3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
3 889
" ድሬዳዋ የአብሮነት የፍቅር የሰላም ከተማ ! "
በድሬዳዋ የተከበረው የጥምቀት በዓል በከተማው በሚገኙ የተለያዩ የእምነት ተከታዮች ወንድማዊ ፍቅር የደመቀ ነው ሲል ድሬዳዋ ፖሊስ አሳውቋል።
ድሬዳዋ ፖሊስ ከከተራ በዓል ጀምሮ ህዝበ ክርስቲያኑ ታቦታቱን አጅበው ወደ ጥምቀተ ባህሩ ሲያቀኑ ድካም ለተሰማቸው ህዝበ ክርስቲያን ቀዝቃዛ ውሃ እንዲሁም የሚበሉ ልዩ ልዩ የምግብ አይነቶችን አዘጋጅቶ በመስጠት ህዝበ ሙስሊሙ ያሳየው ተሳትፎ የቀደመውን የአብሮነት መንፈስ ገልጦ አሳይቷል ሲል ገልጿል።
በዛሬው ዕለት ታቦታቱ ካደሩበት ጥምቀተ ባህር ወደ መንበራቸው ሲመለሱ በከተማው በሚገኙ ሁሉም አካባቢዎች ህዝበ ሙስሊሙ እንዲሁም የተለያዩ የእምነት ተከታዮች በዓሉ በሠላም እንዲከበር ጥበቃ ከማድረግ በላይ ገንዘብ በማዋጣት ለበአሉ ድምቀት በየአካባቢያቸው ባነር በማሠራት ኩኪስና ልዩ ልዩ ጣፋጭ ምግቦች በማዘጋጀት እንዲሁም የታሸገ ውሃ በማቅረብ ፍቅራቸውን በገሀድ አሳይተዋል።
በአብሮነትና በፍቅር መንፈስ ተከብሮ ያለፈውን የዘንድሮ የጥምቀት በዓል በሁሉም የከተማው ነዋሪ ዘንድ ልብን በሀሴት የሞላ እንደነበር ድሬዳዋ ፖሊስ ገልጿል።
የዘንድሮ የጥምቀት በዓል በድሬዳዋ ከተማ በብዙ ፍቅር በመልካም አብሮነት እጅግ በላቀ ሠላም የተከበረ ሲሆን ነገ እና ከነገ በስቲያ ከባህረ ጥምቀቱ ወደ መንበራቸው የሚመለሱ ታቦታት በደመቀ ፍቅር ወደ መንበራቸው እንደሚገቡ ይጠበቃል።
ድሬዳዋ የአብሮነት እና የፍቅር ከተማ መሆኗን በርካቶች ያለምንም መንገራገር በልበ ሙሉነት የሚናገሩት ጉዳይ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የአብሮነት እና የፍቅር ከተማነቷ ተቀዛቅዟል ለሚሉ ሠዎች የዘንድሮ ጥምቀት በዓል የቀደመው ፍቅር እና አብሮነት እንዳለ ሁነኛ ምሳሌ ሆኖ ተጠናቋል ሲል ድሬዳዋ ፖሊስ ገልጿል።
@tikvahethiopia
3 889
#Update
የአፍሪካ ኅብረት 35ኛ የመሪዎች ጉባኤ በቀጣይ ሳምንት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ዛሬ ሳምንታዊ መግለጫ የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ፥ " ጉባኤው ኢትዮጵያ ሠላም አይደለችም የሚለውን የጠላት ሃሳብ ከመሰረቱ ነቅሎ የሚጥል ነው " ብለዋል።
ጉባኤውን ከማስቀረት ባለፈ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫን ከኢትዮጵያ ለማንሳት ዘርፈ ብዙ ጥረቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን ያነሱት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ያላትን ሚና ከግምት በማስገባት በተሠራ ሰፊ የዲፕሎማሲ ሥራ ጉባዔው አዲስ አበባ እንዲካሄድ ተወስኗል ብለዋል።
አፍሪካውያን ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና ታዋቂ ሰዎችም በዲፕሎማሲው ሥራ የራሳቸው አበርክቶ ነበራቸውም ብለዋል።
የጉባኤው ዋና አጀንዳ አልሚ ምግብ ላይ መሆኑን የገለጹት ቃል አቀባዩ፥ ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ነው ሲሉ አሳውቀዋል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
3 889
" ዝም አላልም ለምን፣ እንዴት የሚሉትን የሚያጣራ የህግ አካል ይዞታል ቀጣይ የሚኖሩ ሂደቶችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን " - ሐጅ ዑስማን ዑመር
