en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
#Update የቀድሞ የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣን አምባሳደር ዶ/ር ካሳ ከበደ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈፀማል። የአምባሳደር ዶ/ር ካሳ ከበደ አስከሬን ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ የገባ ሲሆን የቀብር ስነስርዓታቸው
+3
#Update የቀድሞ የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣን አምባሳደር ዶ/ር ካሳ ከበደ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈፀማል። የአምባሳደር ዶ/ር ካሳ ከበደ አስከሬን ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ የገባ ሲሆን የቀብር ስነስርዓታቸው ከሰዓታት በኃላ በቅድስት ስላሴ ካቴደራል ቤተክርስቲያን እንደሚፈፀም ኢዜአ ዘግቧል። አምባሳደር ዶ/ር ካሳ ከበደ በደርግ ዘመን የኢትዮጵያ ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩ ሲሆን በታጠቅ ጦር ሰፈር፣ ህፃናት አምባ ፣ ጀግኖች አምባ መቋቋም ላይ ድርሻ እንደነበራቸው እንዲሁም በኢሰፓ ውስጥ የጎላ ሚና እንደነበራቸው ይነገራል። በተለያዩ ሀገራትም የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ሀገራቸውን አገልግለዋል። በ80 ዓመታቸው በአሜሪካ ሀገር ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት አምባሳደር ዶ/ር ካሳ ከበደ የአንድ ወንድ እና የሁለት ሴት ልጆች አባት ነበሩ። @tikvahethiopia

#Update " በድርቅ ምክንያት የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል " - የሶማሊ ክልል መንግስት በሶማሌ ክልል የተከሰተው ድርቅ ዜጎችን ለሞት እየዳረገ መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታውቋል። የሶማሌ ክል
+1
#Update " በድርቅ ምክንያት የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል " - የሶማሊ ክልል መንግስት በሶማሌ ክልል የተከሰተው ድርቅ ዜጎችን ለሞት እየዳረገ መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታውቋል። የሶማሌ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አብዱልቃድር ረሺድ ለአሀዱ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል በክልሉ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል። በጥቅምት መዝነብ የነበረበት ዝናብ ባለመዝነቡ በክልሉ የሚገኙ 9 ዞኖች ለድርቅ ተጋልጠው የነበረ ሲሆን አሁን ድርቁ ወደ 10ኛው ዞን መሸጋገሩን ኃላፊው ተናግረዋል። በዚህም በተለይም በክልሉ 4 ዞኖች በዳዋ ፣ አፍዴራ፣ ሸበሌ እና ቆራሔ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት 1 መቶ 46 ሺሕ 8 መቶ 6 እንስሳት መሞታቸውን ገልፀዋል፡፡ በድርቁ የሚሞቱ እንስሳት ቁጥር በቅርብ ቀናት ሊጨምር እንደሚችል ስጋት መኖሩንም ጠቅሰው ፤ በድርቁ የተነሳ በክልሉ የሚገኙ 2 ነጥብ 4 ሚሊየን ሕዝብ ለችግር መጋለጡን አስረድተዋል፡፡ ሚያዚያ ወር ላይ የሚጠበቅ ዝናብ እንዳለ የገለፁ ሲሆን ዝናብ ካልዘነበ ድርቁ ከዚህም በላይ የከፋ እንደሚሆንና በርካታ ዜጎችን ሊያሳጣ እንደሚችል ስጋት መኖሩን ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል። @tikvahethiopia

#AliBira አንጋፋው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ በአዳማ ጄኔራል ሆስፒታል ህክምና እየተከታትሉ ይገኛሉ። የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ክቡር ዶ/ር አርቲስት
+2
#AliBira አንጋፋው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ በአዳማ ጄኔራል ሆስፒታል ህክምና እየተከታትሉ ይገኛሉ። የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ህክምና እየተከታተሉ በሚገኙበት ሆስፒታል በአካል በመገኘት እንደጠየቋቸው የጉሙሩክ ኮሚሽን አሳውቋል። ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ለክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ ከህመማቸው ተፈውሰው የሚወዱትን ሙያ እንዲቀጥሉ እና ሀገራቸውን በኪነጥበብ መስክ እንዲያገለግሉ መልካም ምኞታቸውን እንደገለፁላቸው ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። @tikvahethiopia

