en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
የመን ሰነዓ ውስጥ 12 ሰዎች ተገደሉ። በሳዑዲ አረቢያ የሚመራው ጥምር ጦር በየመን ዋና ከተማ ሰነዓ ላይ የአየር ድብደባ ፈፅሟል። የአየር ድብደባ የተፈፀመው ሁቲዎች በተባበሩት አረብ ኤሜሪት ላይ ጥ
የመን ሰነዓ ውስጥ 12 ሰዎች ተገደሉ። በሳዑዲ አረቢያ የሚመራው ጥምር ጦር በየመን ዋና ከተማ ሰነዓ ላይ የአየር ድብደባ ፈፅሟል። የአየር ድብደባ የተፈፀመው ሁቲዎች በተባበሩት አረብ ኤሜሪት ላይ ጥቃት ሰንዝረው 3 ሰዎች መግደላቸው እና 6 ሰዎች መቁሰላቸው ከተሰማ በሰዓታት ውስጥ ነው። በሳዑዲ አረቢያ የሚመራው ጥምረት በሰነዓ በፈፀመው የአየር ድብደባ ከ12 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እንደገለፁ አልጀዚራ ዘግቧል። ሀውቲዎች ግን የሞቱ ሰዎች 20 እንደሚደርሱና በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውን አመልክተዋል። ዩኤኢ ላይ ተጨማሪ ጥቃት ሊፈፅሙ እንደሚችሉ የዛቱት ሁውቲዎች ሲቪሎች እና የውጭ ሀገር ሰዎች ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ ወሳኝ ከሆኑና አስፈላጊ ተቋማት እንዲርቁ አስጠንቅቀዋል። @tikvahethiopia

#Update ትላንት በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (ዩኤኢ) ላይ ከሁቲዎች የተፈፀመውን የድሮን ጥቃት ሀገራት እና ተቋማት እያወገዙት ይገኛሉ። ሳዑዲ አረቢያ ትላንት ሰኞ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ውስጥ
+1
#Update ትላንት በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (ዩኤኢ) ላይ ከሁቲዎች የተፈፀመውን የድሮን ጥቃት ሀገራት እና ተቋማት እያወገዙት ይገኛሉ። ሳዑዲ አረቢያ ትላንት ሰኞ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ውስጥ በሲቪል አካባቢዎች እና መገልገያዎች ላይ ያነጣጠረው የሁውቲ ጥቃት " የሽብር ጥቃት " መሆኑን በመግለፅ በፅኑ አውግዛዋለች። ባህሬን፣ ኩዌት ፣ ኳታር ፣ ሞሮኮ፣ ግብፅ ፣ ኦማን እንዲሁም የአረብ ፓርላማ ጥቃቱን አውግዘዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ የሃውቲውን ጥቃት አውግዘዋል ሁሉም አካላት ከፍተኛ ቁጥጥር እንዲያደርጉ አሳስበዋል። የአንቶኒዮ ጉተሬዝ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች “በሲቪሎች እና በሲቪል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች በአለም አቀፍ ህግ የተከለከሉ ናቸው” ብለዋል። በየመን ላለው ግጭትም ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለው ተናግረዋል። አሜሪካ ጥቃቱን አውግዛ ጥቃቱን ስለመፈፀሙ ኃላፊነት የወደሰው ሀውቲን ተጠያቂ ለማድረግ ይሰራል ስትል ዝታለች። የየመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥቃቱ ባለፈው ሳምንት ሙሉ በሙሉ በሻብዋ እና በነዳጅ ዘይት የበለፀገችው ማሪብ ግዛት ላይ ሚሊሻዎች ከደረሰባቸው ሽንፈት በኋላ የተሰማቸውን ብስጭት ያሳያል ብሏል። ሚኒስቴሩ ሳዑዲ እና ዩኤኢ የሽብር ድርጊቶችን ለመከላከል ፣ የዜጎቻቸውን እና ነዋሪዎቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ የሚወስዱትን እርምጃ እንደሚደግፍም ገልጿል። ጥቃት የተፈፀመባት የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ለተፈፀመባት ጥቃት ምላሽ የመስጠት መብቷ የተጠበቀ መሆኑን የገለፀች ሲሆን ሁቲዎች ተጨማሪ ጥቃት ሊፈፅሙ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል። @tikvahethiopia

