en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
#UPDATE በጎንደር ከተማ የሰዓት እላፊ ገደብ ተነስቷል። በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ በአስቸካይ ጊዜ አዋጅ ተጥለዉ የነበሩ ክልከላዎች ዉስጥ የሰዓት ገደቡ ተነስቷል። ከምሽቱ 4.00 እስከ 11.30
+1
#UPDATE በጎንደር ከተማ የሰዓት እላፊ ገደብ ተነስቷል። በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ በአስቸካይ ጊዜ አዋጅ ተጥለዉ የነበሩ ክልከላዎች ዉስጥ የሰዓት ገደቡ ተነስቷል። ከምሽቱ 4.00 እስከ 11.30 የነበረዉ ክልከላ የተነሳ እና 24 ሰዓት በሰላም ሁሉም አካል ፣ ተሸከርካሪም ጭምር መንቀሳቀስ እንደሚቻል ትላንት ተወስኗል። ሌሎች ክልልከላዎች ግን የሚቀጥሉ ይሆናል። በዚህም መሰረት ፦ • ከተፈቀደለት የጸጥታ አካሉ ዉጭ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው። • ማንኛዉም ሰዉ መሳሪያ/ተተካሽ/ ይዞ ወደ መጥጥ ቤት ይዞ መግባት ሆነ መዝናናት በጥብቅ የተከለከለ ነው። • እንግዶችን ሆነ ማንኛዉንም ሰዉ ማዋከብ መረበሽ የተከለከለ ነው። • አግባብነት የሌለዉ ዋጋ በማናቸዉም ሽያጮች አገልግሎቶች መጨመር የተከለከለ ነዉ። • ማንኛዉም ሰዉ የሚመለከታቸዉ የጸጥታ አካላት መታወቂያ እንዲያሳይ ሲጠየቅ የማሳየት #ግዴታ አለበት። • የብሎክ አደረጃጀት ጥበቃዉ የማይቃረጥና ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። • በፀጥታ አካሉ አማካኝነት የኬላ ፍተሸ የድነገተኛ ፍተሻ ተጠናክረዉ የሚቀጥሉ ይሆናል። የጥምቀት በዓል በሰላም እንዲከበር ዘንድ ሁሉም ሰዉ ከፀጥታ አካሉ ጎን እንዲቆም ፤ ከአቅም በላይ የሆኑ የጸጥታ ችግሮች ሲገጥሙ በአቅራቢያ ለሚገኘዉ የፖሊስ ጣቢያ ሪፖረት ማድረግ ወይም በየአካባቢዉ ለሚገኝ የፀጥታ አካል ሪፖርት በማድረግ የመተባበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ ማሳሰቢያ ተላልፏል። መረጃው ከጎንደር ከተማ አስተዳደር ኮማንድ ፖስት የተገኘ ነው። @tikvahethiopia

ድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ❤️ ሀገራችን ከስምንት አመታት ቆይታ በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው በመመለስ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ዛሬ ምሽት 4:00 ላይ ታደርጋለች። ብሄራዊ ቡድናችን በምድቡ የመክፈቻ ጨዋታ
+1
ድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ❤️ ሀገራችን ከስምንት አመታት ቆይታ በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው በመመለስ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ዛሬ ምሽት 4:00 ላይ ታደርጋለች። ብሄራዊ ቡድናችን በምድቡ የመክፈቻ ጨዋታ ኬፕ ቨርዴን የሚገጥም ይሆናል። ቡድናችን ውድድሩ ሳይጀምር ቀደም ብሎ ካሜሮን በመግባት ጠናካራ ልምምድ ሲያደርግ መቆየቱ አይዘነጋም። በካሜሩን የሚገኙ የቲክቫህ አባላት በቀጥታ ከስፍራው መረጃዎችን @tikvahethsport በኩል ይልኩላችኃል። መልካም እድል ለብሄራዊ ቡድናችን ! @tikvahethsport