ፌልትማን ሀሙስ ኢትዮጵያ ይመጣሉ። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማ ሀሙስ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ተነግሯል። ፌልትማን ኢትዮጵያ የሚመጡት ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣና
+1
ፌልትማን ሀሙስ ኢትዮጵያ ይመጣሉ። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማ ሀሙስ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ተነግሯል። ፌልትማን ኢትዮጵያ የሚመጡት ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር በሰላም ድርድር ጉዳይ ለመነጋገር እንደሆነ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ መናገራቸውን የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ዘግቧል። አምባሳደር ፌልትማን በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ከከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩ ቢገለፅም እነማንን እንደሚያገኙ አልተጠቀሰም። አምባሳደር ፌልትማን በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ወደ ትግራይ ክልል ይሄዱ እንደሆነ ፕራይስ ተጠይቀው ለአሁን መናገር የሚችሉት አምባሳደሩ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ለመነጋገር እንደሆነ አመልክተዋል። ቃል አቀባዩ ፥ በውይይቱ ዝርዝር ላይ መናገር የሚችሉት በማጠቃለያው እንደሆነ እና ዝርዝሩንም በፅሁፍ እንደሚያወጡ ገልፀዋል። ፕራይስ ፥ አምባሳደር ፌልትማን ከኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር እንዲነጋገሩ አሁን ያለው ሁኔታ አመቺ መሆኑን ጠቁመው ሁለቱም ወገኖች ውጊያ እንዲያቆሙና ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንዲቀርቡ ዕድል እንደሚሰጥ አመልክተዋል። አምባሳደር ፌልትማን ኢትዮጵያ ሲገቡ የውይይቱ ይዘት ይኸው እንደሚሆን ገልፀዋል። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማ ከዚህ ቀደም የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት በሰላማዊ መንገድ ይፈታ ዘንድ ጥረት ለማድረግ በተደጋጋሚ ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው ይታወቃል። @tikvahethiopia

ዋንግ ዪ ኤርትራ ገቡ። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማምሻውን ኤርትራ ገብተዋል። ዋንግ ዪን እና የልዑካን ቡድናቸው አስመራ ኤርፖርት ሲደርሱ በኤርትራ
+2
ዋንግ ዪ ኤርትራ ገቡ። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማምሻውን ኤርትራ ገብተዋል። ዋንግ ዪን እና የልዑካን ቡድናቸው አስመራ ኤርፖርት ሲደርሱ በኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ዋንግ ዪ በኤርትራ ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና ከአቻቸው (ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ) ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። Photo Credit : Yemane G. Meskel @tikvahethiopia

#US #Eritrea አሜሪካ በኤርትራ ያሉ የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ አሳሰበች። አሜሪካ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና መንግስታቸው የህሊና እስረኞችን እንዲፈቱ አሳስባለች። አስመራ የሚገኘው የአሜሪካ
+1
#US #Eritrea አሜሪካ በኤርትራ ያሉ የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ አሳሰበች። አሜሪካ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና መንግስታቸው የህሊና እስረኞችን እንዲፈቱ አሳስባለች። አስመራ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ፥ " ፕሬዜዳንት ኢሳያስ እና መንግስታቸው በግእዝ የገና በዓል መንፈስ እና በክርስትናውም ሆነ በእስልምናው እምነት ውስጥ ይቅርታ ያለውን ትልቅ ሚና በመገንዘብ የኤርትራ የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ አሜሪካ ታሳስባለች ። " ብሏል። በአስመራ የሚገኘው አሜሪካ ኤምባሲ ስላሰራጨው መልዕክት በኤርትራ መንግስት ሆነ ባለስጣናት በኩል የተሰጠ ምላሽ/አስተያየት የለም። @tikvahethiopia

