en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
#ETHIOPIA የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል 42ቱን መለየቱን የም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ አሳውቀዋል። አቶ ታገሰ
#ETHIOPIA የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል 42ቱን መለየቱን የም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ አሳውቀዋል። አቶ ታገሰ ፥ ከመላው የሀገሪቱ ክፍሎች 632 የእጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቅረባቸውንና አብዛኛዎቹ ስራውን ለመስራት የሚያስችል ልምድና ዕውቀት ያላቸው መሆኑን መገንዘብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ አዋጁ ለአፈ-ጉባኤውና ለአፈ-ጉባኤው ጽ/ቤት በሰጠው ስልጣን እንዲሁም በአዋጁ በተቀመጠው መስፈርት መሰረት ከቀረቡት 632 ዕጩዎች መካከል 42ቱ መለየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በቀረቡ 42 ዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከአማካሪዎች ጋር ምክክር እየተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ ሳምንት ደግሞ የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች ፣ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት አመራር አካላት በሚገኙበት በዕጩዎች የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልምድ ላይ ምክክር ተደርጎ ግብአት የሚሰበሰብ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ በማስከተልም በም/ቤቱ ድረ-ገጽና በማህበራዊ ሚዲያ የእጩዎችን ማንነት በመግለጽ በቂ ግብአት ከተሰበሰበ በኋላ ሰብሳቢና ም/ሰብሳቢን ጨምሮ 11ዱ ዕጩ ኮሚሽነሮች ለም/ቤቱ ቀርቦ ከፀደቀና ዕጩዎች ከተሰየሙ በኋላ ወደ ስራ እንደሚገባም ገልጸዋል። @tikvahethiopia

#NewsAlert የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ለተለያዩ ግለሰቦች የሙሉ አምባሳደርነት እና የአምባሳደርነት ሹመት ሰጡ። በዚህም መሠረትም፡- 1/ አቶ ተፈራ ደርበው 2/ አቶ ደሴ ዳልኬ
#NewsAlert የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ለተለያዩ ግለሰቦች የሙሉ አምባሳደርነት እና የአምባሳደርነት ሹመት ሰጡ። በዚህም መሠረትም፡- 1/ አቶ ተፈራ ደርበው 2/ አቶ ደሴ ዳልኬ 3/ ዶክተር ስለሺ በቀለ 4/ ጄኔራል ባጫ ደበሌ 5/ ጄኔራል ሀሰን ኢበራሂም 6/ ወ/ሮ ሽትዬ ምናለ 7/ ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ 8/ አቶ ረሻድ መሀመድ 9/ አምባሳደር ጀማል በከር 10/ አቶ ፈይሰል ኦሊይ 11/ አቶ ኢሳያስ ጎታ 12/ አቶ ፀጋአብ ክበበው 13/ አቶ ጣፋ ቱሉ 14/ ዶክተር ገነት ተሾመ 15/ አቶ ዳባ ደበሌ 16/ አቶ ፍቃዱ በየነ የባሉሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ሲሾሙ። 1/ አቶ አሳየ አለማየሁ 2/ አቶ ኃይላይ ብርሃነ 3/ አቶ አወል ወግሪስ 4/ ወ/ሮ ብዙነሽ መሠረት 5/ አቶ አንተነህ ታሪኩ 6/ አቶ አክሊሉ ከበደ 7/ አቶ ሰይድ መሐመድ 8/ አቶ ዮሴፍ ካሳዬ 9/ አቶ ዘላለም ብርሃን 1ዐ/ ወ/ሮ ፍርቱና ዲባኮ 11/ አቶ ወርቃለማሁ ደሰታ በአምባሳደርነት የተሾሙ መሆኑን ከፕሬዝዳንት ፅሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ @tikvahethiopia

ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ ስለብሄራዊ ቡድኑ ምን አሉ ? የጊኒ ብሄራዊ ቡድን በካሜሮን የ2021 አፍሪካ ዋንጫ በጊዜ ከተሰናበቱት ሀገራት መካከል እንደምትገኝበት ይታወቃል። ቡድኑ ወደ ካሜሮን በተሸኘበት
ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ ስለብሄራዊ ቡድኑ ምን አሉ ? የጊኒ ብሄራዊ ቡድን በካሜሮን የ2021 አፍሪካ ዋንጫ በጊዜ ከተሰናበቱት ሀገራት መካከል እንደምትገኝበት ይታወቃል። ቡድኑ ወደ ካሜሮን በተሸኘበት ምሽት አሁን ጊኒን እያስተዳደር ያለው የጁንታ መሪ ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ ለቡድኑ አባላት ያስተላለፉት መልዕክት መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር የሁላችንም ትውስታ ነው። ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ የሀገሪቱን ባንዲራ 🇬🇳 ለቡድኑ ካስረከቡ በኃላ ባስተላለፉት መልዕክት የቡድኑ አባላት ዋንጫውን ይዘው እንዲመጡ ካልሆነ ግን በእነሱ ላይ ኢንቨስት የተደረገውን እያንዳንዱን ገንዘብ እንዲመልሱ /እንዲተኩ ነበር ያሉት። ቡድኑም በአፍሪካ ዋንጫው ሳይሳካለት ቀርቶ በጊዜ ተሰናብቷል ፤ ይህን ተከትሎ የጁንታውን መሪ ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ አስተያየት ብዙዎች ሲጠብቁት ነበር። ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያም ዝም አላሉም። ኮሌኔሉ ብሄራዊ ቡድኑን 'ይቅር' እንዳሉ ገልፀው ፤ በወቅቱ ያን ንግግር የተናገሩት ቡድኑን ለማበረታታ ብቻ መሆኑ አሳውቀዋል። " የቡድን ግንባታ ጊዜ እንደሚወስድ እገነዘባለሁም " ብለዋል። ነገር ግን ለቡድኑ የተሰጠው ገንዘብ ሩብ ፍፃሜ ፣ ግማሽ ፍፃሜ እና የፍፃሜ ጨዋታዎችን የሚሸፍን ሲሆን ያ ገንዘብ ወደ መንግስት ካዝና ይመለሳል ተብሏል። @tikvahethiopia

ፎቶ : ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁ ከእስር ተፈቶ ከቤተሰቦቹ ጋር ተቀላቅሏል። ጋዜጠኛው ከእስር መፈታቱን በተመለከተ በተረጋገጠ ፌስቡክ ገፁ ላይ " ከጥቅምት 18 እስከ ጥር 18 ... በእግዚአብሔር ምህረ
+2
ፎቶ : ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁ ከእስር ተፈቶ ከቤተሰቦቹ ጋር ተቀላቅሏል። ጋዜጠኛው ከእስር መፈታቱን በተመለከተ በተረጋገጠ ፌስቡክ ገፁ ላይ " ከጥቅምት 18 እስከ ጥር 18 ... በእግዚአብሔር ምህረት ተፈትቻለሁ ፤ አመሰግናለሁ " ብሏል። ጋዜጠኛ ክብሮ ወርቁ ላለፉት 3 ወራት በእስር ቆይቷል። ዛሬ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት በ መታወቂያ ዋስትና ነው ከእስር የተፈታው። @tikvahethiopia

ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁ ከእስር ተለቀቀ። ላለፉት 3 ወራት ከሶስት ቀን በእስር ላይ የነበረው የአሐዱ ሬዲዮ የዜና ክፍል ሀላፊ ክብሮም ወርቁ ዛሬ ከሰአት በኃላ ከእስር ተፈትቶ ከቤተሰቦቹ ጋር መቀላቀሉ
ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁ ከእስር ተለቀቀ። ላለፉት 3 ወራት ከሶስት ቀን በእስር ላይ የነበረው የአሐዱ ሬዲዮ የዜና ክፍል ሀላፊ ክብሮም ወርቁ ዛሬ ከሰአት በኃላ ከእስር ተፈትቶ ከቤተሰቦቹ ጋር መቀላቀሉን ጠበቃው አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ መናገራቸውን አሀዱ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን አሳውቋል። @tikvahethiopia

