en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
ቪድዮ : የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል አከባበር በደብረ ሮሐ ቅዱስ ላልይበላ - #Lalibela Credit : ሙልጌታ አንበርብር @tikvahethiopia

እንኳን አደረሰን ፤ አደረሳችሁ ! መላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ። ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት በዓሉን በጦርነት እና ግጭት ምክን
+1
እንኳን አደረሰን ፤ አደረሳችሁ ! መላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ። ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት በዓሉን በጦርነት እና ግጭት ምክንያት ከቀያቸው ተሰደው፣ የሚወዱትን ተነጥቀው በጥልቅ ሀዘን ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን በመደገፍ፣ አብሮ በመብላት ፣ በማፅናናት ፣ ተስፋን በመስጠት እንድታከብሩ እንማፀናለን። በተጨማሪ ሁላችንም በያለንበት በጦርነት እና ግጭት ምክንያት ችግር ላይ የወደቁ ወገኖችን በማሰብ ፤ ስለሀገራችን ዘላቂ ሰላም እና ፍቅር በመፀለይ በዓሉን ልናሳልፍ ይገባል። ፈጣሪ የሁላችን መጠለያ ፣ መሰብሰቢያ ፣ መሸሸጊያ የሆነችውን ሀገራችን ኢትዮጵያን ጠብቆ ፤ ህዝቦቿን አፋቅሮና አዋዶ ያኖርልን ዘንድ እንለምናለን። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት ፣ ያጠፋን የበደልን ያስከፋን ይቅር የምንባባልበት፣ ብሩህ ተስፋ (ቲክቫህ) የምናይበት ይሆን ዘንድ ተመኘን። #TikvahFamily #ETHIOPIA @tikvahethiopia

" ከእስር ከተለቀቁት መካከል ሴቶች ፣ አረጋውያን ፣ የጤና ችግር ያለባቸው ይገኙበታል " - ኢሰመኮ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ
" ከእስር ከተለቀቁት መካከል ሴቶች ፣ አረጋውያን ፣ የጤና ችግር ያለባቸው ይገኙበታል " - ኢሰመኮ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ ከተማ በእስር ላይ የነበሩ በርካታ ሰዎች ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም. ጨምሮ ባለፉት ቀናት ከእስር መለቀቃቸው አበረታች እርምጃ መሆኑን ገልጿል። ከእስር ከተለቀቁት መካከል ሴቶች፣ አረጋውያን፣ የጤና ችግር ያለባቸው እና ሌሎች ጉዳያቸው ተጣርቶ በቀላል ዋስትና የተለቀቁ ሰዎች ይገኙበታል ብሏል። ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ እና በሌሎች የሀገሪቱ ክልሎች ተመሳሳይ እርምጃዎች እንዲቀጥሉ፣ እንዲሁም የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ በሰብአዊ መብቶች ላይ የሚፈጥረውን ተጽዕኖ ከግምት በማስገባት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተደነገገው መሰረት በሀገር አቀፍ ደረጃ አስፈላጊነቱና የተፈጻሚነቱ አካባቢያዊ ስፋት እየተገመገመ ተገቢው ማሻሻያ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል። በተጨማሪም ኢሰመኮ ጋዜጠኞችን ጨምሮ አሁንም በቁጥጥር ስር ያሉ ሰዎች የተያዙበት ጉዳይ የማጣራት ሂደቱ የተፋጠነ እንዲሆን፣ የእስር አያያዝ እንዲሻሻል፣ የታሰሩበት ስፍራ ለቤተሰቦች ያልተገለጸ ሰዎች እንዲገለፅ ፤ እንዲሁም በአጠቃላይ የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ የሰብአዊ መብቶችን መርሆች ባከበረ መልኩ መተግበሩ እንዲረጋገጥ በድጋሚ አሳስቧል። @tikvahethiopia

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። ታህሳስ ወር የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ (የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ) በጥር ወር ባለበት እንደሚቀጥል የንግድ እና ቀጠናዊ ት
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። ታህሳስ ወር የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ (የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ) በጥር ወር ባለበት እንደሚቀጥል የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። @tikvahethiopia

#እንድታውቁት ነገ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። @tikvahethiopia
#እንድታውቁት ነገ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። @tikvahethiopia