#Harari በፖሊስ የአምቡላንስ መኪና የኮንትሮባንድ እቃ ሲያዘዋውሩ የተገኙ አካላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ መሆኑን የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ። የክልሉ ፖሊስ ዛሬ በሰጠው መ
#Harari በፖሊስ የአምቡላንስ መኪና የኮንትሮባንድ እቃ ሲያዘዋውሩ የተገኙ አካላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ መሆኑን የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ። የክልሉ ፖሊስ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በፖሊስ ኮሚሽን የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከያና መቆጣጠሪያ አምቡላንስ በቀን 24/ 4/ 2014 ዓ.ም በህገወጥ መንገድ በርካታ የኮንትሮባንድ እቃዎችን ጭኖ ሲንቀሳቀስ አወዳይ ከተማ ላይ በቁጥጥር ስር እንደዋለ ገልጿል። አምቡላንሱ የኮንትሮባንድ እቃ የጫነ ቢሆንም ታማሚ የያዘ በመምሰልና የአምቡላንስ ድምፅ በማሰማት ሲንቀሳቀስ በቁጥጥር የዋለው። ተሽከርካሪው እና አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን አሽከርካሪው ለጊዜው መሰወሩና በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም የተከሰተውን ህገወጥ ድርጊት በወቅቱ ለበላይ አካል ማሳወቅ ሲገባቸው ያላሳወቁ አባላትም በቁጥጥር ስር ውለዋል። አሽከርካሪው አምቡላንሱን ከኮሚሽኑ ቅጥር ጊቢ ጎማ ለማሰራት በሚል በህገ ወጥ መንገድ ያለ መውጫ ይዞ እንዳወጣ ፖሊስ አሳውቋል። ምንጭ፦ የሀረሪ ክልል ኮሚኒኬሽን @tikvahethiopia

#Ethio_Sudan ለስድስት ወራት የተዘጋው በመተማ - ጋላባት በኩል ኢትዮጵያን ከሱዳን የሚያገናኘው መንገድ ነገ ክፍት ይሆናል ተብሏል። ዛሬ የኢትዮጵያ እና የሱዳን ወታደራዊ አመራሮች እና የሁለቱ
+1
#Ethio_Sudan ለስድስት ወራት የተዘጋው በመተማ - ጋላባት በኩል ኢትዮጵያን ከሱዳን የሚያገናኘው መንገድ ነገ ክፍት ይሆናል ተብሏል። ዛሬ የኢትዮጵያ እና የሱዳን ወታደራዊ አመራሮች እና የሁለቱ ሀገራት አጎራባቸው አስተዳደሮች ማለትም የምዕራብ ጎንደርና በሱዳን በኩል ደግሞ የጋላባት አካባቢ አስተዳደር ተወካዮች በመተማ ተወያይተዋል፡፡ ይህን በተመለከተ የመተማ ከተማ ከንቲባ አቶ ሀብቴ አዲሱ ለአል ዐይን አማርኛ ክፍል በሰጡት ቃል ሐምሌ17 ቀን 2013 ዓ.ም የመተማ-ጋላባት መንገድ በሱዳን በኩል ተዘግቶ ነበር ሲሉ አስታውሰዋል። የሱዳን መንግስት መንገዱን የዘጋው አንድ ወታደራዊ አመራር በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ተገድሎብኛል ብሎ በማሰቡ መሆኑን አቶ ሀብቴ ተናግረዋል፡፡ ከንቲባው እንዳሉት መንገዱ አለምአቀፍ መስመር ስለሆነ እንዲከፈት በአካባቢው አስተዳደር እና በሀገር ሽማግሌዎች ለማስከፈት ጥረቶች ሲደረጉ ቆይተዋል፡፡ በስብሰባው ላይ መንገዱ ተክፍቶ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ እንዲቀጥል መግባባት ላይ መደረሱን የገለጹት አቶ ሀብቴ ከዚህ በተጨማሪም ለሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ምክንያት የሆኑ ጉዳዮችም ተነስተዋል ብለዋል፡፡ በሱዳን ግዛት ውስጥ ሚንቀሳቀሱ የህወሓት ኃይሎች መኖራቸውንና ያሉበትን ቦታ ጭምር በመጥቀስ እና ትክክል እንዳልሆነ ለሱዳን ወታደራዊ አመራር እንደተነገራቸው ከንቲባው ተናግረዋል፡፡ ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ ፎቶ ፦ የምዕራብ ጎንደር ዞን @tikvahethiopia

