en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
#AFCON2021 ⚽️ ኢትዮጵያ 🇪🇹 ከ 🇨🇲 ካሜሮን 🗓 ዛሬ ጥር 5 / 2014 ዓ/ም ⌚️ ማታ 1:00 🏟️ ፖል ቢያ ስታድየም 📍 ካሜሩን - ያዉንዴ 🖥 ሱፐር ስፖርት / ስካይ ስፖርት እ
#AFCON2021 ⚽️ ኢትዮጵያ 🇪🇹 ከ 🇨🇲 ካሜሮን 🗓 ዛሬ ጥር 5 / 2014 ዓ/ም ⌚️ ማታ 1:00 🏟️ ፖል ቢያ ስታድየም 📍 ካሜሩን - ያዉንዴ 🖥 ሱፐር ስፖርት / ስካይ ስፖርት እና ኢቲቪ መዝናኛ ድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ ! #HanaG. More : @tikvahethsport

#ማሳሰቢያ ለሞተር ብስክሌት ባለንብረቶች እና አሽከርካሪዎች ፦ በአዲስ አበባ የምንቀሳቀሱ ሞተር ብስክሌቶች ማሟላት ያለባችሁ ነገሮች ማለትም ፦ 1. የመንቀሳቀሻ ፈቃድ ፣ 2. የታዳሰ የመንቀሳቀሻ ፈ
#ማሳሰቢያ ለሞተር ብስክሌት ባለንብረቶች እና አሽከርካሪዎች ፦ በአዲስ አበባ የምንቀሳቀሱ ሞተር ብስክሌቶች ማሟላት ያለባችሁ ነገሮች ማለትም ፦ 1. የመንቀሳቀሻ ፈቃድ ፣ 2. የታዳሰ የመንቀሳቀሻ ፈቃድ፣ 3. በህጋዊ መንገድ የተሰጠ የመንቀሳቀሻ ፈቃድ፣ 4. የተገጠመለት ጂ.ፒ. ኤስ በትክክል የሚሰራ፣ 5. ቀይ መብራቱ በአግባቡ የሚሰራ መሆኑን ማረጋገጥ እነዚህን ሳያሟሉ ሲያሽከረክሩ ከተገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ 500 ብር፣ ለሁለተኛ ጊዜ ከሆነ እጥፍ ወይም (1000) ብር እንዲከፍሉ በህግ ተቀምጧል። የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ እነዚህ እና መሰል ጉዮችን እየፈተሸ ተገቢውን ክትትል እና ቁጥጥር እያደረገ እንደሚገኝ አሳውቋል። ስለሆነም ማሟላት ያለባችሁን ነገር በማሟላት ካለስፈላጊ ጥፋት እና ቅጣት እራሳችሁን እንድትጠብቁ ማሳሰቢያ ተላልፏል። @tikvahethiopia

#USA በምርጫ ጉዳይ አሜሪካ ሶማሊያን አስጠነቀቀች። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሶማሊያ መሪዎች የምርጫ የጊዜ ሰሌዳውን እንዲያከብሩና ተጨማሪ መዘግየት እንዳይኖር ማስጠነቀቁን ቢቢሲ ዘግቧል።
+1
#USA በምርጫ ጉዳይ አሜሪካ ሶማሊያን አስጠነቀቀች። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሶማሊያ መሪዎች የምርጫ የጊዜ ሰሌዳውን እንዲያከብሩና ተጨማሪ መዘግየት እንዳይኖር ማስጠነቀቁን ቢቢሲ ዘግቧል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ምርጫው የሚዘገይ ከሆነ የቪዛ ገደቦችን ጨምሮ ባለስልጣናት ላይ ያነጣጠሩ ማዕቀቦችን እንደሚጥል አስታውቋል። አገሪቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ልታደርገው ባቀደችው አዲሱን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ የካቲት 18፣ 2014 ዓ.ም ምርጫ መጠናቀቅ እንደሚኖርበት አሜሪካ አስታውቃለች። ሶማሊያ አዲሱ የምርጫ ቀን የወሰነችው በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የክልል አስተዳደር መሪዎች መካከል ለተወሰኑ ቀናት በሞቃዲሾ ሲደረጉ የነበሩ ስብሰባዎችን ተከትሎ ነው። ለህዝብ ተወካዮች የሚደረገው ምርጫ መካሄድ የነበረበት በህዳር ወር ተጀምሮ እስከ ታህሳስ አጋማሽ መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም በነበሩ እሰጣገባዎች ምክንያት ዘግይቷል። በሌላ ከሶማሊያ ጋር በሚገናኝ መረጃ ዛሬ በሞቃዲሾ ከኤርፖርቱ ብዙም በማይርቅ ቦታ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን የነፍስ አድን ሠራተኞች ማስታወቃቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። በጥቃቱ ቢያንስ 9 ሰዎች ተገድለዋል። የጥቃቱ ፈፃሚው ደግሞ አሸባሪው አልሸባብ ነው ተብሏል። @tikvahethiopia