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በይፋዊ ፌስቡክ ገፁ ከትላንት በስቲያ የከተራ በዓል በሚከበርበት ወቅት በባህር ዳር ከተማ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፅ/ቤት ትንኮሳ መፈፀሙን ገልፆ የደረሰውን ጉዳት የክልሉ መንግስት በአስቸኳይ አጣርቶ ትንኮሳውን እና አደጋውን ያደረሱትን ግለሰቦች ለህግ አቅርቦ ተገቢውን ፍትህ እንዲያሰፍን አጥብቆ ጠይቋል።
ምክር ቤቱ ባሰራጨው አጭር መልዕክት ፥ " መንግስት በክልሉ ሙስሊም ላይ በየጊዜው የሚደርሱት መሠል ተደጋጋሚ ትንኮሳዎች እና የመብት ጥሰቶችን በማስቆም የዜጎችን ሰላም የማስከበር ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ እናቀርባለን " ብሏል።
በተመሣሳይ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጸሐፊ ሐጅ ዑስማን ዑመር በጥምቀት በአል ዋዜማ በአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ቢሮ ላይ የተደረገው የቢሮውን የብሉኬት አጥርን የማፈራረስና የተለያዩ ክብረ ነክ ስድቦች መሳደብ እጅግ ሊወገዙና ተከባብሮና ተቻችሎ በመኖር ብቻ ሀገር እንደሚገነባ ፅኑ እምነት ያላቸው የእምነቱ ተከታዮች ድርጊቱን ሊያወግዙ እና በዚህ አፀያፊ ተግባር የተሳተፉ አካሎችን ወደ ህግ ማቅረብ እንዳለባቸው አጥብቀው አሳስበዋል።
ከተፈፀመው ድርጊት ጋር በተያያዘም " ዝም አላልም ለምን፣ እንዴት የሚሉትን የሚያጣራ የህግ አካል ይዞታል ቀጣይ የሚኖሩ ሂደቶችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
3 889
#Update
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) የሰላም ማስከበር ዘመቻ ኃላፊ ጅን ፔሬ ላክሮክስ እንደገለጹት በአብየ ሚገኘውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል የተመተካቱ ሂደት በቀጣይ ወር ይጀምራል፡፡
ሱዳን በአብየ ያለው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር እንዲወጣ ጥያቄ አቅርባ የነበረ ሲሆን ጥያቄዋም በተመድ ተቀባይነት ማግኘቱ ይታወሳል፡፡
ሱዳን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር ይወጣ ያለችው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል በድንበር ጉዳይ አለመግባባት ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ ነው፡፡
ኃላፊዋ ላክሮክስ ይህን ያሉት ከሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ም/ቤት ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ጋር ባደረጉት የስልክ ወይይት ነው ተብሏል፡፡
የሽግግር ም/ቤቱ እንደገለጸው አልቡርሃን ከተመድ ኃላፊ ጋር ያደረጉት ውይይት የተመድ ኢንትሪም ሴኩሪቲ ፎርስ ፎረ አብየ ውስጥ ያሉት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ወታደሮችን በሱዳን መንግስት በተጠየቀው መሰረት ለመተካት የመከረ ነበር፡፡
በስልክ ወይይቱ ወቅት ላክሮክስ የመተካቱና የመተካቱ ስራ በፈረንጆቹ ቀጣይ የካቲት ወር እንደሚጀመርና እስከ ፈረንጆቹ መጋቢት 2022 እንደሚቀጥል ማረጋገጣቸው ተዘግቧል፡፡
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopia
3 889
#Update
በቀናት በፊት በሳዑዲ አረቢያ የነበሩት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ የሆኑት ሞሊ ፊ እና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ሱዳን ገብተው በሱዳን ጉዳይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት አድርገዋል።
ሁለቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በቀጣይ በአዲስ አበባ ተገኝተው ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።
@tikvahethiopia
3 889
#ETHIOPIA
የተመድ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጎተሬዥ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ መልዕክተኛ ክቡር ኦሊሲንጎ ኦቦሳንጆ በኢትዮጵያ ባለው ግጭት ዙሪያ በመቀሌና በአዲስ አበባ ያደረጉትን ግብኝት ተከትሎ በዛሬው እለት የስልክ ውይይት አድርጌያለሁ ሲሉ አስተውቀዋል።
ሰላም ለማስፈን የሚያስችል ተጨባጭ ጥረት በመኖሩ ተደስቻለሁ ብለዋል፡፡
"ኦባሳንጆ በኢትዮጵያ መንግሥትና ህወሓት ግጭቱን ለማስወገድ እያደረጉ ስላሉት ጥረት ገለጻ አድርገውልኛል” ያሉት ዋና ጸሀፊው ግጭቱና ጥቃቱ እንዲያበቃ አሁን ፖሊካዊና ዲፕሎማሲያዊ እልባት ለመስጠት የሚያስችል ትክክለኛ እድልና አጋጣሚ ስለመኖሩ ተስፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
ጉተሬዥ ከአንድ ዓመት በላይ በመላው ኢትዮጵያና በአካባቢው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለጉዳት ከዳረገው ግጭት በኋላ አሁን ሰላም ለማስፈን የሚያስችል ተጨባጭ ጥረት በመኖሩ ተደስቻለሁ ብለዋል፡፡
በአንዳንድ የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች አሁንም የሚካሄደው ውጊያ ለሰላም ሂደቱ መራር ፈተና መሆኑን የገለጹት ዋና ጸሀፊው በሁሉም ወገኖች ዘንድ መተማመን የሚፈጥሩ ጠንካራ እምርጃዎች እየተወሰዱ ነው ብለው ተስፋ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
ጎተሬዥ አሁንም ሰላምን ለማስፈን ትክክለኛው አቅጣጫ ሁሉም ወገኖች ግጭቱን ማቆሙ ያላባቸው መሆኑን ያቀረብኩትን ጥሬዬን እንደገና አቀርባለሁ ብለዋል፡፡
የተባበሩት መንግሥታት ኢትዮጵያ ውስጥ በኢትዮጵያውያን ባለቤትነት የሚመራ ሁሉን አቀፍ ብሄራዊ የሰላም የደህንነትና የእርቅ ሂደትን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ሁሉም ወገኖች ለሰላሙ ሂደት በቅንነትና በቁርጠኝነት እንዲሳተፉ የሚያደርገውን ጥረት መቀጠል አለበት ማለታቸውን ቪኦኤ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
3 889
" የ2014 ዓ/ም የጥምቀት በዓል በሰላም ተጠናቋል " - የፀጥታና ደህንነት የጋራ-ግብረ ኃይል
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ -ግብረ ኃይል የጥምቀት በዓል በሰላም መጠናቀቁን አስታውቋል።
የጋራ-ግብረ ኃይሉ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማን ጨምሮ በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች በዓሉ በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን ገልጿል።
ለበዓሉ በሰላም መጠናቀቅ ሕዝበ ክርስቲያኑ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የደብር ኃላፊዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች እንዲሁም በዓሉን ለማስተባበር በየደረጃው የተዋቀሩ ኮሚቴዎች ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ግብረ-ኃይሉ ምስጋና አቅርቧል።
በተመሳሳይም ይህ ታላቅ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን በብቃት ለተወጡት የግብረ-ኃይሉ አባላት ምስጋና ቀርቧል።
