en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
የማኅደረ ስብሀት ወይብላ ቅድስት ማርያምና ቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ወደ መንበረ ክብራቸው ገቡ። የማኅደረ ስብሐት ወይብላ ቅድስት ማርያምና የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ትላንት ካደሩበት ቀራንዮ መድኅኔዓለም
+4
የማኅደረ ስብሀት ወይብላ ቅድስት ማርያምና ቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ወደ መንበረ ክብራቸው ገቡ። የማኅደረ ስብሐት ወይብላ ቅድስት ማርያምና የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ትላንት ካደሩበት ቀራንዮ መድኅኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በብጹእ አቡነ መልከጼዴቅ ፣ ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ፣በአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ በብዙ መቶ ሺዎች በሚቆጠሩ ምእመናን ታጅቦ ወደ መንበረ ክብሩ ገብቷል። በትላንትናው ዕለት የተፈጠረውን ችግር ለመፍታትም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ መልአከ ህይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፉ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ክፍል ኃላፊ ፤ ከደብሩ ኃላፊ፣ ከወጣቶች ተወካዮች እንዲሁም ከምእመናን ተወካዮች ጋር ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ 6 ሰዓታትን የፈጀ ውይይት በማድረግ በቀጣይ ቀናት አሉ የተባሉ ጥያቄዎችን በተመለከተ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር በኩል እንዲቀርብ ስምምነት ላይ ተደርሷል። የተፈጠረውን ችግር በተመለከተ ከካህናት፣ከሰንበት ትምህርት ቤትና ከምዕመናን ተወካዮች ተውጣጥቶ ከተቋቋመው ኮሚቴ ጋር በጋራ ለመስራትና ጥያቄዎቹ በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ ተቋማዊ የሆነ አሰራርን ተከትሎ በቅድሚያ ለአ/አ ሀገረ ስብከት እንዲቀርብ ስምምነት ላይ መደረሱ ታውቋል። @tikvahethiopia

#UPDATE " መንግሥት ማጣራት በማድረግ ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለሕግ ያቀርባል " - የመንግስት ኮሚኒኬሽን የኢትዮጵያ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፤ የጥምቀት በዓል በመላ ኢትዮጵያ
#UPDATE " መንግሥት ማጣራት በማድረግ ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለሕግ ያቀርባል " - የመንግስት ኮሚኒኬሽን የኢትዮጵያ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፤ የጥምቀት በዓል በመላ ኢትዮጵያ በደመቀና በሰላማዊ መንገድ ቢከበርም በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ እና በቡራዩ አዋሳኝ ወይብላ ማርያም ቤተክርስቲያን አካባቢ በተፈጠረው ችግር በዓሉ መስተጓጎሉና በሰዎች ላይም ሞትና ከባድ ጉዳት መድረሱን አሳውቋል። በዓሉ በተገቢው መንገድ ባለመከበሩ፣ እንዲሁም በደረሰው የሰው ሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት መንግሥት ጥልቅ ኀዘን እንደተሰማው ገልጿል። መንግሥት በስፍራው የተፈጠረውን ክሥተት በማጣራት ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለሕግ እንደሚያቀርብም አስታውቋል። " ለዘመናት የኢትዮጵያዊነታችን መገለጫ እንዲሁም የጠንካራ ማኅበራዊ መስተጋብራችን ማሳያ በሆኑ እንደ ጥምቀት በዓል ያሉ ሀብቶቻችንን ለማደብዘዝ የሚደረግ ማንኛውም ጥረት በሁሉም ኢትዮጵያዊ ትብብር ይከሽፋል። " ብሏል። * ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia

#Update " በእሳት አደጋው 2.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል " - የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ አትላስ አካባቢ በደረሰው
+1
#Update " በእሳት አደጋው 2.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል " - የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ አትላስ አካባቢ በደረሰው የእሳት አደጋ 2.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳውቋል። በአደጋው ከንብረት ውድመት በቀር በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም። የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ተከላካይ ሰራተኞች ባደረጉት ጥረት ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ከውድመት ማዳን መቻሉም ተገልጿል። 8 ሰዓታትን በፈጀው እሳት የማጥፋት ሥራ 119 የአደጋ መከላከል ባለሙያዎች መሳተፋቸውንም ተናግሯል፡፡ የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥የአደጋው መንስኤ አለመታወቁንና 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ መጋዘን ሙሉ በሙሉ መውደሙን ተናግረዋል፡፡ አደጋውን ለመቆጣጠር 14 የእሳት አደጋ ተሽከርካሪዎች፣ 2 አምቡላንሶች፣ 142,000 ሊትር ውሃ እና 155 ሊትር ኬሚካል ጥቅም ላይ መዋሉንም አሳውቀዋል። ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 @tikvahethiopia

#Update ቅዱስ ፓትርያርኩ ህክምናቸውን ጨርሰው ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተመለሱ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ
#Update ቅዱስ ፓትርያርኩ ህክምናቸውን ጨርሰው ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተመለሱ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሆስፒታል ሲደረግላቸው የነበረውን ህክምና ጨርሰው በሙሉ ጤንነት ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ በሰላም ተመልሰዋል። መረጃውን ከኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው ያገኘነው። @tikvahethiopia

#Ethiopia ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በህገመንግስቱ መሰረት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ማቋቋምያ አዋጅን ባለፈው ሳምንት መፈረማቸውን ገልፀዋል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ፥ " መፈረም ኃላፊነቴ ቢሆ
+1
#Ethiopia ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በህገመንግስቱ መሰረት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ማቋቋምያ አዋጅን ባለፈው ሳምንት መፈረማቸውን ገልፀዋል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ፥ " መፈረም ኃላፊነቴ ቢሆንም እውነተኛና አካታች ብሄራዊ ምክክርን ቁልፍነት ስለማውቅ፣ ስለሰራሁበት ፣ ውጤቱንም ስላየሁ አምንበታለሁ " ብለዋል። " እንደዚህ ያለ ምክክር በመሰረታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት እንዲኖር ያደርጋል፤ ሀሳብን በግስ መጫን፣ ጦር መማዘዝን፣ ህዝብን ፣ አገርን አደጋ ላይ መጣልን ... ከመሳሰሉ አደጋዎች ያድናል። የንግግር የመደማመጥ፣ መከባበር አዲስ ባህል ይፈጥራል። እንደ እኛ ከአውዳሚ ጦርነት ማግስት ለሚገኝ አገር ጠቀሜታው ግልፅ ነው " ሲሉ ገልፀዋል። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አባላት ጥቆማ ለአንድ ሳምንት ከተራዘመ በኃላ ጥር 13 (ዛሬ) እንደሚያበቃ የገለፁት ፕሬዜዳንቷ "ለኮሚሽነርነት የተጠቆሙ ሴቶች ቁጥር አነስተኛ ይሆናል ብዬ እሰጋለሁ" ብለዋል። " ሴቶች መጠቆም አለባቸው። ያካሄድነው ጦርነት ያስከተለው ሰቆቃ የሴት መልክ ነው ያለው። በመቐለ እና በደሴ መጠለያ ጣቢያዎች ያነጋገርኳቸው ሴቶች ይህንኑ ያረጋግጣል። ይሁንና እያዘኑ፣ እያለቀሱ ቢያነጋግሩኝም እንባቸውን ጠርገው ጥያቄ አቅርበዋል። የመፍትሄ ሀሳብም ሰጥተዋል " ሲሉ ገልፀዋል። ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ፤ " ጦርነታ በሴቶች ላይ ያስከተለው ሁኔታ ገና ብዙ የሚታይ ነው። ሴት ሰለባ ብቻ ሳትሆን የመፍትሄ አካል መሆንዋ ከግንዛቤ መወሰድ አለበት፤ የሴቶች ኮሚሽነሮች መኖር ካላቸው አጠቃላይ ኃላፊነት ጋር የእነዚህም ሴቶች ድምፅ ይሆናሉ " ብለዋል። አክለው፥ " በቀረው ጠባብ ጊዜ የወጡትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ሴቶችን ትጠቁሙ ዘንድ ለማበረታታት እፈልጋለሁ " ሲሉ ገልፀዋል። * ሙሉ መልዕክቱ ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia

#Gambella " በጥቃቱ የ8 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 5 ሰዎች ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል " - ፖሊስ በጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው በመግባት
+1
#Gambella " በጥቃቱ የ8 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 5 ሰዎች ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል " - ፖሊስ በጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው በመግባት ጥቃት ማድረሳቸውን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። በጥቃቱ የ8 ሠዎች ህይወት ሲያልፍ በ5 ሠዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን ተገልጿል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቡላ ኡቦንግ ፥ በጋምቤላ በዚህ ሰዓት በጋ ስለሆነ እና ክልሉን ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚያጋራው ድንበር ሰፊና ክፍት ስለሆነ የታጣቂዎች የመግባትና የመውጣት አዝማሚያ አለ ብለዋል። የሙርሌ ታጣቂዎች ትናትና ድንበር አቋርጠው በመግባት በኑዌር ዞን አኮቦ ወረዳ በካንካን ቀበሌ ድንገተኛ ተኩስ በመክፈት የ8 ሠዎች ህይወት ወዲያው ሲያልፍ 5 ሠዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን አመልክተዋል። ኮሚሽነር አቡላ አክለውም ክልሉ በአሁኑ ሰዓት ልዩ ኃይሉንና ሚሊሻ በመጠቀም ሰላምና ፀጥታ የማስከበር ስራውን እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ ፤ የአካባቢው ማህበረሰብ የታጣቂ ቡድኑን እንቅስቃሴ ነቅቶ በመጠበቅ ለመንግሥት ተገቢውን ጥቆማ ማድረግ እንደሚኖርበት አሳስበው በደረሰው ጉዳት ማዘናቸውን ገልጸዋል። የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ከዓመታት በፊት፤ በኑዌር ዞን እና አኙዋ ዞኖች ገብተው በርካታ ሕፃናት አፍነው ሲወስዱ፣ ከአንድ መቶ ሰባ በላይ ሰዎች ደግሞ ሕይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል። ከ2 ሺህ በላይ ከብቶች መውሰዳቸውንም ኮሚሽነሩ አስታውሰዋል። በወቅቱ የኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት ወደ ደቡብ ሱዳን በመግባትና ታጣቂዎቹ የሚኖሩበት አካባቢ ላይ ጥቃት በመፈፀም ታፍነው ከተወሰዱት ሕፃናት መካከል ከ100 ሕፃናት በላይ ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለሱን አስረድተዋል። ምንጭ፦ የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት @tikvahethiopia

