en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
#Update የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ ተጠናቆ ለበዓል አከባበር ሥርዓቱ ዝግጁ ሆነ። ከአንድ ወር በፊት የግንባታ ሥራው የተጀመረው የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ መጠናቀቁና ለጥምቀት በዓል ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል። በምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል የባህረ ጥምቀቱን ገንዳ በአዲስና ዘመናዊ መንገድ የመገንባት ፣ የኤሌክትሪክና የውኃ መስመር ዝርጋታ ሥራዎች እንዲሁም ቅጽረ ጊቢውን የማስዋብና ቡራኬ ማከናወኛ ስፍራዎችን የማስጌጥ ሥራዎች ተከናውነዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የጸበል መርጫ መስመሮች የተገጠሙ ሲሆን ብቃት ያላቸው የውኃ መሳቢያ ሞተሮች ገጠማም ተከናውኖ ዝግጁ መሆኑን የማረጋገጥ ሥራም ተከናውኗል። በአጠቃላይ የዘንድሮን የጥምቀት በዓልን በጥሩ ሁኔታ ለማክበር የሚያስችሉ የግንባታሥራዎች፣ የታቦታት ማረፊይያ ቦታዎች፣ የክብር እኝግዶች የሚስተናገዱባቸው ስቴጆችና የድምጽ ማጉያ መስመር ዝርጋታዎች ተከናውኗል። ቀሪ የግንባታ ሥራዎችና ይዞታውን የማስከበር ተግባራትም በዓሉ ከተከበረ በኋላ ተጠናክረው መቀጠል ይችሉ ዘንድ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ አሳውቋል። ቪድዮ : 25 MB (Wi-Fi ተጠቀሙ) @tikvahethiopia

#Somalia የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ በአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ጥቃት ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ገቡ። ዛሬ ጥዋት በሞቃዲሾ የአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ፍንዳታ መድረሱን ፖሊስ ሪፖርት አድርጓል። በአጥ
+1
#Somalia የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ በአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ጥቃት ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ገቡ። ዛሬ ጥዋት በሞቃዲሾ የአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ፍንዳታ መድረሱን ፖሊስ ሪፖርት አድርጓል። በአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቱ የቀድሞው ጋዜጠኛ እና የአሁን የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ መሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ተሽከርካሪ ኢላማ እንደተደረገ እና እሳቸው ላይም ጉዳት እንደደረሰባቸው ተሰምቷል። ቃልአቀባዩ በጥቃቱ ቆስለው ሞቃዲሾ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል እስካሁን የለም። @tikvahethiopia

#Alibaba #ErmiasAmelga የኢትዮጵያን የበይነ መረብ ግብይት ከሥሩ ይቀይራል ተብሎ የሚጠበቀው፣ የአሊባባና የአቶ ኤርሚያስ አመልጋ አዲስ ኩባንያ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ)፣ በሚ
+1
#Alibaba #ErmiasAmelga የኢትዮጵያን የበይነ መረብ ግብይት ከሥሩ ይቀይራል ተብሎ የሚጠበቀው፣ የአሊባባና የአቶ ኤርሚያስ አመልጋ አዲስ ኩባንያ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ)፣ በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ውስጥ ወደ ትግበራ ሊገባ መሆኑ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። በታዋቂው የቻይና ኩባንያ አሊባባ ባለቤት ጃክማና በኢትዮጵያዊው የቢዝነስ ሐሳብ አመንጪ አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ትብብር እየተቋቋመ ያለው አዲሱ የኢ-ኮሜርስ ቴክኖሎጂ ፣ ከሁለቱ የተውጣጣ ጥምር ስም እንደሚሰጠውም ታውቋል፡፡ ድርጅቱ በበይነ መረብ ቴክኖሎጂው ላይ ሁሉንም በኢትዮጵያ የሚገኙ የግብይት ምርቶች መገኛ ዋጋ የሚያሳውቅ መሆኑንና የበይነ መረብ ግዥ ትዕዛዝ፣ የዲጂታል ክፍያና የአቅርቦት አገልግሎትን ያስችላል ተብሏል፡፡ አዲሱ ድርጅት የአቅርቦት (Delivery) አገልግሎቱን ለ " እሺ " ኤክስፕረስ ለመስጠት ስምምነት ላይ መድረሱን ጋዜጣው አረጋግጫለሁ ብሏል። አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ፥ " ወደ ትግበራ ለመግባት ቀጣይ ስድስት ወራት ያስፈልጉናል ፣ በውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያትም የዘገዩብን ሥራዎች አሉ " ሲሉ መናገራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። @tikvahethiopia