#DerartuTulu ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በባልደራስ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት ታህሳስ 29/2014 ዓ.ም ከእስር ለተፈቱት አቶ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ ወ/ሮ ቀለብ ስዮም እና ወ
+1
#DerartuTulu ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በባልደራስ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት ታህሳስ 29/2014 ዓ.ም ከእስር ለተፈቱት አቶ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ ወ/ሮ ቀለብ ስዮም እና ወ/ሮ አስካለ ደምሌ" እንኳን ደስ ያላችሁ ፤ እንኳን ለቤታችሁ አበቃችሁ" በማለት መልካም ምኞቷን ገልፃለች። አትሌቷ ከእስር ለተፈቱት አመራሮች መጭው ጊዜአቸው የተቃና እንዲሆን እና ኢትዮጵያም ሰላሟ፣ አንድነቷ እና ክብሯ እንዲመለስ ያላትን ምኞት ገልፃለች። የባልደራስ ፕሬዝዳንት አቶ እስክንድር ነጋ በበኩላቸው ኮማንሰር አትሎህ ደራርቱ የፓርቲው ፅ/ቤት ድረስ ቃሏን አክብራ በመልካም መንፈስ በመገኘት ይህንን እውቅና በመስጠቷ ከልብ አመስግነዋል። በተጨማሪም "በቀጣይ በኢትዮጰያ ሰላምና ልማት ይሁን። ሲል መልካም ምኞቱን ገልፀዋል። ሌሎች ከእስር የተፈቱ የፓርቲው አመራሮች አትሌቷ ቃሏን አክብራ በባልደራስ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት "የእንኳን ደስ ያላችሁ"መልዕክት በማስተላለፏ የተሰማቸውን ደስታ መግለፃቸውን ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል። በሌላ በኩል ፥ ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ከእስር የተፈቱት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራር አቶ በቀለ ገርባን " እንኳን ለቤትዎት አበቃዎት !! " በማለት መልካም ምኞቷን ገልፃለች። @tikvahethiopia

#Update የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር ለገሰ ፥ መንግስት ለያዘው ሀገራዊ ምክክርና ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠር ሁሉን አካታች የሆነ ውይ
#Update የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር ለገሰ ፥ መንግስት ለያዘው ሀገራዊ ምክክርና ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠር ሁሉን አካታች የሆነ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብለዋል። ይህን ሀገራዊ አንድነት ለማምጣትም ብዙ ተከታይ ያላቸውን እስረኞች ክስ ማቋረጥ ማስፈለጉን ነው የተናገሩት። በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ፣ የተመቻቸ ፖለቲካዊ ሁኔታን ለመዘርጋት ፣ዋስትና ያለው ዲሞክራሲ ለመገንባት ያለመ ነው ውሳኔው ብለዋል። ውሳኔው በየደረጃው የሚመለከተው አካል ተወያይቶበት የወሰነው ሲሆን ዘላቂውን የሀገር ጥቅም ከግምት ያስገባም መሆኑን ነው ሚንስትሩ ያነሱት። ዶ/ር ለገሰ ፥ መንግስት የእነዚህን ግለሰቦች ክስ እንዲቋረጥ ሲያደርግ ግለሰቦቹ ለሀገራዊ መግባባት ያላቸውን ሚና አምኖበት ስለሆነ ለሰላማዊ ምክክር የተሰጣቸውን እድል እንዲጠቀሙበትም ጥሪ ቀርቦላቸዋል ብለዋል። #ኤኤምኤን @tikvahethiopia

ኦባሳንጆ ትላንት መቐለ ነበሩ። የአፍሪካ ህብረት (AU) የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ትላንት ትግራይ ክልል መቐለ ከተማ እንደነበሩ EFE Noti
+1
ኦባሳንጆ ትላንት መቐለ ነበሩ። የአፍሪካ ህብረት (AU) የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ትላንት ትግራይ ክልል መቐለ ከተማ እንደነበሩ EFE Noticias ዘግቧል። ኦባሳንጆ ወደትግራይ ክልል መቐለ የተጓዙት ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሄ ለመፈለግ ነው። በመቐለ ቆይታቸው ከዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር ውይይት ማድረጋቸው እና ውይይቱም ጥሩ የሚባል እንደነበር ተሰምቷል። የTPLF ቃልአቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ መቐለ እንደነበሩ አረጋግጠዋል ፤ ጉዟቸው ለቀውሱ ሰላማዊ መፍትሄ የመፈለግ ተልዕኮ አካል ነው ብለዋል። እሳቸው የመጡበት አውሮፕላን ተነስቶ እንደበረረ ግን የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል ሲሉ ክስ አሰምተዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት እንዲቆም እና ሰላም እንዲወርድ መፍትሄ እያፈላለጉ ያሉት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ከዚህ ቀደምም ወደ ትግራይ ክልል ተጉዘው እንደነበር አይዘነጋም። @tikvahethiopia