#State_of_Emergency ለ6 ወራት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ እንዲያጥር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ውሳኔ አሳልፋል። ም/ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማውጣት የግድ አስ
#State_of_Emergency ለ6 ወራት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ እንዲያጥር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ውሳኔ አሳልፋል። ም/ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማውጣት የግድ አስፈላጊ እንዲሆን አድርጎ የነበረው ሁኔታ የተቀየረ መሆኑን ገልጿል። አክሎም ስጋቱን በመደበኛ የሕግ ማስከበር ስራ መከላከልና መቆጣጠር የሚቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን በመግለፅ ለ6 ወራት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ ማሳጠር አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አሳውቋል። በዚህም አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የ6 ወር ጊዜው ሳይጠናቀቅ ጊዜውን የማሳጠር ስልጣን ያለው ህ/ተ/ም/ቤት የአዋጁን ተፈጻሚነት ቀሪ እንዲያደርገው የሚጠይቅ የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ እንዲተላለፍ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አሳልፏል። @tikvahethiopia

#BREAKING የጠ/ሚኒስትር ፅ/ቤት ፦ " የሚኒስትሮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የሃገር ህልውና እና ሉዐላዊነት ላይ የተደቀነን አደጋ ለመከላከል የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁ
+2
#BREAKING የጠ/ሚኒስትር ፅ/ቤት ፦ " የሚኒስትሮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የሃገር ህልውና እና ሉዐላዊነት ላይ የተደቀነን አደጋ ለመከላከል የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 5/2014 ቀሪ የሚሆንበትን ጊዜ በሚመለከት በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ ሕውሃት እና ግብረአበሮቹ በሃገራችን ህልውና እና ሉአላዊነት ላይ ከፍተኛ አደጋ የደቀኑ በመሆኑ እና ይህን አደጋ በመደበኛው የህግ ማስከበር ስራ መከላከል የማይቻል ሆኖ በመገኘቱ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 23 ቀን 2014 የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 5/2014ን ያወጀ ሲሆን፣ ይህ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ በአዋጅ ቁጥር 1264/2014 ፀድቆ በስራ ላይ የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማውጣት የግድ አስፈላጊ እንዲሆን አድርጎ የነበረው ሁኔታ የተቀየረ በመሆኑ እና ስጋቱን በመደበኛው የሕግ ማስከበር ስራ መከላከልና መቆጣጠር የሚቻልበት ደረጃ ላይ በመደረሱ ለስድስት ወራት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ ማሳጠር አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በመሆኑም በአዋጅ ቁጥር 1264/2014 አንቀጽ 11(2) በተደነገገው መሰረት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የስድስት ወራት የጊዜ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መታወጅ ምክንያት የሆኑ ሁኔታዎች ከተቀየሩ እና በመደበኛው የሕግ ማስከበር ስርዓት ሊከሰቱ የሚችሉ ጉዳዮችን መቆጣጠር ይቻላል ብሎ ካመነ የስድስት ወር ጊዜው ሳይጠናቀቅ ጊዜውን የማሳጠር ስልጣን ያለው በመሆኑ የአዋጁን ተፈጻሚነት ቀሪ እንዲያደርገው የሚጠይቅ የውሳኔ ሃሳብ ቀርቦ በውሳኔ ሃሳቡ ላይ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በጥልቀት ተወያይቶ በማጽደቅ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡ " @tikvahethiopia

