en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
#Update የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ኮሚቴ ሁለት አጀንዳዎችን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡ አጀንዳዎቹ ፦ • የማሕበረሰብ ጤና አቀፍ መድህን ረቂቅ አዋጅ • የ2014 በጀት አመት ተጨማሪ በጀ
+2
#Update የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ኮሚቴ ሁለት አጀንዳዎችን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡ አጀንዳዎቹ ፦ • የማሕበረሰብ ጤና አቀፍ መድህን ረቂቅ አዋጅ • የ2014 በጀት አመት ተጨማሪ በጀት ረቂቅ አዋጅ ናቸው። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ በማሕበረሰብ ጤና አቀፍ መድህን ረቂቅ አዋጅ ላይ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ ረቂቅ አዋጁ መታከም የማይችለው የሕብረሰተብ ክፍል ፍትሃዊ ፣ ተደራሽ እና ጥራት ያለው የጤና ሽፋን በመስጠት እንዲታከም ለማድረግ ያለመ መሆኑን አብራርተዋል። በሌላ በኩል በ2014 በጀት አመት ተጨማሪ በጀት ረቂቅ አዋጅ አስፈላጊነት ላይም ወ/ሮ ሎሚ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ፣ ረቂቅ አዋጁ የተቋረጡ እና በጅምር ላይ ያሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ለማስቀጠል እንዲሁም በኮሮና እና በጦርነቱ ምክንያት የወጡ ወጪዎችን ለመሸፈን እንደሚውል ጠቅሰው ለዚህም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ታይቶ 122 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት እንደቀረበ ነው የገለጹት። #HPR @tikvahethiopia

#SomaliRegion የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በሶማሌ ክልል የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ ተፈናቃዮች ድጋፍ ከሚያደርጉ በርካታ ማኅበረሰቦች
+1
#SomaliRegion የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በሶማሌ ክልል የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ ተፈናቃዮች ድጋፍ ከሚያደርጉ በርካታ ማኅበረሰቦች መካከል አንዱ የሚገኝበትን ቀብሪበያን ዛሬ ማለዳ መጎብኘታቸውን አሳውቀዋል። ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፥ " በጊዜያዊነት የውኃ አቅራቢ ተሽከርካሪዎችን ፣ የምግብ፣ የእንስሳት መኖ እና እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መድኃኒቶችን አቅርቦት እናሳድጋለን " ብለዋል። " ድርቅ እንዳይከሰት በዘላቂነት ለመከላከል በቆላማ አካባቢዎች የውኃ ክምችትና አጠቃቀምን ለማሻሻል የጀመርናቸውን የአነስተኛ ግድቦች ግንባታ ፕሮጀክቶች እናፋጥናለን " ሲሉም ገልፀዋል። በኢትዮጵያ ውስጥ ድርቅ ከተከሰተባቸው ክልሎች አንዱ የሶማሌ ክልል ሲሆን ድርቅ በተከሰተባቸው የክልሉ ዞኖች አስከፊ ሁኔታ መኖሩ በተደጋጋሚ መገለፁ አይዘነጋም። @tikvahethiopia

