en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
ፎቶ : 350 የሶማሊያ ወታደሮች ' መሰረታዊ የኮማንዶ ስልጠና ' ከኳታር የተውጣጡ የስልጠና ባለሞያዎችን በማካተት እየተሰጠ መሆኑን የቱርክ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። ለወታደሮቹ ስልጠና
+3
ፎቶ : 350 የሶማሊያ ወታደሮች ' መሰረታዊ የኮማንዶ ስልጠና ' ከኳታር የተውጣጡ የስልጠና ባለሞያዎችን በማካተት እየተሰጠ መሆኑን የቱርክ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። ለወታደሮቹ ስልጠናው እየተሰጠው የሚገኘው በቱርክ የፀረ-ሽብርተኝነት ስልጠና እና መለማመጃ ማዕከል (Isparta) ዕዝ ውስጥ ነው። ቱርክ እና ኳታር በሶማሊያ በፖለቲካ ውስጥ እንዲሁም በወታደራዊ ዘርፍ ላይ ተፅእኖ እንዳላቸው ይነገራል። @tikvahethiopia

#ሹመት ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር በመሆን ተሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና
#ሹመት ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር በመሆን ተሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አድርገው ሹመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጥር 3 ቀን 2014 ጀምሮ ነው ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረን የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አድርገው የሾሟቸው። @tikvahetiopia

ጦቢያ የቤተሰብ ቀን ልዩ ፌስቲቫል ! ውድ የጦቢያ ቤተሰቦች እሁድ ጥር 8/2014 ከቀኑ 6:00 ጀምሮ " በጊዮን ግሮቭ ጋርደን ዎክ " ከተገኙ ፍራሽ አዳሹ ፍራሽዎን ያድስልዎታል !! ደስታ አስመላሽ
ጦቢያ የቤተሰብ ቀን ልዩ ፌስቲቫል ! ውድ የጦቢያ ቤተሰቦች እሁድ ጥር 8/2014 ከቀኑ 6:00 ጀምሮ " በጊዮን ግሮቭ ጋርደን ዎክ " ከተገኙ ፍራሽ አዳሹ ፍራሽዎን ያድስልዎታል !! ደስታ አስመላሽ የተጎዳ ፍራሽ አዳሽ! ከ12 ዓመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች መግቢያ ነፃ ነው። የመግቢያ ዋጋ 300 ብር ትኬቱን በሁሉም የቡና ባንክ ቅርንጫፎች ያገኛሉ። አለባበስዎ ባህላዊ ቢሆን ቀኑ የደመቀ ይሆናል! #በነፃ_ሃሳብና_በሰከነ_መንፈስ_ኢትዮጵያንና_ኢትዮጵያዊነትን_እናድምቅ በዚህ ሁሉ ውስጥ ኢትዮጵያችን አለች!

