en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
#Telegram ቴሌግራም በተጠናቀቀው 2021 / እ.አ.አ. / ድንቅ የሚባል አመትን እንዳሳለፈ የድርጅቱ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቬል ዱሮቭ ዛሬ ምሽት አሳውቀዋል። ጥር ወር ላይ በመላው ዓ
+2
#Telegram ቴሌግራም በተጠናቀቀው 2021 / እ.አ.አ. / ድንቅ የሚባል አመትን እንዳሳለፈ የድርጅቱ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቬል ዱሮቭ ዛሬ ምሽት አሳውቀዋል። ጥር ወር ላይ በመላው ዓለም ላይ በብዛት ዳውንሎድ የተደረገ መተግበሪያ ፣ በጥቅምት ወር በአንድ ቀን ብቻ ከ70 ሚሊዮን በላይ አዳዲስ ተጠቃሚዎችን መቀበል የቻለ እንዲሁም በታህሳስ ወር በፍጥነት እያደገ ያለ መተግበሪያ ተብሎ መታወጁ ተገልጿል። የድርጅቱ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፥ " የእድገቱ ሁሉ ባለቤቶች ተጠቃሚዎቹ እንደሆኑ እናውቃለን " ያሉ ሲሆን በተጠቃሚዎች የሚሰጡትን አስተያየቶች በጥሞና በማድመጥ አመቱን ሙሉ ቴሌግራም ለተጠቃሚዎቹ የተሻለ እንዲሆን አድርገናል ብለዋል። ቴሌግራም በተጠቃሚዎች ጥያቄ መሰረት በቻናሎች፣ ግሩፖች እንዲሁም የአንድ ለአንድ መልዕክ ልውውጥ ወቅት ሪአክሽን መስጫ (👍👎❤️😢...) እንዲሁም የመልዕክት መተርጎሚያ የተካተተበት በዓመቱ 12ኛ ዋና ማሻሻያ ተደርጎበት ተለቋል። አዲሱ የሪአክሽን ማሻሻያ የሚሰራው የቻናሉ ወይም የግሩፑ ባለቤቶች ክፍት ሲያደርጉ ነው። እንዴት ? (ወደ ቻናሉ /ግሩፕ በመግባት Edit ✍ የሚለውን መጫን ፣ በመቀጠል Enable Reactions የሚለውን ON ማድረግ እና የሚሰጡትን Reaction መምረጥ) ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ዋናውን የቴሌግራም መተግበሪያችሁን (ባለ ሰማያዊ ምልክቱን) Update በማድረግ ማሻሻያዎቹን እንድትመለከቷቸው መልዕክት እናስተላልፋለን። የቴሌግራም መተግበሪያችሁን Update ለማድረግ👇 https://play.google.com/store/apps/details?id=org.telegram.messenger @tikvahethiopia

#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ የውጭ አገራት ገንዘብ በሕገወጥ አሠራር ሲመነዘርባቸው ይታዩ የነበሩ ወይም በጥቁር ገበያ ይሳተፉ የነበሩ በዛ ያሉ ሱቆች መታሸጋቸውን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ዘግ
+1
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ የውጭ አገራት ገንዘብ በሕገወጥ አሠራር ሲመነዘርባቸው ይታዩ የነበሩ ወይም በጥቁር ገበያ ይሳተፉ የነበሩ በዛ ያሉ ሱቆች መታሸጋቸውን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ዘግቧል። በተለይ በብሔራዊ ቴአትር እና አካባቢው ፣ ስታዲየምና ዙሪያ ገባው ፣ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ፊት ለፊት እንዲሁም ኢትዮጵያ ሆቴል አካባቢዎች በሚገኙ ልዩ ልዩ አነስተኛ ሱቆች ውስጥ በሚሰሩ ሰዎች አላፊ አግዳሚው ምንዛሪ ይፈልግ እንደሆን በግላጭ ይጠየቅ ነበር። በእነዚህ አካባቢዎች በተለይ ደግሞ ወጣቶች በብዛት ሲሳተፉበት በሚስተዋለው ይህን መሰል ሕገ ወጥ ተግባር የአሜሪካ ዶላርን ፣ የአውሮፓ መገበያያ ገንዘብ ዩሮን፣ ፓውንድንና እና ሌሎች የውጭ አገራት ገንዘቦችን ብሔራዊ ባንክ በየዕለቱ ከሚያወጣው የውጭ አገራት ገንዘብ የምንዛሪ ተመን ከፍ ባለ የተጋነነ ልዩነት ሕገ ወጥ የገንዘብ ምንዛሪ ተግባር ሲፈፅሙ ማየት የተለመደ ዕለታዊ ክስተት ነበር። ሬድዮ ጣቢያው ዛሬ በአካባቢው አደረኩት ባለው ቅኝት አብዛኞቹ ሱቆች በመደዳ በራቸው ላይ #ታሽጓል የሚል ማኅተም ያረፈበት ወረቀት ተለጥፎባቸው ተዘግተውና ለወትሮው በርከት ብለው ይህንኑ ተግባር በመፈጸም ይታዩ ከነበሩ ሰዎች መንገዶቹ ጭር ብለው ታዝቤያለሁ ብሏል። እነዚህ ሱቆች ሲታሸጉ በአካባቢው የነበረውን ሁኔታ የተመለከቱ ሰዎች የማሸግ እርምጃው ' ቀይ ቀለም ያለው ወታደራዊ መለዮ ባጠለቁ ወታደሮች ' ታኅሣሥ 20/2014 ዓ.ም (ረቡዕ) በድንገት እንደተወሰደባቸው ተናግረዋል። በወቅቱ ይሄንኑ ሕገወጥ ሥራ ሲያከናውኑ የነበሩና የተገኙ ሰዎችም እርምጃው ድንገተኛ ስለነበር በእነዚሁ የፀጥታ አካላት ተይዘው እንደተወሰዱ ለጀርመን ሬድዮ ጣቢያ ገልፀዋል። @tikvahethiopia

