en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
#NDRMC በጦርነቱ በተፈናቁሉ እና እርዳታ በሚያስፈልጋቸው ዜጎች ስም ከሚሰበሰብ እርዳታ ውስጥ የለሽያጭ የሚቀረበና ለማይገባቸው ሰዎችም የሚደርስ እንዳለ የብሔራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን
+1
#NDRMC በጦርነቱ በተፈናቁሉ እና እርዳታ በሚያስፈልጋቸው ዜጎች ስም ከሚሰበሰብ እርዳታ ውስጥ የለሽያጭ የሚቀረበና ለማይገባቸው ሰዎችም የሚደርስ እንዳለ የብሔራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። ይህን ያሳወቀው ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 በሰጠው ቃል ነው። የኮሚሽኑ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ፥ አንዳንድ አካላት ግለሰቦች፣ ቡድኖች፣ ማህበራት እንዲሁም አብዛኛው ተቋማት እያመጡ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ጠቁመው እርዳታውን በራሳቸው መንገድ ለማድረስ የሚሄዱበት አካሄድ ግን እርዳታው ለሚገባቸው ዜጎች በትክክል እንዳይደርስ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ ደበበ ፥ "አንዳንድ ጊዜ እንደውም እዚህ ቦታ ይሂድ ይላሉ ድጋፍ ሰጪው ድጋፍ የሚሰጥበትን ቦታ እሱ መምረጥ ተገቢ አይደለም። የት ቦታ ምን እንደጎደለ እኛ ነን የምናውቀው። ህፃናት ለብቻ ናቸው፣ አጥቢ እናቶች፣ ነፍሠጡሮች ለብቻ ናቸው፣ አቅመ ደካሞች ለብቻ ናቸው። እዚህ ደሴ ያገኘሁትን ነው የምናገረው እርዳታው ለጎረምሳ ቀለብ እየሆነና ለገበያ እየዋለ ነው" ብለዋል። አክለው፥ "ከዛ የሚላከው እዚህ ሲደርስ ተቀንሶ፣ ተቀሽቦ ነው እየደረሰ ያለው ይሄ አግባብ አይደለም። በየመንገዱም የተለያየ ስራ የሚሰራ ከሆነ ትንሽ ኢትዮጵያ እና ህዝቧ እየተደገፈ አይደለም ማለት ችላል" ሲሉ ገልፀዋል። ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች በትክክል ድጋፍ እንዲያገኙ ከተፈለገ በጋራ እና በትብብር መስራት ያስፈልጋል ያሉት አቶ ደበበ ለጋሾች ትክክለኛ መረጃ ኖሯቸው ለሚገባቸው ዜጎች ድጋፍ እንዲያደርሱ ከኮሚሽኑ ጋር አብረው መስራት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ ተናግረዋል። በሌላ በኩል ደብረ ብርሃን ከተማ ተጠልለው የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ መኖሪያቸው በመመለሳቸው መጠለያዎቹ ሙሉ በሙሉ መዘጋታቸውን ኮሚሽኑ ለሬድዮ ጣቢያው አስታውቋል። @tikvahethiopia

#INTERPOL ጆን ሀብቴ ኬንያ፣ ናይሮቢ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውሎ ለኔዘርላንዳስ ተላልፎ ተሰጥቷል። በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ለዓመታት ሲፈለግ የቆየው ትውልደ ኤርትራዊው የኔዘርላንድ ዜጋ ናይሮቢ
+3
#INTERPOL ጆን ሀብቴ ኬንያ፣ ናይሮቢ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውሎ ለኔዘርላንዳስ ተላልፎ ተሰጥቷል። በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ለዓመታት ሲፈለግ የቆየው ትውልደ ኤርትራዊው የኔዘርላንድ ዜጋ ናይሮቢ ውስጥ ተይዞ ለኔዘርላንድስ ተላልፎ መሰጠቱን የኬንያ ፖሊስ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ ቡድንን ሲያንቀሳቅስ ነበር የተባለው የ53 ዓመቱ ጆን ሐብቴ ከ2 ሳምንት በፊት ነው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለው። ጆን ሐብቶን ለመያዝ ዓለም አቀፉ የፖሊስ ተቋም የሆነው ኢንተርፖል አስቸኳይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱን ተከትሎ የኬንያ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቡድን አባላት በዋና ከተማዋ ናይሮቢ ዳርቻ ላይ በሚገኝ ስፍራ በቁጥጥር ስር እንዳዋሉት ገልፀዋል። ተጠርጣሪው ናይሮቢ ውስጥ ለምን ያህል ጊዜ ተደብቆ እንደቆየ ባይታወቅም ከ2 ሳምንት በፊት ነው በቁጥጥር ስር የዋለው። ግለሰቡ ወዲያውኑ ለኔዘርላንድስ ተላልፎ የተሰጠ በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ እዚያው በእስር ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። ኢንተርፖል ፥ ጆን ሐብቴ በድብቅ የሚንቀሳቀስ ዓለም አቀፍ በሕገወጥ መንገድ ሰዎችን የሚያዘዋውር ቡድን መሪ እንደሆነ እንደሚታመን አመልክቶ ፤ በርካታ ሰዎችን ከአፍሪካ ወደ አውሮፓ በሕገ ወጥ መንገድ በማዘዋወር ወንጀል ተጠያቂ ነው ብሏል። ግለሰቡ በተለይ በርካታ ኤርትራውያንን በእስያ በኩል ወደ አውሮፓ እንዲገቡ አድርገዋል ከተባሉ፣ ቢያንስ አራት የተለያዩ የሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀሎች ጋር ስሙ ተያይዞ ይነሳል። ምንጭ፦ ቢቢሲ / https://www.interpol.int/News-and-Events/News/2021/People-smuggling-sting-operation-Kenya-Netherlands-cooperation-lands-renowned-fugitive-in-jail @tikvahethiopia