ዶ/ር ቴድሮስ ምን አሉ ? የአፋር እና የአማራ ክልል ባለስጣናት ምን መለሹ ? የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ፦ " 7 ሚሊዮን ህዝብ የሚኖርበት ክልል ከአንድ አመት በላይ ሙሉ በሙሉ ከበባ ውስጥ ሆናል። በዚህ ምክንያት ህዝቡ ምንም አይነት የምግብ አቅርቦት፣ የህክምና ፣ ኤሌክትሪክ፣ የቴሌፎን ፣ የመገናኛ áŠ áŒˆáˆáŒáˆŽá‰ľ አያገኝም። በመድሃኒት አቅርቦት እጥረት ምክንያት ሰዎች እየሞቱ ነው። በምግብ እጥረት ምክንያት እንደዚሁ ብዙዎች ህይወታቸውን ያጣሉ ከዚያ በላይ በየቀኑ የሚሰነዘረው የድሮን ጥቃት ሰዎችን እየገደለ ነው " ብለዋል። የአፋር ክልል አዳአር ወረዳ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዶ አሊ ፦ " የዓለም ምግብ ፕሮግራምን ጨምሮ የተለያዩ አካላት ወደትግራይ በአፋር #አብዓላ በኩል የምግብ እርዳታ ሲጓጓዝ ቆይተዋል። በቅርብ ጊዜ በአካባቢው ያለውን ሁኔታ ዓለም ያውቀዋል። መጀመሪያ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል የሚገባበት አማራጭ መንገድ የለም፤ ለምን ? በአፋር አብአላ በኩል ያለውን ጦርነት እራሳቸው ከፍተው በአብአላ በኩል ጦርነት እያካሄዱ ነው እነሱ። በቆቦም በኩል ጦርነት እየተካሄደ ነው። እናስገባ ቢባል እንኳን ሁሉም መግቢያ በሮቹ በአፋር በኩል ነበር እስከዛሬ የሚገባላቸው እርዳታ የሚገባው በዛ በኩል እራሳቸው ጦርነት ከፍተው ወረራ አድርገው በአብዓላ ከተማ እስካሁን ድረስ በመድፍ እየደበደቡ ስለሆነ እርዳታ የሚገባበት አማራጭ የለም። እሱ (ዶ/ር ቴድሮስ) ለህወሓት ፕሮፖጋንዳ ነው እንዲህ የሚያደርገው እንጂ የመግቢያ መንገዶቹ በሙሉ የጦርነት ቀጠና እንደሆኑ ያውቃል። " ብለዋል። የአማራ ክልል አደጋ መከላከል ምግብ ዋስትናና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘላለም ልጅዓለም ፦ " ህወሓት ቀበሌ ከምትገኝ የጤና ኬላ ጀምሮ እስከ ትልልቅ ሆስፒታሎች ድረስ የሚችለውን ዘርፎ መውሰድ የማይችለውን አገልግሎት እንዳይሰጥ አድርጎ አውድሟል። ይሄ እንግዲህ መላው የዓለም አቀፍ ተቋማት በግላጭ የሚያውቁት ነው። ይህን እንኳን ሲያወግዙ አይሰማም። በተመሳሳይ ጠላት ከወጣ በኃላ እነዚህ አካባቢዎች ከፍተኛ የመድሃኒት ችግር ፣ አገልግሎት ለማስጀመር የሚያስችል ቁመና ላይ አይደሉም ያሉት ጤና ተቋማቱ መልሶ ለማቋቋም እንኳን የዓለም ጤና ድርጅት አንድም አስተዋጽዖ እያበረከተ አይደለም " ብለዋል። ያብቡ : https://telegra.ph/WHO-01-14-2

#Update ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የጤና ችግር አጋጥሟቸው ሆስፒታል መግባታቸው ተገልጿል።
+1
#Update ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የጤና ችግር አጋጥሟቸው ሆስፒታል መግባታቸው ተገልጿል። ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 6 በመስቀል አደባባይ ጉዳይ ሊያደርግ ያሰበው ስብሰባ በቅዱስነታቸው አለመገኘት ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉ ተነግሯል። ቅዱስነታቸው ፥ በገጠማቸው የጤና ችግር ምክንያት ሆስፒታል ስለገቡና ቅዱስነታቸው በመንበራቸው ላይ በሌሉበት ሁኔታ ጉባኤውን ማካሔድ ስለማይቻል የቅዱስ ፓትርያርኩ ጤና እስከሚመለስ ድረስ ጉባኤው ላልተወሰነ ጊዜ የተላለፈ መሆኑን የቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል። @tikvahethiopia

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለተፈናቃይ ወገኖች 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የምግብ ድጋፍ አደረገች። ቤተክርስቲያኗ ህወሓት በከፈተው ጦርነት ምክንያት ተፈናቅለው በደባርቅ ከተማ
+1
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለተፈናቃይ ወገኖች 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የምግብ ድጋፍ አደረገች። ቤተክርስቲያኗ ህወሓት በከፈተው ጦርነት ምክንያት ተፈናቅለው በደባርቅ ከተማ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖች ነው 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የፊኖ ዱቄት ድጋፍ ያደረገችው። የስዊድን እና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ፣ የሰሜን ጎንደር ዞን እና የጅማ ዞን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ እና ሌሎች አባቶች ደባርቅ ከተማ በሚገኘው የተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ ተገኝተው ድጋፉን አስረክበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ስታደርግ ቆይታለች፤ ወደፊትም የተጎዱ ወገኖችን መደገፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች። ፎቶ ፦ EOTC @tikvahethiopia

" ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ጨዋታ አቁሙ !! " - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ምን አሉ ? ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፦ " ... እሱ ውጭ ሆኖ ወይም ደግሞ ጥግ ይዞ ወይም ህወሓት አዲስ አበባ ይጋባል ብሎ ሻንጣ ሲያዘጋጅ የቆየ መከላከያን ሊገመግም ይፈልጋል። በዚህ ወጣ፣ በዚህ ወረደ፣ ይሄን አላደረገም፣ እንዲህ ነው እንዲያ ነው እያለ ይገመግማል። ለምሳሌ መከላከያ ለምን ጠላት ወደ አማራ ክልል እንዲሰፋ አደረገ ይልሃል ፤ ጦርነት እግር ኳስ ይመስለዋል። ሁለቱ ቡድኖች የሆነ ስታዲየም ተሰርቶ እዛ ውስጥ ተገብቶ በግራ እና ቀኝ በሜትር ተሰምሮ እና ተለክቶ እዛ ውስጥ የምትጋጠም አድርጎ የሚያስብ አለ። ጦርነት የእግር ኳስ ግጥሚያ አይደለም። አጥር የለውም። ልክ እንደእግር ኳስ ስታዲየም አጥር የለውም። ከአጥሩ ለምን ወጣህ የሚል ህግ የለውም። ሲመችህ ጠላትን ትገፋለህ 400 ኪ/ሜ ታስለቅቀዋለህ፤ ሳይመችህ ደግሞ እስኪመችህ ትከላከላለህ። ጦርነትን እንደ አዲስ አበባ ስታዲየም ተከልሎለት የምትገጥም የሚደረግ ግጥሚያ አድርጎ የሚረዳ ሰው ነገሮችን የሚረዳበት መንገድ በጣም ደካማ ነው ወይም ሆን ብሎ ነው ለማበጣበጥ ሊሆን ይችላል። ሆን ብሎ ለማበጣበጥ ደግሞ ግንባር ቀደም ተዋናይ TPLF ነው፤ ወገን መስሎ፣ አማራ መስሎ፣ ኦሮሞ መስሎ ሰራዊቱን ለመገምገም ይሞክራል። ሰራዊት ለመገምገም ቢያንስ 40 ዓመት ሰራዊት ውስጥ ማገልገል አለብህ። ጦርነት ለመገምገም ጦርነት ማወቅ አለብህ፤ ሳይንስ ጥበብ ማወቅ አለብህ። ወጥተህ ወርደህ የሰራዊትን ስነልቦና ማወቅ አለብህ። ብድግ ብሎ የማንም እንትን ... Balloon ሲፈነዳ የሚደነግጥ ሰው ሰራዊት መገምገም የለበትም። ሰራዊት የመጨረሻ ምሽግ ነው። የሉአላዊነት የመጨረሻ ምሽግ ነው። ሰራዊት ብሄር የለውም። ሰራዊት ኢትዮጵያዊነት ነው ያለው። ሰራዊት ውስጥ ገብተህ በፈተፈትክ ቁጥር ፣ ለማጋጨት በሰራህ ቁጥር ፣ በብሄር በከፋፈልከው ቁጥር ፣ በጓደኛ አንዱን ከፍ አድርገህ አንዱን ዝቅ ባደረከው ቁጥር ሀገር ላይ ነው አደጋ የምትፈጥረው። በነገራችን ላይ የኛ ሰራዊት ለእንደዚህ አይነት ነገር ፣ ለአሉባልተኛ ቦታ የለውም፤ ቦታ አይሰጥም። የተገነባባት መሰረቱ ግንቡ ጠንካራ ነው። ለዛ ምቹ አይደለንም እኛ። ለጎጥ፣ ለብሄርተኝነት ምቹ አይደለንም። እኛ ብሄር የለንም ብለን ቃል ገብተናል፣ ለኢትዮጵያዊነት ነው የምንሞት ያለነው። ለኢትዮጵያዊነት ነው ሰው 48 ሰዓት ሳይበላ ሳይጠጣ የሚዋጋ ያለው። ለሀገሩ ነው። ኢትዮጵያን ከመበታተን ለማዳን ነው። እኛ እንደኢትዮጵያ ነው የምናስበው። ለመተቸትም እውቀት ያስፈልጋል። ያለእውቀት የሚተች ወይ ጠላት ነው ሆን ብሎ ለመከፋፈል፣ ለማዳከም፣ ሞራሉን ለማድቀቅ ፣ አመራሩን ለመከፋፈል ጠላት የሚሰራው ነው በአብዛኛው እሱ ነው ብዬ ገምታለሁ። ሌላው ይሄን በማድረግ ትርፍ የሚገኝ እየመሰለው ሊሆን ይችላል ወይ ሌላው ሲያራግብ ጠላት ሲያራግብ የእሱ ወገን ያራገበ መስሎት እያሟሟቀ ይሆናል። ተውት መከላከያን ! መከላከያ ለእያንዳንዳችን ዋስትና ነው። ስለዚህ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ጨዋታ አቁሙ፤ sensitive የሆነ ቦታ እየመረጥክ የምትጫወተው ጨዋታ የጠላት ጨዋታ ነው። ተው !! ተው !! አሁን በኃላ በማያገባው ገብቶ የመከላከያን ህልውና የሚፈታተን ነገር ላይ የተሳተፈ ከሆነ እራሳችንን ለመከላከል እንገደዳለን " @tikvahethiopia