#USA #ETHIOPIA የአሜሪካው ከፍተኛ ባለሥልጣን (ስማቸው ያልተገለፀ) ለጋዜጠኞች ምን አሉ ? • የኢትዮጵያ መንግስት ከአሜሪካ የንግድ ልዑክ የተነሱትን ቅሬታዎች በተመለከተ ተጨማሪ " አዎንታዊ እና ገንቢ " ዕርምጃዎች የሚወስድ ከሆነ ኢትዮጵያ ከተጠቃሚነት የተሰረዘችበትን የ #AGOA ዕድል በተመለከተ የንግግር ሒደት ውስጥ ለመግባት ፈቃደኛ መሆኑን ገልፀዋል። • ታኅሳስ 28 ቀን 2014 ከጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር ንግግር ማድረጋቸው የተገለጸው የቀድሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ያደረጉት " በኢትዮጵያ መንግሥት ጥያቄ " መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ • አዲሱ ተሿሚ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ መቼ ወደ ቀጣናው ለመጓዝ እንዳሰቡ አልታወቀም ፤ ነገር ግን ረዥም [ጊዜ] እንደማይሆን ተገልጿል። • ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በስልክ ንግግር ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ሁለቱ መሪዎች ንግግር ያደረጉት በፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ጥያቄ መሠረት መሆኑን ተናግረዋል። ያንብቡ : https://telegra.ph/USA-ETHIOPIA-01-12 Credit : Reporter Newspaper

3 ልጆችን የተገላገለችው እናት ... በወላይታ ዞን በጠበላ የመጀመሪያ ሆስፒታል አንዲት እናት 3 ልጆችን ተገላገለች። በሁምቦ ወረዳ የኮይሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወይዘሮ ብርቱካን ዳርጮ ሁለት
3 ልጆችን የተገላገለችው እናት ... በወላይታ ዞን በጠበላ የመጀመሪያ ሆስፒታል አንዲት እናት 3 ልጆችን ተገላገለች። በሁምቦ ወረዳ የኮይሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወይዘሮ ብርቱካን ዳርጮ ሁለት ወንድ እና አንድ ሴት 3 ልጆችን በሰላም ተገላግላለች። የተወለዱ ልጆችም ሙሉ በሙሉ ጤነኛና ክብደታቸውም በጥሩ ሁኔታ እንዳለ ከሆስፒታሉ ማረጋገጥ ተችሏል። እናቶች የቅድመ ወሊድ ክትትል በጤና ተቋማት ውስጥ እንዲያደርጉና የባለሙያዎችን ምክር በተገቢው ተግባራዊ እንዲያደርጉ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር መንግሥቱ ሙንኤ አሳስበዋል። ምንጭ፦ የወላይታ ዞን ኮሚኒኬሽን @tikvahethiopia

አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ ዛሬ ባወጡት መግለጫ ምን አሉ ? • የአርቲስት ሃጫሉ ግድያን ተከትሎ "በተሳሳተ መንገድ ለእስር ተዳርገው" ላለፉት 18 ወራት በእስር መቆየታቸውን ገልፀዋል። • እስራቸው " ፖለቲካዊ " እንደነበር ገልፀዋል። ለእስር የተዳረግነው ገዢው ፓርቲ በምርጫ የተሻለ ድምጽ እንዲያገኝ ከፖለቲካዊው ምኅዳር ገለል እንድንል ታስቦ ነው ብለዋል። • በኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር እና አማራ ክልሎች በሲቪሎች ላይ የደረሰው ጉዳት አሳዛኝ ነው ብለዋል። • ባለፉት 13 ወራት በአገሪቱ እና በሕዝቦቿ ላይ የደረሱትን ጉዳቶችን መቀልበስ ባይቻልም፤ ተጨማሪ ጉዳቶችን ማስቀረት የምንችልበት ጠባብ ዕድል አለ ብለዋል። • በቅርቡ መንግሥት ሰላም እና መግባባትን ለመፍጠር ያሳየው አዎንታዊ ምላሽ ተጨባጭ እና በማይቀለበሱ ተግባራት መረጋገጥ አለባቸው ብለዋል። • በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ የሚገኘው የእርስ በእስር ጦርነት በሰላም እንዲጠነናቀቅ እና በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋገት እንዲሰፍን የውጭ አካላት አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ ጠይቀዋል። • የውጭ አካላት ለተዋጊ አካላት ፖለቲካዊ እና ቁሳዊ ድጋፎችን በማቅረብ ግጭቱን ከማባባስ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል። • የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን በተመለከተ ተዓማኒነት ያለው ምርመራ እንዲደረግ፤ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቀዋል። • ከጠበቆቻችን መካከል ለአቶ አብዱልጀባር ሁሴን ልዩ ክብር ለመስጠት እንወዳለን ብለዋል። • በግንኙነታችን ወቅት ልዩ አክብሮትን ላሳዩልን የፌደራል ፖሊስ አባላት እና የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ጥበቃዎች እና አስተዳዳሪዎች አድናቆታችንን እንገልፃለን ብለዋል። ያንብቡ : https://telegra.ph/OFC-01-11 @tikvahethiopia

#Update በሳምንት ከአምስት ጊዜ በላይ ገንዘብ ማስተላለፍ የሚከለክለው መመሪያ ማንሳቱን ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሳምንት ከአምስት ጊዜ በላይ ገንዘብ ማስተላለፍ የሚከለ
+1
#Update በሳምንት ከአምስት ጊዜ በላይ ገንዘብ ማስተላለፍ የሚከለክለው መመሪያ ማንሳቱን ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሳምንት ከአምስት ጊዜ በላይ ገንዘብ ማስተላለፍ የሚከለክለው መመሪያ መነሳቱን ይፋ አድርጓል። ብሔራዊ ባንክ ካለፈው ዓመት መጀመሪያ ጀምሮ የባንኮች ደንበኞች በሳምንት ከአምስት በላይ የባንክ ዝውውሮችን እንዳያደርጉ የሚያዝ መመሪያ ማውጣቱ ይታወሳል። ይህም መመሪያ መደበኛ ባልሆነው የልውውጥ ገበያ ውስጥ ያሉ ተጫዋቾችን ተስፋ ለማስቆረጥ ያወጣው ደንብ መሆኑን አስታውቆ ነበር። ይሁን እንጂ ካሳለፍነው ሳምንት ታህሳስ 27 ቀን 2014 ጀምሮ ይህ መመሪያ መነሳቱን በብሔራዊ ባንክ የባንክ ሱፐርቪዥን ዳይሬክተር ፍሬዘር አያሌው፣ መግለፃቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። “ የዝውውር ገደቡ አሁን ሙሉ በሙሉ በመመርያ ተነስቷል ” ያሉት ፍሬዘር፣ ነገር ግን ባሳለፍነው ዓመት የወጣው የገንዘብ ወጪ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ገደቦችም አሁንም ድረስ ተፈፃሚ ሆነው ይቀጥላሉ ሲሉ ተናግረዋል። ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ / አዲስ ማለዳ ጋዜጣ @tikvahethiopia

#Update የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት ክሳቸው ስለተቋረጠላቸው የህወሓት አመራሮች ምን አሉ ? የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት የሆኑት ዶ/ር ይልቃል ከፍያለ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህ መ
+1
#Update የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት ክሳቸው ስለተቋረጠላቸው የህወሓት አመራሮች ምን አሉ ? የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት የሆኑት ዶ/ር ይልቃል ከፍያለ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህ መግለጫ ወቅት ክሳቸው ስለተቋረጠ የህወሓት አመራሮችም አንስተው ተናግረዋል። ዶ/ር ይልቃል ፥ አመራሮቹ የአማራን ህዝብ ጠላት አድርገው በመሳል ባለፉት በርካታ አመታት በህይወት፣ በንብረትና በስነ ልቦናው ላይ በደል እንዲደርስበት በማድረጋቸው ህዝቡ በአመራሮቹ መፈታት ላይ ቅሬታ ቢይዝ እውነት አለው ብለዋል። የአማራ ህዝብ በተከታታይ ሲደርስበት የነበረው በደል በእነዚህ ሰዎች ጠንሳሽነት እንደነበር ለአፍታም አንዘነጋም ሲሉም ገልፀዋል። ነገር ግን አሁን ማየት ያለብን እና ጠቃሚ የሚሆነው የሰዎቹ መፈታት አለመፈታትን ሳይሆን ሊከፋፍሉንና ሊያዳክሙን የሚችሉ ሀሳቦችን ወደ ጎን በማቆየት በዋና ዓላማችንና መርሃችን ላይ አተኩረን አንድነታችንን መጠበቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ዶ/ር ይልቃል ፥ " የእነስብሃት ነጋ መፈታት አለመፈታት ላይ አተኩረን ከተለያየን እንዳከማለን፤ ለሌላ ጥቃት እንጋለጣለን " ሲሉ አስጠንቅቀዋል። " ለእኛ እንደ አማራ ክልል የሚጠቅመው መርሃችን ላይ ትኩረት በማድረግ አንድነትን በማጠናከር ሊመጣ ከሚችል ዳግም ወረራ ራሳችንን መጠበቅ " ነው ሲሉ ተናግረዋል። #ኤፍቢሲ @tikvahethiopia