#EthiopianCoffee☕️ 11 ሺህ ከረጢት የኢትዮጵያ 🇪🇹 ቡና በአምስት ሰከንድ ውስጥ ተሸጠ። በቻይና በተካሄደ የቀጥታ ሽያጭ ስነስርዓት 11 ሺህ ከረጢት የኢትዮጵያ ቡና በአምስት ሰከንድ ው
+1
#EthiopianCoffee☕️ 11 ሺህ ከረጢት የኢትዮጵያ 🇪🇹 ቡና በአምስት ሰከንድ ውስጥ ተሸጠ። በቻይና በተካሄደ የቀጥታ ሽያጭ ስነስርዓት 11 ሺህ ከረጢት የኢትዮጵያ ቡና በአምስት ሰከንድ ውስጥ መሸጡን የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። በሚኒስቴሩ የአፍሪካ ጉዳይ ጀኔራል ዳይሬክተር ዉ ፔንግ በትዊተር ገጻቸው ፤ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በተገኙበት የተካሄደው የቀጥታ ሽያጭ ሂደት ውጤታማ ነበር ብለዋል። የኢትዮጵያ ቡና በቻይና ገበያ ውስጥ ፍላጎቱ እያደገ መምጣቱን የገለጹት ዉ ፔንግ፤ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ከጥር እስከ ህዳር ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ወደቻይና የገባው የኢትዮጵያ ቡና መጠን ቀደም ካለው ጊዜ አንጻር በ196 በመቶ እድገት ማሳየቱን ገልጸዋል። በመጪዎቹ ዓመታት ቻይና ከአፍሪካ የግብርና ምርቶችን በስፋት እንደምታስገባም ጠቁመዋል። #ENA @tikvahethiopia

#ወይብላ_ማርያም የኢ.ኦ.ተ.ቤ. መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት ፥ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ መቅደሷ ሳትገባ ወደ ኋላ ተመልሳ ቀራ
#ወይብላ_ማርያም የኢ.ኦ.ተ.ቤ. መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት ፥ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ መቅደሷ ሳትገባ ወደ ኋላ ተመልሳ ቀራንዮ መድኃኔዓለም የቆየችውን ወይብላ ማርያም ታቦትን ለማስገባት ምእመናንንም ለማጽናናት በቀራንዮ መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን መገኘታቸውን አሳውቋል። ከእርሳቸው ጋር የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለሀይማኖት ወልዱ በስፍራው መገኘታቸውም ተገልጿል። በክስተቱ ላይ የደረሰውን ጉዳት አስመልክቶ ደግሞ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እና ሌሎች የቤተክርስቲያኗ ክፍሎች የሚሰጡት መረጃ ይፋ ይደረጋል ተብሏል። @tikvahethiopia

ቫይረሱ ቢቀያየርም መፍትሔው አልተቀየረም! ስለክትባት እና ተያያዥ መረጃዎች የጤና ሚኒስቴር መመሪያዎችን ይከተሉ!! #Lifebuoy #LifebuoyEthiopia #COVID19 @tikvahethiopia

Video : የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ፔንታጎን በነሃሴ 29 (እ.ኤ.አ.) በካቡል ከተማ 10 ሰዎች የተገደሉበትን የድሮን ድብደባ የሚያሳይ ቪዲዮ ዛሬ ሀሙስ አውጥቷል። በዚህ የድሮን ድብደባ 7 ህፃናትን ጨምሮ 10 የአንድ ቤተሰብ አባላት መገደላቸው ይታወሳል። በድሮን ለተገደሉት 10 ሰላማዊ ሰዎች የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ፣ ፔንታገን አደጋውን ያደረሱትን የሠራዊቱን አባላት እንደማይቀጣ ማሳወቁ ይታወሳል። @tikvahethiopia