#ATTENTION በ 'ሰሞኑ ጉንፋን መሰል' ወረርሽኝ ላይ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዛሬ ማብራሪያ ሰጥቷል። በማብራሪያው ህብረተሰቡ አሁን በየቤቱ ፣ በየጎረቤትና በየመስሪያ ቤቱ የሚታየ
+1
#ATTENTION በ 'ሰሞኑ ጉንፋን መሰል' ወረርሽኝ ላይ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዛሬ ማብራሪያ ሰጥቷል። በማብራሪያው ህብረተሰቡ አሁን በየቤቱ ፣ በየጎረቤትና በየመስሪያ ቤቱ የሚታየው እንደ ንፍጥ መዝረብረብ ፣ የራስ ምታት፣ የድካም ስሜት ፣ የመገጣጠሚያና የጀርባ ህመም ፣ ሳል እና የመሳሰሉት ምልክቶች የኮቪድ-19 ሊሆን ስለሚችል " የሰሞኑ/አዲሱ ጉንፋን " በሚል መዘናጋት አስፈላጊ አለመሆኑን አሳስቧል። * ሙሉ ማብራሪያው ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia

#UPDATE የወሎ ዩኒቨርሲቲ ከሶስት ወራት በኋላ ወደ መደበኛ መማር ማስተማር ስራ እንደሚመለስ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ማስታወቁን ኢዜአ ዘግቧል። ፎቶ : ፋይል @tikvahethiopia
#UPDATE የወሎ ዩኒቨርሲቲ ከሶስት ወራት በኋላ ወደ መደበኛ መማር ማስተማር ስራ እንደሚመለስ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ማስታወቁን ኢዜአ ዘግቧል። ፎቶ : ፋይል @tikvahethiopia

" በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የኢትዮጵያ ካርታ ተብሎ የሚሰራጨው ምስል ከእኛ ጋር ግንኙነት የለውም " - የአስተዳደር ወሰን እና ማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ከሰሞኑን ማህበራዊ ሚዲያ የኢትዮጵያ ካርታ ተብሎ
+1
" በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የኢትዮጵያ ካርታ ተብሎ የሚሰራጨው ምስል ከእኛ ጋር ግንኙነት የለውም " - የአስተዳደር ወሰን እና ማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ከሰሞኑን ማህበራዊ ሚዲያ የኢትዮጵያ ካርታ ተብሎ የተሰራጨውን መረጃ የአስተዳደር ወሰን እና ማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን እንደማያውቀው ገልጿል። በመረጃው ላይ የተጠቀሰው የአፍሪካ ህብረት የስራ ተቋም የሌለ መሆኑንም ገልጿል። ኮሚሽኑ የአስተዳደር ጉዳዮችን በተመለከተ እያካሄደ ያለውን ሰፊ ጥናት ወደማገባደዱ እየተቃረበ እንደሚገኝ የገለፀ ሲሆን ነገር ግን ውጤቶችን ከመግለፅ ተቆጥቧል፡፡ ችግሮቹ ተለይተው እና ጥልቅ ምርምሮች ከተካሄዱ በኋላ ህዝባዊ ውይይቶችን እንደሚያደርግ ያስታወቀው ኮሚሽኑ በቀጣይም ምክረ ሃሳቦቹን ለሚመለከታቸው አካላት እንደሚያቀርብም አስታውቋል፡፡ ኮሚሽኑ ሃገራችን ካጋጠማት ጦርነት ጋር በተያያዘም ስራዎቹ ላይ እንቅፋት እንደገጠማቸው አስታውቋል፡፡ ከእንቅፋቶቹም መካከል ውስን ዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች አለመተባበራቸው የፀጥታ ስጋት መኖሩ እና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝም ዋና ዋናዎቹ መሰናክሎች እንደነበሩ አስታውቀዋል፡፡ ኮሚሽኑ ከተሰጠው ጊዜ አንፃር አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ የተሻለን ጥናት እና ምክረ ሃሳብ ለማቅረብ እየጣረ እንደሚገኝ የገለፀ ሲሆን ነገር ግን በይድረስ ይድረስ ጥናቱን እንደማያጠናቅቅ አስታውቋል፡፡ በመሆኑም ጉዳዩን ለምክርቤቱ በማቅረብ በአዋጁ መሰረት ኮሚሽኑ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው እንደሚጠይቅ አሳውቋል። የአስተዳደር ወሰን እና ማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን በአዋጅ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ሶስት አመታት ብቻ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 @tikvahethiopia