#ALERT🚨 የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦ • የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 10,073 • ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,131 • ህይወታቸው ያለፈ 👉 19 • ከበሽታው ያገገሙ 👉 835
#ALERT🚨 የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦ • የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 10,073 • ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,131 • ህይወታቸው ያለፈ 👉 19 • ከበሽታው ያገገሙ 👉 835 • ፅኑ ታማሚዎች 👉 433 ዛሬ እና ትላንት በድምሩ የ43 የሰዎች ህይወት አልፏል። @tikvahethiopia

#AFCON2021 ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 2ኛ ጨዋታ በካሜሮን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። More : @tikvahethsport
#AFCON2021 ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 2ኛ ጨዋታ በካሜሮን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። More : @tikvahethsport

#ETHIOPIA የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 35ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እየተደረገ ባለው ዝግጅት ዙሪያ ከህብረቱ አባል ሀገራት ጋር መክሯል። ሚኒስቴሩ እንዳስ
+1
#ETHIOPIA የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 35ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እየተደረገ ባለው ዝግጅት ዙሪያ ከህብረቱ አባል ሀገራት ጋር መክሯል። ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው ለአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች ለጉባኤው እየተደረገ ስላለው ዝግጅት ማብራሪያ ተሰጥቷል። ለጉባኤው ስኬት የሚያስፈልጉ ሁሉንም ነገሮች ከማዘጋጀት ባለፈ የተሳታፊዎች ጤንነት መጠበቅን ለማረጋገጥ የኮቮድ-19 ምርመራ እና ክትባት መስጫ የጤና ማእከላት በመንግስት መቋቋማቸውን ነው የገለፀው።  የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ ላሳዩት አጋርነትም ምስጋናውን አቅርቧል።  በዛሬው የጉባኤውን ዝግጅት አስመልክቶ በተደረገው ገለፃ ላይ ስለተነሱት ጉዳዮችም ለየሀገሮቻቸው መንግስታት እንዲያሳውቁም አሳስቧል። ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር @tikvahethiopia

#AFCON2021 በ #ኢትዮጵያ እና #ካሜሮን መካከል እየተደረገ የሚገኘው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ፍልሚያ የመጀመሪያ አጋማሽ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ሀገራችን ኢትዮጵያ በመጀመሪያ አጋማሽ አ
#AFCON2021 በ #ኢትዮጵያ እና #ካሜሮን መካከል እየተደረገ የሚገኘው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ፍልሚያ የመጀመሪያ አጋማሽ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ሀገራችን ኢትዮጵያ በመጀመሪያ አጋማሽ አስደሳችና እጅግ ማራኪ የሚባል እንቅስቃሴ አሳይታለች። በዘንድሮ ውድድርም የመጀመሪያ ጎል አስቆጥራለች። ድል ለእናት ሀገራችን ኢትዮጵያ ይሆን ዘንድ እንመኛለን። More : @tikvahethsport