#ጥንቃቄ የጤና ባለሙያዎች ህብረተሰቡ ለኮቪድ -19 የሳል ማስታገሻ በሚል ከሚወሰዱ መድኃኒቶች እራሱን እንዲጠብቅ አሳስበዋል። ከኮቪድ - 19 መስፋፋትን ተከትሎ በየፋርማሲዎች የሳል ማስታገሻ መድኃኒ
+1
#ጥንቃቄ የጤና ባለሙያዎች ህብረተሰቡ ለኮቪድ -19 የሳል ማስታገሻ በሚል ከሚወሰዱ መድኃኒቶች እራሱን እንዲጠብቅ አሳስበዋል። ከኮቪድ - 19 መስፋፋትን ተከትሎ በየፋርማሲዎች የሳል ማስታገሻ መድኃኒቶች ፍላጎት መጨመሩን ባለሙያዎች እየገለፁ ይገኛሉ። የአለርት ሆስፒታል የፋርማሲ ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አሸብር ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፥ ከኮቪድና ጉንፋን ወረርሽኞች መስፋፋት ጋር ተያይዞ በርካቶች ያለሐኪም ምክር ከየፋርማሲው የሳል ማስታገሻ መድኃኒቶችን እየወሰዱ ነው ብለዋል። ይህ ልምድ ለተጓዳኝ በሽታዎች መባባስ የሚዳርግ በመሆኑ መጠንቀቅ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በተለይ በከተሞች ላይ የጉንፋን በሽታ ይዞኛል የሚሉ በርካታ ሰዎች “ፍሉ ስቶፕ” የተሰኘውን ማስታገሻ መድኃኒት በመግዛት ያለሐኪም ምክር እየወሰዱ ይገኛሉ ያሉት አቶ ዮናስ፤ ተመሳሳይ መድኃኒቶችን ያለባለሙያ ምክር መውሰድ በተለይ የደምግፊት፣ ስኳር፣ አስምና ሌሎች ተጓዳኝ በሽታዎች ላለባቸው ሰዎች አደገኛ ነው ብለዋል። ተመሳሳይ መድኃኒቶች በመንግሥት ሆስፒታሎች በሚገኙ ፋርማሲዎች ውስጥ ያለሐኪም ትዕዛዝ እንደማይሸጡ የጠቆሙት አቶ ዮናስ፣ በግል ፋርማሲዎች ግን መድኃኒቱን ለጠየቀ ሁሉ የመሸጥ ልምድ እንዳለ አስረድተዋል። ሰዎችም የጉንፋን ምልክት ስላሳዩ ብቻ ያለሐኪም ምክር ማስታገሻዎችን መውሰዳቸው ለከፋ የጤና ችግር እንደሚያጋልጥ በማወቅ በቅድሚያ መመርመር ይኖርባቸዋል ብለዋል። ያለበለዚያ ግን ለውስብስብ የጤና ችግር የመዳረግ እድላቸው ይሰፋል ሲሉ አሳስበዋል። ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/EPA-01-03 ምንጭ፦ ኢፕድ @tikvahethiopia

#Update አሜሪካ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ስልጣን መልቀቅ በኋላ፣ የሱዳን መሪዎች ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው መግባባትን መፍጠር እና ቀጣይነት ያለው የሲቪል አስተዳደርን ማረጋገጥ አለባ
+1
#Update አሜሪካ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ስልጣን መልቀቅ በኋላ፣ የሱዳን መሪዎች ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው መግባባትን መፍጠር እና ቀጣይነት ያለው የሲቪል አስተዳደርን ማረጋገጥ አለባቸው ብላለች። ሀገሪቱን ይህን ያለችው የጠ/ሚር አብደላ ሀምዶክ ስልጣን መልቀቅን ተከትሎ በአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ በኩል ባወጣችው አጠር ያለ መግለጫ ነው። አሜሪካ ቀጣዩ የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር እና ካቢኔ የህዝብን የነጻነት፣ የሰላም እና የፍትህ ግቦች ለማሳካት በህገ-መንግስቱ መሰረት መሾም አለበት ብላለች። አሜሪካ በመግለጫዋ ላይ የሱዳን ሕዝብ ዴሞክራሲን ለማስፈን በሚያደርገው እንቅስቃሴ ከጎናቸው መቆሟን እንደቀጠለች ገልፃ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ጥቃት መቆም አለበት ስትል አስታውቃለች። @tikvahethiopia

#እንድታውቁት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ ከባድ የእርሻና ኮንስትራክሽን መንጃ ፈቃድ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቋል። በአዲሱ የተቋማት አደረጃጀት መሰረት ቀደም ሲል በፌ
+1
#እንድታውቁት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ ከባድ የእርሻና ኮንስትራክሽን መንጃ ፈቃድ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቋል። በአዲሱ የተቋማት አደረጃጀት መሰረት ቀደም ሲል በፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ሲሰራ የነበረው ከባድ የእርሻና ኮንስትራክሽን መንጃ ፈቃድ አገልግሎት ለአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢሮ በውክልና መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት ቢሮው ከባድ የእርሻና ኮንስትራክሽን መንጃ ፈቃድ አገልግሎት መስጠት የጀመረ መሆኑ በመግለፅ ተገልጋዮች አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ገልጿል። አሽከርካሪዎች አዲስ መንጃ ፈቃድ ለማውጣት በሚሄዱበት ወቅት ምን ያስፈልጋቸዋል ? - የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ ወይም የታደሰ ፓስፖርት፣ - ሲኦሲ ዋናውን፣ - የ8ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ ዋናውን፣ - የ10 ክፍል የትምህርት ማስረጃ ዋናውን ሆኖ ትክክለኛነቱ በሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተረጋገጠ ሰነድ በመያዝ በአካል በመቅረብ አገልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል። ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ @tikvahethiopia

#UPDATE ወደ ላሊባላ ከተማ በረራ ተጀምሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላሊበላ ዕለታዊ በረራውን ዛሬ ጀምሯል። አየር መንገዱ ወደ ከተማዋ መጓዝ የሚፈልጉ መንገደኞች በአየር መንገዱ መተግበሪያ
+1
#UPDATE ወደ ላሊባላ ከተማ በረራ ተጀምሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላሊበላ ዕለታዊ በረራውን ዛሬ ጀምሯል። አየር መንገዱ ወደ ከተማዋ መጓዝ የሚፈልጉ መንገደኞች በአየር መንገዱ መተግበሪያ በመጠቀም ቀጠሮ ማስያዝ እንደሚችሉ አስታውቋል። ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ @tikvahethiopia

#UPDATE😷 የኮቪድ-19 ቀውስ ዓለም አቀፍ መረጃ ፦ 🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ በ5 ወር ውስጥ ከፍተኛውን የኮቪድ-19 ኬዝ ሪፖርት አድርጋለች። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1,024 ሰዎች በቫይረሱ መያ
#UPDATE😷 የኮቪድ-19 ቀውስ ዓለም አቀፍ መረጃ ፦ 🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ በ5 ወር ውስጥ ከፍተኛውን የኮቪድ-19 ኬዝ ሪፖርት አድርጋለች። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1,024 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ይህም በ5 ወር የተመዘገበ ከፍተኛው ቁጥር ነው። ባለፈው ወር ሀገሪቱ የመጀመሪያውን የኦሚክሮን ዝርያ ሪፖርት አድርጋለች። 🇮🇱 እስራኤል ካለፈው መስከረም ወር ወዲህ ከፍተኛውን የኮቪድ-19 ኬዝ ሪፖርት አደርጋለች። ባለፉት 24 ሰዓት 4,197 ሰዎች በቫይረሱ መያዘቸው ተረጋግጧል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ናፍታሊ ቤኔት በኦሚክሮን ዝርያ ስርጭት ሳቢያ በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች ሊጨምሩ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል። 🇮🇳 ህንድ ውስጥ በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች ለ5ኛ ተከታታይ ቀን በእጅጉ መጨመር ያሳየ ሲሆን ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከ27 ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። 🇵🇸 á‰ ááˆáˆľáŒ¤áˆ ፤ ጋዛ በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ መምጣቱ የተገለፀ ሲሆን የፍልስጤም ጤና ሚኒስቴር 4ኛው ማዕበል እየመጣ መሆኑን አስጠንቅቋል። 🇶🇦 ኳታር በሶስተኛው የኮሮና ቫይረስ ማዕበል ላይ እንደምትገኝ የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። ነዋሪዎች የማጠናከሪያ/ተጨማሪ ክትባቱን እንዲወስዱ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። 🇪🇹 በሀገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት 3 ቀናት ብቻ 11,213 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ 32 ሰዎች ህይወታቸው አልፋል። @tikvahethiopia

#BREAKING ጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ ስልጣን ለቀቁ። የሱዳኑ ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሃምዶክ ስልጣን መልቀቃቸውን በይፋ አሳውቀዋል። አብደላ ሀምዶክ ከጦር ኃይሉ ጋር በተደረገው የፖለቲካ ስምምነት
+1
#BREAKING ጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ ስልጣን ለቀቁ። የሱዳኑ ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሃምዶክ ስልጣን መልቀቃቸውን በይፋ አሳውቀዋል። አብደላ ሀምዶክ ከጦር ኃይሉ ጋር በተደረገው የፖለቲካ ስምምነት ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣናቸው ከተመለሱ ከ6 ሳምንታት በኋላ ነው ስልጣናቸውን በገዛ ፍቃዳቸው የለቀቁት። ከጥቂት ቀናት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን ሊለቁ መሆኑን የቱርክ መንግስት ዜና ወኪል የሆነው አናዶሉ ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ምንጭ መስማቱን መዘገቡ ይታወሳል። @tikvahethiopia

የጋዜጠኞች ግድያ ... #በ2021 የጎርጎሮሳውያኑ 2021 ተጠናቆ ከትላንት ጀምሮ አዲሱ ዓመት 2022 ገብቷል። በተሰናበተው 2021 በመላው ዓለም 45 ጋዜጠኞች ተገድለዋል። የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች
+1
የጋዜጠኞች ግድያ ... #በ2021 የጎርጎሮሳውያኑ 2021 ተጠናቆ ከትላንት ጀምሮ አዲሱ ዓመት 2022 ገብቷል። በተሰናበተው 2021 በመላው ዓለም 45 ጋዜጠኞች ተገድለዋል። የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው በ2021 የተመዘገበው የጋዜጠኞች ግድያ ከየትኛውም አመት ከተመዘገበው ዝቅተኛ ቁጥር አንዱ ነው ብሏል። በአንድ ሀገር ከፍተኛ የተመዘገበው አፍጋኒስታን ውስጥ ሲሆን 9 ጋዜጠኞች ተገድለዋል እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ ግድያ የተመዘገበባቸው በሜክሲኮ 8 ፣ በህንድ 4 ፣ በፓኪስታን 3 እንደሆነ ተገልጿል። አፍጋኒስታንን የሚያጠቃልለው ኤዥያ-ፓሲፊክ አካባቢ 20 ግድያዎች የተመዘገቡበትና ከፍተኛው ሲሆን አሜሪካ 10 ፣ አፍሪካ 8 ፣ አውሮፓ 6 እና መካከለኛው ምስራቅ እና አረብ ሀገራት 1 ተመዝግቧል። በኢራን በደረሰ “አሰቃቂ አደጋ” የ2 ጋዜጠኞች ሞትም ጠቅሷል። @tikvahethiopia

+1
#Update የሱዳን ፀጥታ ኃይሎች ዛሬ 2 ሰዎችን እንደገደሉ የዶክተሮች ኮሚቴ አስታወቀ። ዛሬ እሁድ በሱዳን ወታደራዊ አገዛዙን ለመቃወም አደባባይ ከወጡ ሱዳናውያን መካከል የፀጥታ ኃይሎች 2 ሰዎችን መገደላቸውን የሱዳን ዶክተሮች ማዕከላዊ ኮሚቴ አስታውቋል። ኮሚቴው እንዳሳወቀው የመጀመሪያው ሰው በሃያዎቹ ውስጥ የሚገኝ ወጣት ሲሆን በዋና ከተማይቱ ካርቱም በጭንቅላቱ ላይ በደረሰ ጉዳት ሲሞት ሁለተኛው ሰው ደግሞ በኦምዱርማን ደረቱ ላይ በተተኮሰ ጥይት ህይወቱ አልፋል። የዛሬው ግድያ እኤአ ከጥቅምት 25 አንስቶ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ ምክንያት የሞቱ አጠቃላይ ሰዎችን ቁጥር ወደ 56 ከፍ ማድረጉ ተገልጿል። የጸጥታ ሃይሎች ስለተገደሉ ሰዎች እስካሁን ያሉት ነገር የለም። የዛሬው የተቃውሞ ሰልፍ ከመፈንቅለ መንግስቱ በኋላ ለ12ኛ ዙር የተደረገ ከፍተኛ ተቃውሞ ነበር። በካርቱም ከተማ ተቃዋሚዎች ወደ ፕሬዚዳንቱ ቤተ መንግስት ሲያመሩ የጸጥታ ሃይሎች አስለቃሽ ጭስ ስለመተኮሳቸው መነገሩን ሮይተርስ አስነብቧል። @tikvahethiopia

#ተጠናቋል የቁስቋም-እንጦጦ መንገድ ተገንብቶ ተጠናቋል። የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ጫካውን በመሰንጠቅ በአጭር ጊዜ ፣ በከፍተኛ ጥራት ግንባታውን ያከናወነው የባለስልጠን መሥሪያ ቤቱ ራ
+1
#ተጠናቋል የቁስቋም-እንጦጦ መንገድ ተገንብቶ ተጠናቋል። የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ጫካውን በመሰንጠቅ በአጭር ጊዜ ፣ በከፍተኛ ጥራት ግንባታውን ያከናወነው የባለስልጠን መሥሪያ ቤቱ ራስ ኃይል መንገድ ግንባታ ክፍል ነው ሲል አሳውቋል። 3.6 ኪ.ሜ. የሚረዝመው ይህ የጫካ ውስጥ ውበት አስቸጋሪውን አሮጌ መንገድ በመተካት የእንጦጦን ጉዞ አቅልሎታል ተብሏል። ምንጭ፦ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን @tikvahethiopia

#UPDATE በሱዳን ካርቱም ኢንተርኔት በድጋሚ ተዘጋ። በሱዳን ሊካሄድ ከታሰበ የተቃውሞ ሰልፍ ጋር በተያያዘ የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት በድጋሚ መዘጋቱ ተሰምቷል። በቅርቡ በተደረጉ ህዝባዊ ተቃው
+1
#UPDATE በሱዳን ካርቱም ኢንተርኔት በድጋሚ ተዘጋ። በሱዳን ሊካሄድ ከታሰበ የተቃውሞ ሰልፍ ጋር በተያያዘ የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት በድጋሚ መዘጋቱ ተሰምቷል። በቅርቡ በተደረጉ ህዝባዊ ተቃውሞዎች በሱዳን የጸጥታ ሃይሎች የተገደሉትን “ ሰማዕታትን ለማስታወስ ” በሚል እንዲሁም ጥቅምት ወር ላይ ወታደራዊ ክንፉ ያደረገውን መፈንቅለ መንግስት በመቃወምና ሙሉ የሲቪል አስተዳደር ይመስረት በሚል ለዛሬ ሰልፍ ተጠርቷል። ከሰልፉ ጋር በተያያዘ በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም የሞባይል ኢንተርኔት ተቋርጧል ፤ በርካታ የፀጥታ ኃይሎችም በከተማይቱ ተሰማርተዋል፤ ከካርቱም ጋር የሚያገናኙ ድልድዮች በፀጥታ ኃይሎች ተዘግተዋል። ከቀናት በፊት ተካሂዶ በነበረው የተቃውሞ ሰልፍ በኦምዱርማን ከተማ በሱዳን ፀጥታ ኃይሎች የተገደሉ ሰዎች 6 ደርሰዋል። የሱዳን ዶክተሮች ማዕከላዊ ኮሚቴ መረጃ የሱዳን ተቃውሞ ከተጀመረ አንስቶ አጠቃላይ የሞቱ ሰዎች 55 መድረሳቸውን ያመለክታል። @tikvahethiopia

#UPDATE በአማራ ክልል ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ የተቋረጠው የኢንተርኔት አገልግሎት ዳግም መጀመሩን አል ዓይን ኒውስ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። በአማራ ክልል የሞባይል ዳታ አገልግሎት መስራት
+1
#UPDATE በአማራ ክልል ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ የተቋረጠው የኢንተርኔት አገልግሎት ዳግም መጀመሩን አል ዓይን ኒውስ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። በአማራ ክልል የሞባይል ዳታ አገልግሎት መስራት ጀምሯል። ከሰሞኑ ኢትዮቴሌኮም በአማራ እና በአፋር ክልል ዳግም አገልግሎቱን ለማስጀመር ከጸጥታ አካላት ጋር ንግግር መጀመሩን ገልጾ ነበር። ከሀገሪቱ የጸጥታ ተቋማት ጋር እየተነጋረ እንደሆነ በገለጸ በቀናት ውስጥ አገልግሎቱ ተጀምሯል። በዚህም መሰረት በባህር ዳር፣ በጎንደር፣ በደብረታቦር፣ ፣ በወልዲያ፣ በደብረ ማርቆስ፣ በደብረብርሃን፣ በላሊበላ የኢንተርኔት አገልግሎት መጀመሩን ከነዋሪዎች ማረጋገጡን አል ዓይን ኒውስ ገልጿል። @tikvahethiopia

#AAU አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ካለባቸው አካባቢዎች የመጡና የተመረቁ ተማሪዎቹ በታኅሳስ መጨረሻ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበ፡፡ እነዚህ 41 የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች፣ ከኦሮሚያ ክልል
+1
#AAU አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ካለባቸው አካባቢዎች የመጡና የተመረቁ ተማሪዎቹ በታኅሳስ መጨረሻ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበ፡፡ እነዚህ 41 የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች፣ ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ አካባቢ፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እና ከትግራይ ክልል የመጡ ሲሆኑ፣ የመጡበት አካባቢ የፀጥታ ችግር በመኖሩ ከተመረቁ በኋላም በዩኒቨርሲቲው ለመቆየት ማመልከቻ አስገብተው ነበር፡፡ ተማሪዎቹ ከተመረቁ በኋላ በግቢው ውስጥ ሆነው የመኝታና የምግብ አገልግሎት ሲያገኙ መቆየታቸውን የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና የተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ማቲዮስ ኤርሳሞ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይ ግን ተማሪዎቹ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ መስጠቱን ተናግረዋል፡፡ አንዳንድ ተመራቂዎቹ አዲስ አበባ ውስጥ ሥራ ካገኙ በኋላም በግቢው መኖር ቀጥለዋል ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ተማሪዎቹ የመጡበት አካባቢ በትክክል የፀጥታ ስጋት ያለበት ስለመሆኑ ማረጋገጥ አለመቻሉን ገልጸዋል። ከትግራይ ክልል የመጡት ተመራቂዎች በጊዜ ሂደት ሥራ በማግኘታቸውና ወደ መኖሪያቸው በመመለሳቸው አሁን ላይ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉ ከትግራይ የመጡ ተማሪዎች ቁጥር 'ጥቂት' መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ''ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያላቸው ሕጋዊ ውል ይቋረጣል'' ያሉት ኃላፊው፤ ዩኒቨርሲቲው ለተመረቁ ተማሪዎች ወጪ የማውጣት ሥልጣን እንደሌለው ገልጸዋል፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን መስከረም 30/2014 ዓ.ም ማስመረቁ ይታወሳል። ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ @tikvahuniversity

#UPDATE😷 የኮቪድ-19 ቀውስ ዓለም አቀፍ መረጃ ፦ 🇫🇷 ፈረንሳይ ለተከታታይ 4ኛ ቀን ከ200,000 በላይ የኮቪድ-19 ኬዝ ሪፖርት አድርጋለች። መንግስት እድሜያቸው 6 እና ከዚያ በላይ ህፃ
+1
#UPDATE😷 የኮቪድ-19 ቀውስ ዓለም አቀፍ መረጃ ፦ 🇫🇷 ፈረንሳይ ለተከታታይ 4ኛ ቀን ከ200,000 በላይ የኮቪድ-19 ኬዝ ሪፖርት አድርጋለች። መንግስት እድሜያቸው 6 እና ከዚያ በላይ ህፃናት ማክስ ማድረግ አለባቸው ብሏል። ማስክ ማድረግ ያለባቸውን ህፃናት እድሜ ከ11 ወደ 6 ዝቅ በማድረግ ከበዓል እረፍት በኋላ ትምህርት ቤቶችን እንደማይዘጋ ተስፋ አድርጓል። ነገ ትምህርት የሚጀምር ሲሆን ህፃናት በህዝብ ትራንስፖርት ፣ የስፖርት እና በፀሎት ስፍራዎች ማስክ እንዲያደርጉ ተብሏል። 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿 የእንግሊዝ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሳጂድ ጃቪድ በእንግሊዝ ውስጥ የኮቪድ-19 ገደቦችን እንደገና መተግበር “ ፍፁም የመጨረሻ አማራጭ ” እንደሚሆን እና ሀገሪቱ “ ከኮቪድ ጋር ለመኖር መሞከር አለባት ” ሲሉ ተናግረዋል። 🇦🇪 የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ እኤአ ከጥር 10 ጀምሮ ያልተከተቡ ዜጎችን ወደ ውጭ አገር እንዳይጓዙ አግዳለች። ሙሉ በሙሉ የተከተቡ ዜጎች ለመጓዝ ብቁ ለመሆን ማጠናከሪያ ክትባት መከተብ አለባቸውም ተብሏል። እገዳው ለህክምና የሚሄዱትን አይጨምርም። 🇺🇸 በአሜሪካ በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች በእጅጉ መጨመሩን ተከትሎ በርካታ ኮሌጆች ትምህርት ወደ ኦንላንይ ሊመልሱ ነው ተብሏል። ተማሪዎች ከክረምት ዕረፍት ሲመለሱ ቢያንስ ለመጀመሪያው ሳምንት ወይም ሴሚስተር እንደገና ትምህርት በኦንላንይ እንዲወስዱ ሊያደርጉ እንደሆነ ተሰምቷል። 🇪🇹 የኢትዮጵያ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮቪድ -19 መከላከያ ክትባት በሁሉም ጤና ጣቢያ እንደሚገኝ አስታውሰው ያልተከተቡ ዛሬ ነገ ሳይሉ ክትባቱን እንዲወስዱ መልዕክት አስተላልፈዋል። እሳቸው ተጨማሪ ክትባት (Booster Dose) መውሰዳቸውን አሳውቀው ከተከተቡ 6 ወር ያለፋቸው ተጨማሪ ክትባቱን እንዲወስዱ መክረዋል። @tikvahethiopia

#Update የ12ኛ ክፍል ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች ፈተናውን የሚወስዱበት ቀን ይፋ ተደረገ። በ2013 የጸጥታ ችግር በተከሰተባቸው አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ላልወሰዱ ተማሪዎች ከጥ
+1
#Update የ12ኛ ክፍል ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች ፈተናውን የሚወስዱበት ቀን ይፋ ተደረገ። በ2013 የጸጥታ ችግር በተከሰተባቸው አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ላልወሰዱ ተማሪዎች ከጥር 24 እስከ ጥር 27 ቀን 2014 ዓ.ም ፈተናው እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል። በሁለተኛ ዙር የሚሰጠውን ፈተና 58 ሺህ 936 ተማሪዎች እንደሚወስዱም የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ፈይሳ ተናግረዋል።  በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች በፀጥታ ምክንያት ፈተና መወሰድ ያልቻሉ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ አቶ ተፈራ አብራርተዋል። የመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያለምንም ችግር መጠናቀቁን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ ሁለተኛ ዙርም በሰላም እንዲጠናቀቅ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ህብረተሰቡና የሚመለከታቸው አካላት ፈተናው በሰላም መጠናቀቅ እንዲችል የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ዳይሬክተሩ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢቢሲ ዘግቧል። @tikvahethiopia

#AFAR " ዲያስፖራዎች እና ባለሀብቶች አፋርን በመጎብኘት በሙሉ አቅማቸውም ኢንቨስት ቢያደርጉ ተጠቃሚ ይሆናሉ " - ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረ ስላሴ የሰዎች ለሰዎች ድርጅት የበጎ ፈቃድ አምባሳደር
+1
#AFAR " ዲያስፖራዎች እና ባለሀብቶች አፋርን በመጎብኘት በሙሉ አቅማቸውም ኢንቨስት ቢያደርጉ ተጠቃሚ ይሆናሉ " - ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረ ስላሴ የሰዎች ለሰዎች ድርጅት የበጎ ፈቃድ አምባሳደር ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ዛሬ አፋር ሰመራ ተገኝተው ድርጅቱ ለአፋር ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች ያደረገውን ድጋፍ አስረክበዋል። በኋላም የክልሉን የቆላማ ሰንዴ ልማት እና ሌሎች የመስኖ ልማት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸው የታዘቡትን ሲናገሩ " እዚህ በረሃ ላይ እንደዚህ እያየኸው ለማመን የሚከብድ ግን እውነት የሆነ ነገር ስመለከት ለካ የአእምሮ በረሃ እንጂ የመሬት በረሃ የለውም፣ ካለሙት መልማት ይችላል" በማለት ገልፀዋል። ሻለቃ ሀይሌ ባዩት ነገር በጣም መደመማቸውን ገልፀው በዚሁ ቦታ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚፈልጉና ይህንንም በቀጣይ 2 እና 3 አመታት ውስጥ ምርት በማምረት ወደ ውጭ ለመላክ እውን ለማድረግ ለራሳቸው ቃል መግባታቸውን ተናግረዋል። ሻለቃ ሀይሌ ዲያስፖራዎች እና ባለሀብቶች አፋርን በመጎብኘት በሙሉ አቅማቸው ኢንቨስት ቢያደርጉ የውሀ፣ የመሬት እና የአየር ንብረት ችግር የለም በተጨባጭ ያየሁትን ነው የምመሰክረው ብለዋል። በም/ርዕሠ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ የሆኑት አቶ አሊ ሁሴን ዌኢሳ በበኩላቸው በአፋር ክልል ካሉ በርካታ ወንዞች ውስጥ ትልቁ የአዋሽ ወንዝ መሆኑን አውስተው ይህን ወንዝ በጣም በትንሹ ነው እየተጠቀምን ያለነውና ገና ብዙ መስራት እንደሚጠበቅና ዲያስፖራዎችና ባለሀብቶች ወደ ክልሉ በመምጣት ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። ምንጭ፦ የአፋር ብዙሀን መገናኛ ድርጅት @tikvahethiopia