ፎቶ : በዝርፊያ ባዶ የቀሩት የWFP መጋዘኖች በሱዳን ፣ ሰሜን ዳርፉር ! በሱዳን ሰሜን ዳርፉር የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን ተዘርፏል። 1,900 ሜትሪክ ቶን ምግብ የተዘረፈ ሲሆን የተዘረፈው ም
+2
ፎቶ : በዝርፊያ ባዶ የቀሩት የWFP መጋዘኖች በሱዳን ፣ ሰሜን ዳርፉር ! በሱዳን ሰሜን ዳርፉር የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን ተዘርፏል። 1,900 ሜትሪክ ቶን ምግብ የተዘረፈ ሲሆን የተዘረፈው ምግብ ለአንድ ወር ከ730,000 በላይ ሰዎችን ለመመገብ በቂ የነበረ ነው። የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዝርፊያውን አጥብቆ አውግዟል። በዝርፊያው ምክንያት በሰሜን ዳርፉር የሚገኘውን የዓለም ምግብ ድርጅት ስራዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ መደረጉን ዴቪድ ባስሌይ (የWFP ዋና ዳይሬክተር) አሳውቀዋል። @tikvahethiopia

" 14 ንፁሃን ተገድለዋል ፤ 9 ሚሊሻዎች ንፁሃኑን ለመታደግ ሲፋለሙ ተሰውተዋል " - የኦሮሚያ ክልል መንግስት የኦሮሚያ ክልል መንግስት አሸባሪው ሸኔ ዛሬ ጥዋት ላይ በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ
" 14 ንፁሃን ተገድለዋል ፤ 9 ሚሊሻዎች ንፁሃኑን ለመታደግ ሲፋለሙ ተሰውተዋል " - የኦሮሚያ ክልል መንግስት የኦሮሚያ ክልል መንግስት አሸባሪው ሸኔ ዛሬ ጥዋት ላይ በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ በፈፀመው ጥቃት 14 ንፁሃን ዜጎች መገደላቸውንና ጥቃቱን ለመከላከል ሲፋለሙ የነበሩ 9 የአካባቢው ሚሊሻዎች ህይወታቸው ማለፉን አሳውቋል። የክልሉ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ በሰጡት ቃል፥ " በምዕራብ ሸዋ ዛሬ ጥዋት አሸባሪው ሸኔ ባደረሰው ጥቃት 14 ንፁሃን ህይወታቸው ሲያልፍ ንፁሃኑን ለመታደግ ሲፋለሙ የነበሩ 9 ሚሊሻዎች ተሰውተዋል። የፀጥታ አካላት በየቦታው ህዝቡን ለማዳን ህይወታቸውን እየሰው ይገኛሉ " ብለዋል። አቶ ኃይሉ ፥ ቡድኑ የፀጥታ አካላትን እንቅስቃሴ እያየ ነው ጥቃት የሚፈፅመው ምንም መዘናጋት አያስፈልግም ፤ ህዝቡም ተደራጅቶ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን እራሱ እና አካባቢውን መከላከል አለበት ሲሉ ተናግረዋል። በጥቃቱ ፈፃሚዎች ላይ እርምጃ ለመውሰድ የፀጥታ አካላት ከአጎራባች ዞኖች ጋር ተናበው እየሰሩ ነው ሲሉም አቶ ኃይሉ አዱኛ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል። @tikvahethiopia