#Balderas " ጉዳት ያደረሱት የፀጥታ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ እንጠይቃለን " - ባልደራስ ፓርቲ ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ ዛሬ ጥር 12/2014 ዓ.ም.
#Balderas " ጉዳት ያደረሱት የፀጥታ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ እንጠይቃለን " - ባልደራስ ፓርቲ ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ ዛሬ ጥር 12/2014 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በስተ ምዕራብ በሚገኘው የወይብላ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለጥምቀት የወጣ ታቦታ እና አጅበውት በነበሩት ህዝበ ክርስቲያን ላይ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሀይል ተኩስ በመክፈት ታቦቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገባ ባደረጉት ክልከላ እና ይህን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት በርካታ ምዕመናን ለጉዳት መዳረጋቸውን አሳውቋል። ፓርቲው፥ " በዚህ ግጭት ከልጅ እስከ አዛውንት የአካል እና የስነ-ልቦና ጉዳት በምዕመናኑ ላይ መድረሱን ተገንዝቤያለሁ " ብሏል። በርካታ ምዕመናን በህክምና መስጫ ተቋማት ህክምና እየተከታተሉ እንደሆነም ለመረዳት ተችሏል፡፡ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በመግለጫው ላይ በደረሰው ጉዳት ጥልቅ ሀዘን የተሰማው መሆኑን ገልፆ ፥ " የኦህዴድ/ብልፅግና ’መንግስት’ አሁንም ህግ የማስከበር ተቀዳሚ ተግባሩን አለመወጣቱን ባልደራስ አበክሮ ያወግዛል " ብሏል። አክሎም ፥ " አሁንም እየደረሰ ላለው ውጥረት እና ግጭት ’መንግስት’ ህግ እንዲያስከብር እንጠይቃለን። ጉዳት ያደረሱትን የፀጥታ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑም ባልደራስ ይጠይቃል " ብሏል በመግለጫው። ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ከኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት ወይም ከኢኦተቤ መገናኛ ብዙሀን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት በኩል የወጣ ተጨማሪ መረጃ ለመፈለግ ጥረት ብናደርግም ለጊዜው ማግኘት አልቻልንም። @tikvahethiopia

#Balderas " ጉዳት ያደረሱት የፀጥታ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ እንጠይቃለን " - ባልደራስ ፓርቲ ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ ዛሬ ጥር 12/2014 ዓ.ም.
#Balderas " ጉዳት ያደረሱት የፀጥታ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ እንጠይቃለን " - ባልደራስ ፓርቲ ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ ዛሬ ጥር 12/2014 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በስተ ምዕራብ በሚገኘው የወይብላ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለጥምቀት የወጣ ታቦታ እና አጅበውት በነበሩት ህዝበ ክርስቲያን ላይ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሀይል ተኩስ በመክፈት ታቦቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገባ ባደረጉት ክልከላ እና ይህን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት በርካታ ምዕመናን ለጉዳት መዳረጋቸውን አሳውቋል። ፓርቲው፥ " በዚህ ግጭት ከልጅ እስከ አዛውንት የአካል እና የስነ-ልቦና ጉዳት በምዕመናኑ ላይ መድረሱን ተገንዝቤያለሁ " ብሏል። በርካታ ምዕመናን በህክምና መስጫ ተቋማት ህክምና እየተከታተሉ እንደሆነም ለመረዳት ተችሏል፡፡ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በመግለጫው ላይ በደረሰው ጉዳት ጥልቅ ሀዘን የተሰማው መሆኑን ገልፆ ፥ " የኦህዴድ/ብልፅግና ’መንግስት’ አሁንም ህግ የማስከበር ተቀዳሚ ተግባሩን አለመወጣቱን ባልደራስ አበክሮ ያወግዛል " ብሏል። አክሎም ፥ " አሁንም እየደረሰ ላለው ውጥረት እና ግጭት ’መንግስት’ ህግ እንዲያስከብር እንጠይቃለን። ጉዳት ያደረሱትን የፀጥታ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑም ባልደራስ ይጠይቃል " ብሏል በመግለጫው። ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ከኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት ወይም ከኢኦተቤ መገናኛ ብዙሀን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት በኩል የወጣ ተጨማሪ መረጃ ለመፈለግ ጥረት ብናደርግም ለጊዜው ማግኘት አልቻልንም። @tikvahethiopia