#AFRICA በ #AFCON_2021 ውድድር ከወዲሁ ምድባቸው ማለፍ የቻሉ አራት ሀገራት ፦ 🇨🇲 ካሜሩን 🇲🇦 ሞሮኮ 🇳🇬 ናይጄሪያ 🇧🇫 ቡርኪናፋሶ ከምድቧ ማለፍ ሳትችል ቀርታ ከውድድሩ ቀድ
#AFRICA በ #AFCON_2021 ውድድር ከወዲሁ ምድባቸው ማለፍ የቻሉ አራት ሀገራት ፦ 🇨🇲 ካሜሩን 🇲🇦 ሞሮኮ 🇳🇬 ናይጄሪያ 🇧🇫 ቡርኪናፋሶ ከምድቧ ማለፍ ሳትችል ቀርታ ከውድድሩ ቀድማ መሰናበቷ የተረጋገጠው ደግሞ ኢትዮጵያ 🇪🇹 ናት። More : @tikvahethsport

እንኳን አደረሰን ፤ አደረሳችሁ ! እንኳን ለከተራ በዓል አደረሰን ፤ አደረሳችሁ። ውድ ቤተሰቦቻችን የከተራ በዓል ድባብ በአካባቢያችሁ ምን ይመስላል ? በ @tikvahethiopiaBot ላይ አጋሩን።
እንኳን አደረሰን ፤ አደረሳችሁ ! እንኳን ለከተራ በዓል አደረሰን ፤ አደረሳችሁ። ውድ ቤተሰቦቻችን የከተራ በዓል ድባብ በአካባቢያችሁ ምን ይመስላል ? በ @tikvahethiopiaBot ላይ አጋሩን። ስትንቀሳቀሱ የምትመለከቷቸውን ሁነቶች በእጅ ስልካችሁ ካሜራ በማስቀረት አጋሩ፤ መልዕክቶቹን ስትልኩ ፎቶውን ያነሳውን ሰው ስምና የተነሳበትን ከተማ መፃፍ እንዳትዘነጉ። #TikvahFamily❤️ @tikvahethiopia

#UAE ዛሬ UAE ውስጥ በድሮን መሆኑ በተገመተ ጥቃት ቢያንስ 3 ሰዎች ሲገደሉ ፤ 6 ሰዎች ቆስለዋል። የዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ (UAE) ባለሥልጣናት የደሃቢ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አካል
+1
#UAE ዛሬ UAE ውስጥ በድሮን መሆኑ በተገመተ ጥቃት ቢያንስ 3 ሰዎች ሲገደሉ ፤ 6 ሰዎች ቆስለዋል። የዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ (UAE) ባለሥልጣናት የደሃቢ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አካል በሆነው ስፍራ የሚገኙ 3 የነዳጅ ማጠራቀሚያ ታንከሮች በድሮን መሆኑ የተገመተ ጥቃት የደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል። የአገሪቱ መንግሥት ዜና አገልግሎት ባለሥልጣናቱን ጠቅሶ እንዳስታወቀው በደረሰው ጥቃት ቢያንስ ሶስት ሰዎች የሞቱ ሲሆን ሌሎች ስድስት ደግሞ መቁሰላቸው ተመልክቷል፡፡ ከሟቾቹ መካከል 2 ህንድ እና 1 የፓኪስታን ዜጋ እንደሚገኙበት ተነገሯል፡፡ ፖሊስ ሁኔታው እየተጣራ መሆኑን ቢገልጽም የየመን ሁቲዎች ዛሬ ሰኞ በሰጡት መግለጫ ወደ ዩናይትድ አረብ ኤምሬት (UAE) ጠልቆ የሚገባ ጥቃት የሰነዘሩ መሆናቸውን ቢያስታውቁም ስለ ሁኔታው ግን ዝርዝር መግለጫ አልሰጡም፡፡ ሁቲዎች ዩናይትድ አረብ ኤምሬት ላይ ተጨማሪ ጥቃት ሊፈፅሙ እንደሚችሉም አስጠንቅቀዋል። የዩናይትድ አረብ ኤምሬት (UAE) እ.ኤ.አ. ከ2015 ጀምሮ የየመን ሁቲዎችን የሚወጋውና በሳኡዲ አረብያ የሚመራው የጦር ህብረት አባል መሆንዋ ይታወቃል፡፡ ዘገባውን ቪኦኤ አሶሼይትድ ፕሬስ እና አጃንስ ፍራንስ ፕሬስን ዋቢ አድርጎ ያዘጋጀው ሲሆን በተጨማሪ የአልጀዚራ መረጃ ተካቶበታል። @tikvahethiopia