#Lalibela የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በዝግጅት ላይ መሆናቸውን የደብረ ሮሀ ቅዱስ ላልይበላ ገዳም ዋና አስተዳዳሪ መምህር አባ ፅጌሥላሴ መዝገብ አሳውቀዋል። ሁሉም
+2
#Lalibela የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በዝግጅት ላይ መሆናቸውን የደብረ ሮሀ ቅዱስ ላልይበላ ገዳም ዋና አስተዳዳሪ መምህር አባ ፅጌሥላሴ መዝገብ አሳውቀዋል። ሁሉም ምዕመን በዓሉን በአካል በመገኘት እንዲታደም ጥሪ አቅርበዋል። መምህር አባ ፅጌሥላሴ መዝገብ ለአሚኮ በሰጡት ቃል ለበዓሉ እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን " ሁላችሁም መጥታችሁ በዓሉን በደስታ አብረን እንድናከብር መልዕክታችን ነው፤ ሁሉም አስፈላጊ የሆነ ዝግጅት ተድረጓል " ብለዋል። በተጨማሪም ወቅቱን ታሳቢ ያደረገ የፀጥታ ፣ የደህንነት ጥበቃ እንዲሚደረግና የየብስም የአየርም የትራንስፖርት አማራጭ መመቻቸቱን ገልፀዋል። የገዳሙ ዋና አስተዳዳሪ ፥ " ሁላችሁም የተዘጋጃችሁ በሙሉ ልብ እግዚአብሔርን በማመን እንድትመጡ መልዕክታችን ነው " ብለዋል። በሌላ በኩል ለአካባቢው ምዕመናን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ምዕመናን የተለመደው አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ እና ጊዜው በሚፈቅደው መልኩ እንግዶችን መቀበል እንዳለባቸው ተናግረዋል። መምህር አባ ፅጌሥላሴ መዝገብ ፥ " ወቅቱ ፈታና ያለበት ነው ሰውን ማመን የማይቻልበት ፤ የማያውቀው ሰው ሲመጣ ፀጉረ ልውጥ የሚባልበት ነው ሆኖም ግን በሀይማኖት እይታ በማየት መጠርጠሩ እንዳለ ሆኖ እንደእባብ ልባሞች እንደእርግብ የዋሆች ሆነን ከቅርሳችን ደህንነት ከአካባቢያችን ደህንነት አኳያ የሚመጡ ሰዎችን መታወቂያቸውን በማያት የመጡበትን በመጠየቅ ማረፊያ መስጠት ፤ እግራቸውን አጥቦ የተለመደውን አብርሃማዊ አገልግሎት እድትሰጡ አደራ እንላለን " ብለዋል። @tikvahethiopia

የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የስያሜ ለውጥ አድርጓል ? ከኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ስያሜ ጋር የተያያዙ በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ደርሰዋል። በጉዳዩ ላይ የዩኒቨርሲቲው የሕዝብ ግን
+1
የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የስያሜ ለውጥ አድርጓል ? ከኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ስያሜ ጋር የተያያዙ በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ደርሰዋል። በጉዳዩ ላይ የዩኒቨርሲቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት መኩሪያ ንጋቱ ለ @tikvahuniversity ማብራሪያ ሰጥተዋል። የቀድሞው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በመቋቋሚያ አዋጁ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ደረጃና ስያሜ የመስጠት መብት ነበረው። በዚህም የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረውን የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት ወደ ዩኒቨርሲቲ የማደግ ጥያቄ ምላሽ ሰጧል። በየካቲት 2013 ዓ.ም ለኢንስቲትዩቱ "የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ" የሚል ስያሜም ሰጥቷል። ይሁን እንጂ የስያሜ ለውጡ ኢንስቲትዩቱ ሲቋቋም የተሰጠው ተልዕኮ በሚኒስትሮች ም/ቤት ደንብ ተሻሽሎ፣ በነጋሪት ጋዜጣ መታወጅ እንደነበረበት ኃላፊው ገልጸዋል። ይህ ሕጋዊ ሂደት ሳይጠናቀቅ በመስከረም 2014 ዓ.ም የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሚኒስቴር ስር መጠቃለሉን አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲም አዲስ በተደራጀው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ስር የተካተተ ሲሆን ''የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት" የሚል ስያሜ እንዲሰጠውም ተወስኗል። ይሁን እንጂ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አባላት ''የስያሜ ለውጥ ውሳኔው በድጋሜ ሊታይ እንደሚገባ ለመንግስት ጥያቄ ማቅረባቸውን'' ኃላፊው ገልጸዋል። "ጥያቄው በተለያዩ ደረጃዎች እየታየና የመንግስት ምላሽ እየተጠበቀ እንደሆነ" ኃላፊው አስረድተዋል። ከመንግስት ምስረታው በኋላ በአዋጅ ለተቋቋሙ እና የደንብ ክለሳ ለሚያስፈልጋቸው ከ50 ያላነሱ ተቋማት የሚኒስትሮች ም/ቤት በቅርቡ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል። More : @tikvahuniversity