የሴራ በዓል በቁሊቶ ከተማ እየተከበረ ነው። በደቡብ ክልል የሀላባ ብሔር የዘመን መለወጫ ሴራ በዓል በቁሊቶ ከተማ እየተከበረ እገኛል። በዓሉ እየተከበረ ያለው በሲምፖዝየም ሲሆን የብሔሩ ባህላዊ አስተ
+1
የሴራ በዓል በቁሊቶ ከተማ እየተከበረ ነው። በደቡብ ክልል የሀላባ ብሔር የዘመን መለወጫ ሴራ በዓል በቁሊቶ ከተማ እየተከበረ እገኛል። በዓሉ እየተከበረ ያለው በሲምፖዝየም ሲሆን የብሔሩ ባህላዊ አስተዳደር መተዳደሪያ ደንብ የሆነውን ሴራን መሰረት አድርጎ የሚከበር እንደሆነ ተጠቁሟል። በዘመን መለወጫ በዓሉ ላይ የዞኑና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ከየወረዳው የተውጣጡ የብሔሩ ተወካዮች እየተሳተፉ ነው። የሴራ በዓል በወረዳ ደረጃ በየዓመቱ እና በዞን ደረጃ ደግሞ በየሁለት ዓመቱ የሚከበር ነው። ምንጭ፦ ኢዜአ @tikvahethiopia

#USA አሜሪካ በአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮዋ በኩል ፥ በትግራይ እየተካሄደ ያለው የአየር ድብደባ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ተቀባይነት የለውም ስትል መግለጫ አውጥታለች። አሜሪካ ፥ ጦርነቱ ባስቸኳ
+1
#USA አሜሪካ በአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮዋ በኩል ፥ በትግራይ እየተካሄደ ያለው የአየር ድብደባ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ተቀባይነት የለውም ስትል መግለጫ አውጥታለች። አሜሪካ ፥ ጦርነቱ ባስቸኳይ እንዲቆም፣ ሁሉን አቀፍ ብሄራዊ ዉይይት እንዲጀመር እና ያለ ምንም እንቅፋት ርዳታ ለተቸገሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰቦች ሁሉ እንዲደርስ ጥሪያችንንም እናቀርባለን ብላለች። @tikvahethiopia

#Tigray በትግራይ ክልል ተፈናቃዮች በተጠለሉበት ካምፕ ላይ ተፈፀመ በተባለ የአየር ጥቃት 56 ሰዎች ሲገደሉ በደርዘን የሚቆጠሩት መቁሰላቸውን ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የእርዳታ ሰራተኞች እንደ
+1
#Tigray በትግራይ ክልል ተፈናቃዮች በተጠለሉበት ካምፕ ላይ ተፈፀመ በተባለ የአየር ጥቃት 56 ሰዎች ሲገደሉ በደርዘን የሚቆጠሩት መቁሰላቸውን ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የእርዳታ ሰራተኞች እንደነገሩት ሮይተርስ ዘግቧል። የአየር ጥቃቱ የተፈጸመው በክልሉ ሰሜናዊ ምዕራብ በምትገኘውና የኤርትራ ድንበር አቅራቢያ ባለች ደደቢት ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት አርብ ዕለት መሆኑንም የእርዳታ ሰራተኞቹ ገልጸዋል። ቅዳሜ የእርዳታ ሰራተኞች ለሮይተርስ እንደተናገሩት የሟቾች ቁጥር በአካባቢው ባለስልጣናት መረጋገጡን ነው። የረድዔት ድርጅት ሰራተኞች ህፃናትን ጨምሮ ሆስፒታል ውስጥ ያነሷቸውን የቆሰሉ ሰዎችን ፎቶግራፍ ለሮይተርስ መላካቸው ተገልጿል። የ ' ሽረ ስሁል አጠቃላይ ሆስፒታል ' ከጎበኙት የረድኤት ሰራተኞች መካከል አንደኛው እንደገለጹት መጠለያ ካምፑ በርካታ በእድሜ አዛውንትናና ህፃናት ያሉበት ነው። ትምህርት ቤቱ እንዴት እና ለምን ጥቃት እንደደረሰበት ግልፅ አይደለም። ሮይተርስ ጥቃቱ በገለልተኛ ወገን አልተረጋገጠም ብሏል። ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ስለጉዳዩ ለመጠየቅ ቢሞክርም እንዳልተሳካለት ፅፏል። ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ መንግስት ብዙ ጊዜ ሲቪሎችን እንደማያጠቃ መግለፁን ሮይተርስ አስታውሷል። UNOCHA ባወጣው መግለጫ ከታህሳስ 10-ታህሳስ 15 ድረስ በትግራይ ላይ በተፈጸሙ የአየር ጥቃቶች በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት መደረጉን አስፍሯል። ታህሳስ 21/2014 ዓ.ም ባወጣው ሪፖርት ከጥቅምት ወር ወዲህ ከተከሰቱት በጣም አስከፊ፣በርካታ ሞቶች ሪፖርት የተደረጉበትና በተከተታይ የተፈጸመ ነው ብሏል። በርካታዎቹ ጥቃቶች ሪፖርት የተደረጉት በአላማጣ፣ ኮረም፣ ማይጨው፣ መኮኒና ሚላዛት መሆኑን ጠቅሷል። #ሮይተርስ @tikvahethiopia