#SUDAN ዛሬ በጎረቤት ሀገር ሱዳን 7 ሲቪሎች ተገደሉ። የሱዳን ዶክተሮች ማዕከላዊ ኮሚቴ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ በዛሬው እለት በተካሄደ የፀረ መፈንቅለ መንግስት ሰላማዊ ተቃውሞ ሰልፍ 7 ንፁ
+1
#SUDAN ዛሬ በጎረቤት ሀገር ሱዳን 7 ሲቪሎች ተገደሉ። የሱዳን ዶክተሮች ማዕከላዊ ኮሚቴ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ በዛሬው እለት በተካሄደ የፀረ መፈንቅለ መንግስት ሰላማዊ ተቃውሞ ሰልፍ 7 ንፁሀን ዜጎች በፀጥታ ሀይሎች በተተኮሰ ጥይት መገደላቸውን አሳውቋል። ኮሚቴው ፥ " የጁንታው ኃይሎች ጭፍጨፋቸውን ቀጥለውበታል፣ ሰላማዊ የሱዳን ተቃዋሚዎች ገዳይ ከሆነ ሃይል ጋር እየተጋፈጡ ነው " ብሏል። በዛሬው ሰልፍ በቀጥታ በተተኮሱ ጥይቶች ምክንያት በርካታ ጉዳቶች ሪፖርት መደረጋቸውን እና ጉዳት የደረሰባቸው ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑንም ገልጿል። ኮሚቴው ፤ መላው ዓለም በሰላማዊ መንገድ ለ ነጻ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊት አገር ወደፊት እየተጓዘ ያለውን የሱዳን ህዝብ ላይ ሆን ተብሎ የሚፈፀመውን አሰቃቂ ወንጀሎች በቅርበት መከታተል እና ለማስቆምም ከበድ ያለ እርምጃ ሊወስድ ይገባዋል ሲል አስገንዝቧል። የሱዳን ዶክተሮች ማዕከላዊ ኮሚቴ ፥ ከወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ወዲህ የተገደሉ ሰላማዊ ሰዎች ቁጥር 71 እንደደረሰ ሪፖርት አድርጓል። @tikvahethiopia

ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ሊቀ ጳጳስ ዘኢሉባቡር አረፉ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬ
ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ሊቀ ጳጳስ ዘኢሉባቡር አረፉ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ጥር 9 ቀን 2014 ዓ.ም ረፋድ ላይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የብፁዕነታቸው የቀብር ሥነሥርዓት እና ቀብራቸው የሚፈጸምበት ቦታን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ካስተላለፈ በኋላ ይገለፃል ተብሏል። መረጃው የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። @tikvahethiopia

“አንድም መንግስት ‘እነዚህ ሰዎች ታስረዋልና ፍታ ብሎ የጠየቀኝ የለም” - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ትላንት በቤተ መንግስት በተዘጋጀ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ፤ በቅርቡ ከእስር የተፈቱ እስረኞችን በተመለከተ “ጉዳዩን እኛም መጀመሪያ ስንሰማ ደንግጠን ነበር” በሚል ለተናገሩት ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል። እስረኞችን ለመፍታት ከውሳኔ ላይ የተደረሰው ከወር በፊት እንደነበር የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሆኖም የሚፈቱ የእስረኞች ዝርዝር እርሳቸውን ጨምሮ ለካቢኔ አባላት የቀረበው የዛሬ ሁለት ሳምንት ገደማ የህዳሴው ግድብ በሚገኝበት ስፍራ በተደረገ የሚኒስትሮች ስብሰባ ወቅት እንደነበር አስረድተዋል። “እውነቱን ለመናገር ፖለቲካሊ እስረኞችን ለመፍታት ‘እነዚህን ጉዳዮች እናሳካ ነው’ ያልነው እንጂ፤ እነማን ይፈቱ የሚለውን በቀደም ህዳሴ [ግድብ] የሚኒስትሮች ስብሰባ እስካደረግንበት ቀን ድረስ እኔም አላውቅም። እንፍታ ብለን ወስነናል። ዐቃቤ ህግ ሲያጠና ቆይቶ፤ ዝርዝር አመጣልን። ‘እነ እንትናማ አይቻልም፤ እነ እንትና ይቻላል’ ተጨቃጭቀን የተወሰኑ ሰዎች ላይ ወስነን መጣን” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ ሂደቱ ገለጻ አድርገዋል። እስረኞችን ለመፍታት ሲወሰን የንግግሩ ማዕከል “ግለሰቦች አልነበሩም” ያሉት አብይ፤ የውይይቱ ማጠንጠኛ “የበጎ ፍቃድ ምልክት (gesture) እና ሆደ ሰፊነት (magnanimity) ያስፈልጋል” የሚል እንደነበር ገልጸዋል። “ሀሳቡ፤ ዝም ብሎ ድርቅ ያለ ነገር አድርገን ሀገራችንን እንዳንጎዳ የሚል ነው” ሲሉም አክለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከውሳኔው ጀርባ “የሌላ ሀገር ግፊት አለ” በሚል ለሚቀርቡ አስተያየቶችም በትላንቱ ንግግራቸው ምላሽ ሰጥተዋል። እስረኞቹ እንዲታሰሩም ሆነ እንዲፈቱ ጥያቄ ያቀረበ “አንድም መንግስት” እንደሌለ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “አንድም መንግስት ‘እነዚህ ሰዎች ታስረዋልና ፍታ ብሎ የጠየቀኝ የለም” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። የእስረኞች ፍቺ ጉዳይ በገዢው ብልጽግና ፓርቲ ውይይት የተደረገበት ከአንድ ወር በፊት መሆኑን የጠቆሙት አብይ፤ ውሳኔው “እስከ ታች ድረስ” ውይይት የተደረገበት እንጂ “እንግዳ ጉዳይ” እንዳልነበር ገልጸዋል። “ሁሉም ክልል ተወያይቶበታል። አሁን ድንገት ደርሶ ‘ድንገት ሆነብኝ’ የሚለው ተቀባይነት የለውም። ከወር በላይ ተወያይተንበታል። አዲስ ነገር አይደለም” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። Credit : ኢትዮጵያ ኢንሳይደር @tikvahethiopia