የገና ሥጦታ ሎተሪ ! የገና ሥጦታ ሎተሪ ሀሙስ ታህሳስ 28/ 2014 ዓ.ም በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸ
+1
የገና ሥጦታ ሎተሪ ! የገና ሥጦታ ሎተሪ ሀሙስ ታህሳስ 28/ 2014 ዓ.ም በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል። 1ኛ. 10,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 1977732 2ኛ. 5,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0341880 3ኛ. 2,500,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0929042 4ኛ. 1,500,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1357756 5ኛ. 1,000,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 1288620 6ኛ. 500,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0614488 7ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው 20,000 ብር የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 18052 8ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 10,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 05609 9ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 5,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 4599 10ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 6941 11ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 883 12ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 250 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 904 13ኛ. 20,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 22 14ኛ. 200,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 50 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 4 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡ ምንጭ፦ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር @tikvahethiopia

#Amhara የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን የገና በዓል እና የጥምቀት በዓል በሰላምና ያለምንም የፀጥታ ስጋት እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን አሳውቋል። የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ከሌሎች የፌዴራል እና የክልል
+1
#Amhara የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን የገና በዓል እና የጥምቀት በዓል በሰላምና ያለምንም የፀጥታ ስጋት እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን አሳውቋል። የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ከሌሎች የፌዴራል እና የክልል የጸጥታ እና የደህንነት አካላት ጋር በጥምረት በመሆን በዓሉ በሰላም ተከብሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ እና የፀጥታ ኃይሉ ስነምግባርን ተላብሶ ተግባራትን እንዲከዉን ዝርዝር ዕቅድ ታቅዶ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና አባላት በቂ ኦረንቴሽን በመስጠት ዝግጅት ተደርጓል። በተለይ ደግሞ በዓሉ በከፍተኛ ሁኔታ በሚከበርባቸው አካባቢዎች ተንቀሳቃሽ እና ቋሚ ጥበቃ ተመድቧል። በዚህም ህዝቡ በዓሉን ያለምንም የፀጥታ ስጋት ሊያከብር ይገባል ተብሏል። ህዝቡ ከፀጥታ ኀይሎች ጎን በመሆን በዓላቱ በሰላም እንዲከበር የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ ተገልጿል። ነዋሪዎች በአማራ ክልል ማንኛውም አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥም በአቅራቢያቸው ለሚገኝ የፀጥታ ኀይል እንዲጠቁሙ መልዕክት ተለልፏል። (የዞኖች ፣ የብሄረሰብ አስተዳደሮች እና ከተሞች የፖሊስ ስልክ ከላይ ተያይዟል - በምትኖሩበት አካባቢ ሁሌም የፀጥታ ኃይሎችን ስልክ ቁጥር መመዝገብ እንዳትዘነጉ) እባክዎትን ስልክ ቁጥሮቹን #Share #ሼር ያድርጉ ! #AmharaPoliceCommission @tikvahethiopia

የሂዩማን ራይትስ ዎች ሪፖርት እና የመንግስት ምላሽ ! ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ትላንት ረቡዕ ባወጣው ሪፖርት፤ ከሳዑዲ አረቢያ የተመለሱ በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ የ
+1
የሂዩማን ራይትስ ዎች ሪፖርት እና የመንግስት ምላሽ ! ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ትላንት ረቡዕ ባወጣው ሪፖርት፤ ከሳዑዲ አረቢያ የተመለሱ በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ የመብት ጥሰት መፈጸሙን ገልጿል። ተቋሙ በሪፖርቱ፤ ከስደት ተመላሾቹ ላይ “የዘፈቀደ እስር እና እንግልት ደርሶባቸዋል፤ ደብዛቸውም ጠፍቷል” ሲል ሪፖርት አድርጓል። የሂዩማን ራይትስ ዎች የስደተኞች እና የስደተኛ መብት ተመራማሪ ናዲያ ሃርድማን “በሳዑዲ እስር ቤት አሰቃቂ በደል የደረሰባቸው የትግራይ ተወላጆች፤ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ በማቆያ እስር ቤቶች እየተቆለፉ ይገኛሉ” ብለዋል። ሙሉ ሪፖርቱ : https://www.hrw.org/news/2022/01/05/ethiopia-returned-tigrayans-detained-abused የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፥ ከሳዑዲ አረቢያ የሚመለሱ የትግራይ ተወላጅ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ ሂዩማን ራይትስ ዎች በትላንትናው ዕለት ያወጣው ሪፖርት “ድርሰት ነው” ሲሉ አጣጥለውታል። አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የተቋሙ ሪፖርት “በኢትዮጵያ ላይ እየተደረጉ ያሉ ጫናዎች አካል ነው” ብለዋል። “በሰፈር፣ በማንነት የተለየ እና የተጎዳ ሰው አልነበረም። እንደዚያ አይነት አሰራርም አልነበረም” ያሉት አምባሳደር ዲና ፥ “ሂዩማን ራይትስ ዎች ኢትዮጵያን በሚመለከት መዓት ድርሰቶች አሉት፤ ይሄም ከድርሰቶቹ አንዱ ነው” ብለውታል። በጉዳዩ ላይ ከዚህ በላይ ማብራሪያ የሚሰጠበት እንዳልሆነም ተናግረዋል። ምንጭ፦ ኢትዮጵየ ኢንሳይደር @tikvahethiopia