#AU ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ኅብረት አባል ሀገራት መሪዎች ተስማምተው የኅብረቱ ጉባኤ በአዲስ አበባ እንዲደረግ በመወሰናቸው በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል። የኅብ
+1
#AU ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ኅብረት አባል ሀገራት መሪዎች ተስማምተው የኅብረቱ ጉባኤ በአዲስ አበባ እንዲደረግ በመወሰናቸው በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል። የኅብረቱን ጉባኤ በአካል በአዲስ አበባ ለማከናወን ያሳለፉትን ውሳኔ ኢትዮጵያ ታደንቃለች ብለዋል። ዶ/ር ዐቢይ ፥ " ወንድማዊ አጋርነታችሁን በምንሻበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ የኮሮናን መስፋፋትንና ወቅታዊውን የጸጥታ ሁኔታ እንደ ምክንያት በማንሣት የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ በአዲስ አበባ እንዳይካሄድ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበሩ አካላት ተግባራቸው ኢትዮጵያን አሳዝኖ ነበር " ብለዋል። አክለው ፥ " በዓመት ሁለት ጊዜ ከሚደረጉት የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤያት መካከል በኮሮና ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የመጀመሪያው ጉባኤ ከ3 ዓመት በኋላ ዳግም በአዲስ አበባ እንዲካሄድ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራትና ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ጋር በመሆን መንግስት ልዩ ልዩ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። " ሲሉ አስረድተዋል። ዶክተር ዐቢይ፥ " ጉባኤው እዚህ መካሄዱ የሚኖረውን ትርጉም የተገነዘቡና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያላትን ጠንካራ አቋም፣ ለአፍሪካ ኅብረት እውን መሆን ያበረከተችውን አስተዋጽኦ እና የአፍሪካ ጉዳዮች በአፍሪካውያን እንዲታዩ ያላትን የጸና መርሕ ከፍ ያለ ዋጋ የሰጡ የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤው በአዲስ አበባ መካሄዱን መርጠዋል። በዚህም ኢትዮጵያ ደስ ተሰኝታለች፤ እንኳን ደስ ያለን " ሲሉ ገልፀዋል። * ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia

መንግሥት ለአገር ሕልውናና ለሕዝብ ነጻነት የተጋደሉና ጀብድ የሠሩ ፋኖዎችን የበለጠ ያደራጃል እንጂ ትጥቅ አያስፈታም ሲሉ የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ተናገሩ፡፡
+1
መንግሥት ለአገር ሕልውናና ለሕዝብ ነጻነት የተጋደሉና ጀብድ የሠሩ ፋኖዎችን የበለጠ ያደራጃል እንጂ ትጥቅ አያስፈታም ሲሉ የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ተናገሩ፡፡ አቶ ግዛቸው ይህን የተናገሩት ለኢፕድ በሰጡት ቃለምልልስ ነው። አቶ ግዛቸው " በአማራ ሕዝብ ታሪክ ውስጥ የአማራን ሕዝብ ከጠላት የሚከላከል፣ ከውርደት የሚታደጉና በልማትና በፖለቲካው መስክ ተጠቃሚ እንዲሆን ዋጋ የሚከፍሉ ሁሉ ፋኖዎች ናቸው፤ በመሆኑም መንግሥት ለአገር ሕልውናና ለሕዝብ ነጻነት የተጋደሉና ጀብድ የሠሩ ፋኖዎችን የበለጠ ያደራጃል እንጂ ትጥቅ አያስፈታም " ብለዋል፡፡ ፋኖ የታጠቀ ኃይል በመሆኑ ክልሉ ላይ አደጋ በተቃጣ ጊዜ እንደማንኛውም ሰው በራሱ አደረጃጀት መሰረት ከሌላው የመንግሥት የፀጥታ ኃይል ጋር ተቀናጅቶ ጠላትን ይመክታል ብልዋል። አቶ ግዛቸው ፥ ፋኖ ሥርዓት የሚያከብርና ለአማራ ሕዝብ ጥቅም ራሱን መስዋዕት የሚያደርግ ነው፡፡ ሥርዓት አልበኛ የሆነ፣ ለመዝረፍ ለመስረቅና ሌላ ብጥብጥ ለማንሳት የሚንቀሳቀስ ኃይል ካለ ፋኖን የሚወክል ስላልሆነ የክልሉ መንግሥት በሕጉ መሰረት ሥርዓት እንደሚያስከብር ገልጸዋል፡፡ ፋኖ ከመንግሥት አቅም በላይ የሆነ ኃይል ሳይሆን ከመንግሥት ሥር ሆኖ እንደሌላው ማኅበረሰብ የሚዳኝ ነው ያሉት አቶ ግዛቸው ከዚህ ያፈነገጠና ሌላ ፍላጎት ያለው አካል ካለ በፋኖ ስም መጠራት የለበትም ብለዋል፡፡ የክልሉ መንግሥት ከፖለቲካ አመራሩ ጀምሮ ትጥቅ እንዴት ነው የሚያዘው፣ በትጥቁ የሆነ ነገር ቢፈጽም ምን ይሆናል የሚሉና መሰል ጉዳዮች ሥርዓት ባለው መንገድ እንዲመራ ፍላጎት እንዳለው ጠቅሰው፤ ይህ ግን ትጥቅ ከማውረድ ጋር የሚገናኝ ሳይሆን የትጥቅ አስተዳደሩ በሂደት ታይቶ በሥርዓት መመራት አለበት ከሚል እሳቤ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ @tikvahethiopia