#SUDAN በሱዳን ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ የተካሄደውን መፈንቅለ መንግስት እንዲሁም የሱዳንን ወታደራዊ ክንፍ በመቃወም እና ሙሉ በሙሉ ሲቪል አስተዳደር በመጠየቅ የሚካሄደው ሰልፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ትላንት በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ 4 ሰዎች በሱዳን የፀጥታ ኃይሎች ተገድለዋል፤ በርካቶች ቆስለዋል። እንደ ሱዳን የዶክተሮች ቡድን መረጃ አራቱ የተገደሉት ዜጎች ኦምዱርማን ከተማ ውስጥ ነው። የሱዳን መንግስት ተቃውሞውን ለመግታት ከፍተኛ የፀጥታ ኃይሎች አሰማርቶ ፤ የስልክ እና ኢንተርኔት ግንኙነትንም አቋርጦ ነበር። አሜሪካ ካርቱም በሚገኘው ኤምባሲዋ በኩል በትላንትናው ሰልፍ በትንሹ 4 ሰዎች መገደላቸው እና በደርዘን የሚቆጠሩ መቁሰላቸውን ገልፃ ድርጊቱን አጥብቃ እንደምታወግዝ አሳውቃለች። በሱዳን ጸጥታ አገልግሎት በሚዲያ ተቋማትና በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው የሃይል ጥቃት እንዳሳዘናት የገለፀችው አሜሪካ ባለስልጣናት የፕሬስ ነፃነትን እንዲያስጠብቁ አሳስባለች። በተመሳሳይ የአውሮፓ ህብረት የትላንቱን ግድያ እንዲሁም በተቃዋሚ ሰልፈኞች ላይ የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ ባወጣው መግለጫ ድርጊቱን እንደሚያወግዝ አሳውቋል። Video Credit : Thomas Linge @tikvahethiopia

#ATTENTION የደብረ ብርሃን ከተማ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት በደብረ ብርሃን ከተማ ኮቪድ መሰል ወረርሽኝ በስፋት እየታየ ስለሆነ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት አስገነዘበ። የፅ/ቤቱ ኃላፊ
+1
#ATTENTION የደብረ ብርሃን ከተማ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት በደብረ ብርሃን ከተማ ኮቪድ መሰል ወረርሽኝ በስፋት እየታየ ስለሆነ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት አስገነዘበ። የፅ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ናደው ወንድማገኝ ፥ በከተማው በሁሉም ቀበሌዎች የኮቪድ ወረርሽኝ በሽታ የሚመስል ምልክት የሚታይባቸው ብዙ ሰዎች መታመማቸውን አስረድተዋል፡፡ አሁን ተከሰተ የተባለው ኮቪድ መሰል በሽታ ፦ ሳል፣ ከፍተኛ ትኩሳት እና የማንቀጥቀጥ ስሜት ያለው ነው ያሉት ኃላፊው ምልክቶቹ ከኮቪድ ጋር ይመሳሰላሉ ብለዋል። ማስክ በማድረግ ፣ ርቀትን በመጠበቅ ፣ የእጅን ንፅህና በመጠበቅ እና ሰው ከተሰበሰበበት ቦታ በመራቅ ህብረተሰቡ ከወረርሽኙ ራሱንና ቤተሰቡን እንዲጠብቅ አሳስበዋል፡፡ መረጃው የደ/ብርሃን ከተማ ኮሚኒኬሽን ነው። @tikvahethiopia

#Asmera ባለፈው ሳምንት ታህሳስ 15 ቀን 2014 ዓ/ም በኬንያ ናይሮቢ በ53 ዓመቱ ህይወቱ ያለፈው ደራሲና ጋዜጠኛ ተስፋዬ ገብረአብ ስርዓተ ቀብር ተፈፅሟል። የጋዜጠኛና ደራሲ ተስፍዬ ስርዓተ ቀ
+4
#Asmera ባለፈው ሳምንት ታህሳስ 15 ቀን 2014 ዓ/ም በኬንያ ናይሮቢ በ53 ዓመቱ ህይወቱ ያለፈው ደራሲና ጋዜጠኛ ተስፋዬ ገብረአብ ስርዓተ ቀብር ተፈፅሟል። የጋዜጠኛና ደራሲ ተስፍዬ ስርዓተ ቀብር የተፈፀመው ትላንት አስመራ ውስጥ ዃዝ ዃዝ በተባለ መካነ መቃብር ነው። በቀብር ስነስርዓቱ ላይ ቤተሰቦቹ፣ የጥበበ አድናቂዎች እና ወዳጆቹ ተገኝተው ነበር። ጋዜጠኛ እና ደራሲ ተስፋዬ በኢትዮጵያ ማስታወቂያ ሚኒስቴር የፕሬስ ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም የእፎይታ መጽሄትና ጋዜጦች ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል፡፡ ተከታታይ ጽሆፍችንና በርካታ መጽሀፍትን ፅፏል። ከፃፋቸው መፅሀፍት መካከል ፦ - የቡርቃ ዝምታ - ያልተመለሰው ባቡር - የቢሾፍቱ ቆሪጦች - የጋዜጠኛው ማስታወሻ - የደራሲው ማስታወሻ - የስደተኛው ማስታወሻ - የቅድሜ ማስታወሻ - የጀሚላ እናት - የኑረነቢ ማህደር - የትራቮሎ ዋሻ የሚሉት የሚገኙበት ሲሆን ህይወቱ ከማለፉ በፊት ደግሞ ወደ ህትመት የገባ " ቀይ ዘመን " የተባለ መጽሐፍን ጨምሮ ሌሎችም ጅምር ሥራዎች እንደነበሩት ቪኦኤ ዘግቧል። @tikvahethiopia