#AddisAbaba የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተወካዮች ምክር ቤት ሽብርተኛ ተብሎ ከተፈረጀው ህውሃት ጋር ባላቸው ልዩ ልዩ ግንኙነት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ ሲጣራባቸው ከነበሩ ግለሰቦች መካከ
#AddisAbaba የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተወካዮች ምክር ቤት ሽብርተኛ ተብሎ ከተፈረጀው ህውሃት ጋር ባላቸው ልዩ ልዩ ግንኙነት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ ሲጣራባቸው ከነበሩ ግለሰቦች መካከል በድርጊታቸው ተፀፅተው ይቅርታ የጠየቁትን፣ ከፍተኛ ወንጀል ያልፈፀሙ እና ከእሥር ቢወጡም ለከተማዉ ስጋት የማይሆኑት በዋስ ከእስር እየተለቀቁ ነው ብሏል። የተቀሩትንም እንደ ድርጊታቸው ክብደትና ቅለት እየታየ ወደፊት እንደሚለቀቁ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ በዋስ የተለቀቁ ግለሰቦች ወደፊት እንደ ጥፋታቸው በህግ እንደሚጠየቁ እና በህግ አካላት ጥሪ ሲደደረግላቸው የመቅረብ ግዴታ አለባቸው ብሏል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ማንኛውም ግለሰብም ሆነ ድርጅት በሽብርተኛ ከተፈረጀው ቡድን ጋር ግንኙነት ማድረግ ሆነ የሽብር ቡድኑን ዓለማ ማራመድ በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን ተረድቶ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ አስገንዝቧል። @tikvahethiopia

#ETHIOPIA❤️ ሀገራችን ኢትዮጵያ🇪🇹የፊታችን እሁድ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ታደርጋለች። ኢትዮጵያችን በመጀመሪያው ጨዋታ ከኬፕ ቨርዴ ጋር የምትፋለም ይሆናል። ይህ ጨዋታ በ " ኦሌ
+4
#ETHIOPIA❤️ ሀገራችን ኢትዮጵያ🇪🇹የፊታችን እሁድ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ታደርጋለች። ኢትዮጵያችን በመጀመሪያው ጨዋታ ከኬፕ ቨርዴ ጋር የምትፋለም ይሆናል። ይህ ጨዋታ በ " ኦሌምቤ ስታዲየም " የሚካሄድ ሲሆን የመክፈቻ ስነ-ስርዓቱን በደማቅ ሁኔታ ለማካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ ነው። የሀገራችን ልጆች ለዚሁ ትልቅ ውድድር ቀደም ብለው ካሜሮን ገብተው ጠንካራ ልምምድ እና ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ። ለአፍሪካ ዋንጫ ካሜሮን የሚገኙት የቲክቫህ ስፖርት አባላት በፎቶ እና በቪድዮ የተደገፉ መልዕክቶችን በ @tikvahethsport በኩል ይልኩላችኃል። https://t.me/+VvwzStMNcNHmhK0x @tikvahethiopia