#AFCON2021 ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው የመጀመሪያ ጎሏን አስቆጠረች። ኢትዮጵያ ከካሜሮን ጋር ፍልሚያዋን እያደረገች ትገኛለች። ጨዋታው ከተጀመረ ጥቂት ደቂቃዎች የተቆጠረ ሲሆን በዳዋ ሆ
#AFCON2021 ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው የመጀመሪያ ጎሏን አስቆጠረች። ኢትዮጵያ ከካሜሮን ጋር ፍልሚያዋን እያደረገች ትገኛለች። ጨዋታው ከተጀመረ ጥቂት ደቂቃዎች የተቆጠረ ሲሆን በዳዋ ሆቴሳ አማካኝነት በዘንድሮ ውድድር የመጀመሪያ ጎል አስቆጥራለች። ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ቀጥሏል። በስፖርት ገፃችን ተከታተሉ : @tikvahethsport

#ETHIOPIA የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በኢትዮጵያ ጉዳይ የግላቸውን አቋም እንዳያንጸባርቁ ኢትዮጵያ ጠየቀች፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ ትናንትና ረቡዕ በሰጡት መግለጫ ላይ
+1
#ETHIOPIA የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በኢትዮጵያ ጉዳይ የግላቸውን አቋም እንዳያንጸባርቁ ኢትዮጵያ ጠየቀች፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ ትናንትና ረቡዕ በሰጡት መግለጫ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል ላሉ ዜጎች ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይደርስ አግዷል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ መንግስት በራሱ ዜጎች ላይ ምግብ፣ መድሃኒት እና ሌሎች የህይወት አድን ድጋፎችን እንዳያገኙ እገዳ ጥሏል ሲሉም ነበር ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡ ይህን ተከትሎ በመንግስታቱ ድርጅት የኢትዮጵያ ተጠሪ ጽህፈት ቤት በትዊተር ገጹ ፖለቲካዊ ውግንና አላቸው ያላቸው ዶ/ር ቴድሮስ ኢትዮጵያን ከተመለከቱ ጉዳዮች ራሳቸውን እንዲያርቁና ገለልተኛ እንዲሆኑ ጠይቋል፡፡ የተሰጣቸውን ዓለም አቀፋዊ ሚና ከመወጣት ይልቅ ከፖለቲካዊ እና ግለሰባዊ ፍላጎት የመነጨ ውግንናቸውን እያንጸባረቁ ነው ያለው ጽህፈት ቤቱ የተመድ ኤጀንሲዎች ስራም በዚሁ ምክንያት እየተስተጓጎለ ይገኛል ብሏል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ ኢትዮጵያን ከተመለከቱ የትኞቹም ጉዳዮች ራሳቸውን እንዲያርቁም ነው በተመድ የኢትዮጵያ ተልዕኮ ጽ/ቤት የጠየቀው፡፡ ኢትዮጵያ በጦርነቱ ምክንያት የጤና ተቋማት ሲወድሙ ምንም አላለም በሚል የዓለም ጤና ድርጅትን መውቀሷ ይታወሳል። ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ @tikvahethiopia

#COOP #MICHU የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከክፍያ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂስ ጋር በመተባበር ምቹ የተባለ አዲስ ያለዋስትና ብድር ማግኘት የሚያስችል ዲጂታል ቴክኖሎጂ አስተዋውቋል። በሀገሪቱ የመጀ
+2
#COOP #MICHU የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከክፍያ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂስ ጋር በመተባበር ምቹ የተባለ አዲስ ያለዋስትና ብድር ማግኘት የሚያስችል ዲጂታል ቴክኖሎጂ አስተዋውቋል። በሀገሪቱ የመጀመሪያ የሆነው ምቹ ዲጂታል ዋስትና አልባ የብድር አገልግሎት በዋስትና ምክንያት የብድር አገልግሎት ማግኘት የማይችሉትን በዝቅተኛና መካከለኛ ንግድ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችን በእጅጉ ይጠቅማል ተብሎ ይታመናል። ምቹ የብድር መጠየቂያ እና ማግኛ መተግበሪያ ሲሆን አጠቃቀሙም በሞባይል ስልክ ላይ በመጫን ነው፡፡ ብድር ጠያቂው በመተግበሪያው ላይ ጥያቄው ያቀርባል፣ ብድሩን ለማግኘት የሚጠየቁ መስፈርቶች ይሞላል መተግበሪያው በደቂቃዎች ውስጥ ውጤቱን ያሳውቃል ተብሏል፡፡ ጥቃቅን፣ አነስተኛ እና መካከለኛ የሥራ መስኮች ያለ ዋስትና ብድሩ የቀረበላቸው ሲሆን እንደ ስራው ዓይነትና የመመለሻ ጊዜ የብድር መጠኑ ከ30 ሺ ብር እስከ 150 ሺ ብር ይደርሳል። ምንጭ፦ የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ @tikvahethiopia

#ሹመት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ፥ ካናዳ ሞንትሪያ በሚገኘው የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ምክር ቤት የኢትዮጵያ ተወካይ ሆነው በማገልገል ላይ የነበሩትን አቶ ጌታቸው መንግስቴን የኢት
+2
#ሹመት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ፥ ካናዳ ሞንትሪያ በሚገኘው የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ምክር ቤት የኢትዮጵያ ተወካይ ሆነው በማገልገል ላይ የነበሩትን አቶ ጌታቸው መንግስቴን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አድርገው ሾመዋል። አቶ መንግስቱ ንጉሴን ደግሞ የኤር ናቪጌሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አድርገው መሾማቸውን ተቋሙ አስታውቋል። አቶ ጌታቸው መንግስቴ፤ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት ረዘም ላለ ጊዜ ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት ሲያገለግሉ የነበሩት ኮሎኔል ወሰንየለህ ሁነኛውን በመተካት ነው። #አልዓይን @tikvahethiopia

#ተራዝሟል የኢፌዲሪ የህዘብ ተወካዮች ም/ቤት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 ማጽደቁ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሠረት የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ ከታህሳስ 26/2014
#ተራዝሟል የኢፌዲሪ የህዘብ ተወካዮች ም/ቤት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 ማጽደቁ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሠረት የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ ከታህሳስ 26/2014 - ጥር 6/2014 ዓ.ም ድረስ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ምክር ቤቱ እስካሁን ዕጩ ኮሚሽነሮችን ለመጠቆም ዜጎች ያሳዩት ተነሳሽነትና እያደረጉ ያሉት ተሳትፎ የሚያበረታታ ነው ብሏል። ይሁንና ኮሚሽኑ ከሚኖረው ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት አንፃር ተጨማሪ ዕጩዎችን ህዝቡ እንዲጠቁም እንዲሁም የአገሪቱን ብዝሃነት ታሳቢ በማድረግና በተለያዩ ምክንያቶች መጠቆም ላልቻሉ ዜጎች ዕድሉን ለመስጠት የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ እስከ ጥር 13/2014 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ መሆኑን ገልጿል። ለመጠቆም በም/ቤቱ ድህረ ገጽ http://www.hopr.gov.et/web/guestpublicatons-acticles ወይም በ FB ገጽ http://www.facebook.com/hoprpariament ላይ የተቀመጠውን አድራሻ ይጠቀሙ፡፡ (የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት) @tikvahethiopia

#Update በስልክ በትግረኛ ቋንቋ áˆˆáˆ›á‹áˆŤá‰ľ እና ማስታወሻ ደብተር እንድንይዝ ይፈቀድልን ሲሉ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ማረሚያ ቤቱ መልስ ሰጥቷል። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ልደታ ምድብ 1ኛ የፀረ ሽብርና የህገመንግስት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ለዛሬ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር በ6 ተከሳሾች በተነሱ አቤቱታዎች ላይ መልስ እንዲሰጥ በያዘው ቀጠሮ ችሎቱ የተሰየመ ሲሆን áŠ á‰¤á‰ąá‰ł አቅርበው ከነበሩ ስድስት ተከሳሾች ውስጥ 11 ኛ ተከሳሽ ወ/ሎ ሙሉ ገ/እግዛብሔር ክሳቸው በመቋረጡ አቤቱታቸው ታልፏል። በዛሬው ቀጠሮ 8ኛ ተከሳሽ ወ/ሎ ኬሪያ ኢብራሂም እና 19 ኛ ተከሳሽ ዶ/ር ሰለሞን ኪዳኔ á‰ áˆ…መም ምክንያት በችሎት ያልቀረቡ ሲሆን 20ኛ ተከሳሽ አሰፉ ሊላይ 43 ኛ ተከሳሽ ተክላይ አብርሐ እና 44 ኛ ተከሳሽ ዘሚካኤል አንባዬ áŒáŠ• ቀርበዋል። የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የቀድሞ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈጉባዬ የነበሩት ወ/ሎ ኬሪያ ኢብራሂም á‰ á‰ľáŒáˆ¨áŠ› ቋንቋ ስልክ ለማውራት ስለተከለከልን እንዲፈቀድልት ይታዘዝልን ስትል ያቀረበችው አቤቱታን በተመለከተ ማረሚያ ቤቱ በስልክ ማውራትም á‹¨á‰°áŠ¨áˆˆáŠ¨áˆˆá‹ ለሀገሪቷ ደህንነት ክትትል ስለሚደረግ መሆኑን በጽሁፍ ምላሽ ሰጥቷል። በተጨማሪም የማስታወሻ ደብተር á‰°áŠ¨áˆáŠ­áˆˆáŠ“áˆ ሲሉ ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ማረሚያ ቤቱ ከፍርድ ቤት ማህተም ካለበት áˆ°áŠá‹ľ ውጪ መያዝ á‹¨á‰°áŠ¨áˆˆáŠ¨áˆˆá‹ በደህንንነት መከታተያ ስርአት መሰረት መሆኑን áˆáˆ‹áˆ˝ ሰጥቷል። ያንብቡ : https://telegra.ph/UPDATE-01-13-3 ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