800,000💵 ትላንትና ምሽት በታላቁ ቤተ-መንግስት " በገበታችን ሀገር እንገንባ ፤ በትብብር ወገን እናግዝ " በሚል መርህ በተካሄደ የእራት መርሀ ግብር ከትኬት ሽያጭ ብቻ ከ800 ሺህ ዶላር በላ
+1
800,000💵 ትላንትና ምሽት በታላቁ ቤተ-መንግስት " በገበታችን ሀገር እንገንባ ፤ በትብብር ወገን እናግዝ " በሚል መርህ በተካሄደ የእራት መርሀ ግብር ከትኬት ሽያጭ ብቻ ከ800 ሺህ ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ መገኘቱ ተሰምቷል። የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ በትላንት ምሽቱ የእራት መርሀ ግብር ከትኬት ሽያጭ በቀጥታ ከ800 ሺህ ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን አስታውቋል። በመረሐግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዳያስፖራ አደረጃጀት መሪዎች፣ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ተገኝተው ነበር። @tikvahethiopia

#AddisAbaba የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ የጥምቀት በዓልን ለማክበር የሚወጣው ምዕመን ግጭት ቀስቃሽ ጽሑፎችን እና አርማ የሌላቸውን ባንዲራ ይዞ መውጣት እንደማይችል አስታወቀ:: ፖሊስ ኮሚሽኑ በ
+1
#AddisAbaba የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ የጥምቀት በዓልን ለማክበር የሚወጣው ምዕመን ግጭት ቀስቃሽ ጽሑፎችን እና አርማ የሌላቸውን ባንዲራ ይዞ መውጣት እንደማይችል አስታወቀ:: ፖሊስ ኮሚሽኑ በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል፡፡ የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ለአሀዱ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ምዕመኑ ከበዓሉ አላማ ውጭ የሆኑ ድርጊቶችን ከማድረግ ተቆጥበው በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት ሲሉ ተናግረዋል:: በዓሉ ያለምንም የፀጥታ ስጋት በሰላም እንዲጠናቀቅ ከበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ጋር በመሆን የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል:: በዓሉ የአደባባይ በመሆኑ በሁሉም አካባቢዎች ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲኖር በግልጽና በስውር የተጠናከረ ጥበቃ መኖሩን ጠቅሰዋል። በዓሉ በሚከበርባቸው ሁለት ቀናት ወደ ማክበሪያ ቦታው መግባት የሌለባቸው ግጭት የሚቀሰቅሱ ጽሑፎች ፣ አርማ የሌለው ባንዲራ እንዲሁም ስለታማ ነገሮች ይዞ መግባት እንደማይቻልም አጽኖት ሰጥተው ተናግረዋል:: ምንጭ : አሀዱ ሬድዮ (ፎቶ - ከኢዜአ) @tikvahethiopia