#SUDAN ሌ/ጄኔራል አብዱል ፋታህ አል-ቡርሃን ሚመሩት የሱዳን ጦር ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ሳያሳትፍ ለሱዳን አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሾም እንደማይደግፉ አሜሪካ ፣ ብሪታኒያ፣ ኖርዌይ እና የአውሮ
#SUDAN ሌ/ጄኔራል አብዱል ፋታህ አል-ቡርሃን ሚመሩት የሱዳን ጦር ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ሳያሳትፍ ለሱዳን አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሾም እንደማይደግፉ አሜሪካ ፣ ብሪታኒያ፣ ኖርዌይ እና የአውሮፓ ህብረት አስጠንቅቀዋል። በሱዳን ወታደራዊ ኃይሉ ላይ አሁንም ተቃውሞ እና የሚደርስበት ጫና ቀጥሏል። የሱዳን ጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ ከቀናት በፊት በገዛ ፍቃዳቸው ከስልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል። ይህን ተከትክሎ የሱዳን መንግስት ሙሉ ለሙሉ በጦር ሰራዊቱ ቁጥጥር ስር እንዲገባ ያደርገዋል የሚል ስጋት ፈጥሯል። @tikvahethiopia

አሜሪካ ? እዚሁ አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከዚህ ቀደም ከፀጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ ከ15 ጊዜ በላይ ዜጎቹ ሀገር ለቀው እንዲወጡ ሲወተውት ነበር። ኤምባሲው አሁንም በዚሁ ጥሪው የቀጠለ
+1
አሜሪካ ? እዚሁ አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከዚህ ቀደም ከፀጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ ከ15 ጊዜ በላይ ዜጎቹ ሀገር ለቀው እንዲወጡ ሲወተውት ነበር። ኤምባሲው አሁንም በዚሁ ጥሪው የቀጠለ ሲሆን ዛሬም " በኢትዮጵያ ያለው የፀጥታ እና የደህንነት ሁኔታ አሳሳቢ ነው ያለምንም ማስጠንቀቂያ ሊበላሽ ይችላል " በማለት የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ሀገር ለቀው እንዲወጡ አሳስቧል። ይህ የኤምባሲው መልዕክት እንደሁል ጊዜው እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያንን ያስቆጣ ሲሆን የኤምባሲው ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ አስተያየት መስጫ የአሜሪካን ድርጊት በሚያወግዙ መልዕክቶች ተሞልቷል። አሜሪካ ዜጎቼ ውጡ እያለች ባለችበት በዚህ ጊዜ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን / የአሜሪካ ዜግነትም ያላቸው የሌሎችም ሀገራት ዜጎች ለበዓል ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ይገኛሉ። የ " ደህንነት ሁኔታ አሳሳቢ ነው " በሚል ዜጎቼ ውጡ እያለች የምትወተውተው አሜሪካ በአንድ በኩል ደግሞ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋን ከፍተኛ የስራ ኃላፊ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማንን ዛሬ ወደኢትዮጵያ እንደምትልካቸው ይጠበቃል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የአሜሪካ ኤምባሲ ሆነ ሌሎች በኢትዮጵያ ጉዳይ ሀሰተኛ መረጃ ከማሰራጨት እንዲታቀቡ ፤ ደህንነት አልተሰማንም ካሉም / ለሰራተኞቻቸው ምቹ ሁኔታ የለም ካሉ በየትኛውም ጊዜ መውጣት መብታቸው እንደሆነ ፤ ኢትዮጵያ ግን ሰላሟን፣ ደህንነቷን ይዛ እንደምትቀጥል የኤምባሲዎች መኖር የኢትዮጵያን ደህንነት እንደማያረጋግጥ ማሳወቋ ይታወሳል። @tikvahethiopia

ዋንግ ዪ ኬንያ ይገኛሉ። የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ትላንት የኤርትራ የስራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ኬንያ ሄደዋል። በኬንያ የሁለት ቀን ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን ትላንት ሞምባሳ ኤር
+1
ዋንግ ዪ ኬንያ ይገኛሉ። የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ትላንት የኤርትራ የስራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ኬንያ ሄደዋል። በኬንያ የሁለት ቀን ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን ትላንት ሞምባሳ ኤርፖርት ሲደርሱ የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሪይቼል ኦማሞ ተቀብለዋቸዋል። የዋንግ ዪ ጉብኝት በኬንያ እና በቻይና መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ስትራቴጂያዊ ትብብር ስምምነቶችን በመፈረም የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እድል ይሰጣል ተብሏል። @tikvahethiopia