" ውይይት እና እርቅ የሚጀምርበት ጊዜ ነው " - አንቶኒዮ ጉተሬዝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ስቃይ ልቤ እንደተሰበረ ነው ብለዋል። አንቶኒዮ ጉተሬዝ
+1
" ውይይት እና እርቅ የሚጀምርበት ጊዜ ነው " - አንቶኒዮ ጉተሬዝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ስቃይ ልቤ እንደተሰበረ ነው ብለዋል። አንቶኒዮ ጉተሬዝ ፥ " ሁሉም ኢትዮጵያውያን ለስደተኞች ባደረጉት ቸርነት እና መስተንግዶ አርአያ መሆናቸውን እመሰክራለሁ። ኢትዮጵያውያን ሰላም ይገባቸዋል " ሲሉ በትዊተር ገፃቸው ላይ ፅፈዋል። አክለውም ፥ " ለሁሉም ወገኖች የማቀርበው ጥሪ ፦ ግጭቱን በሁሉም መልኩ ያቁሙ። ሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ሁሉ በተቻለ ፍጥነት እርዳታ ሊደርሳቸው ይገባል " ሲሉ ገልፀዋል። አንቶኒዮ ጉተሬዝ ፥ ውይይት እና እርቅ የሚጀምርበት ጊዜ ነውም ብለዋል። @tikvahethiopia

#Ethio_Sudan በሱዳን ኃይሎች የተያዘው የአልፋሽቃ መሬት ሰላማዊ መፍትሄ ካላገኘ በኢትዮጵያ በኩል በኃይል የመፍታት እድል ይኖረው እንደሆነ ከጀርመን ሬድዮ የተጠየቁት የመከላከያ ሰራዊት ግንባታ
+1
#Ethio_Sudan በሱዳን ኃይሎች የተያዘው የአልፋሽቃ መሬት ሰላማዊ መፍትሄ ካላገኘ በኢትዮጵያ በኩል በኃይል የመፍታት እድል ይኖረው እንደሆነ ከጀርመን ሬድዮ የተጠየቁት የመከላከያ ሰራዊት ግንባታ ሥራዎች ዋና አስተባባሪ ጄነራል ባጫ ደበሌ፥ "በእኛ በኩል መንግስታችን ከሱዳን ጋር ተዋጉ የሚል ትዕዛዝ አልሰጠንም" ብለዋል። አክለውም፥ "እኛ የያዝነው ውጊያ አለ፤ ከእነዚህ ሰዎች (ከሱዳኖች) ጋር ድሮውንም እንዳልነው ነው በውይይት የምንፈታው ነገር ነው። እነሱ ከነበሩበት የቀጠሉት የለም። ስለዚህ ትኩረት የተነፈገው አይደለም። በሚገባ እየተከታተልን ነው ያለነው" ሲሉ ገልፀዋል። ጄነራል ባጫ፥ " ሁሉንም ድስት ጥደህ አንዱንም ሳታማስል ሊያርብህ አይገባም። ሆኖም በየትኛውም አካባቢ በኢትዮጵያ ድንበር ላይ የሚመጣ ችግር ካለ ግን ይሄን መመለስ የሚችል አቅሙ አለን " ብለዋል። በሌላ በኩል ከአል ዓይን ኒውስ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት በኢትዮጵያ የሱዳን አምባሳደር ጀማል አል ሼክአምባሳደር ጀማል አል ሼክ፤ በሱዳን ቁጥጥር ስር ስለሚገኘውና የይገባኛል ጥያቄና ክርክር እየተነሳበት ስላለው ስፍራ የሱዳንን አቋም አንፀባርቀዋል። አምባሳደሩ፥ "አሁን ክርክር እያስነሳ ያለው መሬት ሱዳን የኔ ነው ብላ ታምናለች" ያሉ ሲሆን " ሱዳን ጉዳዩ ከፖለቲካ እና ዲፕሎማሲ ውጭ በሌሎች አማራጮች ይፈታል ብላ አታምንም " ብለዋል። አምባሳደሩ፥ " እነዛ ቦታዎች የሱዳን ናቸው፤ ለዚህ ማስረጃም እንደፈረንጆቹ 1902 በሁለቱም ሀገራት የተደረሰው ታሪካዊ ስምምነት እንዳለ ይታወቃል፤ ስለዚህም የድንበር ውዝግቡ የስምምነቱን ዋና ዋና ጉዳዮች መሰረት በማድረግ ሊፈታ ይችላል የሚል እምነት አለኝ" ሲሉ ተናግረዋል። ሱዳን ጉዳዩን በዲፕሎማሲ እና ፖለቲካዊ ውይይት ለመፍታት ፍላጎት እንዳላት ገልፀዋል። @tikvahethiopia