#Update በኢትዮጵያ 🇪🇹 የመጀመሪያ የሆነውን የፊልድ ማርሻል ወታደራዊ ማዕረግ ለጀነራል ብርሃኑ ጁላ ተሰጠ። በተጨማሪ ፦ • 4 ሌትናል ጀነራሎች ወደ ሙሉ ጀነራልነት፣ • 14 ሜጀር ጀነራሎች
#Update በኢትዮጵያ 🇪🇹 የመጀመሪያ የሆነውን የፊልድ ማርሻል ወታደራዊ ማዕረግ ለጀነራል ብርሃኑ ጁላ ተሰጠ። በተጨማሪ ፦ • 4 ሌትናል ጀነራሎች ወደ ሙሉ ጀነራልነት፣ • 14 ሜጀር ጀነራሎች ወደ ሌትናል ጀነራልነት፣ • 24 ብርጋዴር ጀነራሎች ወደ ሜጀር ጀነራልነት፣ • 58 ኮሎኔሎች ወደ ብርጋዴር ጀነራልነት በአጠቃላይ 100 ከፍተኛ የጦር አመራሮች እድገት ተሰጥቷል። ሹመቱ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አህመድ አቅራቢነት በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በኩል ነው የተሰጠው። መረጃው የኢብኮ ነው። @tikvahethiopia

#FDREDefenseForce መከላከያ ሰራዊት ሲጠቀምባቸው የነበሩ የማዕረግ ምልክቶች ላይ ማሻሻያ አድርጓል። በምልክቶቹ ውስጥ ጋሻና አንበሳን ጥቅም ላይ ማዋሉን ነው የተገለጸው። ማሻሻያ ያስፈለገው
+4
#FDREDefenseForce መከላከያ ሰራዊት ሲጠቀምባቸው የነበሩ የማዕረግ ምልክቶች ላይ ማሻሻያ አድርጓል። በምልክቶቹ ውስጥ ጋሻና አንበሳን ጥቅም ላይ ማዋሉን ነው የተገለጸው። ማሻሻያ ያስፈለገው የሠራዊቱ ማዕረግ አገራዊ ይሁን ወታደራዊ ታሪካዊ ይዘት ያለውና የሠራዊቱንም ባህሪ ሊገልፅ የሚችል ሆኖ እንዲዘጋጅ በማስፈለጉ መሆኑ ተገልጿል። @tikvahethiopia

#Balderas በትላንትናው ዕለት ከእስር የተፈቱት የባልደራስ ለእዉነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች እነ አቶ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ ወ/ሮ ቀለብ (አስቴር) ስዩም በዋና ጽ/ቤ
#Balderas በትላንትናው ዕለት ከእስር የተፈቱት የባልደራስ ለእዉነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች እነ አቶ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ ወ/ሮ ቀለብ (አስቴር) ስዩም በዋና ጽ/ቤት አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል። @tikvahethiopia