#ETHIOPIA የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ የአምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ወደ ኢትዮጵያ መምጣት በተመለከተ ምን አሉ ? ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ፦ " የፌልትማን ወደ
#ETHIOPIA የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ የአምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ወደ ኢትዮጵያ መምጣት በተመለከተ ምን አሉ ? ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ፦ " የፌልትማን ወደ ኢትዮጵያ መምጣት አዲስ ጉዳይ አዲስ ነገር ይዞ ይኖራል ወይ የሚለው የሚመጡት እሳቸው ስለሆኑ የሚመጡበትን አጀንዳ ይዘው ሲመጡ ወቅቱም የገና በዓል ነው ከበዓሉም ጋር አስተሳስረን እንቀበላቸዋለን። በፍቅር መቀበል ኢትዮጵያዊ ባህል ነው። ስለዚህ አዲስ ነገር ይዘው መጡ አዲስ ነገር ይዘውም አልመጡ ያው ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የረጅም ጊዜ የታሪክ ግንኙነት ባለቤቶች ናቸው የትኛውንም ሀሳብ ይዘው ከመጡ ኢትዮጵያን የሚጠቅም እስከሆነ ድረስ ፤ ህዝቦቿን የሚጠቅም እስከሆነ ድረስ ኢትዮጵያ ትቀበላለች። የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ፣ የኢትዮጵያን ህብረ ብሄራዊ አንድነት ፣ የኢትዮጵያን ልማት ኢትዮጵያን አለማቀፋዊ ተሳትፎ ፣ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፋዊ ተሰሚነት የሚገዳደር ከየትኛውም ወገን ይምጣ ከየት ኢትዮጵያ አትቀበልም። ስለዚህ የፌልትማን መምጣት በዚህ አቅጣጫ መሰረት የሚፈፀም እና የሚመራ ይሆናል። " @tikvahethiopia

የአምባሳደር ፌልትማን ጉዞ ተሰርዟል ? ሮይተርስ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን በተያዘው ወር መጨረሻ ከኃላፊነታቸው እንደሚለቁ ዘግቧል (የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያ
+1
የአምባሳደር ፌልትማን ጉዞ ተሰርዟል ? ሮይተርስ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን በተያዘው ወር መጨረሻ ከኃላፊነታቸው እንደሚለቁ ዘግቧል (የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያለው ነገር ባይኖርም) ። ይህ የተሰማው ትላንት ለሊት ፌልትማን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ እና ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በሰላም ድርድር ጉዳይ እንደሚነጋገሩ ከተሰማ ከሰዓታት በኃላ ነው። ምንም እንኳን አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን በዚህ ወር ከኃላፊነት እንደሚለቁ ቢገለፅም የሀሙስ የኢትዮጵያ ጉዟቸው እንደተጠበቀ መሆኑን ለመስማት ተችሏል። አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን በዚህ ወር ከኃላፊነታቸው ሲለቁ ይተኳቸዋል የተባሉት በቱርክ የአሜሪካ አምባሳደርነት ጊዜያቸውን የጨረሱት አምባሳደር ዴቪድ ሰተርፊልድ ናቸው። @tikvahethiopia

#GERD የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የታላቁ ህዳሴ ግድብን የግንባታ ሂደት ጎበኙ፡፡ በጉብኝት መርሀ ግብሩ የተለያዩ የፌ
+5
#GERD የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የታላቁ ህዳሴ ግድብን የግንባታ ሂደት ጎበኙ፡፡ በጉብኝት መርሀ ግብሩ የተለያዩ የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ሚኒስትሮች ተሳትፈዋል፡፡ የሁሉም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የ100 ቀናት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በህዳሴ ግድብ መገኛ በሆነችው ጉባ እየተካሄደ ነው፡፡ Credit : FBC @tikvahethiopia

#EXCLUSIVE ፌልትማን በዚህ ወር ከኃላፊነታቸው ይለቃሉ። በነገው ዕለት ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ ተብሎ የሚጠበቁት በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ከሃላፊነታቸ
+1
#EXCLUSIVE ፌልትማን በዚህ ወር ከኃላፊነታቸው ይለቃሉ። በነገው ዕለት ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ ተብሎ የሚጠበቁት በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ከሃላፊነታቸው ሊለቁ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል። ሮይተርስ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ከ9 ወራት የስልጣን ቆይታ በኋላ በዚህ ወር ከኃላፊነታቸው እንደሚለቁ ዘግቧል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ እስካሁን የሰጠው አስተያየት የለም። አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ይተኳቸዋል ተብለው የሚጠበቁት #በቱርክ የአሜሪካ አምባሳደርነት ጊዜያቸውን የጨረሱት ዴቪድ ሰተርፊልድ መሆናቸውን ሮይተርስ ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች መስማቱን ገልጿል። ምንጭ፦ ሮይተርስ @tikvahethiopia