#SUDAN በሱዳን የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬም ቀጥሏል። በሺህዎች የሚቆጠሩ ሱዳናውያን ወታደራዊውን አስተዳደር በመቃወም አደባባይ ወጥተዋል። የሱዳን የጸጥታ ኃይሎች በሀገሪቱ የተደረገውን መፈንቅለ መንግሥት
+1
#SUDAN በሱዳን የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬም ቀጥሏል። በሺህዎች የሚቆጠሩ ሱዳናውያን ወታደራዊውን አስተዳደር በመቃወም አደባባይ ወጥተዋል። የሱዳን የጸጥታ ኃይሎች በሀገሪቱ የተደረገውን መፈንቅለ መንግሥት በመቃወም በካርቱም በፕሬዝደንቱ መኖሪያ አካባቢ የተሰባሰቡ ሰልፈኞችን ለመበተን አስለቃሽ ጭስ መጠቀማቸውን እማኞች መገልፃቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል። ዛሬ ከካርቱም በተጨማሪ በኦምዱርማን ከተማ ሱዳናውያን አደባባይ ወጥተው ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥቱን አውግዘዋል። በሌሎች ከተሞችም ፖርት ሱዳንን ጨምሮ ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፎች መኖራቸውን አሶሴትድ ፕረስ ዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ከሥልጣናቸው መልቀቃቸውን በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ካሳወቁ በኋላ የሱዳን የፖለቲካ ቀውስ ተባብሷል። መረጃው የዶቼቨለ እና አሶሼትድ ፕሬስ ነው። @tikvahethiopia

#Dessie #Hayq ትምህርት ሚኒስቴር በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ እና ሀይቅ ከተሞች በህወሓት የሽብር ቡድን ወረራ ምክንያት ከ2 ወር በላይ ተቋርጦ የቆየው ትምህርት በድጋሚ እንደጀመረ አሳውቋል። ምንጭ
+3
#Dessie #Hayq ትምህርት ሚኒስቴር በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ እና ሀይቅ ከተሞች በህወሓት የሽብር ቡድን ወረራ ምክንያት ከ2 ወር በላይ ተቋርጦ የቆየው ትምህርት በድጋሚ እንደጀመረ አሳውቋል። ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን (ጋዜጠኛ ነፃነት ጌታቸው) @tikvahethiopia

#GeneralQasemSoleimani ጄነራል ቃሲም ሱሌይማኒ የተገደሉበት 2ኛ ዓመት በኢራን እየታሰበ ነው። የኢራኑ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቃሴም ሱ
+1
#GeneralQasemSoleimani ጄነራል ቃሲም ሱሌይማኒ የተገደሉበት 2ኛ ዓመት በኢራን እየታሰበ ነው። የኢራኑ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቃሴም ሱሌይማኒ ግድያ ክስ ካልቀረበባቸው እና ተጠያቂ ካልተደረጉ የበቀል እርምጃ እንደሚወስዱ ቃል እንደገቡ ኤኤፍፒ ዘግቧል። ፕሬዜዳንቱ ፥ " አጥቂው እና ዋናው ገዳይ በወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የነበሩት (ዶናልድ ትራምፕ) ፍትህ እና ቅጣት ሊጠብቃቸው ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል። ፕሬዜዳንቱ አክለው ትራምፕ፣ (የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር) ማይክ ፖምፒዮ እና ሌሎች ወንጀለኞች ተይዘው የፍርድ ሂደታቸው ፍትሃዊ በሆነ ፍርድ ቤት ለአሰቃቂ ወንጀሎቻቸው እና ለድርጊታቸው ተጠያቂ ከሆኑና ፍትህ የሚያገኝ ከሆነ ምንም ችግር የለውም ብለዋል። "አለበለዚያ ግን ለመላው የአሜሪካ መሪዎች የምነግራቸዉ ያለጥርጥር የበቀል ክንዳችን እንደሚያርፍባቸው ነው " ሲሉ ፕሬዜዳንቱ ተናግረዋል። ጄነራል ቃሲም ሱሌይማኒ ፤ ከኢራቃዊው ሌተናንት አቡ ማህዲ አል ሙሃንዲስ ጋር እኤአ ጥር 3 ቀን 2020 በአሜሪካ ድሮን ኢራቅ፣ ባግዳድ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ መገደላቸው ይታወሳል። @tikvahethiopia