#OFC ባለፈው ሳምንት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራሮች አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ጃዋር መሀመድ ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ ፣ አቶ ሀምዛ ቦረና እና ሎሎችም በአቶ ጃዋር መዝገብ ስር ያሉ ግለሰቦች
+1
#OFC ባለፈው ሳምንት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራሮች አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ጃዋር መሀመድ ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ ፣ አቶ ሀምዛ ቦረና እና ሎሎችም በአቶ ጃዋር መዝገብ ስር ያሉ ግለሰቦች ከእስር መፈታታቸው ይታወሳል። ከእስር ስለተፈቱ ግለሰቦች ኦፌኮ አሰተያየቱን ለቪኦኤ ሰጥቷል። ኦፌኮ የፓርቲው አመራሮች እና አባላት መፈታታቸው ደስ እንዳሰኘው የፓርቲው የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ጥሩነህ ገምታ ተናግረዋል። አቶ ጥሩነህ ፥ " በጣም ደስ ብሎናል ደስታችን ወደር የለውም፤ እነዚህ አባሎቻችን በመፈታታቸው አመራሮች ናቸው ያው ኦፌኮ አመራር የተሟላ ይሆናል ብለን ስለምናስብ እነሱም ከቤተሰቦቻቸው ፣ ከወዳጆቻቸው ፣ ከዘመዶቻቸው ጋር መቀላቀላቸው በጣም ደስ አሰኝቶናል። በዚህም የተነሳ አባሎቻችን ፣ ደጋፊዎቻችን ፣ መላው ህብረተሰባችን ፣ በሀገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጭ የሚገኙ በዚህ መጥፎ ጊዜ ከጎናችን በመቆማቸው አመስግነናቸዋል " ብለዋል። አክለውም ፥ " ያሰራቸው መንግስትም ስለፈታቸው ፣ የተፈቱበት ምክንያት የፈለገው ነገር ይሁን እነዚህ ወገኖቻችን በመፈታታቸው ግን መንግስትንም አመስግነናል ደስ ብሎናል " ሲሉ ተናግረዋል። መንግስት አሁን እየተዘጋጀበት ያለውን የብሄራዊ ውይይት ኦፌኮ በ2009 ዓ/ም ነው መጠየቅ የጀመረው ያለቱ አቶ ጥሩነህ የፓርቲው አመራሮች እና አባላት መፈታት ለውይይቱ ትልቅ አስተዋጾ ይኖረዋል ብለዋል። መንግስት አሁን ጀመረውን ታሳሪዎችን የመፍታት እርምጃ አጠናክሮ መቀጠል አለበት ያለቱ አቶ ጥሩነህ ፥ የኦፌኮ አባላት፣ የዞንና የወረዳ ኃላፊዎች ዛሬም ቢሆን እስር ላይ ናቸው እነዚህ ሁሉ ቢፈቱና የሀገሪቱን፣ ሰላም ፣ እድገት፣ ልማት አብረን እጅ ለእጅ ብንገነባ የተሻለ ይሆናል ይሄ ጥሪያችን አሁንም ይቀጥላል " ብልዋል ለሬድዮ ጣቢያው። @tikvahethiopia

' ሁሉም በሀገር ያምራል ' ' ሁሉም የሀገር ያምራል ' ዳያስፖራዎች እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ወደ አገር ቤት የተደረገላቸውን ጥሪ ተከትሎ የተዘጋጀው 'Made in Ethiopia Great Homecom
+3
' ሁሉም በሀገር ያምራል ' ' ሁሉም የሀገር ያምራል '  ዳያስፖራዎች እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ወደ አገር ቤት የተደረገላቸውን ጥሪ ተከትሎ የተዘጋጀው 'Made in Ethiopia Great Homecoming' ባዛር ትላንት በአዲስ አበባ ከተማ " ወዳጅነት አደባባይ " ተከፍቷል። ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚካሄድ ይሆናል። በባዛሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና የቱሪስት አገልግሎት ሰጭዎች ምርትና አገልግሎታቸውን በማስተዋወቅ ግብይት የሚፈጽሙበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። #MADE_IN_ETHIOPIA @tikvahethiopia

#ተጠናቋል የሐዋሳ አውሮፕላን ማረፊያ ቢሻን ጉራቻ የመንገድ ግንባታ ተጠናቋል። 35 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የሐዋሳ አውሮፕላን ማረፊያ ቢሻን ጉራቻ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግ
+1
#ተጠናቋል የሐዋሳ አውሮፕላን ማረፊያ ቢሻን ጉራቻ የመንገድ ግንባታ ተጠናቋል። 35 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የሐዋሳ አውሮፕላን ማረፊያ ቢሻን ጉራቻ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ሁለት ክፍሎች ያሉት ሲሆን፥ የመጀመሪያው 14 ኪሎ ሜትር ከቢሻን ጉራቻ በመነሳት ወደ ሐዋሳ አውሮፕላን ማረፊያ የሚሄድ ነው። መንገዱን ገንብቶ ለማጠናቀቅ የወሰደው 592 ሚሊየን 84 ሺህ ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ሲሆን፥ የመንገዱን ግንባታ አለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ አከናውኖታል። በማማከርና በቁጥጥር ስራው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ሱፐርቪዥን ኮርፖሬሽን መሳተፉን ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ምንጭ፦ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር @tikvahethiopia

#Amhara ህወሓት በአማራ ክልል በከፈተው ጦርነት ምክንያት ከሐምሌ 2013 ዓ.ም ጀምሮ ከመኖሪያ ቀዬአቸው ከተፈናቀሉት ዜጎች ውስጥ፣ 1.2 ሚሊዮን የሚሆኑት ወደ ቀደመ መኖሪያቸው መመለሳቸቸው ተገ
+1
#Amhara ህወሓት በአማራ ክልል በከፈተው ጦርነት ምክንያት ከሐምሌ 2013 ዓ.ም ጀምሮ ከመኖሪያ ቀዬአቸው ከተፈናቀሉት ዜጎች ውስጥ፣ 1.2 ሚሊዮን የሚሆኑት ወደ á‰€á‹°áˆ˜ áˆ˜áŠ–áˆŞá‹Ťá‰¸á‹ መመለሳቸቸው ተገልጿል። የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽነር አቶ ዘለዓለም ልጃለም ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል፥ በአሁኑ ወቅት ህወሓት በሰሜን ጎንደር አልፎ አልፎ በሚያደርገው ትንኮሳ ምክንያት በቅርቡ እንደሚመለሱ ከሚጠበቁትና በደባርቅ መጠለያ ውስጥ ከሚገኙት 200 ሺህ ተፈናቃዮች ውጪ፣ በሌሎች አካባቢዎች በመጠለያ የነበሩት ተፈናቃዮች ሙሉ በሙሉ ተመልሰዋል ብለዋል። በጦርነቱ ከተፈናቀሉት በተጨማሪ ቀደም ሲል በአጣዬ ከተማ በተቀሰቀሰ ግጭት የተፈናቀሉ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የቤንሻንጉል ነፃ አውጪ ነኝ እያለ በሚንቀሳቀሰው ኃይል የተፈናቀሉ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በኦነግ ሸኔ ጥቃት ደርሶባቻው ተፈናቅለው በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች ቁጥር 900 ሺ መድረሱን ገልጸዋል፡፡ ህወሓት በከፈተው ጦርንት ምክንያት ተፈናቅለው ወደ ቀዬአቸው የተመለሱትን ጨምሮ ተወረው በነበሩ አካባቢዎች በደረሰው ዝርፊያ፣ ውድመትና የኢኮኖሚ ቀውስ ሳቢያ በክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር 11.4 ሚሊዮን መድረሱን አክለዋል፡፡ ወደ ቀዬአቸው የተመለሱ ዜጎች ወደአምራችነት እስኪገቡና መቋቋም እስኪችሉ ለመመገብ በየወሩ 1.2 ሚሊዮን ኩንታል ምግብ የሚያስፈልግ ቢሆንም አሁን መቅረብ የቻለው 426 ሺ ኩንታል ምግብ ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ክልሉ የመልሶ ማቋቋምና ግንባታ ሼል በማከናወን ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ ባለሙያዎችና ጉዳት የደረሰባቸው ተቋማት መሪዎች á‹¨á‰°áŠŤá‰°á‰ąá‰ á‰ľáŠ“ 6 ቡድን የያዘ የአጥኚዎች ስብስብ በአጠቃላይ በጦርነቱ የደረሰውን ጉዳት እያጠና ነው። @tikvahethiopia

#TPLF ጠቅላይ ሚኒስትሩ TPLFን በተመለከተ ምንድነው ያሉት ? ዶክተር ዐቢይ አህመድ ፦ " ... አሁን ወደ ትግራይ ክልል ዘልቀን የማንገባበት በርካታ ምክንያቶች ያሉን ቢሆንም አንገባም ብለን ከቆምን በኃላ ነገሩን በተለየ መንገድ ለማየት ጥረት እያደረግን ባለንበት በዚህ ወቅት አሁንም TPLF አላረፈም። አሁንም TPLF በግራ በቀኝ ሊነካካን ይፈልጋል።  ለ7ኛው ስህተት የሚጓዘው TPLF በፍፁም ድል ማግኘት የማይችል እንኳን ቢሆን በወጣቶች የትግራይ ልጆች ላይ በህይወት የመቀጠፍ የመቁሰል አደጋ የሚያስከትል ስለሆነ 7ኛው ስህተቱ መሾመር ስቶ ሳይሄድ መማር የሚችልበት እድል መፍጠር የራሱ (TPLF) ቢሆንም እንኳ እንደባላንጣ አትንኩን ፤ እረፉ ለማለት እወዳለሁ። የነካካችሁን እንደሆነ በተለመደው መንገድ የከፋ ቅጣት ይደርስባችኃልና። ትላንትና እንኳን ክስ አቋርጠን እስረኞች ይውጡ ስንል የTPLF ጀሌዎች ከፊሉ የአማራ አካውንት ከፊሉ የኦሮሞ አካውንት አስመስሎ በመክፈት እኛን ለማባላት ሳይተኙ አድረዋል። አማራ መስለው ፣ኦሮሞ መስለው ብዙ ጥረት አድርገዋል። " ያንብቡ : https://telegra.ph/Dr-Abiy-Ahmed-01-09