#Update ወ/ሎ ኬሪያ ኢብራሂም እና ዶ/ር ሰለሞን ኪዳኔ ባለንበት ማረሚያ ቤት በትግረኛ ቋንቋ ስልክ ለማውራት እና በማረሚያ ቤት በተለያየ ቦታ ላይ የታሰርነው ተገናኝተን ለመወያየት ይፈቀድልን ሲሉ ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ማረሚያ ቤት አስተዳደር አስተያየት እንዲሰጥበት ታዘዘ። አቶ ተክላይ አብርሐ ፖስፖርቴንና መንጃ ፍቃዴን ለማሳደስ ለዩንቨርስቲ መታወቂያ ላላቸው ቤተሰቦቼ ውክልና እንድሰጥ ይፈቀድልኝ ሲሉም ላቀረቡት አቤቱታ አስተያየት እንዲሰጥ ታዟል። ፍርድ ቤት በወ/ሎ ኬርያ ፣ ዶ/ር ሰለሞን ኪዳኔ እና በአቶ ተክላይ አብርሐ በተጠየቁ አቤቱታዎች ላይ ጥር 5 ቀን á‹¨áˆ›áˆ¨áˆšá‹Ťá‰¤á‰ľ አስተዳደር አስተያየት እንዲሰጥበት ትዛዝ ሰቷል። ወ/ሎ ሙሉ ገ/እግዛብሔርን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ በጎፋ ገብርኤል ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ ታስራብኛለች ያሏት ልጃቸውን በጥንቃቄ á‰ áŠ áŒƒá‰˘ እንዲጠይቋት ፈቅዷል። ወ/ሎ ሙሉ ገ/እግዛብሔር áˆáŒ„ን እንዲጠይቅ በፍርድ ቤቱ በተሰጠኝ ፈጣን ምላሽ á‹°áˆľ ብሎኛል ሲሉ ምስጋና አቅርበዋል።  ወ/ሎ ሙሉ ከዚህ በፊት በጽሁፍ አመልክቻለው ያሉትን በፓርላማ የተከፈተላቸው á‹¨á‹°áˆžá‹ መቀበያ የባንክ ሒሳባቸው እና የጋራ መኖሪያ ቤት ገንዘብ መቆጠቢያ የባንክ ሒሳብ áŠĽáŒá‹ľ እንዲነሳላቸው ጠይቀዋል። በምርመራ ተይዞቦኛል ያሉት ኮምፒዩተር እንዲሁም ስልክ እንዲመለስላቸውም አመልክተዋል። ከሳሽ ዓቃቢህግ በበኩሉ በፖሊስ ስለተያዘ ንብረት ለፖሊስ እንዲጻፍ áŠ áˆľá‰°á‹Ťá‹¨á‰ľ የሰጠ ሲሆን የባንክ ሒሳብ እግድን በተመለከተ ግን አጣርተን ምላሽ እንሰጣለን ብሏል። የቀድሞ የትግራይ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ ለነበሩት á‹ˆ/ሎ አሰፉ ሊላይ ዓቃቢህግ የሰነድ ማስረጃ እንዲያደርሳቸው ታዞ የነበረ ሲሆን ትዛዙን የሚፈጽመው ሀላፊ በመታመሙ ምክንያት ማድረስ አለመቻሉን ጠቅሷል ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል። ፍርድ ቤቱም ዓቃቢህግ በቀጣይ ቀጠሮ ማለትም ጥር 5 ቀን የሰነድ ማስረጃ ለ20 ኛ ተከሳሽ እንዲያደርስ ታዟል። ዛሬ በችሎት የቀረቡት ወይዘሮ ኬርያ እና ዶክተር ሰለሞን ጨምሮ ስድስቱ ተከሳሾች ችሎቱ ትዛዝ ሲሰጥ ከወንበር ባለመነሳታቸው ምክንያት á‰ľá‹›á‹ :ብይን እና ፍርድ ሲሰጥ ከወንበራቸው ተነስተው መቆም እንዳለባቸው የችሎት ስርአትን እንዲረዱ ፍርድ ቤቱ áŠ áˆľáŒˆáŠ•á‹á‰§á‰¸á‹‹áˆá˘ ያንብቡ : https://telegra.ph/Tarik-Adugna-01-05 ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