" ... ህወሓት በከፍተኛ ደረጃ ሀይል እያሰባሰበና ሊወጋ እየተዘጋጀ መሆኑን የሚያሳዩ እንቅስቃሴዎች እያደረገ ነው " - አቶ ግዛቸው ሙሉነህ የአማራ ክልል መንግስት ህወሓትን ማጥፋት ካልተቻለ የኢት
" ... ህወሓት በከፍተኛ ደረጃ ሀይል እያሰባሰበና ሊወጋ እየተዘጋጀ መሆኑን የሚያሳዩ እንቅስቃሴዎች እያደረገ ነው " - አቶ ግዛቸው ሙሉነህ የአማራ ክልል መንግስት ህወሓትን ማጥፋት ካልተቻለ የኢትዮጵያ ስጋት ሆኖ መቀጠሉ አይቀሬ ነው አለ። የክልሉ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ግዛቸው ሙሉነህ ለአሀዱ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል " አሸባሪውን የሕወሓት ቡድን ተባብሮ ሙሉ በሙሉ ማጥፋት ካልተቻለ የኢትዮጵያ ስጋት መሆኑን ይቀጥላል " ብለዋል። ቡድኑ አሁንም በአማራ ክልል የተለያዩ ስፍራዎች ላይ በየቀኑ ጥቃቶችን እየሰነዘረ ንፁሃንን እያሰቃየና እየገደለ ነው ሲሉም አቶ ግዛቸው ከሰዋል። አክለው ፥ "በማይፀብሪ ፣ አዳርቃይ ፣ ቆቦ ፣ኮረም ፣አላማጣ በየቀኑ ጥቃት የሚሰነዝርባቸው እና ከጦርነት አርፈው የማያውቁ አካባቢዎች ናቸው። ቡድኑ በእነዚህ አካባቢዎች አሁንም ፍላጎት እንዳለው ያሳያል " ብለዋል፡፡ ዳይሬክተሩ ፤ ህወሓት በከፍተኛ ደረጃ ሀይል እያሰባሰበና ሊወጋ እየተዘጋጀ መሆኑን የሚያሳዩ እንቅስቃሴዎች እያደረገ እንደሆነም አመልክተዋል። አሁንም ልክ እንደ በፊቱ በሀሰት ትርክቱ እያሳመነ እንዲሁም እያስገደደ የትግራይ ህዝብን እያሰለጠነ እና እያዘመተ ነው ብለዋል፡፡ አሁን ባለዉ ሁኔታም ወረራ ለመፈፀም የተለያዩ ሙከራዎችን ቢያደርግም እንዳልተሳካለት እና ለሌላ ጥቃት እየተዘጋጀ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ ይህ ኃይል እስካልከሰመ ድርስ አርፎ የሚተኛ አይደለም ያሉት ዳይሬክተሩ እሰካሁንም ሽንፈቱን አምኖ ያልተቀመጠ እና ከስህተቱ የማይታረም መሆኑን እያሳየ ነዉ ብለዋል ለቴሌቪዥን ጣቢያው። ምንጭ፦ አሀዱ ቴሌቪዥን @tikvahethiopia

#NorthKorea ሰሜን ኮሪያ ዛሬ ማክሰኞ 2 ተጨማሪ የክሩዝ ሚሳዬሎችን በመተኮስ መሞከሯን የደቡብ ኮሪያ ጦር አስታወቀ፡፡ ይህ በአዲሱ የአውሮፓውያን ዓመት አምስተኛው የሚሳዬል ሙከራ መሆኑም ተመል
#NorthKorea ሰሜን ኮሪያ ዛሬ ማክሰኞ 2 ተጨማሪ የክሩዝ ሚሳዬሎችን በመተኮስ መሞከሯን የደቡብ ኮሪያ ጦር አስታወቀ፡፡ ይህ በአዲሱ የአውሮፓውያን ዓመት አምስተኛው የሚሳዬል ሙከራ መሆኑም ተመልክቷል፡፡ የደቡብ ኮሪያ ጦር ዝርዝሩ እየተጠና መሆኑን አስታውቋል፡፡ ሰሜን ኮሪያ በአዲሱ ዓመት ውስጥ ብቻ ባደረገቸው 5 ሙከራዎች 8 ሚሳዬሎችን መተኮሷ ተገልጿል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1950 የተካሄደውን የኮሪያ ጦርነት ስምምንት መሠረት አሜሪካ በደቡብ ኮሪያ ወደ 28ሺ ወታደሮችን አስፍራለች፡፡ አሜሪካ ፤ የሰሜን ኮሪያ ሚሳኤል ሙከራዎቹን በማወገዝ አሳሳቢ መሆናቸውንም እየገለጸች ሲሆን በተከታታይ የእንነጋገር ጥሪዋን ስታሰማ መቆየቷን የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ዘግቧል። @tikvahethiopia