" ወደቤታቸው አትሂዱ " የኦሮሞ የፖለቲካ እስረኞች ጠበቆች ቡድን ፥ የኦፌኮ አመራር የሆኑት አቶ ጃዋር መሀመድ በአሁን ሰዓት ባለው የደህንነት ሁኔታ ሊጠይቋቸው የሚመጡ ሰዎችን ሊቀበሉ እንደማይችሉ
" ወደቤታቸው አትሂዱ " የኦሮሞ የፖለቲካ እስረኞች ጠበቆች ቡድን ፥ የኦፌኮ አመራር የሆኑት አቶ ጃዋር መሀመድ በአሁን ሰዓት ባለው የደህንነት ሁኔታ ሊጠይቋቸው የሚመጡ ሰዎችን ሊቀበሉ እንደማይችሉ አሳውቋል። የጠበቆች ቡድኑ ፥ የአቶ ጃዋር ጠያቂዎች ወደ መኖሪያ ቤታቸው ቢሄዱ ሊገቡ እንደማይችሉ በማወቅ ወደ ቤታቸው እንዳይሄዱ መልዕክት አስተላልፏል። ሁኔታዎች ሲመቻቹና እሳቸው ጠያቂዎቻቸውን መቀበል ሲችሉ እንደሚያሳውቅ የኦሮሞ የፖለቲካ እስረኞች ጠበቆች ቡድን ገልጿል። @tikvahethiopia

ፎቶ : የኦሮሞ ፌዴራሊት ኮንግረስ / #ኦፌኮ / ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል። Credit : Boontuu Baqqalaa @tikvahethiopia
+1
ፎቶ : የኦሮሞ ፌዴራሊት ኮንግረስ / #ኦፌኮ / ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል። Credit : Boontuu Baqqalaa @tikvahethiopia

#Update የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ፥ በኢትዮጵያ ቁልፍ ተቃዋሚዎችን ጨምሮ በርካታ እስረኞች ከእስር መፈታታቸውን በደስታ እቀበላለሁ ብለዋል። ዋና ፀሀ
+1
#Update የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ፥ በኢትዮጵያ ቁልፍ ተቃዋሚዎችን ጨምሮ በርካታ እስረኞች ከእስር መፈታታቸውን በደስታ እቀበላለሁ ብለዋል። ዋና ፀሀፊው ፥ ሁሉም ወገኖች ግጭት እንዲቆምና ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት በማድረግ ፣ እንዲሁም ተአማኒና ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ ውይይትና የእርቅ ሂደት እንዲጀመር በመስማማት ይህን ትልቅ የመተማመን ግንባታ ሂደት እንዲያጎለብቱ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል። ጉተሬዝ ፥ በኢትዮጵያ ግጭት እንዲቆም እና ሰላምና መረጋጋትን ወደነበረበት ለመመለስ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በንቃት እሰራለሁ ሲሉም አሳውቀዋል። @tikvahethiopia

#Update እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ከእስር ተፈቱ። የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ጃዋር መሀመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ሀምዛ አዳነ ከእስር ተፈተዋል። ከሰዓታት በፊት
+2
#Update እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ከእስር ተፈቱ። የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ጃዋር መሀመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ሀምዛ አዳነ ከእስር ተፈተዋል። ከሰዓታት በፊት ከጠበቃቸው መካከል ከሆኑት አቶ ቱሊ ባይሳ እነአቶ ጃዋር መሀመድ ስለመሸ እንደማይወጡ እንደነገሯቸው ለቢቢሲ ቢገልፁም ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ከማረሚያ ቤት ወጥተዋል። ሶስቱን እስረኞች የጫነ ተሽከርካሪ የቃሊቲ ማረሚያ ቤትን ለቅቆ የወጣው ከምሽቱ አራት ሰዓት ተኩል ገደማ እንደነበር ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። እስረኞቹን የያዘው ተሽከርካሪ፤ የመከላከያ ሰራዊት እና የፌደራል ፖሊስ አባላትን በጫኑ ሶስት ፒክ አፕ መኪናዎች ታጅቦ ወደ ቦሌ አቅጣጫ ሲጓዙም እንደነበር ተገልጿል። እነ ጃዋር ከእስር ሲለቀቁ አቀባበል ለማድረግ በርካታ ደጋፊዎቻቸው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቅራቢያ ሆነው ለሰዓታት ሲጠብቁ ቆይተዋል። ከእነ አቶ ጃዋር ቀደም ብሎ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ ሸምሰዲን ጣሃ ሌሎችም በአቶ ጃዋር መዝገብ ስር ያሉ እስረኞች ተፈተዋል። @tikvahethiopia