#ተጨማሪ ከእስር ስለተፈቱት ግለሰቦች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን ተናገሩ ? ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦ " ... ክስ የተቋረጠላችሁ ወገኖች ስላሸነፍን መበቀል እየቻልን ይቅር ማለትን ስለመረጥን ክስ አቋርጠን
#ተጨማሪ ከእስር ስለተፈቱት ግለሰቦች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን ተናገሩ ? ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦ " ... ክስ የተቋረጠላችሁ ወገኖች ስላሸነፍን መበቀል እየቻልን ይቅር ማለትን ስለመረጥን ክስ አቋርጠን እናተን ሳይሆን ከእናተ ጀርባ ያለውን ህዝብ አክብረን የወሰን መሆናችንን አውቃችሁ ይህን እድል ሳታበላሹ እንድትጠቀሙበት ላሳስባችሁ እፈልጋለሁ። ክስ ማቋረጥ ማለት ምህርተ መስጠት ማለት አይደለም። ክስ የተቋረጠለት ሰው በአግባቡ መጠቀም ካልቻለ መልሶ የክስ መዝገቡን መምዘዝ የሚቻል ስለሆነ። በዚህ ጉዳይ ያዘኑ፣ የተቆጡ፣ የኢትዮጵያ ቁርጥ ቀን ልጆች እንዲገነዘቡ የምፈልገው የወሰድነው መድሃኒት ማስታገሻ አይደለም የወሰድነው መድሃኒት ፈዋሽ በመሆኑ የጎንዮሽ ጉዳት አለው ፤ ይጎረብጣል ያማል ! ለማዳን ብቻ ሳይሆን በጎንም የመጎርበጥ ባህሪ አለው። ለጊዜው የሚያስታግስ ሳይሆን ለልጆቻችንም የድልና የአሸናፊነት መንፈስ የሚያላብስ ስለሆነ እንደኛ ደጋግማችሁ ስታስቡት ጠቀሜታው ጎልቶ ይታያችኃል እናም ደግማችሁ ለማሰብ ልባችሁና አእምሯችሁ እንዲከፈት ዋናው አላማ የምትወዷትን ሀገር ኢትዮጵያን አንድ አድርገን ለማፅናት ካለን ፍላጎት አንፃር ብቻ የመነጨ መሆኑን እንድትገነዘቡ ቢያንስ ቢያንስ ጉቦ በልተን እንዳለቀቅናቸው እንድታስቡ ላሳስባችሁ እፈልጋለሁ። " @tikvahethiopia

#ማስታወሻ #AFCON2021 ⚽️ ኢትዮጵያ 🇪🇹 ከ 🇨🇻 ኬፕቨርዴ 🗓 ዛሬ ጥር 01 / 2014 ዓ/ም ⌚️ ማታ 4:00 (10:00pm) 🏟️ ኦለምቤ ስታድየም 📍 ካሜሩን - ያዉንዴ 🖥 ሱፐር
#ማስታወሻ #AFCON2021 ⚽️ ኢትዮጵያ 🇪🇹 ከ 🇨🇻 ኬፕቨርዴ 🗓 ዛሬ ጥር 01 / 2014 ዓ/ም ⌚️ ማታ 4:00 (10:00pm) 🏟️ ኦለምቤ ስታድየም 📍 ካሜሩን - ያዉንዴ 🖥 ሱፐር ስፖርት / ስካይ ስፖርት እና ኢቲቪ መዝናኛ ድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ ! #HanaG. More : @tikvahethsport