#ETHIOPIA የዓለም ጤና ድርጅት ስራ አስፈፃሚ ቦርድ በድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ንግግር እንዳያደርጉ መከልከሉ ተቀባይነት እንደሌለው ኢትዮጵያ ገልፃለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፤ ኢትዮጵያ የድር
#ETHIOPIA የዓለም ጤና ድርጅት ስራ አስፈፃሚ ቦርድ በድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ንግግር እንዳያደርጉ መከልከሉ ተቀባይነት እንደሌለው ኢትዮጵያ ገልፃለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፤ ኢትዮጵያ የድርጅቱን ዋና ዳይሬክተርን የስነ ምግባር ጥሰት በተመለከተ ቦርዱ እንዲመረምር በይፋ ቅሬታ ማቅረቧን አስታውሷል። ምንም እንኳ ቀደም ሲል የአፍሪካ እና ሌሎች ወዳጅ ሀገራትን በማስተባበር ዋና ዳይሬክተሩን እጩ አድርጋ በማቅረብ እና የወዳጅ አፍሪካ ሀገራትን በማንቀሳቀስ ብታስመርጣቸውም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል በህወሓት አማካኝነት ጦርነት ሲነሳ ግን የግለሰቡ ትክክለኛ ማንነት መገለጡንና ከሀገራቸው ይልቅ ህወሓትን መምረጣቸውን አመልክቷል። የተመረጡበትን ሀላፊነት የቡድኑን ፕሮፓጋንዳ ለማሠራጨት እንደተጠቀሙበት ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። ይህ ድርጊት ከድርጅቱ የስምግባር መርህ ጋር የሚጣረስ ድርጊትን ስራ አስፈፃሚ ቦርዱ እንዲመረምር ኢትዮጵያ በይፋ ብታመለክትም ቦርድ ጥያቄውን ተቀብሎ ከመመልከት ይልቅ ይብስኑ የኢትዮጵያ ተወካይ ይህን ጉዳይ እንዳያብራሩ መከልከሉን ገልጿል። በአባል ሀገር ላይ እንዲህ ዓይነቱን ድርጊት መፈፀሙ ተቀባይነት እንደሌለው ሚኒስቴሩ አስታውቋል። ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ ኤፍቢሲ @tikvhaethiopia

#BurkinaFaso የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) የቡርኪናፋሶ ጦር በአስቸኳይ ያሰራቸውን የሀገሪቱን ፕሬዜዳንት እንዲፈታ በጥብቅ አሳስቧል። በቡርኪናፋሶ የተደረገውን መፈንቅለ መንግስት
#BurkinaFaso የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) የቡርኪናፋሶ ጦር በአስቸኳይ ያሰራቸውን የሀገሪቱን ፕሬዜዳንት እንዲፈታ በጥብቅ አሳስቧል። በቡርኪናፋሶ የተደረገውን መፈንቅለ መንግስት የአፍሪካ ህብረት ፣ ECOWAS እና አሜሪካ አውግዘዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ፕሬዜዳንት ላይ የመፈንቅለ መንግስት መደረጉን ህብረቱ እንደሚያወግዝ ገልፀዋል። ECOWAS በተመሳሳይ መፈንቅለ መንግስቱን በጥብቅ አውግዟል። አሜሪካ በበኩሏ በቡርኪናፋሶ ያለው ሁኔታ እንደሚያሳስባት ገልፃ በአስቸኳይ የሲቪል አስተዳደር ወደቦታው እንዲመለስ አሳስባለች። ፕሬዜዳንት ሮች ካቦሬ በወታደሮች እንደታሰሩ ናቸው። @tikvahethiopia