ዛሬ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ አውጥቶ ነበር። በዚህም መግለጫው ላይ TPLF ለትግራይ ህዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይቀርብ እንቅፋት ሆኖ መቀጠሉን አስገንዝቧል። የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፥
+2
ዛሬ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ አውጥቶ ነበር። በዚህም መግለጫው ላይ TPLF ለትግራይ ህዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይቀርብ እንቅፋት ሆኖ መቀጠሉን አስገንዝቧል። የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፥ " እንደ ዓለም ጤና ድርጅት አይነት ለሁሉም ሰው በእኩል ቆመናል የሚሉ አለምአቀፍ ተቋማት ግን አሸባሪው ቡድን የአማራና አፋር ክልሎችን በወረረበት ወቅት ሀስፒታሎችንና የጤና ጣቢያዎችን ሲዘርፍና ሲያወድም ንፁሃንን ሲደፍርና ሲገድል የሽብር ቡድኑን ድርጊት ሲያወግዙ አልተደመጡም " ብሏል። " ይልቁንም መንግስት ወደ ትግራይ ክልል እርዳታ እንዳይገባ እያደረገ ነው በሚል የአሸባሪው ቡድን የሚያሰማውን ፕሮፖጋንዳ ተቀብለው እያስተጋቡት ይገኛል። ይህ በመንግስት ዘንድ ፍፁም ተቀባይነት የለውም " ሲል አሳውቋል። የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፥ " አሁንም ለአንድ ወገን ባጋደለው አቋማቸው በመጽናት የሽብር ቡድኑ ወደ ትግራይ የሰብአዊ እርዳታ እንዳይገባ እንቅፋት መሆኑን በግልጽ አለማንሳታቸው በተዛባ አመለካከታቸው መጽናታቸውንና ውግንናቸው ለህዝብ ጥቅም ሳይሆን ለፖለቲካ አጀንዳ መሆኑን ያመለክታል " ሲል ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግሥት ለትግራይ ክልል ህዝብ የዕለት ደራሽ ዕርዳታ ያለ ምንም መስተጓጎል እንዲቀርብ ለማስቻል በየጊዜው ከአጋር አካላት ጋር ምክክር በማድረግ እየሠራ ይገኛል ሲል አሳውቋል። * ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopoa

#Balderas የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ዛሬ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። ፓርቲው በመግለጫው የተለያዩ ጉዳዮችን ያነሳ ሲሆን ከነዚህ መካከል የሰሜኑ ጦርነት እ
+1
#Balderas የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ዛሬ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። ፓርቲው በመግለጫው የተለያዩ ጉዳዮችን ያነሳ ሲሆን ከነዚህ መካከል የሰሜኑ ጦርነት እና የእነ አቶ ስብሃት ነጋ ክስ ማቋረጥ ጉዳይ አንዱ ነበር። ፓርቲው የሰሜኑ ጦርነት መነሻ ህወሓት የጀመረው ቅድመ ጥቃት እንደሆነ እረዳለሁ ብሏል። የፌዴራል መንግስቱ በርካታ የአፈፃፀም ችግሮች ቢኖሩበትም ያደረገው የመከላከል ጦርነት ፍትሃዊ እንደሆነ ባልደራስ እንደሚያምን አሳውቋል። በዚህም ፓርቲው ፖለቲካዊ ድጋፍ ከማድረግም ባለፈ በአካል ቦታው ድረስ በመሄድ ቁሳዊ እገዛ ማድረጉን አስታውሷል። ነገር ግን መንግስት " ምዕራፍ አንድ " ያለውን ዘመቻ የኢትዮጵያን ሉኣላዊነት ሳያረጋግጥ ማቆሙ ትልቅ አደጋ ያዘለ መሆኑን ፓርቲው መገምገሙን ገልጿል። ዘመቻውን ያቆመበት አመከንዮ ከማስረዳት አኳያ ሆነ እሱን ተከትሎ ከህዝብ ከሚነሳው ተጨባጭ ስጋት ዙሪያ በቂ ምላሽ አልሰጠም። ባልደራስ ፓርቲ ፥ " መንግስት ' ተከድተናል ' ለሚለው የኢትዮጵያ ህዝብ እያሳየ ያለውን ንቀት ማስተካከል ይገባዋል። ህወሓት አሁንም የሀገሪቱን አንድነት ሊፈታተን በሚችል ወታደራዊ ቁመና ላይ ይገኛል። የዘመቻው ፍፃሜ የኢትዮጵያ አንድነት አደጋ ላይ የሚጥለውን የህወሓት ወታደራዊ አቅምን በመስበር መቋጨት ይገባል። " ብሏል። በተጨማሪም የህወሓት የፖለቲካ እና የጦርነቱ ዋነኛ ቀስቃሽ የሆኑ ጉዳያቸውን በህግ ጥላ ስር ሆነው እየተከታተሉ የነበሩ እስረኞችን ሰሞኑን መፍታት መጀመሩ የህግ የበላይነትን የጣሰ ውሳኔ ሆኖ ማግኘቱን ባልደራስ በመግለጫው ላይ ገልጿል። ያንብቡ : telegra.ph/Tikvah-01-13 @tikvahethiopia

" የአሜሪካ ትኩረት በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ጦርነት ወደ ፍፃሜው ማምጣት ነው " - ኔድ ፕራይስ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል ሀገራቸው አሜሪካ ትኩ
+1
" የአሜሪካ ትኩረት በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ጦርነት ወደ ፍፃሜው ማምጣት ነው " - ኔድ ፕራይስ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል ሀገራቸው አሜሪካ ትኩረቷ በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ጦርነት ወደ ፍፃሜው ማምጣት ነው ብለዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት የተንሰራፋውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፣ ረገጣና ስቃይ ለማስቆም ከሁሉ የተሻለው መንገድ ጦርነቱ መቋጫ የሚያገኝበትን መንገድ መፈለግ እንደሆነ ኔድ ፕራንስ ተናግረዋል። ለዚህ አሜሪካ ልዩ ትኩረት ለሰጠችው ጉዳይ ጠንካራ ዴፕሎማሲ እየተከተለች ነው ብለዋል። ኔድ ፕራስ ፥ " ጠንካራ ዴፕሎማሲ እየተከተልን ነው። በመሪዎች ደረጃ የተካሄደው የስልክ ውይይት የዚህ አካል ነበር። አምባሳደር ፌልትማን እና የአሁኑ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ስታርፊልድ በዚህ ውስጥ በጥልቀት ተሰማርተዋል። ከቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉ ኦባሳንጆ ጋር በቅርበት በመስራት ላይ ነን " ሲሉ ገልፀዋል። ቃል አቀባዩ ፕራስ ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ጋር የመነጋገር እድል እንዳገኙ አንስተዋል። ንግግሩ አንዱ የዲፕሎማሲው አካል ነው ብለዋል። ኔድ ፕራስ አሁን ያለው ሁኔታ በግጭት ውስጥ ላሉት ወገኖች መልካም እምነትን ለማሳየት እድል ይሰጣል ብለን እናምናለን ያሉ ሲሆን ውጊያ አቁመው ወደ ድርድር ጠረጴዛ ሊመጡ ይህ ደግሞ ግጭቱ እንዲዘጋ ሊያደርገው ይችላል ሲሉ ማመልከታቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል። @tikvahethiopia