#Update ዛሬ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ መግለጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር ለገሰ ቱሉ፥ የመከለከያ ኃይል የያዘቸዉን አካባቢዎች አፅንቶ እንዲቆይ በታዘዘዉ መሠረት ይዞታዉን
#Update ዛሬ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ መግለጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር ለገሰ ቱሉ፥ የመከለከያ ኃይል የያዘቸዉን አካባቢዎች አፅንቶ እንዲቆይ በታዘዘዉ መሠረት ይዞታዉን በማጠናከር በነበረበት ምሽጉን ይዞ ቆሟል ብለዋል። "መንግስት ወደ ትግራይ ክልል የመከላከያ ሠራዊቱ እንዳይገባ የወሰነዉ የትግራይ ህዝብ በመጀመሪያዉ ዙር ያባከነዉን የማስተዋል ጊዜ ዳግም እንዲያጤናዉና ራሱን ከአሸበሪዉ ሃይል ነጥሎ ለጥቅሞቹና መብቶቹ መከበር እንዲቆም ተጨማሪ እድል ለመስጠት ሲባል ነዉ" ብለዋል። ሚኒስትሩ፥ "በአሁኑ ወቅት የትግራይ ህዝብ በርካታ ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ዉስጥ እንደሉ መንግስት መገንዘብ ብቻ ሳይሆን የህዝባችን አንዱ አካል በመሆኑ እነዚህ ችግሮቹ እንዲፈቱለት የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ ነዉ" ሲሉም ተናግረዋል። "እነዚህ ጥቅሞቹና መብቶቹ እንዲከበሩ ከተፈለገ በጦርነት ብቻ የመኖር ፍላጎትና ጥማት ያለዉን አሸባሪው የጥፋት ሃይል ዳግም የትግራይን ህፃናት በጦርነት እንዳይማግድ የሽብር ቡድኑን የጦርነትና የግጭት አባዜን ማስቆም ይኖርበታል" ብለዋል። ዶ/ር ለገሰ፥ "ለጥቂት የሽብር ቡድኑ አባላት ፍላጎትና የስልጣን ጥማት ሲባል ምንም አይነት ጥቅም ያላስገኘለትን ይልቁንም ልጆቹ የተማገዱበትንና ህይወቱ እንዲመሰቃቀል ያደረገዉን ቡድን ድርጊት ማውገዝ ብቻ ሳይሆን በጥብቅ መቃወም፤ መታገል መጀመር መቻል አለበትም" ሲሉም ተናግረዋል። "በትግራይ ክልል በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች እና በዉጭ ያለዉ የትግራይ ማህበረሰብም የትግራይ ክልልና ህዝብ ወደ ሰላማዊ ህይወቱ እንዲመለስ፣ ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ችግሮቹ እንዲፈቱና ዘላቂ ጥቅሞቹ እንዲረጋገጡ የበኩለቸዉን ድርሻ መወጣት ይኖርባቸዋል" ብለዋል። ያንብቡ - telegra.ph/UPDATE-01-05-2 @tikvahethiopia

#Update የኖርዌይ የስደተኞች ካውስል እገዳው እንደተነሳለት አሳወቀ። የኖርዌይ የስደተኞች ካውንስል / NRC / በሰብአዊ ድጋፍ ስራው ላይ ለ5 ወራት ተጥሎበት የነበረው እገዳ እንደተነሳለት በኢት
+1
#Update የኖርዌይ የስደተኞች ካውስል እገዳው እንደተነሳለት አሳወቀ። የኖርዌይ የስደተኞች ካውንስል / NRC / በሰብአዊ ድጋፍ ስራው ላይ ለ5 ወራት ተጥሎበት የነበረው እገዳ እንደተነሳለት በኢትዮጵያ ባለስልጣናት እንደተገለፀለት አሳውቋል። እግዱ የተነሳለት ከታህሳስ 22/2014 ጀምሮ እንደሆነ ተገልጿል። ይህን አስመልክቶ ድርጅቱ ያወጣው መግለጫ ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia