en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
" ውድድሩ በሰላም ተጠናቋል " - አ/አ ፖሊስ ለ21ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ የተካሄደው የታላቁ ሩጫ ውድድር በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ
+4
" ውድድሩ በሰላም ተጠናቋል " - አ/አ ፖሊስ ለ21ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ የተካሄደው የታላቁ ሩጫ ውድድር በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያዘጋጀው 21ኛው የሩጫ ውድድር በሰላም ተጠናቋል፡፡ ፖሊስ ፥ " የታለቁ ሩጫ ውድድር በሠላም መጠናቀቁ ኢትዮጰያ ሰላም አይደለችም የሚል መረጃ የሚያሰራጩ አካላትን መረጃቸው ትክክለኛ ያልሆነና ሀሰተኛ መሆኑን ያረጋገጠ ከመሆኑም ባሻገር ከተማችን አዲስ አበባ አስተማማኝ ሰላም የሰፈነባትና መሰል ፕሮግራሞችን ለማዘጋጀት ምቹ መሆኗን የሚያሳይ ነው " ብሏል። በመጪው ሳምንት አገራችን 35ኛውን የአፍሪካ ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ የምታስተናግድ ስለሆነ ህብረተሰቡ የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል። የዛሬው ውድድር በሠላም እንዲጠናቀቅ ድጋፍ ላደረጉ አካላትና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ የፀጥታ አካላት የአዲስ አበባ ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል። ፎቶ : ሶሻል ሚዲያ ፣ ኤፍ ቢ ሲ፣ Heddo Siebs @tikvahethiopia

ውሸት ነው ! አንጋፋው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ " ህይወታቸው አለፈ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ነጭ ውሸት ነው። በማህበራዊ ሚዲያው በፌስቡክ፣ ዩት
+1
ውሸት ነው ! አንጋፋው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ " ህይወታቸው አለፈ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ነጭ ውሸት ነው። በማህበራዊ ሚዲያው በፌስቡክ፣ ዩትዩብ፣ ቴሌግራም፣ ትዊተር በመሳሰሉት ለገንዘብ ፣ ተከታይ ፣ ላይክ እና ኮሜት ለማፍራት ሲባል ብቻ እንዲህ ያለ ፀያፍ ድርጊት መፈፀም ከአንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የማይጠበቅ ፍጹም ያፈነገጠ ስነምግባር ነው። ከዚህ ቀደም በበርካታ በሀገራችን የሚከበሩ እና ታዋቂ ሰዎች ላይ ተመሳሳይ በህይወት እያሉ ሀሰተኛ መረጃ ሲሰራጭ እንደነበር ይታወቃል። የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ዛሬ ላይ በህይወት የሌሉት በእናታችን ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ላይ የተሠራጨው ሀሰተኛ መረጃ አንዱ ነበር። ውድ የቲክቫህ አባላት ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሚፃፍ ሁሉ እውነት አይደለምና የምታዩትን ነገር ደጋግማችሁ ለማረጋገጥ እንድትሞክሩ እንዲሁም ደግሞ እርግጠኛ ያልሆናችሁበትን መረጃ ለወዳጆቻችሁ ከማጋራትም እንድትቆጠቡ አደራ እንላለን። መሰል ሀሰተኛ መረጃዎችን ባጋራን ቁጥር የሰዎችን ህይወት እየረበሽን መሆናችንን፤ ይህ ስራ ለሚሰሩት ደግሞ የገንዘብ ምንጭ መሆናችንን አውቀን መቆጠብ ይኖርብናል። @tikvahethiopia

ለፓርላማ የተመራው የክልል መለያ ተሽከርካሪዎች ሰሌዳ እንዲነሳ የሚያደርገው ረቂቅ አዋጅ ምንድነው ? (ከሪፖርተር ጋዜጣ) የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ወጥነት ያለው ብሔራዊ የተሽከርካሪ ሰሌዳ አሠራር ለመዘርጋት አልሟል፡፡ በሚኒስቴሩ የሕግ አማካሪ አቶ አበጀ ማሞ 🗣 • " ለተወካዮች ምክር ቤት የተመራው ረቂቅ አዋጅ ከፀደቀ በኋላ የክልል መለያ የያዙ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች ተግባራዊ የሚሆኑት አዲስ ብሔራዊ ሰሌዳ ይፋ እስኪደረግ ብቻ ነው " • " ተሽከርካሪ ዓለም አቀፍ ቁስ ነው፣ አንድ መኪና ከዚህ ተነስቶ ኬንያም ሆነ ሱዳን ሲሄድ የአገሮቹ መንግሥት ግራ ሊጋቡ አይገባም። ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ ተግባራዊ የሚደረገው የሰሌዳ ዓይነት የሚገልጸው ተሽከርካሪነታቸውን ብቻ ይሆናል " • " በሚኒስትሮች ምክር ቤት የፀደቀው ይኼ ረቂቅ አዋጅ፣ የክልል መለያ በሰሌዳዎች ላይ እንዲኖር የሚያዘውን አባሪ እንዲሻር ቢያደርግም፣ በቀጣይ የሚኖረውን የሰሌዳ ዓይነት አይደነግግም፡፡ ' ምን ዓይነት ሰሌዳ ይደረግ? ' የሚለው ከአዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚደረግ ጥናት ይወሰናል። ሰሌዳው ግን ' የኢትዮጵያ ሰሌዳ ' ነው የሚባለው " • " አሁን ባለው የሰሌዳ አሠራር ምክንያት ተሸርካሪዎች ከክልል ወደ ክልል ሲንቀሳቀሱ 'ሥጋት' እና 'ፍራቻ' በውስጣቸው ሊፈጠር አይገባም። አሁን ባለው የአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ይኼንን ዓይነቱን ችግር መፍቻ አንዱ መፍትሔ ብሔራዊ ሰሌዳን መተግበር ነው። " • " የተሽከርካሪ ሰሌዳው ከየት እንደወጣ ወይም የት እንደተመዘገበ የሚገልጽ መለያ ሙሉ ለሙሉ ይቀራል ማለት አይደለም። ነገር ግን ወደፊት በሚወጣው አዲስ አተገባበር ሰሌዳው የወጣበትን ቦታ የሚገልጸው መለያ የሚቀመጠው 'በተቻለ መጠን' የትራፊክ ፖሊሶችና የትራንስፖርት ተቆጣጣሪዎች ብቻ እንዲያውቁት በሚያስችል መንገድ ነው " ያንብቡ : https://telegra.ph/ETH-01-23

ውሸት ነው ! "ለኢትዮጲያ ብሄራዊ ውይይት አመቻች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት አብላጫ ድምፅ ያገኙ እጩዎች ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ ያለው መረጃ ፍጹም ውሸት ነው" - አቶ ሄኖክ ስዩም (የህዝብ
ውሸት ነው ! "ለኢትዮጲያ ብሄራዊ ውይይት አመቻች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት አብላጫ ድምፅ ያገኙ እጩዎች ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ ያለው መረጃ ፍጹም ውሸት ነው" - አቶ ሄኖክ ስዩም (የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፅ/ቤት ምክትል ዋና ፀሀፊ) @tikvahethiopia

#OFC በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራሮች እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና ሌሎችም በአዲስ አበባ በሚገኘው የፓርቲው ፅ/ቤት አቀባበል ተደርጎላቸ
+5
#OFC በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራሮች እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና ሌሎችም በአዲስ አበባ በሚገኘው የፓርቲው ፅ/ቤት አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ኦፌኮ ፤ አሁንም በእስር ላይ ያሉ የቀሩ አባላቱ ከእስር እንዲፈቱ ፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮችና ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ በድጋሚ ጥሪውን አቅርቧል። @tikvahethiopia

ትግራይ ፣ አማራ ፣ አፋር 📍 ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ : የሕክምና አገልግሎት አቅራቢዎች መሠረታዊ ግብዓቶችን እያገኙ አይደለም፤ እንዲሁም በአንዳንድ መሠረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደር
+3
ትግራይ ፣ አማራ ፣ አፋር 📍 ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ : የሕክምና አገልግሎት አቅራቢዎች መሠረታዊ ግብዓቶችን እያገኙ አይደለም፤ እንዲሁም በአንዳንድ መሠረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የመድኃኒት እና ሕክምና መስጫ መሳሪዎች እጥረት ከጤና መሠረተ ልማት ውድመቶች ጋር ተደማምሮ የጤና አገልግሎት አቅርቦትን እጅግ አስቸጋሪ አድርጎታል። በአማራ እና አፋር ክልሎች የICRC ተወካይ ሚቻ ዌዲኪንደ 🗣 " በአማራ ክልል አንዳንድ ሆስፒታሎች በመድኃኒት እጥረት ምክንያት ተዘግተዋል። ሥር የሰደዱ በሽታዎች ያለባቸው ሰዎች በየዕለቱ እየሞቱ ነው። የጤና ተቋማት አገልግሎት እየሰጡ ባለመሆናቸው፤ ውሃ ወይም መብራት ስለማይኖራቸው እናቶች በቤት ውስጥ እየወለዱ ነው። ...በአፋር በተመሳሳይ ከፍተኛ የሆነ መድኃኒትና የሕክምና ቁሳቁሶች እጥረት አለ " በኢትዮጵያ ICRC የጤና አስተባባሪ አፖሎ ባራሳ 🗣 " በትግራይ ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ እንደ ጓንት፣ የቀዶ ሕክምና ቁሳቁሶች እና ሰውነት ውስጥ የሚገቡ የሕክምና ቱቦዎች ሳይቀሩ እየታጠቡ ዳግም ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ ነው። ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ መዋል ያለባቸውን የጤና መሳሪያዎችን ዳግም መጠቀም፤ ለኢንፌክሽን የመጋለጥ እድልን ያሰፋል። በአንዳንድ አካባቢዎች ታካሚዎች የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው መድኃኒቶችን ከመውሰዳቸውም በተጨማሪ ሐኪሞች የሰዎችን ቁስል ለማጽዳት ጨው ለመጠቀም ተገደዋል። " ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በጦርነቱ ተሳታፊ የሆኑ ሁሉም አካላት በፍጥነት የሰብዓዊ እርዳታ እንዲደርስ የበኩላቸውን እንዲወጡ በመግለጫው ጠይቋል። ያንብቡ : www.icrc.org/en/document/dwindling-medical-supplies-in-northern-ethiopia @tikvahethiopia

#DrAbiyAhmed የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሀገር ቤት ጥሪን ተከትለው ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ ማህበራት ተወካዮች እና አባላትን አግኝተዋ
+2
#DrAbiyAhmed የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሀገር ቤት ጥሪን ተከትለው ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ ማህበራት ተወካዮች እና አባላትን አግኝተዋል። በበርካታ ጉዳዮችም ላይ መወያየታቸውን የጠ/ሚ ፅ/ቤት አሳውቋል። @tikvahethiopia

#Tigray በትግራይ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ሕይወት አደጋ እንደተጋረጠበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) አስታወቀ። በጦርነቱ ምክንያት የስደተኞቹ ኑሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበላሸ መሆኑንም ገልጿል። በቅርቡ ማይ ዓይኒ እና አዲ ሐሩሽ በሚባሉ አካባቢዎች በሚገኝ የስደተኞች ጣብያ የሚኖሩ ስደተኞችን የመንግሥታቱ ድርጅት ሰራተኞች ጎብኝተዉ እንደነበር ድርጅቱ አስታውቋል። ከ3 ሳምንት በፊት አካባቢዉ የአየር ድብደባ ከደረሰበት ወዲህ የድርጅቱ ሰራተኞች ስደተኞቹን መጎብኘት አልቻሉም ነበር። ኤርትራዉያኑ ስደተኞች በቂ ምግብ፣ መድሐኒትና ንጹህ የመጠጥ ዉኃ የላቸዉም። ባለፉት 6 ሳምንታት ዉስጥ 20 ስደተኞች በመድሐኒት እጦት መሞታቸዉን ስፍራዉን የጎበኙት የUNHCR ሰራተኞች አስታዉቀዋል። ትግራይ ዉስጥ የሚገኙ 25 ሺህ የኤርትራ ስደተኞን ወደ ሌላ ቦታ ለማዛወር ተኩስ አቁም እንዲደረግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠይቋል። በሌላ በኩል ፤ በጦርነት ለተጎዳዉ የትግራይ ሕዝብ የሚሰጠዉ የአስቸኳይ ጊዜ ርዳታ እየተሟጠጠ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ባወጣው ሪፖርት አሳውቋል። ሙሉ ሪፖርት : https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/?s=09 ምንጭ፦ UNHCR , UN OCHA , DW @tikvahethiopia

ነገ በአዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች ! ነገ የታላቁ ሩጫ ይካሄዳል። የ2014 ዓ/ም ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በሰላም እንዲጠናቀቅ የፀጥታ ዝግጅት መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። የሩጫ ውድድር የሚካሄድባቸው መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አመራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ ተጠይቋል፡፡ የ2014 ታላቁ ሩጫ መነሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ የሚጀምር ሲሆን በአዲስ አበባ ስታዲዮም፣ ሜክሲኮ አደባባይ፣ በልደታ ቤተክርስቲያን በማድረግ ፣በዛጉዌ ህንፃ በመታጠፍ-በጌጃ ሰፈር ፣ጎማ ቁጠባ በፍልውሃ ፣በማድረግ በካዛንቺስ ፣በኡራኤል ቤተክርስቲያን ወደ ባንቢስ በመታጠፍ መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደርጋል፡፡ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይኖርና አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን መጠቀም እንዲችሉ ለተሸከርካሪ ዝግ የሆኑ መንገዶች እንደሚኖሩ ፖሊስ ገልጿል። በዚህም መሰረት ፦ • ኮቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ህንፃ፤ • ከጎተራ ማሳለጫ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ የቀድሞ አራተኛ ክፍለጦር፤ • ከቡልጋሪያ ማዞሪያ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኬኬ ህንፃ ወይም ጨርቆስ ማዞሪያ፦ • ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባበይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ገብርኤል መሳለሚያ፤ • ከሳር ቤቶች አደባባይ ወደ ሜክሲኮ ለሚመጡ አፍሪካ ህብረት አደባባይ ፤ • ከካርል አደባባይ ወደ ከፍተኛ ፍ/ቤት የሚወስደው መንገድ ልደታ ፀበል፤ •ከጦር-ኃይሎች ወደ ሚክሲኮ ለሚመጡ ኮካ መገንጠያ ፤ • ከሜክሲኮ ልደታ ኮንደሚኒዬም መብራት፤ • ከመርካቶ በጎማ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ለሚመጡ በርበሬ በረንዳ፤ • ከተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በጎማ ቁጠባ የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር (ሼልድሬንስ) • ከቸርቸር ጎዳና ወደ አምባሳደር ፣ ከሜክሲኮ እና ለገሃር ለሚመጡ አገር አስተዳደር/ኢምግሬሽን/ መብራት ፤ • ከአዋሬ ወደ ካዛንቺስ ለሚመጡ ሴቶች አደባባይ- ከመገናኛ ወደ 22 ለሚመጡ ዘሪሁን ህንፃ፤ • ከቦሌ መድሃኔዓለም የሚመጡ አትላስ ሆቴል አካባቢ፤ ከጠዋቱ 11፡30 ሰዓት ጀምሮ ውድድሩ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ። በተጨማሪም ፥ አሽከርካሪዎች የውድድሩ ተሳታፊዎች ወደ ሚያልፉባቸው መንገዶች ተሽከርካሪ ይዞ መውጣት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ተገልጿል። ማንኛውም አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥም ሆነ ለፖሊስ መረጃ ለመስጠት 011-1-11-01 11 እና በ991 ነፃ የስልክ ቁጥሮች መጠቀም እንደሚቻል የአዲስ አበባ ፖሊስ ያሳውቋል። @tikvahethiopia