#Update 📍ሱዳን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ የሆኑት ሞሊ ፊ እና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ዛሬ በሱዳን ከሉዓላዊው ምክር
+1
#Update 📍ሱዳን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ የሆኑት ሞሊ ፊ እና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ዛሬ በሱዳን ከሉዓላዊው ምክር ቤር ወታደራዊ መሪዎች ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል። ሁለቱ የአሜሪካ ባለስልጣናት ሀገራቸው አሜሪካ ለሱዳን ህዝብ ነፃነት፣ ሰላም እና ፍትህ ቁርጠኛ መሆኗል ግልፀው ፤ ብጥብጥ እና ሁከት ሳይቆም የፖለቲካ ሂደቱ ሊቀጥል እንደማይችል ግልጽ አድርገዋል። በተጨማሪም ባለስልጣናቱ ከዶክተር ኤል ሃዲ ኢድሪስ ጋር በቅርቡ በካርቱም እና በዳርፉር ስለተከሰተው ሁከትና ብጥብጥ እንዱሁም ሱዳን አሁን ካለችበት የፖለቲካ ችግር እንዴት ልትወጣ እንደምትችል ተነጋግረዋል። ሞሊ ፊ እና ዴቪድ ሳተርፊልድ ባወጡት መግለጫ የሱዳን ጦር በተቃዋሚዎች ላይ የሚወስደውን የኃይል እርምጃ ያወገዙ ሲሆን ግጭት ካልቆመና የሱዳንን ህዝብ ፍላጎት የሚያንፀባርቅ በሲቪል የሚመራ መንግስት ወደቦታው ካልተመለሰ የቆመው የአሜሪካ እርዳታ እንደማይቀጥል አሳውቀዋል። (ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል) በቀጣይ በአዲስ አበባ በተለይ በሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ዙሪያ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ይነጋገራሉ። @tikvahethiopia

ቪኪ ፎርድ ኢትዮጵያ ናቸው። የዩናይትድ ኪንግደም (UK) የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ቪኪ ፎርድ እዚህ ኢትዮጵያ ይገኛሉ። ቪኪ ፎርድ ዛሬ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር ተገናኝ
ቪኪ ፎርድ ኢትዮጵያ ናቸው። የዩናይትድ ኪንግደም (UK) የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ቪኪ ፎርድ እዚህ ኢትዮጵያ ይገኛሉ። ቪኪ ፎርድ ዛሬ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን ገልፀዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በተገናኙበት ወቅት ዩናይትድ ኪንግደም የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት እንደሚያሳስባት ገልፀው ነገር ግን ዘላቂ ሰላም በኢትዮጵያ እንደሚሰፍን ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። በቅርቡ የተካሄደውን የእስረኞች መፈታት እና የብሔራዊ ውይይቱን በደስታ እንደሚቀበሉ አሳውቀዋል። የዩናይትድ ኪንግደም እና ኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ አጋርነት እና መልሶን ግንባታን በተመለከተ የዩናይትድ ኪንግደምን ድጋፍ በተመለከተ መነገራቸውን ቪኪ ፎርድ አሳውቀዋል። በተጨማሪ ቪኪ ፎርድ ከገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ጋር መገናኘታቸውን ገልፀዋል። እንዲሁም ደግሞ ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴንም ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ ስላለው ሰላም አስፈላጊነት እና ስለ ዩናትድ ኪንግደም እና ኢትዮጵያ ግንኙነትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ውይይት ማካሄዳቸውን ገልፀዋል። @tikvahethiopia

#GeneralAbebawTadesse ጄነራል አበባው ታደሰ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ወደ ትግራይ ዘልቆ ያልገባበትን ምክንያትም ከፋና ቴሌቪዥን ጣቢያ ተጠይቀው መልሰዋል። ጄነራል አበባው ታደሰ ምን አሉ
#GeneralAbebawTadesse ጄነራል አበባው ታደሰ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ወደ ትግራይ ዘልቆ ያልገባበትን ምክንያትም ከፋና ቴሌቪዥን ጣቢያ ተጠይቀው መልሰዋል። ጄነራል አበባው ታደሰ ምን አሉ ? " ... ለምንድነው የቆምነው ? የሚለው በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው። ... ለምን ቆምን የሚለው ሲገለፅ ምዕራፍ አንድን ጨርሰናል ነው የሚለው ስለዚህ ምዕራፍ አንድን ጨርሰናል ማለት ቃል በቃል ምዕራፍ ሁለት አለ ማለት ነው። መቐለና ትግራይ ግን የኢትዮጵያ ግዛት ነው ፤ ማንም እኛን አያቆመንም ፤ እንገባለን ጠላት እናጠፋለን ፤ ይሄ ምንም የሚያሻማ ነገር የለም። የኢትዮጵያ ህዝብም እንዳለቀ አድርጎ አይደለም እራሱ መውሰድ ያለበት ፤ አላለቀም። በዚህ በኩል ሸኔ ነኝ፣ እንደዚህ ቅማንት ነኝ ፣ በዚህ ምናምን ነኝ የሚባል ነገር ከዚህ በኃላ እየሰራም፤ የጊዜ ጉዳይ ነው፤ አሁን አንድ ትልቅ ግዳጅ ስላለን ጠላት ስላለን ነው እንጂ ይሄ የጊዜ ጉዳይ ነው መጥፋት አለበት። መጥፋት ማለት ምን ማለት ነው ? ይሄ ትጥቅ አንስቶ በሀገር ውስጥ መዋጋት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ስልጣኔ አይደለም ፤ ስልጣኔው በሀሳብ ነው ሀሳቡን ይሽጥ " ሲሉ ተደምጠዋል። @tikvahethiopia

#GeneralAbebawTadesse ህወሓት ወደ አዲስ አበባ ከተማ ተቃረብኩኝ ባለበት ወቅት የውጭ ሀገር ኃይሎች አዲስ አበባን ለመቆጣጠር ኃይል አዘጋጅተው እንደነበር የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ምክትል
#GeneralAbebawTadesse ህወሓት ወደ አዲስ አበባ ከተማ ተቃረብኩኝ ባለበት ወቅት የውጭ ሀገር ኃይሎች አዲስ አበባን ለመቆጣጠር ኃይል አዘጋጅተው እንደነበር የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ምክትል ኢታማዦር ሹሙ ጄነራል አበባው ታደሰ በፋና ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው ተናግረዋል። ጄነራል አበባው፤ " ጣርማ በር ... ሲገባ እኮ ሰላም አስከባሪ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ፣ እገሌ አገር እገሌ አገር ልል እችላለሁ ፥ ሚሲነሪ ወታደር እየተዘጋጀ እነሱን የሚያግዝ ፣ ሽግግር መንግስት እየቆመ፣ ሽግግር መንግስት ለማቋቋም ሰነድ ተዘጋጅቶ የስልጣን ክፍፍል እየተጀመረ፣ ሸኔም የኦሮሞን የመገንጠል እንዲያነሳ ጥያቄ እየተስተካከል ሀገር ነው እኮ የነበረው " ብለዋል። ነገር ግን በተካሄደው የ " ዘመቻ ለህብረ ብሄራዊ አንድነት " ሀገርን ከብተና ማዳን እንደተቻለና ሀገር እንደዳነ ጄነራሉ ተናግረዋል። ጄነራል አበባው ፥ " የመጀመሪያው ውጤት ሀገር ነው የዳነው ፣ ሀገር ከብተና ነው የዳነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲገቡ የእኔ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ከሀገር በላይ አይደለም፤ ምንም ማለት አይደለም ነው፤ ይሄን ሁሉ ጉድ ስለሚያውቁ ስለዚህ ሀገር ከማውቀው ወንድሞቼ ጋር ሆኜ ደረቴን ሰጥቼ መዋጋት አለብኝ ብለው ነው የሄዱት። ያን ያክል የሚያስኬድ ነገር ነበራቸው ወይ ? ተብሎ ከተጠየቀ ግን ኢትዮጵያን ሊያፈርሷት ጫፍ ደርሰው ነበር " ብለዋል። @tikvahethiopia

#AddisAbaba 📍ቦሌ አትላስ አካባቢ የደረሰው አደጋ 9:20 አካባቢ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል። ዛሬ ከሰዓት 8 ሰዓት አካባቢ ቦሌ አትላስ አካባቢ የሚገኙት የግንባታ ዕቃዎች መጋዘኖች ላይ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል። የእሳት አደጋው በቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስትያን እና በአትላስ እንዲሁም በፀጋ ሆስፒታል መሃል ላይ በሚገኙት የንግድ ሱቆች መጋዘኖች ላይ የደረሰው። የአደጋው መነሻ እስካሁን አልታወቀም። ቁጥራቸው 7 የሚደርስ የአዲስ አበባ ከተማ አደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽን እሳት አደጋ መከላከል ተሸከርካሪዎች የእሳት አደጋው ወደ ሌሎች አካባቢዎች አንዳይዛመት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል። እሳቱ 9፡20 አካባቢ ማጥፋት ተችሏል። የአካባቢው ነዋሪዎች በተለይም ወጣቶች እሳቱን ለማጥፋት ያደርጉት የነበረው ርብርብ የሚደነቅ እንደነበር ተገልጿል። Credit : ETHIO FM 107.8 ቪድዮ : አቤል @tikvahethiopia

#Adama የአርቲስት ኑሆ ጎበና የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ በአዳማ ከተማ ተፈፅሟል። በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ ቤተስቦቹ፣ አርቲስቶች፣ ወዳጆቹ ፣ አድናቂዎቹ እንሲሁም የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተ
+3
#Adama የአርቲስት ኑሆ ጎበና የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ በአዳማ ከተማ ተፈፅሟል። በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ ቤተስቦቹ፣ አርቲስቶች፣ ወዳጆቹ ፣ አድናቂዎቹ እንሲሁም የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር። አርቲስት ኑሆ ጎበና በድሬደዋ ቀፊራ ገንደጋራ በ1940 ዓ.ም ነበር የተወለዱት ፤ ለረጅም አመታት ለኦሮሞ ኪነ ጥበብና ለአፋን ኦሮሞ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አንጋፋ አርቲስት ነበሩ። ፎቶ ፦ ኦቢኤን @tikvahethiopia

+3
#FireAlert🚨 በአዲስ አበባ ከዑራኤል ወደ አትላስ በሚወስደው መንገድ የእሳት አደጋ መከሰቱን የቲክቫህ ቤተሰቦች ሪፖርት አድርገዋል። ፎቶ እና ቪድዮ : Rebka F. & Israel Taye (Tikvah-Family) @tikvahethiopia

" ምንም አይነት የቴሌግራም ገፅ የለንም " - ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት ምንም አይነት የቴሌግራም ገፅ እንደሌለው አሳውቋል። ሳፋሪኮም በቅርቡ የተለያ
" ምንም አይነት የቴሌግራም ገፅ የለንም " - ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት ምንም አይነት የቴሌግራም ገፅ እንደሌለው አሳውቋል። ሳፋሪኮም በቅርቡ የተለያዩ የቴሌግራም ገጾች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስም ተከፍተው መረጃ እያሰራጩ መሆኑን ተረድተናል ብሏል። ድርጅቱ እስከአሁን ምንም የቴሌግራም ገጽ እንደሌለው እያስታወቀው ሳፋሪኮም በገጾቹ የሚተላለፉት መረጃዎች በድርጅቱ እውቅና እንደሌላቸው አረጋግጦልናል። የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በፌስቡክ፣ ትዊተር ፣ ሊንክድኢን እና ቲክቶክ ላይ ይፋዊ ገፆች ያሉት ሲሆን በፌስቡክ፣ ትዊተር እና ቲክቶክ አድራሻው #SafaricomET እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። የLinkedIn አድራሻው Safaricom Telecommunication Ethiopia PLC. እንደሆነም ገልጿል። @tikvahethiopia