#ሰሜን_ኮሪያ ሰሜን ኮሪያ ሁለት የተጠረጠሩ የአጭር ርቀት ባላስቲክ ሚሳኤሎችን (SRBM) በመዲናዋ ፒዮንግያንግ ከሚገኝ አውሮፕላን ማረፊያ መተኮሷን የደቡብ ኮሪያ ጦር ማሳወቁን ሮይተርስ ዘግቧል::
#ሰሜን_ኮሪያ ሰሜን ኮሪያ ሁለት የተጠረጠሩ የአጭር ርቀት ባላስቲክ ሚሳኤሎችን (SRBM) በመዲናዋ ፒዮንግያንግ ከሚገኝ አውሮፕላን ማረፊያ መተኮሷን የደቡብ ኮሪያ ጦር ማሳወቁን ሮይተርስ ዘግቧል:: ጃፓን በተመሳሳይ መወንጨፉን ሪፖርት አድርጋ ድርጊቱን የሰላም እና የፀጥታ ጠንቅ ነው ስትል አውግዛለች። ቻይና በበኩሏ ሁሉም ወገኖች የቀጠናውን መረጋጋት እንዲያስጠብቁ ስትል አሳስባለች:: ዛሬ ሰሜን ኮሪያ እንዳስወነጨፈች የተነገረው የሚሳኤል ሙከራ በዚህ ወር 4 ኛው ነው ተብሏል:: ኒውኩሌር የታጠቀችው ሰሜን ኮሪያ ከዛሬ በፊት ከ2 ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ 3 የሚሳኤል ሙከራዎች አድርጋለች:: ይህም ያልተለመደ ፈጣን ተከታታይ ሙኩራ ነው ተብሏል:: @tikvahethiopia

#ጥምቀት የኢፌዴሪ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ዛሬ ባወጣው መግለጫ የጥምቀት በዓል በሰላም ተከብሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉን አሳውቋል። የበዓሉ ታዳሚዎችና እንግዶች ደ
+1
#ጥምቀት የኢፌዴሪ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ዛሬ ባወጣው መግለጫ የጥምቀት በዓል በሰላም ተከብሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉን አሳውቋል። የበዓሉ ታዳሚዎችና እንግዶች ደህንነታቸው የተጠበቀ እንዲሆንና በዓሉን በሰላም እንዲከበር ግብረ ኃይሉ ከወትሮው በተለየ መልኩ በቂ ዝግጅት በማድረግ ስምሪት ወስዶ ወደ ተግባር መግባቱን ገልጿል፡፡ ግብረኃይሉ ፥ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በርካታ የፀጥታ አካላት ማሰማራቱን ገልፆ በታቦታት ማደሪያ ስፍራዎችና በርካታ የበዓሉ ታዳሚዎች በሚገኙበት አካባቢ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ ከጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የደህንነት ስጋቶችን አስቀድሞ ለመከላከል የተከላከሉ ተግባራት ፦ • ከበዓሉ ጋር በተያያዘ ርችት መተኮስ ፍፁም የተከለከለ ነው። • በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ ከሚመለከተው አካል ፈቃድ የሌላቸው ግለሰቦች እና ተቋማት ድሮን ማብረር ወይንም ማንቀሳቀስ አይችሉም። • ምንም አይነት የጦር መሳሪያ፣ ተቀጣጣይም ሆነ ስለታማ ቁሳቁስ ይዞ መንቀሳቀስ አይቻልም። የበዓሉ ታዳሚዎች ለደህንነት ሲባል ፍተሻ የሚደረግ መሆኑን ከወዲሁ በማወቅ እና በመረዳት ትብብር እንዲያደርጉ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል። አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ በፍጥነት ለጋራ ግብረ-ኃይሉ ጥቆማ ለመስጠት በስልክ ቁጥር ፦ • +251115-52-63-03፣ • +251115-52-40-77፣ • +251115-54-36-78 እና • +251115-54-36-81 እንዲሁም በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች መጠቀምና በአካባቢው ላለ የፀጥታ ኃይል መረጃውን በአካል ማድረስ ይቻላል። * ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia

#DireDawa የቀድሞ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ 3.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የመኪና ስጦታ ተበረከተላቸው። ለቀድሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ አስተዳደሩ በአመራርነት ዘመናቸ
+2
#DireDawa የቀድሞ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ 3.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የመኪና ስጦታ ተበረከተላቸው። ለቀድሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ አስተዳደሩ በአመራርነት ዘመናቸው ላበረከቱት መልካም ስራዎች የምስጋና ኘሮግራም ተካሄዶል። በዚሁ ፕሮግራም ላይ 3.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ዘመናዊ የመኪና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል። የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጆሀር በምስጋና ፕሮግራሙ ላይ " ጥቂት ብንዘገይም፤ እጅግ ለምንወዳቸው የቀድሞ ከንቲባችን እና ወንድማችን አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ ዛሬ ያደረግነው ሽኝትና የሰጠነው ስጦታ፤ በአመራርነት ዘመኑ ካደረጉት አሰተወፅኦ አንፃር ለሳቸው ያንስባቸዋል እንጂ አይበዛም " ሲሉ ተናግረዋል። ስጦታው በባለሀብቶች ተሳትፎ የተበረከተ መሆኑ ተገልጿል። የቀድሞው ከንቲባ ለሶስት ዓመት ሙሉ ከተማዋ የነበረባትን የፀጥታ ችግር የፀጥታ አካላትን በማሰባሰብ ፣ አመራሮችን በማቀናጀት የከተማዋ ሰላም በአስተማማኝነት እንዲረጋገጥ እና ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ አመራር የሰጡ ጠንካራ መሪ እንደነበሩ ተገልጿል። በትላንትናው ዕለት ከቀድሞ ከንቲባው በተጨማሪ የድሬዳዋ ፀጥታ አካላት ፣ የፀጥታ ምክር ቤት አባላት ከ25 ሺህ ብር እስከ 100 ሺህ ብር በየደረጃው ተሸልመዋል። አጠቃላይ ሽልማቱ ከ700 ሺህ ብር በላይ እንደሆነ ተመላክቷል። ብሩ የተገኘው ከባለሀብቶች ሲሆን የመንግስት በጀት እንዳልተነካ ተገልጿል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተጠይቀው ቀና ምላሽ ለሰጡ የከተማው ባለሀብቶች ምስጋና አቅርቧል። @tikvahethiopia

ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ምድቧን የማለፍ እድል አላት ? የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በምድብ ሀ ሦስተኛ የጨዋታ መርሐ ግብር ከቡርኪና ፋሶ አቻው ጋር ዛሬ ምሸት 1 ሰዓት ላይ በባፎሳም ስታዲየ
+1
ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ምድቧን የማለፍ እድል አላት ? የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በምድብ ሀ ሦስተኛ የጨዋታ መርሐ ግብር ከቡርኪና ፋሶ አቻው ጋር ዛሬ ምሸት 1 ሰዓት ላይ በባፎሳም ስታዲየም ያካሂዳል። ለመሆኑ ሀገራችን ኢትዮጵያ ምድቧን የማለፍ እድል አላት ? ትላንት መግለጫ የሰጡት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ተከታዩን ተናግረዋል ፦ " ሁለት ቡድኖች በቀጥታ ከምድቡ ያልፋሉ። ጥሩ ሶስተኛ ሆኖ የሚያልፍም ይኖራል። ጨዋታውን ማሸነፍ በሌሎች ውጤት ላይ የሚወሰን ቢሆንም የመጀመርያው ነገር ጨዋታውን ማሸነፍ ነው። የማለፍ ጉዳይ በቀጣይ የሌሎች ውጤትን ተመርኩዞ ነው የሚወሰነው። ከዚህ ባሻገር በቡድናችን ላይ ችግሮች ተመልክተናል ፤ በተለይ በአእምሮው ረገድ። በዛ ላይ ከሰራን ፣ ባለን ነገር ላይ እምነት ካለን እና እህንንም ወደ ተጫዋቾቹ ማስረፅ ከቻልን ማድረግ እንደምንችል አምናለሁ። እድሉ አለን ፤ እንደምናሳካም አምናለሁ። " @tikvahethiopia

#ነፃ_ዋይፋይ ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ ፣ እንጦጦ ፣ አንድነት ፓርክ እና የወዳጅነት አደባባዮች በከፍተኛ ወጪ የዋይፋይ (WiFi) አገልግሎት ገንብቶ በነጻ ማቅረቡን ዛሬ
#ነፃ_ዋይፋይ ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ ፣ እንጦጦ ፣ አንድነት ፓርክ እና የወዳጅነት አደባባዮች በከፍተኛ ወጪ የዋይፋይ (WiFi) አገልግሎት ገንብቶ በነጻ ማቅረቡን ዛሬ ገልጿል። @tikvahethiopia