#ETHIOPIA የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ጄነራል መሐመድ ሀምዳን ዳጋሎ አዲስ አበባ ሲደርሱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስ
+1
#ETHIOPIA የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ጄነራል መሐመድ ሀምዳን ዳጋሎ አዲስ አበባ ሲደርሱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ እና የብሄራዊ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎና የልዑካን ቡድናቸው በኢትዮጵያ በሚኖረው ቆይታ ከተለያዩ የመንግሰት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ ይጠበቃል። በዉይይታቸው የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ትብብር ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ይጠበቃል። በተጨማሪም የሁለቱን ሀገራ ፍላጎት ባስጠበቀ መልኩ የጋራ ጉዳዮችን ማሳደግ እና መደገፍ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሏል። ምንጭ ፦አል ዓይን ኒውስ ፣ ኢብኮ እና የሱዳን ዜና አገልግሎት (ሱና) @tikvahethiopia

#AddisAbaba እድሳት የተደረገለት የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ህንፃ በነገው እለት እንደሚመረቅ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል። ይህ ታሪካዊ እና የከተማዋ ምልክት የሆነ ህንፃ ከ57
+4
#AddisAbaba እድሳት የተደረገለት የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ህንፃ በነገው እለት እንደሚመረቅ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል። ይህ ታሪካዊ እና የከተማዋ ምልክት የሆነ ህንፃ ከ57 ዓመት በኋላ ለእድሳት የበቃ መሆኑና የከተማዋ የዘመናት ጉዞ አሻራ የያዘ ታላቅ ቅርስ ጭምር መሆኑ ተገልጿል። የከተማው አስተዳደር ፤ ህንፃውን እጀግ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲታደስ ማድረጉን ገልጾ ለተገልጋይ ምቹና አስፈላጊ አገልግሎቶችን ሁሉ ባሟላ መንገድ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ እንዲሆን ታስቦ መሰራቱን አሳውቋል። @tikvahethiopia

#SomaliRegion የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ከዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ሚካኤል ደንፎርድ ጋር ተወያይተዋል። አቶ ሙስጠፌ በውይይቱ ፤ በሶማሌ
#SomaliRegion የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ከዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ሚካኤል ደንፎርድ ጋር ተወያይተዋል። አቶ ሙስጠፌ በውይይቱ ፤ በሶማሌ ክልል በተከሰተው ድርቅ ሁኔታ ዙሪያ መክረዋል። በተከሰተው ድርቅ ምክንያት የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመከላከል እና ህይወትን ለማዳን ለተጎዱ ወገኖች የሚደረገውን የምግብ እርዳታን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተውበታል። ምንጭ፦ የአቶ ሙስጠፌ የተረጋገጠ የትዊተር አካውንት @tikvahethiopia

#Kenya #Ethiopia " ... ምንም እንኳን ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም ኢትዮጵያ ከስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስችል አቅም አላት" - ራይቼል ኦማሞ ኬንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ቀውስ መፍትሔ ያገ
#Kenya #Ethiopia " ... ምንም እንኳን ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም ኢትዮጵያ ከስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስችል አቅም አላት" - ራይቼል ኦማሞ ኬንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ቀውስ መፍትሔ ያገኝ ዘንድ የምታደርገውን ጥረት ሁሉ በሰከነ ሁኔታ ተቀራርባ በመስራቷ እንደምትቀጥል አሳውቃለች። የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራይቼል ኦማሞ አገራቸው ኢትዮጵያን ችላ እንደማትላትና የሰከነና የተለሳለሰ ዲፕሎማሲን በመጠቀም በአገሪቱ የተከሰተው ችግር እንዲያበቃ አብራት መስራቷን ትቀጥላለች ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። ሚኒስትሯ ይህንን የተናገሩት ትላንት የኬንያን የውጭ ፖሊሲ እና አካባቢያዊ ሁኔታዎች በተመለከተ ናይሮቢ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። ራይቼል ኦማሞ ፥ " ምንም እንኳን ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም ኢትዮጵያ ከስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስችል አቅም አላት " ብላ ኬንያ እንደምታምን ገልጸው፣ ለዚህም በቅርቡ የፖለቲካ እስረኞች የመለቀቃቸው እርምጃን እንደ በጎ ጅማሬ ጠቅሰዋል። ሚኒስትሯ አክለውም በአገሪቱ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አኳያ በብሔራዊ ውይይት ፣ በተኩስ አቁም እና ሰብአዊ እርዳታ እንዲቀርብ መንገድ ማመቻቸትን በሚመለከት ከኢትዮጵያ ጋር ተቀራርበው ሲሰሩ እንደነበር መናገራቸውን ቢቢሲ በዘግባው አስፍሯል። @tikvahethiopia

#Update ኢትዮጵያ 📍 ሞሊ ፊ እና ዴቪድ ሳተርፊልድ ኢትዮጵያ ናቸው። የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሀመት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች
+2
#Update ኢትዮጵያ 📍 ሞሊ ፊ እና ዴቪድ ሳተርፊልድ ኢትዮጵያ ናቸው። የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሀመት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ የሆኑት ሞሊ ፊ እና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድን ተቀብለው አነጋግረዋል። ሙሳ ፋኪ መሀመት ከሁለቱ የአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር በነበራቸው ቆይታ የሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ገልፀዋል። ሁለቱ የአሜሪካ ባለስልጣናት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በተለይ ለሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት መፍትሄ ለማፈላለግ ነው። @tikvahethiopia

#Safaricom " ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ ያደርጋል " - አንዋር ሱሳ የኬንያው የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢት
#Safaricom " ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ ያደርጋል " - አንዋር ሱሳ የኬንያው የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ መዋዕለ ነዋይ እንደሚያፈስ ገልጿል። የሳፋሪኮም የኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አንዋር ሱሳ ኩባንያው በተያዘው የፈረንጆቹ 2022 ወደ 300 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በኢትዮጵያ ፈሰስ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ኩባንያው በኢትዮጵያ ስራውን ለመጀመር የኔትወርክ ዝርጋታ እያካሄደ መሆኑንና የመጀመሪያ የመረጃ ማዕከሉን በ100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ መዘርጋቱን ተናግረዋል። ሳፋሪኮም በመጪዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ አገልግሎቱን በይፋ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል። #ኢዜአ @tikvahethiopia

#Tigray በትግራይ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ሕይወት አደጋ እንደተጋረጠበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) አስታወቀ። በጦርነ
+1
#Tigray በትግራይ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ሕይወት አደጋ እንደተጋረጠበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) አስታወቀ። በጦርነቱ ምክንያት የስደተኞቹ ኑሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበላሸ መሆኑንም ገልጿል። በቅርቡ ማይ ዓይኒ እና አዲ ሐሩሽ በሚባሉ አካባቢዎች በሚገኝ የስደተኞች ጣብያ የሚኖሩ ስደተኞችን የመንግሥታቱ ድርጅት ሰራተኞች ጎብኝተዉ እንደነበር ድርጅቱ አስታውቋል። ከ3 ሳምንት በፊት አካባቢዉ የአየር ድብደባ ከደረሰበት ወዲህ የድርጅቱ ሰራተኞች ስደተኞቹን መጎብኘት አልቻሉም ነበር። ኤርትራዉያኑ ስደተኞች በቂ ምግብ፣መድሐኒትና ንጹህ የመጠጥ ዉኃ የላቸዉም። ባለፉት 6 ሳምንታት ዉስጥ 20 ስደተኞች በመድሐኒት እጦት መሞታቸዉን ስፍራዉን የጎበኙት የUNHCR ሰራተኞች አስታዉቀዋል። ትግራይ ዉስጥ የሚገኙ 25 ሺህ የኤርትራ ስደተኞን ወደ ሌላ ቦታ ለማዛወር ተኩስ አቁም እንዲደረግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠይቋል። በሌላ በኩል. በጦርነት ለተጎዳዉ የትግራይ ሕዝብ የሚሰጠዉ የአስቸኳይ ጊዜ ርዳታ እየተሟጠጠ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ባወጣው ሪፖርት አሳውቋል። ሙሉ ሪፖርት : https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/?s=09 #ዶቼቨለ @tikvahethiopia