የፍትሕ ሚኒስቴር ፦ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር፣ በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የወንጀል ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሕገ-መንግስት እና የሽብር ችሎት እየታየ ከነበሩት ተ
የፍትሕ ሚኒስቴር ፦ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር፣ በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የወንጀል ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሕገ-መንግስት እና የሽብር ችሎት እየታየ ከነበሩት ተከሳሾች መካከል በነጃዋር ሲራጅ መሃመድ እና በእነ እስክንድር ነጋ ፈንታ መዝገብ ያሉ ተከሳሾች ክሳቸው በአዋጅ ቁጥር 943/2008 መሰረት እንዲነሳ ተደርጓል። ክሱ እንዲነሳ የተደረገው በቀጣይ የሚደረገውን ሃገራዊ የምክክር መድረክ ሂደት ውጤታማነት እና አካታችነት ከፍ ለማድረግ በማሰብ መሆኑ ተገልጿል። እንዲሁም በእነ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል መዐሾ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ውስጥ የጤና እና የዕድሜ ሁኔታን ከግምት በማስገባት የስድስት ግለሰቦች ክስ እንዲነሳ መደረጉን ፍትሕ ሚኒስቴር ዛሬ ምሽት አሳውቋል። @tikvahethiopia

#BREAKING ከእስር በምሕረት እንዲፈቱ የተወሰነላቸው ፦ 1. አቶ ስብሐት ነጋ 2. ወ/ሮ ቅዱሳን ነጋ 3. አቶ ዓባይ ወልዱ 4. አቶ አባዲ ዘሙ 5. ወ/ሮ ሙሉ ገብረ እግዚአብሔር 6. አቶ ኪሮስ
#BREAKING ከእስር በምሕረት እንዲፈቱ የተወሰነላቸው ፦ 1. አቶ ስብሐት ነጋ 2. ወ/ሮ ቅዱሳን ነጋ 3. አቶ ዓባይ ወልዱ 4. አቶ አባዲ ዘሙ 5. ወ/ሮ ሙሉ ገብረ እግዚአብሔር 6. አቶ ኪሮስ ሐጎስ 7. አቶ ጃዋር መሐመድና በእርሳቸው መዝገብ የተከሰሱ ሁሉ 8. አቶ እስክንድር ነጋና በእርሳቸው መዝገብ የተከሰሱ ሁሉ @tikvahethiopia

#Update በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የተከሰሱት ግለሰቦች ከማረሚያ ቤት እንዲወጡ እንደተነገራቸው ቢቢሲ ዘግቧል። የእነ አቶ ጃዋር ጠበቃ የሆኑት አቶ ቱሊ ባይሳ ፥እነ አቶ ጃዋር ከማረሚያ ቤ
#Update በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የተከሰሱት ግለሰቦች ከማረሚያ ቤት እንዲወጡ እንደተነገራቸው ቢቢሲ ዘግቧል። የእነ አቶ ጃዋር ጠበቃ የሆኑት አቶ ቱሊ ባይሳ ፥እነ አቶ ጃዋር ከማረሚያ ቤት እንዲወጡ እንደተነገራቸው እና ዛሬ በመምሸቱ አንወጣም ማለታቸውን ገልጸዋል። @tikvahethiopia

ፎቶ : አቶ እስክንድር ነጋ እና አቶ ስንታየሁ ቸኮል ከቂሊንጦ መፈታታቸውን የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አሳውቋል። @tikvahethiopia
+1
ፎቶ : አቶ እስክንድር ነጋ እና አቶ ስንታየሁ ቸኮል ከቂሊንጦ መፈታታቸውን የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አሳውቋል። @tikvahethiopia

#BREAKING የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ከእስር መፈታታቸውን ፓርቲው አሳውቋል። @tikvahethiopia
#BREAKING የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ከእስር መፈታታቸውን ፓርቲው አሳውቋል። @tikvahethiopia