#Update የዓለም ጤና ድርጅት በዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ቅሬታ እና ክስ ቢቀርብም በጦርነት ለተጎዳው የትግራይ ክልል ህዝብ እርዳታ መጠየቁን እንደሚቀ
+1
#Update የዓለም ጤና ድርጅት በዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ቅሬታ እና ክስ ቢቀርብም በጦርነት ለተጎዳው የትግራይ ክልል ህዝብ እርዳታ መጠየቁን እንደሚቀጥል አስታውቋል። ባለፈው ዓርብ የኢትዮጵያ መንግስት ዶክተር ቴድሮስ ጎጂ እንዲሁም የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት እና TPLFን በመደገፍ የተሳሳተ ተግባር ላይ መሳተፋቸውን በመግለፅ ከሶ ድርጅቱ ምርመራ እንዲያከናውን መጠየቁ ይታወሳል። ዛሬ የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ መንግስት በይፋ ክስ ማቅረቡን አረጋግጧል። ድርጅቱ ግን 7 ሚሊዮን ለሚደርሰው የትግራይ ክልል ህዝብ መሰረታዊ አገልግሎት እንዲደርስ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲፈቅድ መጠየቁን እንደሚቀጥል አሳውቋል። ባለፈው ዓርብ ዕለት የኢትዮጵያ መንግስት ቅሬታውን ያቀረበው ባለፈው ሳምንት ዶ/ር ቴድሮስ መንግስት ወደትግራይ ክልል መድሃኒትና የነፍስ አድን እርዳታዎች እንዳይገባ እየከለከለ ነው በማለት በክልሉ ያለው ሁኔታ ሲኦል ነው ብለው ከገለፁ በኃላ ነው። መንግስት ፥ ዶ/ር ቴድሮስ የሰጡት አሰተያየት የዓለም የጤና ድርጅትን ተአማኒነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚጥል ፤ የተጣለባቸውን ህጋዊ እና ሞያዊ ኃላፊነት ጥሰው በመገኘታቸው ምርመራ እንዲደረግ ጠይቆ ነበር። በተመድ የኢትዮጵያ ልዑክም ዶ/ር ቴድሮስ የፖለቲካ ውግንና እንዳላቸው በመግለፅ ኢትዮጵያን ከሚመለከቱ ጉዳዮች እራሳቸው እዲያርቁ ጠይቆ እንደነበር የፈረሳይ ዜና አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል። ዶ/ር ቴድሮስ ከሰጡት አስተያየት ጋር በተያያዘ የአማራ እና አፋር ክልል ባለስልጣናት ጠንካራ ትችት ሰንዝረው ዶ/ር ቴድሮስ የተናገሩት ለህወሓት ፕሮፖጋንዳ መሆኑንና በአፋር እና አማራ ክልል ህወሓት ስላደረሰው ጥፋት ተናግረው እንደማያውቁ መግለፃቸው አይዘነጋም። @tikvahethiopia

#GERD🇪🇹 አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዚህ ሳምንት በሰጡት መግለጫ ከተናገሩት ፦ (ከሪፖርተር) " ... የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኤሌክተሪክ ማመንጨት የሚጀምርበትን ቀን
+1
#GERD🇪🇹 አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዚህ ሳምንት በሰጡት መግለጫ ከተናገሩት ፦ (ከሪፖርተር) " ... የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኤሌክተሪክ ማመንጨት የሚጀምርበትን ቀን ይህ ነው ብሎ መነገር ባይቻልም፣ በጣም በቅርብ ጊዜ ይጀምራል። የግድቡ ጉዳይ ሊለወጥ የማይችልና ያለቀ ነገር በመሆኑ፣ የታችኛው ተፋሰስ አገሮች ከዚህ ካለቀ ጉዳይ ጋር አብረው መቆም አለባቸው። ከዚህ በኋላ ግድቡ ሲያመነጭ ለግብፆችም ሆነ ለሱዳኖች ጠቃሚ ከመሆኑም በላይ ፣ á‰ áˆšáˆ˜áŠáŒ¨á‹ ኃይል ሌሎችም አገሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እነዚህ አገሮች ቢሠሩ መልካም ነው። ነገር ግን የሦስትዮሽ ድርድሩ ይቁም ማለት አይደለም። ሱዳን እና ግብፅ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከጀመራቸሁ ችግር ይፈጠራል፣ ሰማዩ ይገለባበጣል የሚሉት ነገር አዲስ አይደለም፡፡ ቀድሞውንም ሙሌት ከጀመራችሁ አደጋ ይፈጠራል፣ ጉድ ይፈላል ሲሉ ነበር ይህ ፉከራ የተለመደ ቢሆንም አሁን ግን ያረጀና ጊዜው ያለፈበት ሆኗል። በህዳሴ ግድቡ ውኃው ተርባይኑን አንቀሳቅሶ አልፎ ስለሚሄድ መጠኑ ስለማይቀንስ፣ ሱዳኖች የግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመር ሊያስደስታቸው እና ሊያከብሩት ይገባል። " @tikvahethiopia

የአዲስ አበባ ድጋፍ ፦ አዲስ አበባ ከተማ ዛሬ እና ትላንት ለሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን በድምሩ የ150 ሚሊዮን ብር የአይነት ድጋፍ አድርጋለች። ዛሬ በኦሮሚያ ክልል በቦረና
+2
የአዲስ አበባ ድጋፍ ፦ አዲስ አበባ ከተማ ዛሬ እና ትላንት ለሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን በድምሩ የ150 ሚሊዮን ብር የአይነት ድጋፍ አድርጋለች። ዛሬ በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የ50 ሚሊዮን ብር የአይነት ድጋፍ ተደርጓል። በመጀመርያ ዙር 51 ሚሊዮን ብር የሚገመት ድጋፍ የተደረገ ሲሆን በሁለት ዙር በአጠቃላይ 101 ሚሊዮን ብር የሚሆን ድጋፍ ማድረስ ተችሏል። ትላንት ደግሞ በሶማሌ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በድርቅ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ100 ሚሊዮን ብር የምግብ ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጓል። ምንጭ፦ የአ/አ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፅ @tikvahethiopia