#BORANA " የዱር እንስሳቱ ለሞትና ስደት ተዳርገዋል " - ቦረና ብሄራዊ ፓርክ በቦረና የተከሰተው ድርቅ በአካባቢው በሚኖረው ማህበረሰብ እንዲሁም በቤት እንስሳት ላይ ያደረሰውን ተፅእኖ ከዚህ ቀ
+1
#BORANA " የዱር እንስሳቱ ለሞትና ስደት ተዳርገዋል " - ቦረና ብሄራዊ ፓርክ በቦረና የተከሰተው ድርቅ በአካባቢው በሚኖረው ማህበረሰብ እንዲሁም በቤት እንስሳት ላይ ያደረሰውን ተፅእኖ ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ መረጃ መለዋወጣችን አይዘነጋም። ድርቁ ወገኖቻችንን እና እንስሳቶቻችን ክፉኛ እየጎዳ ሲሆን አሁን ደግሞ እንደተሰማው በድርቁ ሳቢያ በቦረና ብሄራዊ ፓርክ ውስጥ የሚገኙ የዱር እንስሳት ለከፍተኛ የውሃና የምግብ ችግር ተዳርገዋል።  የዱር እንስሳቱ ለከፍተኛ የውሃ እና የምግብ ችግር በመዳረጋቸው ለሞትና ስደት መዳረጋቸውን የፓርኩ አስተዳደር ለኢዜአ ገልጿል። በርካታ ቁጥር ያላቸው የሜዳ አህያ፣ ከርከሮዎችና ሌሎችም መሞታቸውን ሪፖርት ተደርጓል። የዱር እንስሳቱ ሞትና ስደት ፓርኩ ባሉት አምስት ክፍሎች ወይም ብሎኮች ውስጥ የሚታይ ሲሆን በፓርኩ ከሚገኙት የዱር አንስሳት መካከል በተለይም ግሪዝ ዜብራ፣ አጋዘን እና ከርከሮ በድርቁ ሳቢያ ህልውናቸው ጥያቄ ውስጥ መግባቱ ተገልጿል። በአካባቢው የሚገኙ አንዳንድ አርሶ አደሮች በሞተር ታግዘው ከመሬት ወስጥ በሚያወጡበት ውሃ ለዱር እንስሳቱ ውሃ ሲሰጡ ነው የቆዩት። የዱር እንስሳቱ አደጋ ውስጥ በመሆናቸው መንግስት እና የሚመለከታቸው አካላት አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። የድርቁ ችግር በዚሁ ከቀጠለ በፓርኩ ባሉት በርካታ የዱር እንስሳት የመኖር ህልውና ላይ አደጋ ጋርጧል ብለዋል። በቦረና ብሔራዊ ፓርክ ግሬዝ ዜብራ፣ አጋዘን፣ የሜዳ አህያ፣ ሰጎን፣ ቀጭኔ እና አንበሳን ጨምሮ ሌሎች ከ286 በላይ የአእዋፋት ዝርያዎች ይገኛሉ።  የቦረና ብሔራዊ ፓርክ በ2005 ዓ.ም ህጋዊ እውቅናን አግኝቶ የተቋቋመ ሲሆን 5 ክፍሎች ወይም ብሎኮች እንዳሉት የኢዜአ ዘገባ ያሳያል። @tikvahethiopia

#CSAኢትዮጵያ የታኅሣሥ ወር አገራዊ የዋጋ ግሽበት 35.1 በመቶ ጭማሪ የምግብ ዋጋ ግሽበት 41.6 በመቶ መድረሱ ተገለጸ። ማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ ባወጣው ወርሐዊ ሪፖርት ላይ እንደገለጸው የታ
#CSAኢትዮጵያ የታኅሣሥ ወር አገራዊ የዋጋ ግሽበት 35.1 በመቶ ጭማሪ የምግብ ዋጋ ግሽበት 41.6 በመቶ መድረሱ ተገለጸ። ማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ ባወጣው ወርሐዊ ሪፖርት ላይ እንደገለጸው የታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ጥቅምት ወር 2014 ጋር ሲነጻጸር በ1.4 ነጥብ ከመቶኛ እና የምግብ የመጠቁሙ (ኢንደክሱ) ክፍሎች በ0.5 ነጥብ ከመቶኛ መጠነኛ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡ በተመሳሳይ ወቅት የምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት በ2.8 ነጥብ ከመቶኛ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ የታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ታኅሣሥ ወር 2013 ዓ.ም ጋር ሲነጻጸር በ35.1 ከመቶ ከፍ ብሏል፡፡ የምግብ ዋጋ ግሽበት የታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ታኅሣሥ ወር 2013 ዓ.ም. ጋር ሲነጻጸር በ41.6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ በያዝነው ወር በእህሎችየዋጋ በአብዛኛው ቅናሽ የታየ ሲሆን የአትክልት ዋጋ ላይ ጭማሪታይቷል፡፡ ሩዝ፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንቡራና ምስር የዋጋ ቅናሽ አሳይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ስጋ፣ ወተት፣ ዐይብና ዕንቁላል፣ ቅመማ ቅመም (በዋናነት ጨውና በርበሬ) ጭማሪ አሳይተዋል፡፡ የምግብ ዘይት ዘይትና ቅቤም በመጠኑ ዋጋ ጨምሯል፡፡ ቡናና ለስለሳ መጠጦች የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል። በሌላ በኩል ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት የታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. ካለፈው ዓመት ታኅሣሥ ወር 2013 ዓ.ም. ጋር ሲነጻጸርም የ26.6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ ምንጭ፦ ሲራራ ጋዜጣ @tikvahethiopia

#EthiopianAirlines " የማክስ አውሮፕላናችንን ዳግም ወደ በረራ ለመመለስ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውናል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፌዴራል አቪዬሽን አድሚኒስትሬሽን /FAA/ ፣ የአውሮ
#EthiopianAirlines " የማክስ አውሮፕላናችንን ዳግም ወደ በረራ ለመመለስ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውናል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፌዴራል አቪዬሽን አድሚኒስትሬሽን /FAA/ ፣ የአውሮፓ ህብረት አቪየሽን ደህንነት ኤጀንሲ /EASA/ ፣ CAAC ፣ ECAA እንዲሁም ሌሎች በርካታ የአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ ጥልቅ ምርመራና ፍተሻ ካደረጉና ዳግም ማረጋገጫ ከሰጡ በኋላ የማክስ አውሮፕላኖችን ዳግም ወደ በረራ ለመመለስ ጥቂት ቀናት ብቻ እንደቀረው ገልጿል። አየር መንገዱ ፤ " ለደህንነት ቅድሚያ እንደመስጠታችንና ማክስ አውሮፕላንን ወደ ስራ ለመመለስ ከመጨረሻዎቹ አየር መንገዶች ተርታ እንደምንሆን በገባነው ቃል መሰረት እስካሁን 36 አየር መንገዶች አውሮፕላኑን ወደበረራ በመመለስ ከ330 ሺህ በላይ በረራዎችን አድርገዋል " ብሏል። የአውሮፕላን አብራሪዎች፣ መሃንዲሶች፣ የአውሮፕላን ጥገና ባለሞያዎች እንዲሁም የበረራ አስተናጋጆች 737 ማክስ አውሮፕላኖቻችንን ወደ በረራ ለመመለስ ሙሉ በሙሉ ተዘጋጅተዋል ሲል አየር መንገዱ በዛሬው ዕለት አሳውቋል። @tikvahethiopia

#ETHIOPIA የኢትዮጵያ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ የዓለም ጤና ድርጅት ስራ አመራር ቦርድ ውሳኔን ( ድርጅቱ የቀረበለትን የምርመራ ጥያቄ ማዘግየቱ) አስመልክቶ
#ETHIOPIA የኢትዮጵያ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ የዓለም ጤና ድርጅት ስራ አመራር ቦርድ ውሳኔን ( ድርጅቱ የቀረበለትን የምርመራ ጥያቄ ማዘግየቱ) አስመልክቶ ለሮይተርስ የተናገሩት ፦ " የዓለም ጤና ድርጅት ገለልተኛ አይደለም። የኢትዮጵያ መንግስት አሁንም በዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ወገንተኝነት ጉዳይ የቀረበለትን ምርመራ እንዲያደርግ በድጋሚ ያሳስባል " @tikvahethiopia

" የኢትዮጽያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር" ትላንት በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀፅ 57(1) መሠረት የተቋቋመው "የኢትዮጽያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር" ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንቱን እና ምክትል ፕሬ
+1
" የኢትዮጽያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር" ትላንት በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀፅ 57(1) መሠረት የተቋቋመው "የኢትዮጽያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር" ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንቱን እና ምክትል ፕሬዜዳንቱን መርጧል። በዚህም ወ/ሮ ስንዱ አለሙ ኘሬዘዳንት ፤ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ደግሞ ምክትል ኘሬዘዳንት ሆነው ተመርጠዋል። የፍትህ ሚኒስቴር በህጉ በተደነገገው መሰረት ጉባዔውን በመጥራት የማህበሩ ፕሬዘዳንት እና ም/ል ፕሬዘዳፈንት እንዲሁም የስራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት እንዲመረጡ አድርጓል። በተመሳሳይ ጠቅላላ ጉባኤው 7 /ሰባት/ የስራ አስፈፃሚ አባላትን መርጧል። በዚህም መሠረት:- 1. ሂሩት መለሠ; 634 2. ፊሊጶስ አይናለም; 628, 3. ሊቁ ወርቁ; 522, 4. ዮሴፍ አዕምሮ;514, 5. ሆሳና ነጋሽ; 492, 6. ትደነቂያለሽ ተስፋ;424, 7. ሰለሞን እምሩ; 418, የስራ አስፈጻሚ አባል ሆነው ትላንት ተመርጠዋል። @tikvahethiopia

በአፋር በኩል ጦርነት ቀጥሏል። የአፋር ክልል መንግስት ፥ " አሽባሪው ህወሓት በኪልበቲ ረሱ ዞን በኩል በአብአላና በመጋሌ ወረዳ የከፈተውን ውጊያ አጠናክሮ ቀጥሏል " ሲል ዛሬ አሳውቋል። ቡድኑ በን
በአፋር በኩል ጦርነት ቀጥሏል። የአፋር ክልል መንግስት ፥ " አሽባሪው ህወሓት በኪልበቲ ረሱ ዞን በኩል በአብአላና በመጋሌ ወረዳ የከፈተውን ውጊያ አጠናክሮ ቀጥሏል " ሲል ዛሬ አሳውቋል። ቡድኑ በንፁሀን ዜጎች ላይ ከባድ መሳሪያ በመክፈት እያሸበረ እንደሚገኝም ገልጿል። ዛሬ ሰኞ በኪልበቲ ረሱ (ዞን) በተለያዩ ቦታዎች የአፋር ክልልን ወሰን ጥሶ በመግባት በአብአላ፣ በመጋሌ እና በበራህሌ በኩል በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጦርነት በመክፈት በርካታ ንፁሀንን ለጉዳት መዳረጉን የአፋር ክልል አስታውቋል። ህወሓት በአፋር ክልል በተለያዩ ወረዳዎች በኩል ዘልቆ በመግባት ንፁሀን የጎዳ ቢሆንም ጥቃት እንደተፈፀመበት አስመስሎ በማቅረብ አሁንም ማደናገሪያውን እየነዛ ይገኛል ብሏል። የአፋር ክልል በድጋሚ የትግራይ ህዝብ የህወሓትን እብደት በቃህ ሊል ይገባል ያለ ሲሆን በግልፅ እየወጣ ያለውን ሴራውንና ተንኮሉን በመረዳት ከህዝብ የሚበልጥ የለምና እንደ ህዝብ ሊቃወም ግድ ይላል ብሏል። ከጥቂት ቀናት በፊት ህወሓት በምላዛትና በዳንደ በአፋር ልዩ ኃይል ጥቃት እንደተፈፀመና የአፋር የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት ጎሳ መሪዎች ከድርጊቱ እንዲቆጠብ እንዲያደርጉ ሲል ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ የአፋር ክልል እስልምና ጉዳዩች ጠቅላይ ሸሪአ ፍርድ ቤት እና የሀገር ሽማግሌዎች በሰጠው ምላሽ " በከባድ መሳሪያ በየቀኑ የንፁሀን ነፍስ እያጠፋችሁ ፣ በውሸት ተወረርን በማለት እና ሰላም ፈላጊ መስሎ መቅረብ የተለመደው ማደናገሪያችሁ ከመሆን ውጪ በፍፁም ተቀባይነት የለውም " ብሏል። በጠቀሱት ቦታዎች ላይ አንድም የአፋር ልዩ ሀይል እንደሌለ አስገንዝበዋል፤ የህወሓት ክስ ዓለምን በውሸት የማደናገሪያ ተግባር ነው ሲሉ ገልፀውታል። @tikvahethiopia

" 5 ተማሪዎች እና 1 በንግድ ስራ የተሰማራ ግለሰብ ታግተዋል " - የፌደራል የደኅንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል በኦሮሚያ ክልል ፣ ምስራቅ ወለጋ 5 ተማሪዎች እና አንድ በንግድ ስራ የሚተዳደር
" 5 ተማሪዎች እና 1 በንግድ ሾል የተሰማራ ግለሰብ ታግተዋል " - የፌደራል የደኅንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል በኦሮሚያ ክልል ፣ ምስራቅ ወለጋ 5 ተማሪዎች እና አንድ በንግድ ሾል የሚተዳደር ግለሰብ በድምሩ 6 ሰዎች ታግተዋል። የፌደራል የደኅንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል እገታውን ሸኔ እንደፈፀመ ገልፆ የታገቱትን ግለሰቦች ለማስለቀቅ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አሳውቋል። ግብረ ኃይሉ ፥ ታጋቾቹ ከአዲስ አበባ ወደ አሶሳ ሲጓዙ ምስራቅ ወለጋ ጎቡ ሰዮ ወረዳ ልዩ ስሙ ባፋኖ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ነው ጥር 15 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰአት አካባቢ በሸኔ ታፍነው የተወሰዱት ብሏል።   ግብረ ኃይሉ ታጋቾችን የማስለቀቁ እንቅስቃሴ እየተካሄደ መሆኑንና እርምጃዎችን ተከትሎ የሚገኘውን ውጤት በቀጣይ ለህዝቡ እንደሚያሳወቅ ገልጿል። @tikvahethiopia

#Update የብፁዕ አቡነ ሚካኤል የኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሥርዓተ ቀብር ተፈፅሟል። የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
#Update የብፁዕ አቡነ ሚካኤል የኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሥርዓተ ቀብር ተፈፅሟል። የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ሓላፊዎች፣ የኢሊባቡር ሀገረ ስብከት ሓላፊዎችና ምእመናን በተገኙበት ነው በደብረ ሊባኖስ ገዳም የተፈፀመው። @tikvahethiopia

ፕሬዝዳንት ካቦሬ በወታደሮች ታስረዋል። የቡርኪና ፋሶ ፕሬዝዳንት በሀገሪቱ ወታደሮች መታሰራቸው ተነግሯል። ፕሬዝዳንት ሮች ካቦሬ የታሰሩት በአማጺ ወታደሮች ሲሆን፤ በሀገሪቱ መዲና ኡጋዱጉ ባለ አንድ
+1
ፕሬዝዳንት ካቦሬ በወታደሮች ታስረዋል። የቡርኪና ፋሶ ፕሬዝዳንት በሀገሪቱ ወታደሮች መታሰራቸው ተነግሯል። ፕሬዝዳንት ሮች ካቦሬ የታሰሩት በአማጺ ወታደሮች ሲሆን፤ በሀገሪቱ መዲና ኡጋዱጉ ባለ አንድ ወታደራዊ ማዘዣ ውስጥ እንደሚገኙ ተገልጿል። የቡርኪና ፋሶ መንግስት በትናንትናው ዕለት የወታደሮቹ እንቅስቃሴ መፈንቅለ መንግስት አለመሆኑን ገልጾ ነበር። በቡርኪና ፋሶ ወታደሮች ውስጥ ጥያቄ እንዳነሱ የሚነገርላቸው አማጺ ወታደሮች አዛዦቻቸውን ጨምሮ መሪዎችን ገድለዋል። ይሄንን ተከትሎም የቡርኪና ፋሶ መንግስት ከትናንት ምሽት ጀምሮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ጨምሮ የሰዓት ገደብ ጥሎም ነበር፡፡ በምዕራብ አፍሪካ ሀገራት መፈንቅለ መንግስት ማድረግ የተለመደ ሲሆን አሁን ደግሞ ተራው የቡርኪና ፋሶ ሆኗል። የማሊ ወታደሮች በኮለኔል አስሚ ጎይታ የተመራ መፈንቅለ መንግስት በማድረግ አሁን ላይ የሽግግር ጊዜያዊ መንግስት መስርተው ማሊን በማስተዳደር ላይ ይገኛል። ኢኳቶሪያል ጊኒም መፈንቅለ መንግስት በማድረግ የሀገሪቱን ሲቪል አስተዳድር በማስወገድ ወታደረዊ መንግስት የመሰረተ ሲሆን እነዚህ ወታደራዊ መሪዎች ስልጣናቸውን በህዝብ ለተመረጡ መንግስታት እንዲያስረክቡ ኢኮዋስን ጨምሮ አፍሪካ ህብረት እና ሌሎች ተቋማት በማሳሰብ ላይ ናቸው። ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ / ሮይተርስ @tikvahethiopia

#ይበቃል ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ያሉ ዜጎቻችን ፍትህን እንዲያገኙ የሚጠይቅ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን ተመልክተናል። ዘመቻው ሳዑዲ ያሉ ዜጎቻችን እምነበረድ ላይ ለብሰው የሚተኙትን ጥቁር
+6
#ይበቃል ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ያሉ ዜጎቻችን ፍትህን እንዲያገኙ የሚጠይቅ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን ተመልክተናል። ዘመቻው ሳዑዲ ያሉ ዜጎቻችን እምነበረድ ላይ ለብሰው የሚተኙትን ጥቁር ፌስታል በመልበስ አጋርነት የሚገለፅበት ነው። ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በርካታ ዜጎቻችን እጅግ አስከፊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ይታወቃል። የሳኡዲ አረቢያ መንግስት መሰረታዊ የእስረኛ አያያዝ ህግን እንዲተገብር፣ ፍትሃዊ የሆነ ምላሽም እንዲሰጥ የሚጠየቅበት የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ነው እየተካሄደ ያለው። #ይበቃል #ጥቁር_ፌስታል #الحرية_للسجناء_الاثيوبيين #العدالة_للسجناء_الاثيوبيين Credit : Ali Amin & Social Media @tikvahethiopia

#ONLF ኦብነግ ከሶማሊያ የሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ። የሶማሊያ ካቢኔ እ.ኤ.አ. በ2017 ( የቀድሞው ካቢኔ ) የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) ን “አሸባሪ ድርጅት” ሲል
+4
#ONLF ኦብነግ ከሶማሊያ የሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ። የሶማሊያ ካቢኔ እ.ኤ.አ. በ2017 ( የቀድሞው ካቢኔ ) የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) ን “አሸባሪ ድርጅት” ሲል ያሳለፈው ውሳኔ ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ሽሮታል። ኦብነግ ከ5 ዓመት በኃላ ከሽብረተኛ ድርጅትነት ተሰርዟል። ካቢኔው የኦብነግ ኮማንደር አብዲከሪም ሼክ ሙሴን ወደ ኢትዮጵያ ተላልፎ መሰጠትንም “ህገወጥ” ሲል ገልጿል። አብዲከሪም ሼክ ሙሴ እ.ኤ.አ. በ2018 በኢትዮጵያ ከመጣው ለውጥ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ መንግስት ከእስር ነፃ መደረጋቸው ይታወሳል። የዛሬው የሶማሊያ ካቢኔ ውሳኔ በ23 ድምጽ ድጋፍ ፣ በ1 ተቃውሞ እና በ1 ድምፀ ተአቅቦ ነው የፀደቀው። ኦብነግ በትዊተር ገፁ በጠቅላይ ሚኒስትር መሀመድ ሁሴን ሮብሌ እና በካቢኔያቸው ዛሬ የተላለፈውን ውሳኔ በደስታ መቀበሉን ገልፆ ውሳኔውን " ታሪካዊ ነው " ብሎታል። ኢትዮጵያ እንደ እ.ኤ.አ. በ2018 የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ)ን ከሽብርተኛ ድርጅቶች ዝርዝር መሰረዟ ይታወሳል። @tikvahethiopia

#Update እድሳት ሲደረግለት የቆየው የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ህንፃ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ለእድሳቱ ከ1.
+3
#Update እድሳት ሲደረግለት የቆየው የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ህንፃ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ለእድሳቱ ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ መሆኑ ተሰምቷል። ህንፃው ከ57 ዓመታት በኋላ ነባር ገፅታውን ሳይለቅ ነው መሰረታዊ እድሳት የተደረገለት። ህንፃው አዳዲስና ደረጃቸውን የጠበቁ አገልግሎቶችን በውስጡ ያካተተ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ፦ - የህፃናት መዋያ፣ - ቤተ-መፃሕፍት፣ - የስልጠናና የምርምር ክፍሎች፣ - ክሊኒክ፣ - የቴአትር አዳራሽ፣ - የስብሰባ አዳራሾች፣ - የመኪና ማቆሚያ፣ - አረንጓዴ ስፍራዎችና የከተማ ግብር ናሙናዎች ይገኙበታል። የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከነገ ሰኞ ጀምሮ ለህዝብ ክፍት እንደሚደረግ እና መጎብኘት እንደሚቻል አሳውቀዋል። ፎቶ : አ/አ ከንቲባ ፅ/ቤት @tikvahethiopia

የክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ቤተሰቦች ስለ አንፋጋው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ምን አሉ ? ፍርድዮስ ዩሱፍ ለኤፍ ኤም 97.1 ሬድዮ የተናገሩት ፦ " ... አሊ በራ ሞተ ምናምን እያሉ በየጊዜ ያወ
+1
የክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ቤተሰቦች ስለ አንፋጋው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ምን አሉ ? ፍርድዮስ ዩሱፍ ለኤፍ ኤም 97.1 ሬድዮ የተናገሩት ፦ " ... አሊ በራ ሞተ ምናምን እያሉ በየጊዜ ያወጣሉ። ነገር ግን የትላንትናው በጣም እኛንም የጎዳ ያሳዘነን ነው። ከትላንት ወዲያ ነው ከሆስፒታል የወጣው ፤ በጤንነት ጥዋት ላይ ደግሞ የሚገርመው በእግሩ እኔ ሄዳለሁ አብራችሁኝ ሂዱ ብሎ በመኪና ይዘነው ሄደን ባንክ ሄዶ ለእራሱ የሆነ ትራስዛክሽን ሰርቶ ነው የመጣው። እንግዲህ ይህ ሰው ዊልቸር ላይ የለም፤ ወይም ደግሞ አልጋ ላይ የለም። በእግሩ ጥዋት ሄዶ ነው የተመለሰው። እዛው ነው ያደርነው (የአሊ መኖሪያ ቢሾፍቱ) ። ለሊት ላይ ብቻ ስልክ ይጮሃል ምንድነው የተፈጠረው ? እንደተለመደው ሞተ ሊሉኝ ነው ስል በጣም በጣም ከማልጠብቀው ሰው ነው ፌስቡክ ላይ ፖስት ሲያደርግ ሳይ ለማን ነው RIP የምትሉት ኧረ ባካችሁ አንሱ እሱ በጤና ነው ያለው እያልኩኝ ለሊት ሙሉ አልተኛሁም። ይሄ ነገር ተደጋገመ ፤ ያልተጣራ መረጃ እየለጠፉ ቤተሰብን ያሳዝናሉ ፣ ይሄነገር ባህል ሆነብን እንዴ ? ብቻ አላውቅም በጣም ተደጋጋመ ነገር ግን የትላንት ማታው በጣም ያሳዘነን ነው። ከዚህ ቢቆጠቡ ይሻላል በጣም ደስ የማይል ነገር ነው እያደረጉ ያሉት። ...አሊ ቢራ እጅግ በጣም ጥሩ ሁኔታ ላይ ጥሩ ጤንነት ላይ ነው ያለው። ፀልዩለት ! ሰው ሲፖስት ደግሞ ዝም ብለው ከእስር እያነሱ የሚፖስቱት ደግሞ ቢቆጠቡ። ቤተሰብ አለ፣ ስንት የሚሰማው ሰው አለ ስለዚህ በዚህ ላይክ እና ሼር ለማድረግ ብላችሁ እንዲህ አይነት ነገር ብትቆጠቡ እላለሁ። " @tikvahethiopia

25 ሱደናውያን ከእስር ተለቀቁ። የጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎን የኢትዮጵያ ጉብኝትን ተከተሎ ኢትዮጵያ 25 ሱዳናዊያንን ከእስር ለቀቀች፡፡ የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ጄ
25 ሱደናውያን ከእስር ተለቀቁ። የጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎን የኢትዮጵያ ጉብኝትን ተከተሎ ኢትዮጵያ 25 ሱዳናዊያንን ከእስር ለቀቀች፡፡ የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ በኢትዮጵያ የነበራቸውን የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት አጠናቀው ወደ ካርቱም ተመልሰዋል፡ ኢትዮጵያ 25 ሱዳናዊያን እስረኞችን መፍታቷን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ሱዳናዊያን እስረኞቹ የተፈቱት ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸውን ተከትሎ ነው መሆኑን አል ዓይን ዘግቧል። እስረኞቹ የተፈቱት ሁለቱ ሀገራት የጋራ ድንበር ጉባኤ ከአንድ ወር በፊት በብሉናይል እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች መካከል የሰላም እና የደህንነት ጉባኤ ካደረጉ በኋላ በተስማሙት መሰረት ነው፡፡ ዛሬ የተፈቱት ሱዳናዊያን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዋና ከተማ አሶሳ ማረሚያ ቤት ታስረው የነበሩ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ Credit : አል ዓይን ኒውስ @tikvahethiopia

" ከሱዳን ጋር ተቀራርበን መስራት እንደሚገባን መግባባት ላይ ደርሰናል " - ዶ/ር አብርሃም በላይ ከሱዳን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን መስራት እንደሚገባን መግባባት ላይ ደርሰናል ሲሉ የ
" ከሱዳን ጋር ተቀራርበን መስራት እንደሚገባን መግባባት ላይ ደርሰናል " - ዶ/ር አብርሃም በላይ ከሱዳን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን መስራት እንደሚገባን መግባባት ላይ ደርሰናል ሲሉ የአገር መከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ ገልፀዋል። የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ በኢትዮጵያ የነበራቸውን የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት አጠናቀው ዛሬ ወደ አገራቸው ሲመለሱ ዶክተር አብርሃም አሸኛኘት አድርገውላቸዋል። የጄኔራል ዳጋሎን የኢትዮጵያ ቆይታን በተመለከተ ዶክተር አብርሃም ለኢዜአ እንደገለጹት ፤ በኢትዮጵያ እና በሱዳን የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዷል። “አብረንና ተቀራርበን መስራት እንደሚገባን ተግባብተናል” ሲሉም ገልጸዋል። ትናንት አዲስ አበባ የገቡት ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል። ጄኔራሉ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪ ከአገር መከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ እና ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር መወያየታቸው ይታወሳል። #ኢዜአ @tikvahethiopia