#ETHIOPIA የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ዛሬ “ ጀግና ሕዝብ - በቀኝ እጁ ድልን የሚጨብጥ፣ በግራ እጁ ይቅርታና ምህረትን የሚቸር ነው! ” በሚል መልዕክት አስታላልፈዋል።
+1
#ETHIOPIA የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ዛሬ “ ጀግና ሕዝብ - በቀኝ እጁ ድልን የሚጨብጥ፣ በግራ እጁ ይቅርታና ምህረትን የሚቸር ነው! ” በሚል መልዕክት አስታላልፈዋል። በዚህ መልዕክታቸው ከድላችን ማግስት 4 ነገሮችን መርሖቻችን አድርገን እንድሄድባቸዋለን ብለዋል። እነዚህም ፦ 1ኛ. ድላችንን እንዳይቀለበስ አድርገን በሁለንተናዊ መስክ እናጠብቀዋለን። 2ኛ. ድላችን ዘላቂ እንዲሆን በፖለቲካዊና ሰላማዊ መንገዶች እንዲቋጭ እናደርገዋለን። 3ኛ. ድላችንን ለመጠበቅና ድላችን ዘላቂ ለማድረግ እንድንችል በአሸናፊ ምሕረት ግጭቱ የፈጠረውን ውጥረት እናረግባለን። 4ኛ. ያጠፋ እንዲቀጣ፣ የበደለ እንዲክስ የሚያደርግ ሁሉን አቀፍ ፍትህ በሽግርር እና በተሀድሶ ፍትህ እይታ ፣ ሀገራዊ ባህሎቻችን እና እሴቶቻችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ፍትህ እናሰፍናለን ፤ ሲሉ ገልፀዋል። እነዚህ 4ቱ መርሖች አንዱ ሌላውን ሳይተካ ሁላችንንም አሸናፊ በሚያደርግ መልኩ እንደ አስፈላጊነታቸው ሁሉ እንተገብራለን ሲሉም አሳውቀዋል። ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በመልዕክታቸው በድል ፣ በምህረትና ትህትና ኢትዮጵያን ዘላቂና የፀናች አሸናፊ እንደርጋታለንም ብለዋል። * ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia

#Update የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ጋር ትናንት ሃሙስ መነጋገራቸው ተገልጿል። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ እና አምባሳደር ፌ
+1
#Update የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ጋር ትናንት ሃሙስ መነጋገራቸው ተገልጿል። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ እና አምባሳደር ፌልትማን መነጋገራቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ትናንት ሃሙስ እንደተነጋገሩ ከመግለጽ ውጪ በምን ዐይነት መንገድ ተነጋገሩ በስልክ ወይስ በአካል ስለሚለው የገለጸው ነገር የለም፡፡ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ሆነ ጽህፈት ቤታቸው ስለጉዳዩ ያሉት ነገር የለም፡፡ ንግግሩን ተከትሎ በተለይ ዓመት ያስቆጠረውን ጦርነት በተመለከተ የሚገኙ አዎንታዊ ነገሮች ይኖራሉ በሚል አሜሪካ ተስፋ ማድረጓን ሮይተርስ ሚኒስቴሩን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን በዚህ ወደ ከኃላፊነታቸው ይለቃሉ። ምንጭ፦ አል ዓይን / ሮይተርስ @tikvahethiopia

በሰላም ተጠናቋል ! በደብረ ሮሐ ቅዱስ ላልይበላ የተከበረው የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እጅግ በታላቅ ድምቀት በሰላም መጠናቀቁን የአማራ ክልል መንግስት ሪፖርት አድርጓል። በዓሉ በሰላም እንዲከ
በሰላም ተጠናቋል ! በደብረ ሮሐ ቅዱስ ላልይበላ የተከበረው የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እጅግ በታላቅ ድምቀት በሰላም መጠናቀቁን የአማራ ክልል መንግስት ሪፖርት አድርጓል። በዓሉ በሰላም እንዲከበር ላደረጉ ሁሉ ምስጋና ቀርቧል። @tikvahethiopia