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእስር ስለተፈቱ ግለሰቦች ምን አሉ ? ዶክተር ዐቢይ አህመድ ፦ " ... ትላንት ክስ የተቋረጠላቸው የተሸነፉ ኃይሎች ክስ እንዲቋረጥ እና ከእስር ቤት እንዲወጡ ሲደረግ ከፍተኛ ቁጣ ቀስቅሷል። ይህ ቁጣ የተቀሰቀሰው በሁለት ቡድኖች ነው። አንደኛው ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ጭር ሲል የማይወድ ፣ ሁል ጊዜ እያጋጨ በሰበር ዜና ብር የሚሰበስብ፣ የት እንዳለ የማይታወቅ ካለበት ሆኖ ስንዋጋ ጦርነር አቁሙ የሚል ስናቆም ተዋጉ የሚል አጓጉል ብልጣብልጥነት የሚያጠቃው እና እንብዛም ጆሯችንን የማንገልጥለት ቡድን ነው። ሁለተኛው ቡድን በዜናው ድንገተኝነት የደናገጠ፣ በነበረው ተጋድሎ እና ሁኔታ ጊዜውን ፣ ገንዘቡን፣ ህይወቱን ለመስጠት የወሰነ ከያለበት ሀገር እና ክልል ተሞ ከሀገር እና ከህዝብ ጋር የዘመተ ይህን እኩይ ጠላት አምርሮ የሚጠላና ከዚህ ጠላት ጋር የሚደረግ ማንኛውም ንግግር ኢትዮጵያን ይጎዳል ብሎ የሚያምን ቅን ተቆጪ ነው። የዚህን ቅን ተቆጪ ኃይል መንግስት ሙሉ በሙሉ ይረዳል ያደምጣል ለማስገንዘብም ጥረት ያደርጋል። እነዚህ ቅን ሀገር ወዳድ ኢትዮጵየውያን በውስጥም በውጭም የሚገኙ የአንዳንዶችን ከኛ ይቅር ማለት አምርረው የጠሉና የደናገጡ ወንድም እና እህቶቻችን እንዲገነዘቡልን የምንፈልገው ይህ ጉዳይ እኛም መጀመሪያ ስንሰማው ያስደነገጠ መሆኑን ነው። ነገር ግን ደጋግመን ስናመነዥገው ግራ ቀኙን ስንፈትሽ ለኢትዮጵያ የሚበጅ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም የሚያግዝ፣ የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ ጠላቶች የሚቀንሥ ፣ በአውደ ውጊያ ያገኘነውን ድል በሰላሙ መድረክ እንድንደግም የሚያደርግ የአባቶቻችን ልጆች መሆናችንን የማያረጋግጥ በመሆኑ እየመረረን የዋጥነው እውነት ነውና እናተም ለሀገራችሁ ዘላቂ ድል ስትሉ ፣ ለሀገራችሁ ክብር እና አሸናፊነት ስትሉ ደጋግማችሁ በማሰብ ይህን ውሳኔ እንድትቀበሉ በትህትና ጠይቃችኃለሁ። ውሳኔውን ለምን ? ለምትሉ ይህ ውሳኔ የተወሰደው ኢትዮጵያን በጠንካራ አለት ላይ ለማኖር ነው። ጠላቶቿን ለመቀነስ ነው። ጉልበት ለመሰብሰብ ነው። ያልገባውና የሚከተል ማህበረስብ ካለ አይኑን ገልጦ ማየት እና ከጥፋት ጎዳና እንዲመለስ ለማድረግ ነው። ሌላም ባርካታ ምክንያቶች አሉት። ነገር ግን ትላንት ክስ አቋርጠን ከእስር ቤት እንዲፈቱ ያደርገናቸው ግለሰቦች ሁሉም በሚባል ደረጃ የመንግስት ስልጣን ይዘው በዚህ ሁኔታ ውስጥ የተሳተፉ ፣ በቀጥታ የሚወስኑ፤ በቀጥታ የሚያዙ አይደሉም። አንዳንዶች በታሪካቸው ምክንያት አግዝፈን የምናያቸው ቢሆንም አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከሁሉም የውሳኔ ሰጭነት መድረክ በቀጥታ የማይሳተፉ ኃይሎች ናቸው። ከዚህም በላይ ኢትዮጵያዊ ማንነታችን እና ጀግንነታችን ሽማግሌዎች በእስር ቤት እንዲሞቱ የሚፈልግ ፣ የሚፈቅድ አይደለምና ጀግኖች ስለሆንን አዛውንቶች ሲቻል ወደገዳም ፣ አልያም ወደቤታቸው እንጂ በእስር ቤት እንዳይቆዩ ወስነናል። ይህ ውሳኔ ዛሬ የሚመረንም ቢሆን እንኳን ውሎ ሲያደር ልጆቻችንን የሚያኮራ የኢትዮጵያን አንድነት የሚያፀና መሆኑን ቅንጣት አንጠራጠርም። " @tikvahethiopia

#Update ወደር የሌለው የጥቁር አንበሳ ጀግና ሜዳይ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተሽለሙ ፦ 1. ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ 2. ጀነራል አበባው ታደሰ 3. ጀነ
+4
#Update ወደር የሌለው የጥቁር አንበሳ ጀግና ሜዳይ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተሽለሙ ፦ 1. ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ 2. ጀነራል አበባው ታደሰ 3. ጀነራል ባጫ ደበሌ 4. ሌ/ጀ አለምሸት ደግፌ የአደዋ ድል ጀግና ከፍተኛ ሜዳይ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተሽለሙ ፦ 1. ጀነራል ጌታቸው ጉዲና 2. ሌ/ጀነራል በላይ ስዩም 3. ሌ/ጀነራል ዘውዱ በላይ 4. ሌ/ጀነራል መሰለ መሠረት 5. ሌ/ጀነራል ሹማ አብደታ 6. ሌ/ጀነራል አብዱራህማን እስማኤል 7. ሌ/ጀነራል ይልማ መርዳሳ 8. ሌ/ጀነራል ሰለሞን ኢተፋ የኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት የመዘከሪያና የመከላከያ ሠራዊት ዋና መሥሪያ ቤት የማስመረቅ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል። #PMOEthiopia #FDREDefenseForce @tikvahethiopia