#Update " የክልል መለያን የያዙ ሰሌዳዎችን የሚያስቀር ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ተመራ በሚል በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሠራጨ ያለዉ መረጃ የተሳሳተ ነዉ " - አቶ ካሳሁን ጎፌ ሪፖርተር ጋዜጣ " የክልል መለያ ተሽከርካሪዎች ሰሌዳን " በተመለከተ ዛሬ አንድ ዘገባ በፊት ገፁ ይዞ ወጥቶ ነበር። (ከላይ በ Reply) ማግኘት ይቻላል። ጋዜጣው በዘገባው ላይ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የህግ አማካሪ አቶ አበጀ ማሞን ተጨማሪ ዝርዝር ማብራሪያ ይዞ ነው የወጣው። ከደቂቃዎች በፊት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ፥ " የክልል መለያን የያዙ ሰሌዳዎችን የሚያስቀር ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ተመራ በሚል በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሠራጨ ያለዉ መረጃ የተሳሳተ ነዉ " ብለዋል። ሚኒስትር ዴኤታው አራተኛው መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ የመንገድ ትራንስፖርት ረቂቅ አዋጅ ላይ አስፈላጊዉን ግብዓቶችን በማካተት እንዲፀድቅ ወደ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት መምራቱን አስታውሰዋል። ሆኖም ግን ከረቂቅ አዋጁ ይዘት ዉጭ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የክልል መለያ ከተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ላይ እንዲነሳ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ መመራቱን የሚገልጽ ዜና እየተዘገበ ስለመሆኑ አረጋግጠናል ብለዋል። አቶ ካሳሁን ጎፌ ፥ " በመጀመሪያ መረጃዉ የተሳሳተ እና ከረቂቅ አዋጁ ይዘት ዉጭ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን " ያሉ ሲሆን " በቀድሞ አዋጁ የነበረዉ የተወሰኑ ክልሎችን ታርጋ ዝርዝር የያዘ አባሪ በዚህ ረቂቅ አዋጅ የቀረዉ መንግስት ተጨማሪ ክልሎች ሲወጡ በየጊዜዉ በአዋጁን ማሻሻል ሳያስፈልገዉ ተግባራዊ ለማድረግ እንዲችል ታስቦ መሆኑ ታዉቆ የክልል መለያ ሰሌዳን ከተሸከርካሪዎች ላይ የማንሳት የረቂቅ አዋጁ ሀሳብና ይዘት አካል እንዳልሆን ሊታወቅ ይገባል " ሲሉ አስረድተዋል። አክለው " ረቂቅ አዋጁ የመንገድ ትራንስፖርትን አስመልክቶ የፌዴራሉንና የክልል አስፈጻሚ አካላት የተሰጣቸውን ሥልጣንና ተግባር በማያሻማ ሁኔታ የሚያስቀምጥ ከመሆኑም በላይ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዕድገት የመንገድ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ የበለጠ ለማጎልበት ዘርፉ አስተማማኝ፤ የተቀናጀ፤ ዘመናዊና ደኅንነቱ የተረጋገጠ ሆኖ እንዲራመድ የሚያስችል ሲሆን በቅርቡም ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ቀርቦ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ሰፊ ዉይይት ተደርጉበት አስፈላጊዉ ማሻሻያ ተደርጎበት እንደሚጸድቅ ይጠበቃል " ብለዋል። @tikvahethiopia

#GeneralDagallo ጄነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር እንዲሁም ከሌሎች አመራሮች ጋር መገናኘታቸውን ገልፀዋል። ጄነራሉ ባ
+2
#GeneralDagallo ጄነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር እንዲሁም ከሌሎች አመራሮች ጋር መገናኘታቸውን ገልፀዋል። ጄነራሉ ባጋሩት ፎቶ : ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፣ ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ከሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ጋር መገናኘታቸውን ያሳያል። ሄሜቲ ጉብኝቱን በተመለከተ ፥ " ... ዛሬ አዲስ አበባን በመጎብኘቴ እና የዚህችን ውብ ሀገር መሪዎች በወንድማማችነት መንፈስ በማግኘቴ ደስተኛ ነኝ። ይህም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ጥልቀት እና ጥንካሬ ያረጋግጣል " ብለዋል። @tikvahethiopia

#AU #SUDAN የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሀመት ትላንት አዲስ አበባ ከገቡት የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳ
+1
#AU #SUDAN የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሀመት ትላንት አዲስ አበባ ከገቡት የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) ጋር ተወያይተዋል። ሊቀመንበሩ ፤ ውይይቱ የነበረው አሁን ላይ በሱዳን ስላለው አሳሳቢ ሁኔታ መሆኑን ገልፀዋል። @tikvahethiopia