" እየተፈጠረብን ያለውን ችግር ለመፍታት ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል" - ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በማኅደረ መለኮ
+1
" እየተፈጠረብን ያለውን ችግር ለመፍታት ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል" - ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው " እየተፈጠረብን ያለውን ችግር ለመፍታት ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል" ሲሉ አስታውቀዋል። ብፁዕነታቸው በቦታው ተገኝተው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያፅናኑ እና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን እየተፈጠሩ ያሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮች እስከ ሕይወት መስዋዕትነት እያስከፈለ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል ሲል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በፌስ ቡክ ገጹ አስነብቧል። የተፈጠረውን ችግር ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ሪፖርት ማድረጋቸውን በመግለፅ ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ብፁዕነታቸው አስታውቀዋል። አክለውም ብፁዕነታቸው ምዕመናን አንድነታቸውንና ኅብረታቸውን በማጠናከር ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ እንዳለባቸው አሳስበዋል ሲል ሀገረ ስብከቱ ገልጿል። ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት @tikvahethiopia

ግዙፉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ህንፃ ሊመረቅ ነው። ባንኩ ፥ " ከምስራቅ አፍሪካ ረጅሙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲሱ የዋና መ/ቤት ህንፃ ምርቃት ከባንኩ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ጋር ገጥሟል፡ "
+1
ግዙፉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ህንፃ ሊመረቅ ነው። ባንኩ ፥ " ከምስራቅ አፍሪካ ረጅሙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲሱ የዋና መ/ቤት ህንፃ ምርቃት ከባንኩ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ጋር ገጥሟል፡ " ብሏል። በትክክል የሚመረቅበት ቀን ይፋ ይሆንም በቅርቡ ግን ህፃው እንደሚመረቅ ተገልጿል። @tikvahethiopia

photo content

#twitter ትዊተር ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ "ህግ የጣሱ " ያላቸዉን ተጠቃሚዎች ማገዱን ዛሬ አሳውቋል። ትዊተር እንዳለው ብዙ አካዉንቶች ታግደዋል፤ ከታገዱት መካከል በመቶዎች የሚቆ
#twitter ትዊተር ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ "ህግ የጣሱ " ያላቸዉን ተጠቃሚዎች ማገዱን ዛሬ አሳውቋል። ትዊተር እንዳለው ብዙ አካዉንቶች ታግደዋል፤ ከታገዱት መካከል በመቶዎች የሚቆጠሩት የትግራይ ደጋፊ ተጠቃሚዎች ይመስላሉ ብሏል። ይሁንና ትዊተር የታገደዉ አካዉንት መጠን ምን ያህል እንደሆን በውል አልገለፀም። ትዊተር እርምጃዉ የተወሰደው "የትዊተርን ህግ በመጣስ፣ የተወሰኑ ሃሽታጎች እና የትዊተር ገፆች፤ በተለጠፈዉ መረጃ ላይ በተደጋጋሚ በአላስፈላጊ ሁኔታዎች በማካተታቸው ነው። በተጨማሪ ርምጃዉ " በኢትዮጵያ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተገናኘ በትዊተር ላይ የሚደረጉ ውይይቶች ደኅንነታቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲሄድ ከምናደርገው ጥረት ጋር የተገናኘ ነው " ብሏል። እገዳዉን በተመለከተ " በተጨባጭ በአካውንቶቹና ይዘቶቹ ላይ ያተኮሩ " መሆኑን እና " ከፖለተካዊ ማንነት እና ርዕዮተ ዓለም ገለልተኞች ነን " ሲል ገልጿል። ምንጭ፦ ቢቢሲ / ዶቼቨለ @tikvahethiopia