#ENDF በመከላከያ ሰራዊት የብሄራዊ ተዋፅኦን የማመጣጠን ጉዳይ በተመለከተ የመከላከያ ጀነራል ኢንስፔክተር ቢሮ ኃላፊ ሜጀር ጄነራል áŠ­áŠ•á‹ą ገዙ ምን አሉ ? ሜጀር ጄነራል áŠ­áŠ•á‹ą ገዙ (በኢቲቪ ቀርበው የተናገሩት) ፦ " ... ከሰሞኑ የማዕረግ ሹመት ጋር ሲታይ ትኩረቱ የተወሰኑ ብሄሮች ላይ ነው.. ሌሎች ተረስተዋል ... ምናምን የሚባሉ ነገሮች አሉ። ውትድርና ከባድ ሞያ ነው ፤ የሰው ልጅ ያክል ጭንቅላት አሳምነህ ውጊያ ውስጥ አስገብተህ እንዲሞት አሳምነህ የምትመራበት ሾል ነው ፤ ቢቻል ሳይሞት እንዲወጣ አድርገህ የምትመራበት ሾል ነው ያ ልምድን ችሎታን፣ ብቃትን ይጠቃል እንጂ ዝም ብለህ የብሄር ተዋፅኦ ለመጠበቅ ብለህ ከግራም ከቀኝም ሰብስበህ መሾም ሀገርንም ተቋምንም ይገድላል። ሰሞኑ በነበረው የማዕረግ ሹመት እንደ አንድ የካውንስል አባል ስለሚመለከተኝ የነበረውን ሂደት ስለማውቀው በተቻለ መጠን የብሄር ተዋፅኦ በጠበቀ መንገድ ለመስራት ተሞክሯል። አንዳንዶቹ በጣም Junior ሳሉ የብሄር ተዋፅኦውን ለማምጣት ሲባል ከ Senior ዎች ጋር እንዲሾሙ የተደረጉ አሉ። ... መከላከያ የሚያስቀድመው አሁንም ስራን ማዕከል ያደረገ፣ የተቋሙን ተልዕኮ ሊያስፈፅም የሚችል፣ በሚመራው አሀዱ ተቀባይነት ያለው፤ በሚሰራው ሾል ብልጫ ላሳየ ኦፊሰር ቅድሚያ ይሰጣል። " ያንብቡ : https://telegra.ph/ENDF-01-15

#DrAbiyAhmed #JustinTrudeau ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ አስታውቀዋል። ውይይ
+1
#DrAbiyAhmed #JustinTrudeau ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ አስታውቀዋል። ውይይቱ በወቅታዊ ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ እንደ ካናዳ ያሉ ወዳጅ ሀገራት የሚሰጧትን ድጋፍ እንደምታደንቅ ገልፀዋል። የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ፥ ትላንት ከሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ጋር በተያያዘ ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መዕክተኛ እና የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ጋር መነጋገራቸው ይታወሳል። @tikvahethiopia

#Ethio_Sudan በሱዳን ኃይሎች የተያዘው የአልፋሽቃ መሬት ሰላማዊ መፍትሄ ካላገኘ በኢትዮጵያ በኩል በኃይል የመፍታት እድል ይኖረው እንደሆነ ከጀርመን ሬድዮ የተጠየቁት የመከላከያ ሰራዊት ግንባታ
+1
#Ethio_Sudan በሱዳን ኃይሎች የተያዘው የአልፋሽቃ መሬት ሰላማዊ መፍትሄ ካላገኘ በኢትዮጵያ በኩል በኃይል የመፍታት እድል ይኖረው እንደሆነ ከጀርመን ሬድዮ የተጠየቁት የመከላከያ ሰራዊት ግንባታ ሥራዎች ዋና አስተባባሪ ጄነራል ባጫ ደበሌ፥ "በእኛ በኩል መንግስታችን ከሱዳን ጋር ተዋጉ የሚል ትዕዛዝ አልሰጠንም" ብለዋል። አክለውም፥ "እኛ የያዝነው ውጊያ አለ፤ ከእነዚህ ሰዎች (ከሱዳኖች) ጋር ድሮውንም እንዳልነው ነው በውይይት የምንፈታው ነገር ነው። እነሱ ከነበሩበት የቀጠሉት የለም። ስለዚህ ትኩረት የተነፈገው አይደለም። በሚገባ እየተከታተልን ነው ያለነው" ሲሉ ገልፀዋል። ጄነራል ባጫ፥ " ሁሉንም ድስት ጥደህ አንዱንም ሳታማስል ሊያርብህ አይገባም። ሆኖም በየትኛውም አካባቢ በኢትዮጵያ ድንበር ላይ የሚመጣ ችግር ካለ ግን ይሄን መመለስ የሚችል አቅሙ አለን " ብለዋል። በሌላ በኩል ከአል ዓይን ኒውስ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት በኢትዮጵያ የሱዳን አምባሳደር ጀማል አል ሼክአምባሳደር ጀማል አል ሼክ፤ በሱዳን ቁጥጥር ስር ስለሚገኘውና የይገባኛል ጥያቄና ክርክር እየተነሳበት ስላለው ስፍራ የሱዳንን አቋም አንፀባርቀዋል። አምባሳደሩ፥ "አሁን ክርክር እያስነሳ ያለው መሬት ሱዳን የኔ ነው ብላ ታምናለች" ያሉ ሲሆን " ሱዳን ጉዳዩ ከፖለቲካ እና ዲፕሎማሲ ውጭ በሌሎች አማራጮች ይፈታል ብላ አታምንም " ብለዋል። አምባሳደሩ፥ " እነዛ ቦታዎች የሱዳን ናቸው፤ ለዚህ ማስረጃም እንደፈረንጆቹ 1902 በሁለቱም ሀገራት የተደረሰው ታሪካዊ ስምምነት እንዳለ ይታወቃል፤ ስለዚህም የድንበር ውዝግቡ የስምምነቱን ዋና ዋና ጉዳዮች መሰረት በማድረግ ሊፈታ ይችላል የሚል እምነት አለኝ" ሲሉ ተናግረዋል። ሱዳን ጉዳዩን በዲፕሎማሲ እና ፖለቲካዊ ውይይት ለመፍታት ፍላጎት እንዳላት ገልፀዋል። @tikvahethiopia