#UPDATE😷 የኮቪድ-19 ቀውስ ዓለም አቀፍ መረጃ፦ 🇫🇷 በፈረንሳይ ለ2ኛ ተከታታይ ቀን ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ሪፖርት ተደረገ። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 206,243
#UPDATE😷 የኮቪድ-19 ቀውስ ዓለም አቀፍ መረጃ፦ 🇫🇷 በፈረንሳይ ለ2ኛ ተከታታይ ቀን ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ሪፖርት ተደረገ። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 206,243 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። 🇲🇽 በሜክሲኮ የሟቾች ቁጥር ወደ 300 ሺህ እየተጠጋ ይገኛል፤ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 153 ሰዎች መሞታቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ሟቾች 299,285 ደርሰዋል። 🇷🇺 በሩሲያ በኦሚክሮን የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን እስካሁን 106 ሰዎች መያዛቸው ተረጋግጧል። ተጋላጭ ናቸው ከተባሉ ሀገራት የሚገቡ ተጋዦች ላይ ጠንካራ ምርመራ እየተደርገ ነው። 🇮🇱 እስራኤል የመጀመሪያውን የPfizer ፀረ-ኮቪድ ክኒን ተቀብላለች። 🇵🇹 á–ርቚጋል ለኮቪድ-19 ተጋላጫ የሆኑ ሰዎች እራሳቸውን ለይተው እንዲቀመጡ የሚያስገድደውን መመሪያ ከ10 ቀን ወደ 7 ቀን አሻሽላለች። የጤና ባለሞያዎች ውሳኔውን አደገኛ ብለውታል፤መንግስት ድጋሚ እንዲያስብበት አሳስበዋል። 🇿🇦 á‹°á‰Ąá‰Ľ አፍሪካ በኦሚክሮን ምክንያት ጥላው የነበረውን ሰዓት እላፊ ገደብ አንስታለች። ባለሥልጣናት አገሪቱ 4ኛውን የኮቪድ-19 ማዕበል ጫፍን እንዳለፈች ገልፀዋል። የኦሚክሮን ዝርያ በከፍተኛ ፍጥነት የሚዛመት ቢሆንም ከቀደሙት ዝርያዎች ሲነጻጻር ወደ ሆስፒታል የሚገቡ ሰዎች ቁጥር ዝቅተኛ ነው ተብሏል። በቫይረሱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ደግሞ በመጠኑ መጨመሩን ጠቅሰዋል። 🇺🇸 CDC አሜሪካ ውስጥ የኦሚክሮን ቫይረስ በከፍተኛ መጠን እየተስፋፋ ቢሆንም ወደ ሆስፒታል የሚገቡ እና በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸውን የሚያጡ ሰዎች ቁጥር በአንጻራዊነት ሲታይ ዝቅተኛ ነው ብሏል። ባለፉት ሳምንታት ውስጥ ኦሚክሮን በመላ አገሪቱ በከፍተኛ ፍጥነት የተስፋፋ ሲሆን በተከታታይ ሳምንታትም በዚሁ መልኩ ይቀጥላል ሲል CDC አሳውቋል። @tikvahethiopia

#ProfessorSenaitFisseha ዛሬ የጤና ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ አዳዲስ ምሩቃን ሀኪሞችን በቅጥር ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል ፕሮጀክት ከክልል እና ከከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮዎች
#ProfessorSenaitFisseha ዛሬ የጤና ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ አዳዲስ ምሩቃን ሀኪሞችን በቅጥር ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል ፕሮጀክት ከክልል እና ከከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮዎች ጋር ተፈራርሟል። ፕሮጀክቱ ዘንድሮ ጀምሮ ለ3 ዓመት ይቆያል። በመጀመሪያ አመት 2,898 ሃኪሞች ወደስራ ለማስገባት ታቅዷል። ለዚሁ ለመጀመሪያው ዓመት ስራ የሚያስፈልገው ገንዘብ ከፌዴራል እና ከልማት አጋር ድርጅቶች በሚደረግ ድጋፍ የሚሞላ ነው። ፕሮጀክቱ እንዲጀምር የበፌት ፋውንዴሽን የመጀመሪያውን ዓመት 175 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። የፋውንዴሽኑ የዓለም አቀፍ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር የሆኑት ፕሮፌሰር ሰናይት ፍሰሃ ዛሬ በተካሄደው የፊርም ስነ-ስርዓት ላይ በበይነ መረብ ንግግር አድርገዋል። ፕሮፌሰር ሰናይት የተደረገው ድጋፍ በተለይ ጤና ሚኒስቴር የእናቶችን ሞት 50 በመቶ ለመቀነስ ያስቀመጠውን ግብ እንዲያሳካ እንደሚያግዝ ገልፀዋል። በተጨማሪ ኢትዮጵያውያን ሃኪሞችን ወደ ስራ በማስማራት የባለሙያዎችን እጥረት ለመቅረፍና ኮቪድ-19 በእናቶችና ስነ-ተዋልዶ ጤና አጠባበቅ ላይ ሰፊ ተጽዕኖ እንዳያሳድር ወረርሽኙን ለመከላከል ከሚደረግ ሰፊ እንቅስቃሴ ጎን ለጎን የጤና ተቋማት ፤ የእናቶች ጤና እና የቤተሰብ ዕቅድ ጨምሮ ሌሎችም መሰረታዊ የስነ-ተዋልዶ አገልግሎቶችን አጠናክረው መስጠት እንዲችሉ ሰፊ እገዛ እንደሚያደርግ ፕሮፌሰር ሰናይት ተናግረዋል። ምንጭ፦ ጤና ሚኒስቴር @tikvahethiopia

#MoH አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን ወደ ስራ ማስገባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ። የጤና ሚኒስቴር አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን በቅጥር ወደ ስራ ማስገባት የሚያስችል የፕሮጀክት ስምምነት ከክልል እና ከከ
+1
#MoH አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን ወደ ስራ ማስገባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ። የጤና ሚኒስቴር አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን በቅጥር ወደ ስራ ማስገባት የሚያስችል የፕሮጀክት ስምምነት ከክልል እና ከከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮዎች ጋር ተፈራረመ። የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ፕሮክጀቱ በብዙ ልፋት ተመርቀው ስራ ላይ ያልተሰማሩ ሃኪሞችን ወደ ስራ የሚያሰማራ በመሆኑ በጤናው ዘርፍ ትልቅ እምርታ ነው ብለዋል፡፡ ከተያዘው አመት ጀምሮ የሚተገበረው ይህ ፕሮጀክት የሶስት ዓመት ቆይታ እንደሚኖረው ገልፀዋል። በመጀመሪያው ዓመት 2 ሺ 898 ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማሰማራት መታቀዱን ተናግረዋል። ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልገው በጀትም የመጀመሪያው ዓመት ከፌዴራል መንግሥት እና ከአጋር ድርጅቶች በተገኘ ገንዘብ የሚሸፈን ሲሆን፥ ሁለተኛው እና ሶስተኛው ዓመት ከፌዴራል፣ ከክልልና ከከተማ አስተዳደሮች እና ከአጋር የልማት ድርጅቶች ድጋፍ በተገኘ ገንዘብ የሚተገበር ይሆናል። ከአራተኛው ዓመት በኋላ ሙሉ በሙሉ በክልሎች አቅም እንደሚተገበርም ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል። ምንጭ፦ ጤና ሚኒስቴር @tikvahethiopia

#ETHIOPIA ሀገራችን ኢትዮጵያ በአቋም መፈተሻ ጨዋታ ሱዳንን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፋለች። አማኑኤል ገብረ ሚካኤል 2 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን አንዱን ጎል ሽመልስ በቀለ አስቆጥሯል። የብሄራዊ
#ETHIOPIA ሀገራችን ኢትዮጵያ በአቋም መፈተሻ ጨዋታ ሱዳንን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፋለች። አማኑኤል ገብረ ሚካኤል 2 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን አንዱን ጎል ሽመልስ በቀለ አስቆጥሯል። የብሄራዊ ቡድናችን ከአፍሪካ ዋንጫ መጀመር አስቀድሞ ካሜሮን በመግባት ለውድድሩ አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ እያደረገ ይገኛል። More : @tikvahethsport

#LALIBELA ከፊታችን ታህሳስ 25 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ታሪካዊቷ ከተማ ላሊበላ እለታዊ የበረራ አገልግሎት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ አሳውቋል። @tikvahethiopia
#LALIBELA ከፊታችን ታህሳስ 25 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ታሪካዊቷ ከተማ ላሊበላ እለታዊ የበረራ አገልግሎት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ አሳውቋል። @tikvahethiopia

#ጠቁሙ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ባካሄደው 2ኛ ልዩ ስብሰባው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265 /2014 ማጽደቁ ይታወሳል፡
#ጠቁሙ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ባካሄደው 2ኛ ልዩ ስብሰባው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265 /2014 ማጽደቁ ይታወሳል፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 12 ንዑስ አንቀጽ 1 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የዕጩ ኮሚሽን አባላትን ከህዝብ፣ ከፖለቲካ ድርጅቶች ና ከሲቪል ማህበራት እንደሚቀበል ተደንግጓል፡፡ በዚህም መሰረት የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቀበያ ጽ/ቤት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቋቁሟል፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 13 መሰረት ለኮሚሽነርነት የሚያበቁ መሥፈርቶችም፡- 1/ ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ የሆነ፤ 2/ ሁሉንም ሃይማኖቶች፣ የተለያዩ ብሔሮችን፣ ብሔረሰቦችን እና ሕዝቦችን በእኩል ዓይን የሚያይ፤ 3/ የማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ፤ 4/ ለአገራዊ መግባባት ጉልህ አስተዋፅዖ ሊያበረክት የሚችል ፤ 5/ መልካም ሥነ-ምግባርና ስብዕና ያለው፤ 6/ በሕዝብ ዘንድ ዓመኔታ ያለው፣ 7/ በከባድ ወንጀል ተከሶ የጥፋተኝነት ውሳኔ ያልተላለፈበት ፤ 8/ የኮሚሽኑን ሥራ በአግባቡ ለመሥራት የሚያስችል የተሟላ ብቃት ያለው፤ 9/ ሙሉ ጊዜውን ለኮሚሽኑ ስራ ለማዋል ፍቃደኛ የሆነ። የሚሉ ናቸው፡፡ የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ ፡- • በቀጥታ ስልክ 0111300340 ወይም 9988 • በፋክስ ቁጥር 0111233007 • በኢ-ሜል dialoguecommission@gmail.com ወይም • በ info@hopr.gov.et ወይም • በአካል በም/ቤቱ መረጃ ማአከል መስጠት ይቻላል። በቀጣይ ሶስት ቀናት ውስጥ ጠቆማ የሚሰጥበትን ቅጽ www.hopr.gov.et እንደሚጭን የህ/ተ/ምክር ቤት አሳውቋል። @tikvahethiopia

#ETHIOPIA #SUDAN ዛሬ #ኢትዮጵያ ሀገራችን ከጎረቤት ሀገር #ሱዳን ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታዋን እያደረገች ትገኛለች። ይህ ጨዋታ እየተካሄደ የሚገኘው የሁለቱም ሀገራት ብሄራዊ ቡድኖች በአፍ
+2
#ETHIOPIA #SUDAN ዛሬ #ኢትዮጵያ ሀገራችን ከጎረቤት ሀገር #ሱዳን ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታዋን እያደረገች ትገኛለች። ይህ ጨዋታ እየተካሄደ የሚገኘው የሁለቱም ሀገራት ብሄራዊ ቡድኖች በአፍሪካ ዋንጫ ለመካፈል ባቀኑባት ካሜሮን ሀገር ነው። የሀገራችን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት በትልቁ የአፍሪካ የእግር ኳስ ውድድር የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ከውድድሩ ቀደም ብሎ ወደ ካሜሮን አቅንቷል። ቡድናችን ካሜሮን ከደረሰ በኃላ በየዕለት ልምምድ እየሰራ ውድድሩ እስኪጀመር እየተጠባበቀ ይገኛል። ዛሬ አቋሙን የሚፈትሽበት ጨዋታ እያደረገ ነው። ሀገራችን በተወከለችበት ትልቁ የአፍሪካ የእግር ኳስ ውድድር መድረክ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትም ወደ ስፍራው ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር ያቀኑ ሲሆን በስፖርት ገፃችን ላይ መረጃዎችን ያካፍላሉ። የቲክቫህ ስፖርት ገፅ ፦ https://t.me/+VvwzStMNcNHmhK0x @tikvahethsport

አልሸባብ ? ሶማሊያ ውስጥ ያለው ውጥረትና በፕሬዜዳንቱ እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ መካከል ያለው ቅራኔ ለአልሸባብ የሽብር ቡድን በር እንዳይከፍት ተሰግቷል። ዛሬ ጥዋት ላይ የ #አልሸባብ ታጣቂዎች ከዋና
አልሸባብ ? ሶማሊያ ውስጥ ያለው ውጥረትና በፕሬዜዳንቱ እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ መካከል ያለው ቅራኔ ለአልሸባብ የሽብር ቡድን በር እንዳይከፍት ተሰግቷል። ዛሬ ጥዋት ላይ የ #አልሸባብ ታጣቂዎች ከዋና ከተማይቱ ሞቃዲሾ በስተሰሜን በምትገኝ ከተማ ላይ ጥቃት ሰንዝረው ከተማውንም ለመቆጣጠር ሞክረው እንደነበር ተዘግቧል። አልሸባብ ጥቃቱን የከፈተው ከሞቃዲሾ 30 ኪ.ሜ ያህል በምትርቀው ስትራቴጂክ ከተማ #ባላድ እንደሆነ የተሰማ ሲሆን በጥቃቱ ሰዎች ተገድለዋል። እንደ ቪኦኤ ዘገባ ከሆነ ፥ የሶማሊያ ጦር ኃይል በወሰደው የመልሶ ማጥቃት እርምጃ የሽብር ቡድኑን ባላድን የመያዝ ሙከራውን አክሽፏል። በአሁን ሰዓት ከተማዋ ሙሉ በሙሉ በመንግስት እጅ ስር እንዳለችም ገልጿል። በዛሬው ጥቃት 4 የመንግስት ወታደሮች እንደተገደሉ ቪኦኤ ሲዘግብ የሶማሊያ መንግስት ሚዲያ በበኩሉ በጥቃቱ 9 የአልሸባብ ታጣቂዎች መገደላቸውን እና በአሸባሪዎች በተተኮሰ ሞርታር 5 ንፁሀን ዜጎች መሞታቸውን ዘግቧል። @tikvahethiopia