#አብርሆት ከአንድ ነጥብ አንድ (1.15) ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ወጥቶበታል የተባለው የአብርሆት ቤተ-መጽሐፍት ዛሬ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
+5
#አብርሆት ከአንድ ነጥብ አንድ (1.15) ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ወጥቶበታል የተባለው የአብርሆት ቤተ-መጽሐፍት ዛሬ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ተመርቋል። አብርሆት በ19ሺህ ካሬ ሜትር ላይ የተገነባ እጅግ ዘመናዊ ቤተ-መጽሐፍት ሲሆን ዓለም አቀፍ ደረጃዉን ጠብቆ የተገነባ እንደሆነ ተገልጿል። በውስጡ በ4 ወለሎች 1.5 ኪሜ እርዝመት ያለውና 1.4 ሚሊዮን መፃህፍትን መያዝ የሚችል መደርደሪያ አለው። ከ240 ሺህ በላይ የሚሆኑ የወረቅት አልባ መጽሐፍትና 300 ሺህ ጥናታዊ ፅሁፎችን የያዘ መሆኑም የተገለፀ ሲሆን ወላጆች ከልጆቻቸዉ ጋር ማንበብ የሚችሉበትም ነው ተብሏል። ቤተ መጽሐፍቱ የህፃናት ማንበቢያና ማረፊያ ስፍራን ይዟል። ማየት ለተሳነቸው አንባቢዎች በቂ የብሬይል መጽሐፍት አቅርቦት እንዳለው ተገልፃል። በተጨማሪ ዘመናዊ የካፍቴሪያና የመሰብሰቢያ አዳራሾችን፣ ስምንት የመፅሃፍትና ተጓዳኝ አገልግሎት መስጫ ሱቆችን፣ አምፊ ትያትርና መጫወቻ ቦታዎችን እንዲሁም ደህንነቱ የተጠበቀ በአንዴ 115 መኪኖችን ማስተናገድ የሚችል የመኪና ማቆሚያ ስፍራን ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል። @tikvahethmagazine

አብዱልዋሀብ መሐድ ከአሶሳ ማረሚያ ቤት አመለጠ። የቤንሻጉል ሕዝቦች ነጻ አውጭ ንቅናቄ (ቤሕነን) የቀድሞ ሠራዊት መሪ አብዱልዋሀብ መሐድ ታሥሮ ከነበረበት አሶሳ ዞን ማረሚያ ቤት ማምለጡን አንድ ስማቸው ያልተገለፀ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ እንደነገሩት አዲስ ማለዳ ጋዜጣ አስነበበ። የ9 ዓመት ዕሥር የተፈረደበት አብዱልዋሀብ ያመለጠው ታኅሣሥ 18/2014 መሆኑ ተገልጿል። ግለሰቡ ከዚህ በፊትም እንዲሁ 2001 ዓ/ም የዕድሜ ልክ ዕሥራት ተፈርዶበት የነበረ ሲሆን፣ 2002 ላይ ከማረሚያ ቤት አምልጦ ወደ ኤርትራ በመግባት ኢትዮጵያን ከሚወጉ ኃይሎች ጋር ሲሠራ እንደነበር ተገልጿል። ከዚያ በመቀጠል 2009 ዓ/ም ላይ የፌዴራሉ እና የክልሉ መንግሥት ግለሰቡ ከሚመራው ቡድን ጋር ባደረጉት የሠላም ድርድር ተስማምቶ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ሠላማዊ ኑሮ መምራት ጀምሮ ነበር። ግለሰቡ ይመራቸው የነበሩ ታጣቂዎች ከመንግሥት 20 ሚሊዮን ብር መቋቋሚያ ተቀብለው ተበታትነው ከቆዩ በኋላ፣ ሰኔ 2010 ዳግም አሶሳ ላይ ጥቃት በፈጸሙበት ወቅት መሪው ራሱ ተሳታፊ በመሆን የሰው ነፍስ አጥፍቷል ተብሏል። በዚህም ግለሰቡ ተከሶ ሲከራከር ከቆዬ በኋላ፣ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ16 ዓመት ከስድስት ወር ዕሥራት ተፈርዶበት እንደነበር ታወቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ፍርደኛው ለፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ይግባኝ አቅርቦ ቅጣቱ ወደ ዘጠኝ ዓመት ዕሥር ዝቅ ተደርጎለት የነበረ ቢሆንም፣ ዐቃቤ ሕግ በቅጣት ውሳኔው ባለመስማማቱ በፍርድ ክርክር ሒደት ላይ ሳለ ግለሰቡ አምልጦ መጥፋቱ ነው የተነገረው። ግለሰቡ ፍርድ የተሠጠው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተዘዋዋሪ ችሎት ሆኖ ለቤተሰብ እንዲቀርብ በሚል ወደ አዲስ አበባ ሌሎች ፌዴራል ማ/ ቤቶች እንዳልተወሠደ ነው የተጠቆመው። ታሳሪው በፌዴራልና በክልሉ መንግሥት በጥብቅ ሲፈለግ እና ከፍተኛ ክትትል ሲደረግብት የነበረ ከመሆኑም አንጻር፣ በርካታ ዕሥረኞች ካሉበት ማረሚያ ቤት ቀን ላይ በግልጽ ለኹለተኛ ጊዜ ማምለጡ፣ ሴራ ሳይኖርበት እንዳልቀረ ያመላክታል ሲሉ ስማቸው ያልተሀለፀድ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊው ጠቁመዋል። በአሁን ሰዓት የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፀጥታ ኃይሎች እሥረኛውን እየፈለጉት ቢሆንም ቦታው ለሱዳን ካለው ቅርበት እንዲሁም ሰውዬው መውጫ እና መግቢያውን የሚያውቅ፣ በትግልም ለ20 ዓመት ገደማ የቆዬበት በመሆኑ በቀላሉ ሊገኝ ይችላል ተብሎ እንደማይታሰብ ነው የሥራ ኃላፊው የገለጹት። ግለሰቡ ሱዳን ከገባ በኋላም እንደከዚህ ቀደሙ ወጣቶችን መልምሎ በማሠልጠን፣ በመተከልና አሶሳ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ ወረዳዎች ላይ ተመሳሳይ የሆነ የሽብር ድርጊቱን ሊቀጥል እንደሚችል ነው የተመላከተው። የአብዱልዋህብ አጋር የነበሩ ሰዎች ሱዳን ውስጥ በርካታ ወጣቶችን በማሰልጠን ክልሉ ውስጥ ረብሻ ሲፈጥሩ ቆይተዋል ያሉት ኃላፊ ፥ በዚህ የሰውዬው ከእስር ማምለጥ ለአካባቢው ሠላምና ደኅንነት አደገኛ ነው ብለውታል። የአሶሳ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ሐሩን አብዱራማን ፥ አብዱልዋህብ ከተፈረደበት ከስድስት ወር በኋላ የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተጣለበት ቅጣት ላይ ጥያቄ ማቅረቡ ስሜታዊ እንዳደረገው እና ለልማት ሥራ በሚል ከማረሚያ ቤት ሲወጣ በነበረበት ወቅት ላይ እንዳመለጠ ለጋዜጣው ተናግረዋል። ከአብዱልዋህብ መሐድ ውጭ ከማረሚያ ቤቱ ያመለጠ ሌላ ታራሚ እንደሌለ የተናግሩት ኃላፊው ፣ እሱም በቅርብ ቀን በቁጥጥር ሥር ይውላል የሚል ግምት እንዳለቸው ተናገረዋል። ግለሰቡ ወደ ሱዳን እንዳይወጣ ሁሉም ቦታዎች በፀጥታ ኃይሎች መዘጋታቸውን ገልጸው፣ እሥረኛው ወደ ሱዳን ከመሸሽ ይልቅ ተጸጽቶ ተመልሶ ይመጣል የሚል ዕምነት እንዳለቸው ተናግረዋል። ያንብቡ : https://telegra.ph/Addis-Maleda-01-01 ምንጭ፦ #አዲስ_ማለዳ_ጋዜጣ