#ENDF በመከላከያ ሰራዊት የብሄራዊ ተዋፅኦን የማመጣጠን ጉዳይ በተመለከተ የመከላከያ ጀነራል ኢንስፔክተር ቢሮ ኃላፊ ሜጀር ጄነራል áŠ­áŠ•á‹ą ገዙ ምን አሉ ? ሜጀር ጄነራል áŠ­áŠ•á‹ą ገዙ (በኢቲቪ ቀርበው የተናገሩት) ፦ " ... ከሰሞኑ የማዕረግ ሹመት ጋር ሲታይ ትኩረቱ የተወሰኑ ብሄሮች ላይ ነው.. ሌሎች ተረስተዋል ... ምናምን የሚባሉ ነገሮች አሉ። ውትድርና ከባድ ሞያ ነው ፤ የሰው ልጅ ያክል ጭንቅላት አሳምነህ ውጊያ ውስጥ አስገብተህ እንዲሞት አሳምነህ የምትመራበት ሾል ነው ፤ ቢቻል ሳይሞት እንዲወጣ አድርገህ የምትመራበት ሾል ነው ያ ልምድን ችሎታን፣ ብቃትን ይጠቃል እንጂ ዝም ብለህ የብሄር ተዋፅኦ ለመጠበቅ ብለህ ከግራም ከቀኝም ሰብስበህ መሾም ሀገርንም ተቋምንም ይገድላል። ሰሞኑ በነበረው የማዕረግ ሹመት እንደ አንድ የካውንስል አባል ስለሚመለከተኝ የነበረውን ሂደት ስለማውቀው በተቻለ መጠን የብሄር ተዋፅኦ በጠበቀ መንገድ ለመስራት ተሞክሯል። አንዳንዶቹ በጣም Junior ሳሉ የብሄር ተዋፅኦውን ለማምጣት ሲባል ከ Senior ዎች ጋር እንዲሾሙ የተደረጉ አሉ። ... መከላከያ የሚያስቀድመው አሁንም ስራን ማዕከል ያደረገ፣ የተቋሙን ተልዕኮ ሊያስፈፅም የሚችል፣ በሚመራው አሀዱ ተቀባይነት ያለው፤ በሚሰራው ሾል ብልጫ ላሳየ ኦፊሰር ቅድሚያ ይሰጣል። " ያንብቡ : https://telegra.ph/ENDF-01-15

#DrAbiyAhmed #JustinTrudeau ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ አስታውቀዋል። ውይይ
+1
#DrAbiyAhmed #JustinTrudeau ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ አስታውቀዋል። ውይይቱ በወቅታዊ ሀገራዊ እና ከባቢያዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ እንደ ካናዳ ያሉ ወዳጅ ሀገራት የሚሰጧትን ድጋፍ እንደምታደንቅ ገልፀዋል። የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ትላንት ከሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ጋር በተያያዘ ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መዕክተኛ እና የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ጋር መነጋገራቸው ይታወሳል። @tikvahethiopia

#Update ቅዱስ ፓትርያርኩ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባጋጠ
#Update ቅዱስ ፓትርያርኩ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት ህክምናቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ። በዚህም መሰረት ቅዱስነታቸው በአሁኑ ሰዓት በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ህክምናቸውን በንቃት እየተከታተሉ እንደሚገኙ ታውቋል። ከኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት የተላለፈውን መልዕክት ያንብቡ : https://telegra.ph/EOTC-01-15 @tikvahethiopia

#BahirDar በፕሬዜዳንቱ አቶ እስክንድር ነጋ የሚመራው የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አመራሮች ቡድን ዛሬ ከሰዓት ወደ አማራ ክልል መዲና ባህር ዳር መግባቱን ፓርቲው አሳውቋል። ቡድኑ ባህ
+2
#BahirDar በፕሬዜዳንቱ አቶ እስክንድር ነጋ የሚመራው የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አመራሮች ቡድን ዛሬ ከሰዓት ወደ አማራ ክልል መዲና ባህር ዳር መግባቱን ፓርቲው አሳውቋል። ቡድኑ ባህር ዳር ሲደርስ በከተማዋ ወጣቶችና የፋኖ አባላት አቀባበል እየተደረገለት ፓርቲው ገልጿል። በቅርቡ ከእስር የተፈቱት አቶ እስክንድር ነጋ የሚመሩት የባልደራስ ፓርቲ አመራሮች ቡድን ትላንት አፋር ክልል በመግባት በዱቢቲ ሪፈራል ሆስፒታል የሚገኙ በግንባር የተጎዱ የጦር አባላትን መጠየቁ እንዲሁም በአዋሽ ወንዝ ላይ እየለማ ያለውን የስንዴ ምርት መጎብኘቱ መገለፁ ይታወሳል። @tikvahethiopia

ቪድዮ : ቡጢ የተሰናዘሩት የሶማሊላንድ ፓርላማ አባላት👊 ዛሬ ጥዋት የ2022 በጀት ላይ የጦፈ ክርክር ላይ የነበሩት የፓርላማ አባላቱ ቡጢ ሲሰናዘሩ እና ሲደባደቡ በቀጥታ ስርጭት ታይተዋል። @tikvahethiopia