የአሜሪካ ወታደሮች ባሉባቸው የጦር ሰፈሮች የድሮን ጥቃት ተሰንዝሮ መክሸፉ ተነገረ። ኢራቅ ውስጥ ISISን የሚዋጋው በአሜሪካ የሚመራው ጥምር ጦር የአሜሪካ ወታደሮች ባሉበት የጦር ሰፈር የተሰነዘሩ የ
+1
የአሜሪካ ወታደሮች ባሉባቸው የጦር ሰፈሮች የድሮን ጥቃት ተሰንዝሮ መክሸፉ ተነገረ። ኢራቅ ውስጥ ISISን የሚዋጋው በአሜሪካ የሚመራው ጥምር ጦር የአሜሪካ ወታደሮች ባሉበት የጦር ሰፈር የተሰነዘሩ የድሮን ጥቃቶችን ማክሸፉን ገለፀ። በ24 ሰዓት ሁለት ጊዜ የድሮን ጥቃቶች መፈፀማቸው የተነገረ ሲሆን በአሜሪካ የሚመራው ጥምር ኃይሉ ሁለቱም ጥቃት ማክሸፉን አሳውቋል። የዓለም አቀፉ ወታደራዊ ጥምረት ባለስልጣን ዛሬ ማክሰኞ እንደተናገሩት ፥ 2 የታጠቁ ድሮኖች በምእራብ አንባር ግዛት ወደሚገኘው ጦር ሰፈር ሲቃረቡ ተመተው ተጥለዋል። የጥቃቱ ሙከራ አለመሳካቱንም ተናግረዋል። ጥምረቱ ትላንት ሰኞ በባግዳድ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ ወደሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር ሲቃረቡ የነበሩ ሁለት የታጠቁ ድሮኖች ተመተው መጣላቸውን አሳውቋል። እስካሁን ኃላፊነት የወሰደ አካል እንደሌለ ተነግሯል። @tikvahethiopia

#Kombolcha ከነገ ታህሳስ 27 ጀምሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኮምቦልቻ እለታዊ የበረራ አገልግሎቱን እንደሚጀምር አስታውቋል። ተጓዦች የጉዞ ምዝገባ ለመያዝ 👉 https://www.ethio
+1
#Kombolcha ከነገ ታህሳስ 27 ጀምሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኮምቦልቻ እለታዊ የበረራ አገልግሎቱን እንደሚጀምር አስታውቋል። ተጓዦች የጉዞ ምዝገባ ለመያዝ 👉 https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app መጠመቀም እንደሚችሉ አየር መንገዱ ገልጿል። @tikvahethiopia

#AddisAbaba የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ከአሽከርካሪዎች ውጭ ሌላ ተሳፋሪ እንዳይጭኑ እገዳ ተጣለ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ከአሽከ
+1
#AddisAbaba የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ከአሽከርካሪዎች ውጭ ሌላ ተሳፋሪ እንዳይጭኑ እገዳ ተጣለ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ከአሽከርካሪዎች ውጭ ሌላ ተሳፋሪ እንዳይጭኑ እገዳ ጥሏል፡፡ ቢሮው በመዲናዋ በሞተር ብስክሌት ምክንያት የሚደርሱ የትራፊክ አደጋዎችንና ህገ ወጥ ድርጊቶችን መከላከል የሚያስችል የሞተር ብስክሌት ፈቃድና ቁጥጥር መመሪያ በማውጣት ወደስራ መገባቱ አስታውሷል። በአሁኑ ወቅት ውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ወደ ሀገር ቤት እንዲገቡ የቀረበውን ጥሪ ተከትሎ በርካታ የዲያስፖራ አባላት ወደሀገራቸው እየገቡ ይገኛል፡፡ በተያያዘ ወቅቱ የበዓል ሰሞን እንደመሆኑ በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች ከቦታ ቦታ በብዛት እንቅስቃሴ እያደረጉ ሲሆን፥ ይህን ተከትሎ በከተማዋ የትራፊክ መጨናነቅ እና የዝርፊያ ምልክቶች እየታዩ ነው ሲል አሳውቋል። ስለሆነ ከታህሳስ 22/2014 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ከአሽከርካሪዎች ውጭ ሌላ ተሳፋሪ እንዳይጭኑ ቁጥጥር እንዲደረግ እና እርምጃ እንዲወሰድ ቢሮው ለሚመለከተው አካል የስራ ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡ ምንጭ ፦ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት @tikvahethiopia

