማራ(ፋኖ) በፍኖተ ሰላም 6. የአማራ (ፋኖ) በባሕርዳር ሲሆኑ እያንዳንዳቸው ከ20 ፋኖ በላይ ተወካይ በመላክ ጥምረቱ ተፈጥሯል ብለዎል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#በምስራቅ ጎጃም ዞን "ተማሪወች ጭኖ ሲጓዝ የነበረ መኪና መገልበጡ ተነገረ!!! @በምስራቅ ጎጃም ዞን ከእናርጅ እናውጋ ወረዳና ከደብረ ወርቅ ከተማ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች
+2
#በምስራቅ ጎጃም ዞን "ተማሪወች ጭኖ ሲጓዝ የነበረ መኪና መገልበጡ ተነገረ!!! @በምስራቅ ጎጃም ዞን ከእናርጅ እናውጋ ወረዳና ከደብረ ወርቅ ከተማ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተና ወደ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ የፈተና ጣቢያ ሲጓዙ አንበር ከተማ አካባቢ በተፈጠረ የትራፊክ አዳጋ ከአንድ ሠው መጠነኛ ጉዳት በስተቀር በሌሎች ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩን ከአነደድ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጸ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ዩክሬን በሞስኮ የድሮን ጥቃት ፈጸመች "የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ "ጥቃት ለማድረስ የተላኩትን የዩክሬን ድሮኖች መትቶ መጣሉን ገልጿል!!! @የዩክሬን ሶስት ድሮኖች ዛሬ ማለዳ በሩሲያ መዲና ሞስኮ ጥቃት ለማድረስ መሞከራቸው ተገለጸ።በሁለት ህንጻዎች ላይም ቀላል ጉዳት መድረሱን የሞስኮ ከተማ ከቲባ ሰርጌ ሶብያኒን ተናግረዋል። @የድሮን ጥቃት ሙከራውን ተከትሎ ቭኑኮቭ የተሰኘው አውሮፕላን ማረፊያ በጊዜያዊነት መዘጋቱ ነው የተገለጸው።ኬቭ በሞስኮ ከተማ ላይ በአንድ ሳምንት ውስጥ ሶስተኛውን የድሮን ጥቃት ለማድረስ ሞክራለች።ጥቃቱን “የሽብር ጥቃት ሙከራ ነው” ያለው የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አንዷ ድሮን ተመታ መውደቋን አስታውቋል። @ሁለቱ ድሮኖች ደግሞ በሞስኮ የገበያ ማዕከል ላይ መውደቃቸውን ነው የገለጸው።ዩክሬን ባለፈው ሳምንት ሰኞ ወደ ሞስኮ ከላከቻቸው ሁለት ድሮኖች አንደኛው ከክሬምሊን በ3 ኪሎሜትር ርቀት ላይ መውደቁ ይታወሳል። @ሌላኛው ድሮንም በደቡባዊ የከተማዋ ክፍል የሚገኝ ረጅም ህንጻ ላይ ጉዳት ማድረሱን አሶሼትድ ፕረስ አስታውሷል። ኬቭ ለዛሬውም ሆነ ከዚህ ቀደም በሞስኮ ላይ ለፈጸመቻቸው የድሮን ጥቃት ሙከራዎች ሃላፊነቱን አልወሰደችም። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#ጋና ጥንቆላ" የሚያስከስስ ወንጀል መሆኑን የሚያስቀር "ህግ ልታጸድቅ መሆኑ ተነገረ!!! @ጥንቆላ ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት በተለይም በገጠሩ ማህበረሰብ ያልተለመደ ነገር ባይሆንም ሴትዮዋ ተደብደበው የተገደሉበት መንገድ ከፍተኛ የህዝብ ቁጣ አስከትሏል። @አፍሪካዊቷ ጋና ጥንቆላ በወንጀል የሚያስከስስ መሆኑን የሚያስቀር ህግ ልታጸድቅ ትችላለች ተብሏል።በታዋቂዋ የቡልጋሪያ ጠንቋይ ባባ ቫንጋ ትንበያ መሰረት በአዲሱ 2023 ዓመት ምን ሊከሰት ይችላል። @ባለፈው አርብ እለት የጋና ፖርላማ በጥንቆላ የተከሰሱ ሰዎችን ለመከላከል የሚያስችል ረቂቅ ህግ አጽድቋል። በሀገሪቱ በጥንቆላ የተሰማሩ ሰዎች ማህበሰሰባዊ መገለል እና ጥቃት ይደርስባቸዋል። @ይህ ረቂቅ ህግ የቀረበው በፈረንጆቹ 2020 በሳቫና ግዛት የ90 አመት አዛውንት ሴት በቡድን በመደብደባቸው እና ድርጊቱ በሀገሪቱ እና በአለም አቀፍ የመብት ተሟጋቾች በመወገዙ ምክንያት መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል። @ጥንቆላ ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት በተለይም በገጠሩ ማህበረሰብ ያልተለመደ ነገር ባይሆንም ሴትዮዋ ተደብደበው የተገደሉበት መንገድ ከፍተኛ የህዝብ ቁጣ አስከትሏል።ረቂቅ አዋጁ በማህበረሱ የተገለሉ ጠንቋዮች የሚኖሩበት መጠለያም እንዲፈርስ ያዛል። @500 የሚሆኑ በዋናነት ህጻናት በእድሜ የገፉ ሴቶች በሀገሪቱ ሰሜናዊ ግዛት በእንዲህ አይነት አምስት መጠለያዎች እንደሚኖሩ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት አድርጎ ነበር። @"አዲሱ ህግ አጥፊዎች የሚከሰሱበትን ተጎጅዎችን ወደ ማህበረሰቡ እና ወደ ቤተሰቦቻቸው የሚቀላቀሉበትን የህግ ማዕቀፍ ያዘጋጃል" ብለዋል በፖርላማው የህገመንግስት፣ የህግ እና የፖርላሜንታዊ ጉዳዮች ሊቀመንበር ክዋሜ አይማንዱ አንትቲዊ። @ህጉ ተግባራዊ እንዲሆን የጋናው ፕሬዝደንት ናኖ አኩፎ ማጽደቅ ይኖርባቸዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content