" ግጭቱ በባህላዊ እርቅ ተቋጭቷል " በምስራቅ መስቃን ቤተ ጉራጌና ማረቆ የሰላም ጉባኤ በጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ ኢንሴኖ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው። በምስራቅ መስቃን ቤተ ጉራጌና ማረቆ መ
+1
" ግጭቱ በባህላዊ እርቅ ተቋጭቷል " በምስራቅ መስቃን ቤተ ጉራጌና ማረቆ የሰላም ጉባኤ በጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ ኢንሴኖ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው። በምስራቅ መስቃን ቤተ ጉራጌና ማረቆ መካከል ተፈጥሮ የነበረው ግጭት በባህላዊ እርቅ ተቋጭቷል። የእርቅ ስነ-ስርዓቱ ግጭቱ በተከሰተበት ቦታ ኢንሴኖ የተካሄደ ሲሆን የክልልና የዞን አመራሮች የአገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል፡፡ ግጭቱ የተነሳው ከአከላለል ጋር በተያያዘ ሲሆን ከግጭቱ ለማትረፍ ፍላጎት ያላቸው አካላት እንዲባባስ ያደረጉ እንደነበር ተገልጿል፡፡ በዚህም የሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን ዜጎችም ከቤት ንብረታቸው እንዲፈናቀሉ አድርጓል። ግጭቱም የግብርና እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ጫና ፈጥሮ መቆየቱ ነው የተገለጸው፡፡ ሁለቱ ወገኖች ልዮነታቸውን በባህላዊ የዕርቅ መንገድ መፍታታቸውን ተከትሎ የእርቅ ጉባኤ በጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን መረዳ ኢንሴኖ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ #ENA @tikvahethiopia

#USA አምባሳደር ሳተርፊልድ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ። አዲሱ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ #ኢትዮጵያን ጨምሮ ሱዳን እና ሳዑዲ አረቢያን እን
#USA አምባሳደር ሳተርፊልድ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ። አዲሱ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ #ኢትዮጵያን ጨምሮ ሱዳን እና ሳዑዲ አረቢያን እንደሚጎበኙ ተገልጿል። አምባሳደር ሳተርፊልድ እኤአ ከጥር 17-20 ባሉት ቀናት ነው ሃገራቱን የሚጎበኙት፡፡ በቅድሚያ ወደ ሪያድ እንደሚጓዙ የሚጠበቁት ልዩ መልዕክተኛው ቀጥሎ ካርቱምንና አዲስ አበባን ይጎበኛሉ ተብሏል፡፡ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ረዳት ጸሃፊ ሞሊ ፊ አብረዋቸው ወደ ሃገራቱ እንደሚጓዙ ተገልጿል። አምባሳደር ሳተርፊልድ በሪያድ ቆይታቸው በሱዳን ያለውን ወታደራዊ አገዛዝ እንዲያበቃ የሚጠይቁትን የለውጥ ኃይሎችን እንደሚያገኙና በመንግስታቱ ድርጅት አመቻችነት ለማካሄድ ስለታሰበው ሃገራዊ ውይይት እንደሚነጋገሩ ይጠበቃል፡፡ ወደ ካርቱም ተጉዘው ከተለያዩ የለውጥና የዴሞክራሲ ኃይሎች ጋር እንዲሁም ከወጣት አደረጃጀቶች ጋር ይወያያሉ፡፡ በኢትዮጵያ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል። መንግስት የተገኘውን የሰላም ጭላንጭል እንዲያጠናክር፣ የአየር ጥቃቶችን እንዲያቆም እና ሌሎችም መቃቃሮች እንዲያበቁ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚነጋገሩም ነው የተገለጸው፡፡ ተኩስ እንዲቆም፣ እስረኞች አሁንም እንዲለቀቁና ሰብዓዊ እርዳታዎች ሳይስተጓጎሉ እንዲቀርቡ ይጠይቃሉ ተብሏል፡፡ መረጃውን #አል_ዓይን_ኒውስ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ዋቢ አድርጎ ነው በድረገፁ ላይ ያስነበበው። @tikvahethiopia