#Tigray ዩኒሴፍ፣ የዓለም ጤና ድርጅትና አጋሮቻቸው በትግራይ ክልል መዲና መቐለ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ጀምረዋል። ከ5 አመት በታች የሆኑ ህጻናትን ከዚህ በጣም ተላላፊ ነገር ግን
+3
#Tigray ዩኒሴፍ፣ የዓለም ጤና ድርጅትና አጋሮቻቸው በትግራይ ክልል መዲና መቐለ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ጀምረዋል። ከ5 አመት በታች የሆኑ ህጻናትን ከዚህ በጣም ተላላፊ ነገር ግን በቀላሉ መከላከል ከሚቻል በሽታ ለመጠበቅ ከ850,000 በላይ ክትባቶች ወደ ክልሉ መግባታቸው አይዘነጋም። Credit : UNICEF ETHIOPIA @tikvahethiopia

#ETHIOPIA😷 የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦ • የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 6,176 • ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,140 • ህይወታቸው ያለፈ 👉 11 • ከበሽታው ያገገሙ 👉 1,
#ETHIOPIA😷 የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦ • የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 6,176 • ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,140 • ህይወታቸው ያለፈ 👉 11 • ከበሽታው ያገገሙ 👉 1,490 በአሁን ሰዓት 442 ሰዎች በፅኑ ታመዋል። @tikvahethiopia

#EthiopianAirlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ A350 የተሰኘውን ግዙፍና ዘመናዊ አውሮፕላን ከሚያበሩ አምስት ግዙፍ የአለማችን አየር መንገዶች አንዱ ሆኗል። Simple Flying እ
+1
#EthiopianAirlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ A350 የተሰኘውን ግዙፍና ዘመናዊ አውሮፕላን ከሚያበሩ አምስት ግዙፍ የአለማችን አየር መንገዶች አንዱ ሆኗል። Simple Flying እንዳስነበበው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፈው ዓ.ም በኤርባስ A350 አውሮፕላኖቹ 6437 መደበኛ በረራዎች አድርጓል። https://simpleflying.com/airbus-a350-operators-2021/amp/ ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ @tikvahethiopia

#Update በሳዑዲ አረቢያ በስቃይ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ጉዳይ በተመለከተ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምላሽ ሰጥቷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃ
+1
#Update በሳዑዲ አረቢያ በስቃይ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ጉዳይ በተመለከተ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምላሽ ሰጥቷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃል ፥ ሚኒስቴሩ ከሳኡዲ አረቢያ መንግስት እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር በእስር ላይ ያሉ ዜጎችን ወደ አገራቸው áˆ˛áˆ˜áˆáˆľ áˆ˜á‰†á‹¨á‰ąáŠ• አስታውቋል፡፡ አምባሳደር ዲና ፥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ሃገራቸው የመመለሱ ሂደት አለመቆሙን ጠቁመው የተወሰነ መቀዛቀዝ ግን ነበር ብለዋል፡፡ ይሁንና እንደከዚህ በፊቱ በአስቸጋሪ ህይወት ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ሃገራቸው ለመመለሾ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። በቅርቡ በሳዑዲ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ወደ አገራቸው የመመለሱ ዘመቻ ይጀመራል ሲሉ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃል ተናግረዋል። ከቀናት በፊት በሳዑዲ አረቢያ በእስር ላይ እየተሰቃዩ ያሉ ዜጎች ያሉበት ሁኔታ ተስፋ አስቆራጭ መሆኑን በመግለፅ በእስር ቤት የሚደርስባቸውን ግፍ ህዝብ እንዲሰማላቸው እና የሚመለከተው አካልም መፍትሄ እንዲሰጣቸው መማፀናቸው አይዘነጋም https://t.me/tikvahethiopia/66047?single @tikvahethiopia