#Update የሶማሊያ ጠቅላይ ሚንስትር መሀመድ ሁሴን ሮቤል በሀገሪቱ መንግስት ቃል አቀባይ መሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ላይ ያነጣጠረውን አሰቃቂ ያሉትን የሽብር ጥቃት አወገዙ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሽብር
+1
#Update የሶማሊያ ጠቅላይ ሚንስትር መሀመድ ሁሴን ሮቤል በሀገሪቱ መንግስት ቃል አቀባይ መሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ላይ ያነጣጠረውን አሰቃቂ ያሉትን የሽብር ጥቃት አወገዙ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሽብር ጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው ቃል አቀባዩ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ብለዋል። ጠ/ሚ መሀመድ ሁሴን ሮብሌ ፥ ለመሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ፈጣን ማገገምን ተመኝተዋል። እስካሁን ለአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም። @tikvahethiopia

" በአፋር በኩል ጦርነቱ አልቆመም "- አፋር ክልል የአፋር ክልል መንግስት ፥ ህወሓት በሰላም ወዳዱ የአፋር ህዝብ ላይ በድጋሚ እያካሄደ ያለውን የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ በአስቸኳይ ማቆም አለበት ሲል
+1
" በአፋር በኩል ጦርነቱ አልቆመም "- አፋር ክልል የአፋር ክልል መንግስት ፥ ህወሓት በሰላም ወዳዱ የአፋር ህዝብ ላይ በድጋሚ እያካሄደ ያለውን የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ በአስቸኳይ ማቆም አለበት ሲል አስጠንቅቋል። ክልሉ ፥ " አሸባሪው ህወሓት በኪልበቲ ረሱ / ዞን ሁለት / በአብአላ በኩል ከታህሳስ 10/2014 ጀምሮ በከፈተው አዲስ ግንባር በተከታታይ እየተኮሰ ባለው ከባድ መሳሪያ ንፁሀን ዜጎችን መጨፍጨፉን ቀጥሏል" ብሏል። አክሎ ፥ "የትግራይን ህዝብ ከሁሉም ኢትዮጵያውያን ጋር ለማናከስ ቆርጦ የተነሳው አሸባሪው ህወሀት በትግራይ ክልል አዋሳኝ በሆነው በዚሁ አካባቢ የትግራይን ህዝብ ከጎረቤቱ ጋር በማናከስ፣ ጉርብትና እንዲሻክርና ጎረቤቶችን በማጣላት የራሳቸውን እድሜ ለማራዘም አፋር እና ትግራይ ጎረቤት ህዝቦችን እያናከሰ ይገኛል" ሲል አሳውቋል። ክልሉ፥ "ጎረቤታሞች በሰላም ውሎ እንዳያድር ትልቅ ጥረት በማድረግ ላይ ነው" የሚለው የአፋር ክልል" የትግራይ ህዝብም ይሄንን የጀንታውን እብደት ሊቃወም ይገባል፤ በቃቹህ ሊሉ ይገባል" ሲል አስገንዝቧል። ቡድኑ በንፁሀን የአፋር ህዝብ ላይ በተለይም በኪልበቲ ረሲ ዞን አብአላና መጋሌ በኩል የከፈተውን በጥብቅ ሊያወግዝ ይባልም ብሏል። የአፋር ክልሉ መንግስት " ህወሓት በከባድ መሳሪያ ንፁሀንን የመግደል የመጨፍጨፍ ተግባሩን አሁንም አላቆመም፣በአፋር በኩል ጦርነቱ አልቆመም፣ ንፁሀን ሴት፣ ህፃናት እና አዛውንት አሁንም ሰለባ እየሆኑ ነው" ብሏል። የዓለም ህብረተሰብ የህወሓትን ድርጊት እንዲያወግዝ ጥሪ አቅርቧል። ህወሓት ፥ በሚቆጣጠረው የትግራይ ቲቪ በኩል ባወጣው መግለጫ የአፋር ልዩ ኃይል በህዝባችን ላይ ተከታታይ ግፎችና ጭፍጨፋዎች እየፈፀመ ሰንብቷል ሲል ከሷል። ያንብቡ : telegra.ph/Afar-Tigray-01-16 @tikvahethiopia