#Abala በአፋር ክልል ፣ አብአላ ከተማ በሚሰነዘር የከባድ መሳሪያ ድብደባ የከተማው ነዋሪ ከቄዬው እየተሰደደ መሆኑን የከተማው ከንቲባ ተናገሩ። ከንቲባው ይህን የተገሩት ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
+1
#Abala በአፋር ክልል ፣ አብአላ ከተማ በሚሰነዘር የከባድ መሳሪያ ድብደባ የከተማው ነዋሪ ከቄዬው እየተሰደደ መሆኑን የከተማው ከንቲባ ተናገሩ። ከንቲባው ይህን የተገሩት ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ነው። ከመቐለ ከተማ 40 ኪ/ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው የአፋር የንግድ ከተማ አብአላ ከንቲባ አቶ ጣሂር ሀሰን ህወሓት ተቆጣጥሯቸው ከነበሩት የአፋር እና አማራ ክልሎች እንዲወጣ ከተደረገ በኃላ አብአላ ላይ ተደጋጋሚ ጉዳት ደርሷል ብለዋል። የከተማው ከንቲባ ፥ " አሁንም ድረስ አላቋረጠም ንፁሃን መደብደብ ፤ በከባድ መሳሪያ መደብደብ እንስካሁን አላቆመም። በእግረኛም ወረራ እየሞከረ ነው። መጀመሪያውንም እንደሚታወቀው በየአካባቢው የሚያደርገውን ወረራ እና የንፁሃን ጭፍጨፋ ሙከራ ነው ያደረገው ያኔም አልተሳካለትም እስካሁን አላቋረጠም። በከባድ መሳሪያ ንፁሃንን እየደበደበ ነው፤ በእግረኛም እየሞከረ ነው ዘረፋ ለማድረግም እየሞከረ ነው ቢሆንም ግን አልተሳካለትም። ወደላይ ተመልሷል እስካሁን ግን የቆመ ነገር የለም ፤ ከከተማው ራቅ ብሎ ከባድ መሳሪያ እየተኮሰ ነው " ብለዋል። እየተፈፀመ በሚገኘው ጥቃት ከንፁሃን በተጨማሪ የአምልኮ ቦታዎች ፣ የመንግስት እና የግል ባለሀብቶች ንብረት ላይ ጉዳት መደረሱ ተገልጿል። የደረሰውን ጉዳት በቁጥር ደረጃ ለመግለፅ ጥናት እየተደረገ መሆኑን የአብአላ ከንቲባ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል። @tikvahethiopia

በጦቢያ የቤተሰብ ቀን ልዩ ፌስቲቫል ! ውድ የጦቢያ ቤተሰቦች እሁድ ጥር 8/2014 " በጊዮን ግሮቭ ጋርደን ዎክ " ከቀኑ 6ሰአት ጀምሮ - በማርሽ ባንድ ኢትዮጵያን ይዘምራሉ! - በድንቅ ገጣሚያን
በጦቢያ የቤተሰብ ቀን ልዩ ፌስቲቫል ! ውድ የጦቢያ ቤተሰቦች እሁድ ጥር 8/2014 " በጊዮን ግሮቭ ጋርደን ዎክ " ከቀኑ 6ሰአት ጀምሮ - በማርሽ ባንድ ኢትዮጵያን ይዘምራሉ! - በድንቅ ገጣሚያን የግጥም ጥምዎን ያረካሉ! - በፍራሽ አዳሹ ፍራሽዎ ይታደሳል! - በመረዋ ኳየር የተቀነባበረ ስልተ ድምፅ ይደመማሉ! - በኢትዮጵያነት የውዝዋዜ ቡድን አዲስ ስራዎች ይዝናናሉ። በዚህ ሁሉ ውስጥ ኢትዮጵያችን አለች!! #በነፃ_ሃሳብና_በሰከነ_መንፈስ_ኢትዮጵያንና_ኢትዮጵያዊነትን_እናድምቅ! ከ12 ዓመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች መግቢያ በነፃ! የመግቢያ ዋጋ 300 ብር ትኬቱን በሁሉም የቡና ባንክ ቅርንጫፎች ይገኛል። ለመረጃ 0919787878

#Update የደሴ - ወልዲያ የኤሌክትሪክ መስመር ጥገና እየተገባደደ ነው። ፍተሻው በስኬት ከተጠናቀቀ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች በሰዓታት ውስጥ ኤሌክትሪክ ሊያገኙ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ኤሌ
+2
#Update የደሴ - ወልዲያ የኤሌክትሪክ መስመር ጥገና እየተገባደደ ነው። ፍተሻው በስኬት ከተጠናቀቀ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች በሰዓታት ውስጥ ኤሌክትሪክ ሊያገኙ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል። ተቋሙ እስከዛሬ ድረስ በተከናወነው ጥገና ጉዳት የደረሰበት መስመርና ምሰሶ ከ97 በመቶ በላይ ተጠናቋል ብሏል። ቀሪ ሥራዎችን በርብርብ በማጠናቀቅ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች ማምሻውን አልያም እስከ ነገ እኩለ ቀን ድረስ መብራት እንዲያገኙ ይደረጋል ሲል አሳውቋል። @tikvahethiopia