#Update የሊቀ ጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ አስክሬን በውሃ እንዲሟሟ ሊደረግ ነው። የነጻነት ትግል ቁንጮው ሊቀ ጳጳስ ዴዝሞንድ ከባቢ አየርን በማይጎዳ ሁኔታ አስክሬናቸው በውሃ እንዲሟሟ እንደሚደረግ መገ
+1
#Update የሊቀ ጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ አስክሬን በውሃ እንዲሟሟ ሊደረግ ነው። የነጻነት ትግል ቁንጮው ሊቀ ጳጳስ ዴዝሞንድ ከባቢ አየርን በማይጎዳ ሁኔታ አስክሬናቸው በውሃ እንዲሟሟ እንደሚደረግ መገለፁን ቢቢሲ አስነብቧል። ዴዝሞንድ ቱቱ የአካባቢ መብት ተቆርቋሪ ስለነበሩ አስክሬናቸው በውሃ እንዲሟሟ ተናዘዋል ተብሏል። የነጻነት ታጋዩ አስክሬን በውሃ የሚሟሟበት ሂደት አኳሜሽን (Aquamation) ተብሎ ይጠራል። የሊቀ ጳጳስ ዴዝሞንድ አስክሬን በኬፕ ታውን በሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ውስጥ ተቀምጦ በሺዎች የሚቆጠሩ ደቡብ አፍሪካውያን እየተሰናበቱት ነው። ከመሞታቸው በፊት በተናዘዙት መሠረት "ቅንጡ የቀብር ሥነ ሥርዓት" አይፈልጉም። አስከሬናቸው በጣም ርካሽ በሆነ ሬሳ ሳጥን እንዲቆይ እና በሬሳ ሳጥናቸው ላይ የሚቀመጠው አበባ ከቤተ ክርስቲያን የተገኘ እንዲሆን ተናዘዋል። የአስክሬናቸው ቅሪትም በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ይቀበራል። አስክሬን በውሃ የሚሟሟው እንዴት ነው? አኳሜሽን የሚባለው ሂደት የሚከናወነው የአንድን ሰው አስክሬን በውሃ እና ሀይድሮክሳይድ ውህድ ውስጥ በማሟሟት ነው። መጀመሪያ የግለሰቡ አስክሬን ይመዘናል። ከዚያም የውሃ እና ሀይድሮክሳይድ ውህዱ በ150 ሴንቲ ግሬድ እንዲፈላ ይደረጋል። ከዚያም አስክሬኑ ይሟሟል። ይህ ሂደት ሳይንሳዊ መጠሪያው አልካሊን ሀይድሮሊስስ (alkaline hydrolysis) ይባላል። ለ90 ደቂቃ ያህል አስክሬኑ ከቆየ በኋላ የግለሰቡ ሰውነት ሲሟሟ፣ አጥንቱ ይቀራል። የሟሟውን አስክሬን ለማድረቅ 120 ሴንቲ ግሬድ ሙቀት ይለቀቃል። የግለሰቡ አስክሬን በዚህ መንገድ ሟምቶ አመድ ከወጣው በኋላ አስክሬኑን መቅበር ወይም በሟች ኑዛዜ መሠረት በሚመርጡት አካባቢ መበተንም ይቻላል። ምንጭ፦ ቢቢሲ @tikvahethiopia