@tikvahethiopia
3 889
የፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ የኢትዮጵያ ቆይታ ፦
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ግብዣ ወደ ኢትዮጵያ እንደመጡ የተነገረላቸው የሶማሊላንድ ፕሬዤዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ወደ ሀርጌሳ ተመልሰዋል።
ፕሬዚዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ላይ የሲዳማ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈው ነበር።
@tikvahethiopia
3 889
#Update
እስር ላይ ከነበሩት ጋዜጠኞች መካከል ጋዜጠኛ እና አክቲቪስት ኢያስፔድ ተስፋዬ ዛሬ ከእስር ተፈቷል።
ኡቡንቱ የተባለው ሚዲያ መስራችና ጋዜጠኛ እያስፔድ ተስፋዬ ዛሬ ከቀትር በኋላ ነው ከእስር እንደተፈታ ሚዲያው የገለፀው።
ጋዜጠኛ እና አክቲቪስት እያስፔድ 43 ቀናት በእስር ሲቆይ ፖሊስ አንድም ጊዜ ፍርድ ቤት እንዳላቀረበው እና ክስም እንዳልመሠረተበት ሚዲያው ገልጿል።
በትላንትናው ዕለት ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ ከእስር መፈታቷ ይታወቃል።
ሌሎች በእስር ላይ ከሚገኙ ጋዜጠኞች መካከል ተራራ ኔትዎርክ የተባለው ሚዲያ መስራች ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ የአሐዱ ሬዲዮ ባልደረባ ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁ ስለመፈታታቸው የተባለ ነገር የለም።
@tikvahethiopia
3 889
#AliBira
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እንዲሁም የኦሮሚያ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፤ ክቡር ዶክተር አሊ ቢራን ህክምና በሚከታተሉበት ሆስፒታል ተገኝተው ጠይቀዋቸዋል።
ከዚህ ቀደም አንጋፋው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ በአዳማ ጄኔራል ሆስፒታል ህክምና እየተከታትሉ እንደሚገኙ መገለፁ ይታወሳል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ህክምና እየተከታተሉ በሚገኙበት ሆስፒታል በአካል በመገኘት እንደጠየቋቸው መገለፁ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
3 889
#Photo
የጥምቀት በዓል እየተከበረ ይገኛል።
የበዓሉን ገፅታ የሚያሳዩ ፎቶች ከአ/አ፣ ደሴ፣ ጎንደር፣ ሀይቅ ፣ ኮምቦልቻ፣ ቡሌ ሆራ ፣ ነቀምቴ፣ ቦንጋ፣ አርባ ምንጭ ፣ ሀዋሳ ፣ ወላይታ ሶዶ ፣ ጋምቤላ፣ አሶሳ ፣ ግልገል በለስ ፣ ድሬዳዋ ፣ሀዋሳ እንዲሁም ከሌሎች ከተሞች በማሰባሰብ ወደ ስልካችሁ ልከናል።
የፎቶ ስብስቦቹ ይመልከቱ 👉 https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-19
ሁሉም ፎቶዎች ምንጫቸው የተገለፀበት ነው።
3 889
አርቲስት ኑሆ ጎበና ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
አርቲስት ኑሆ ጎበና ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡
አርቲስት ኑሆ ጎበና በአፋን ኦሮሞና በተለያዩ ቋንቋዎች በርካታ ዜማዎችን ለአድማጭ አበርክቷል፡፡
አርቲስት ኑሆ ፤ ከአባቱ አቶ መሃመድ ጎበና እና ከእናቱ ወይዘሮ ፋጡማ አደም በ1940 ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ነበር የተወለደው፡፡
#ኤፍቢሲ/#ኦቢኤን
@tikvahethiopia
3 889
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ !
ውድ የክርስትና እምነት ተከታይ የቲክቫህ - ኢትዮጵያ አባላት የጥምቀት በዓልን ስናከብር ከአጠገባችን በችግር ላይ ያሉ የተጎዱ ወገኖችን በማገዝ ፣ አቅም የሌለንም ስለእነሱ በማሰብ እና ፈጣሪን በመለመን ፣ ለሀገር ሰላም እና ለሰው ልጆች ሁሉ ደህንነት በመፀለይ እንዲሆን አደራ እንላለን።
ዛሬም በሀገራችን የተለያዩ አቅጣጫዎች በችግር እና ስቃይ ያሉ ወገኖች በርካቶች መሆናቸውን በመገንዘብ ፣ እንደኛ ይህን በዓል በሰላም እና በደስታ ማክበር የማይችሉ ወገኖቻችን መኖራቸውን በማወቅ ፈጣሪ ለሁላችን ሰላም እና ፍቅር ፣ መተሳሰብና አንድነት አድሎ በጋራ በሰላም በመሰባሰብ እንድናከብር እንዲረዳን እንለምናለን።
ያዘኑ ወገኖችን ምናፅናናበት፣ የተጣላን የምንታረቅበት፣ የተኳረፍን የምንነጋገርበት ፣ ያስቀየምን ይቅርታ የምንጠይቅበት፣ የበደልን የምንክስበት፣ ያስከፋን የምናስደስትበት ፣ የታመሙ የተጎዱ የሚፈወሱበት ፣ የተጨነቁ ከጭንቀት ነፃ የሚሆኑበት የሰላም ፣ የደስታ፣ የአንድነት፣ የፍቅር በዓል ይሆን ዘንድ እንመኛለን።
መልካም በዓል !
@tikvahethiopia
3 889
ፎቶ : የከተራ በዓል በጥንታዊቷና ታሪካዊቷ ጎንደር ❤️ ከተማ ፤ ጥር 10 ቀን 2014 ዓ/ም ።
የፎቶ ባለቤት 👉 ፎቶግራፈር አቤል ጋሻው
@tikvahethiopia
3 889
" የጥምቀት ከተራ በአል ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ተከብሯል " - ድሬዳዋ ፖሊስ
የጥምቀት ከተራ በአል በሀይማኖታዊ ስርአቱ መሰረት በደማቅ ሁኔታ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ በድሬደዋ የተከናወነ ሲሆን ታቦታቱም ከማደሪያቸው ጥምቀተ ባህሩ መድረሳቸውን የድሬደዋ ፖሊስ ገልፆል።
በመሆኑም ለጥምቀት ከተራ በአል ፍፁም ሰላማዊነት ምዕመኑ ፣ መላው የድሬደዋ ነዋሪ እና የፀጥታ ሀይሉ ላበረከተው አስተዋፆና ተኪ የለሽ ሚና የድሬደዋ ፖሊስ ምስጋናውን አቅርባል።
ምንጭ፦ ድሬዳዋ ፖሊስ
@tikvahethiopia
3 889
#Update
በእስር ላይ ከነበሩ ጋዜጠኞች መካከል ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ ዛሬ ተፈታለች።
ጋዜጠኛ መዓዛ ከ39 ቀናት እስር በኃላ ዛሬ ማምሻውን እንደተፈታች ጠበቃዋ አዲሱ ጌታነህ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ አሳውቀዋል።
@tikvahethiopia
3 889
ድሬ❤️
"ተዋዶ ያለበት እስላም ክርስቲያኑ
ከቶ አይዘነጋም ድሬ ላይ መሆኑ! "
በድሬዳዋ ሁሌም ቢሆን የነዋሪዎቿ #ፍቅር ፣ #አንድነት እና #አብሮነት ብሎም አሁናዊ የከተማዋ ሰላም ለሌሎች ምሳሌና ማሳያ ነው መባሉ በምክንያት ነው።
በጥምቀት ከተራ በዓል የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ ወንድምና እህቶች በቀፊራ ፣ በለገሀሬ ፣ ኮኔል ፣ በድልድይ መጋላ እና በሌሎችም አካባቢዎች ለህዝበ ምእመኑ ውሀ፣ ኩኪሲችና ጣፍጭ ምግቦችን በማቅረብ እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ ወንድማዊና ቤተሰባዊ ፍቅራቸውን ገልፀዋል።
ፎቶ ፦ ድሬ ፖሊስ ሚዲያ
@tikvahethiopia
3 889
#Hosaena
የከተራ በዓል በሆሳዕና ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞች ዘንድ የሚከበረው የከተራ በዓል በሆሳዕና ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው።
ፎቶ ፦ የሀድያ ዞን ኮሚኒኬሽን
@tikvahethiopia
3 889
#Update
ቅዱስ ሲኖዶስ የብፁዕ አቡነ ሚካኤል የኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሥርዓተ ቀብር ጥር 16/2014 ዓ.ም በታላቁ የደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም እንዲፈጸም ወሰነ።
ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ጥር 9 ቀን 2014 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወቃል።
ብፁዕ አቡነ ሚካኤል በሀገረ ስብከታቸው ርዕሰ መንበረ ጵጵስና መቱ በአገልግሎት እያሉ ሕመም አጋጥሟቸው ወደ ሆስፒታል አቅንተው ሕመማቸው ከባድ በመሆኑ በአምፑላንስ ወደ ጋምቤላ ሄደው ለተሻለ ሕክምና ከጋምቤላ በልዩ አውሮፕላን ወደ አዲስ አበባ መጥተው በሀሌሉያ ሆስፒታል የሕክምና ድጋፍ ሲደረግላቸው ቢቆይም ከዚህ ዓለም ድካም ጥር 9 አርፈዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሰጡት መመሪያ መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬ ዕለት ተሰብስቦ የብፁዕነታቸው ሥርዓተ ቀርብር ጥር 16 ቀን 2014 ዓ.ም በታላቁ የደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም እንዲፈጸም ወስኗል፡፡
በዚሁ መሠረት ወዳጅ ዘመዶቻቸውና የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው በዕለቱ ተገኝተው ብፁዕነታቸውን መሸኘት እንደሚችሉና በሥርዓተ ቀብራቸውም ላይ መገኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።
ምንጭ፦ ኢኦተቤ ቴቪ
@tikvahethiopia
3 889
#Update
ዴቪድ ሳተርፊልድ እና ሞሊ ፊ ሳዑዲ አረቢያ ይገኛሉ።
በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ የሆኑት ሞሊ ፊ እና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ትላንት ሳዑዲ አረቢያ ገብተዋል።
የሳውዲ አረቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሃን ሁለቱን የአሜሪካ ባለስልጣናት ተቀብለው አነጋግረዋል።
በውይይታቸው ወቅት በሳዑዲ አረቢያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት እና ሁሉን አቀፋዊ ትብብርና የጋራ ቅንጅት የሚያስፈልጋቸውን ዘርፎች ማሳደግ የሚቻልባቸው መንገዶችን አስንተዋል ተወያይተዋል።
ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የጋራ ጉዳዮቻቸው ላይም ተወያይተዋል።
በአፍሪካ አህጉር ሰላም፣ ደህንነት እና መረጋጋትን ለማጠናከር፣ ለአፍሪካ ህዝቦች እና ሀገራት እድገትና ብልፅግና ሁለቱ ሀገራት የሚያበረክቱት ሁሉን አቀፍ ጥረት ላይም ተወያይተዋል ተብሏል።
በውይይቱ ላይ የሳዑዲ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ምክትል ሚኒስትር አምባሳደር ኢድ አልታቃፊ እና በሳዑዲ አረቢያ የአሜሪካ ኤምባሲ ኃላፊ ማርቲና ስትሮንግ ተገኝተው እንደነበር ተገልጿል።
ሞሊ ፊ እና ዴቪድ ሳተርፊልድ በቀጣይ ወደ ሱዳን እና ኢትዮጵያ በመምጣት ከከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል።
በተለይም በኢትዮጵያ ጉዳይ ዲፕሎማቶቹ የአየር ድብደባ እና ሌሎች ግጭቶች እንዲቆሙ፣ በድርድር ላይ የተመሰረተ ተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች እንዲለቀቁ፣ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት እንዲመቻችና ለሁሉ አቀፍ ብሔራዊ ውይይት የሚያስፈልጉ ነገሮች እንዲመቻቹ በአሁኑ ወቅት የተከፈተውን የሰላም ዕድል እንዲጠቀሙበት የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናትን ያበረታታሉ ተብሏል።
@tikvahethiopia