#ችሎት አቶ ስብሐት ነጋን ጨምሮ 5 ተከሳሾች በህመም ምክንያት ዛሬ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ። አሞናል በማለት ፦ - አቶ ስብሐት ነጋ ፣ - አቶ አባዲ ዘሙ፣ - አቶ ዘሚካኤል አንባዬ፣ - ዶ/ር ሙላት ይርጋ እና አቶ ቴድሮስ ሀጓስ ዛሬ ፍርድ ቤት አልቀረቡም። የማረሚያ ቤት ተወካይ 5ቱ ተከሳሾች አሞናል በማለታቸው ምክንያት áŠĽáŠ•á‹łáˆ‹áˆ˜áŒŁá‰¸á‹ አስረድቷል። ቀሪዎቹ ማለትም ፦ - ወ/ሎ ኬሪያ ኢብራሂም ፣ - አንባሳደር አባይ ወልዱ ፣ - ዶ/ር አብርሐም ተከስተ ፣ - ዶ/ር ሰለሞን ኪዳኔ፣ - አንባሳደር አዲስ አለም ባሌማ ፣ - ወ/ሎ ሙሉ ገ/ እግዛብሔርን ጨምሮ 16 ተከሳሾች ግን በችሎት ተገኝተዋል። 16 ቱ ተከሳሾች የቀረቡት በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የፀረ ሽብርና የህገመንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። ችሎቱ የተከሳሾች የክስ መቃወሚያ ውጤት ለመጠባበቅ እና " ሹር ኮንስትራክሽን " ን ጨምሮ በክሱ የተካተቱ ድርጅቶች áˆ˜áŒĽáˆŞá‹Ť እንዲደርሳቸው የተሰጠውን ትዛዝ ማረጋገጫ ውጤት ለመጠባበቅ ነበር ዛሬ የተሰየመው። በተጨማሪ በ44 ኛ ተከሳሽ áˆˆáˆáˆ­áˆ˜áˆŤ የተያዘብኝ ሰነዶች ይመለሱልኝ ሲሉ ያቀረቡት አቤቱታ áˆ‹á‹­ ትዛዝ ለመስጠት ነው። የችሎት ውሎውን ንብቡ : https://telegra.ph/Trial-12-30-2 ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

#MinistryofFinance የ122 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ተዘጋጀ። በገንዘብ ሚኒስቴር የተዘጋጀ የ122 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀረበ፡፡ ተጨማሪ በጀቱ ፦ • ለሀገር
#MinistryofFinance የ122 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ተዘጋጀ። በገንዘብ ሚኒስቴር የተዘጋጀ የ122 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀረበ፡፡ ተጨማሪ በጀቱ ፦ • ለሀገር ደህንነት ማስጠበቂያ፣ • ለሰብአዊ እርዳታ፣ • በጦርነትና ግጭቶች ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ማቋቋሚያ እንዲሁም ለሌሎች አስፈላጊ የመንግስት ስራዎች ማስፈጸሚያ የሚውል ነው፡፡ ተጨማሪ በጀቱን ማዘጋጀት ያስፈለገው ፦ • በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተካሄደው ጦርነት ምክንያት ተጨማሪ ወጪ በማስፈለጉ፣ • መንግስት በሚሰበስበው ገቢ አሁን ያለውን የክፍያ ጥያቄ መመለስ አስቸጋሪ በመሆኑ • የተጨማሪ ወጪ ፍላጎትን በበጀት ሽግሽግ ማስተናገድ አዳጋች በመሆኑ ነው። የተጨማሪ በጀት ጥያቄው በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውይይት ተደርጎበት እንደ ጸደቀ በቀጥታ ስራ ላይ እንደሚውል ታውቋል፡፡ ምንጭ፦ የገንዘብ ሚኒስቴር @tikvahethiopia