#Ethiopia #Kenya #Egypt ከቀናት በፊት እዚህ ኢትዮጵያ የነበሩት የአሜሪካው ባለስልጣን ኬንያ ሄደው ከፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ተወያይተዋል። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ
+1
#Ethiopia #Kenya #Egypt ከቀናት በፊት እዚህ ኢትዮጵያ የነበሩት የአሜሪካው ባለስልጣን ኬንያ ሄደው ከፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ተወያይተዋል። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ዴቪድ ሳተርፊልድ ከኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር በናይሮቢ ባደረጉት ውይይት ሁለቱም አካላት በኢትዮጵያ የሚታየዉ ጦርነት እንዲያበቃ ጥረታቸዉን እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል። ሳተርፊልድ ፤ ፕሬዝዳንት ኬንያታ በኢትዮጵያ መንግስት እና በTPLF መካከል ያለውን ግጭት ለማስቆም ላደረጉት ቁርጠኝነት አመስግነዋል። ሳተርፊልድ ለኬንያዉ ፕሬዚዳንት "የእርስዎ ሚና (የኢትዮጵያን ግጭት ለማስቆም በመርዳት) በጣም ጠቃሚ እንደነበረ እናምናለን። ኬንያ በአፍሪቃ ቀንድ አካባቢ እየተጫወተች ያለውን ሚናም እናደንቃለን። በኢትዮጵያ የእናንተን እርዳታ እና ድጋፍ እንጠይቃለን። በዚያች አገር የሰራችሁት ሥራ እንዲባክን አንፈልግም" ብለዋቸል። ኬንያታ በበኩላቸዉ ኬንያና ኢትዮጵያ ጥሩ አጋር መሆናቸውን ጠቁመው በሀገሪቱ ያለው የውስጥ ግጭት የተፈጠረውን እድገት የሚሸረሽር በመሆኑ እንዲቀጥል መፍቀድ እንደሌለበት ጠቁመዋል። "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለኛ ጠቃሚና አስፈላጊ ነች። ለዚህም ነው ግጭቱ እልባት እንዲያገኝ የምንችለውን ሁሉ ለማድረግ ቁርጠኛ አቋም የያዝነው" ብለዋል። ከኢትዮጵያ ግጭት በተጨማሪ ፕሬዝዳንት ኬንያታ እና ሳተርፊልድ በሱዳንና በሶማሊያ ስላለው የሰላምና የፀጥታ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል። በሌላ መረጃ፦ ዴቪድ ሳተርፊልድ ዛሬ ግብፅ የገቡ ሲሆን የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ እንደተቀበሏቸው የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል። በምን ጉዳይ እንደተወያዩ የተገለፀ ነገር የለም። ምንጭ፦ የኬንያ ፕሬዜዳንት ፅ/ቤት (ዶቼ ቨለ) እና የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር @tikvahethiopia

#ተጠናቋል የእንጦጦ ፖርክ የመኪና ማቆሚያ የግንባታ ስራ መጠናቀቁ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በቅርቡ ስራ የጀመረው የእንጦጦ ፖርክ የመኪና ማቆሚያ የግንባታ ስራ ሙሉ በሙሉ
+2
#ተጠናቋል የእንጦጦ ፖርክ የመኪና ማቆሚያ የግንባታ ስራ መጠናቀቁ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በቅርቡ ስራ የጀመረው የእንጦጦ ፖርክ የመኪና ማቆሚያ የግንባታ ስራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆኑን አሳውቋል። ይህ ኘሮጀክት በአጠቃላይ ሶስት የመኪና ማቆሚያ ግንባታዎችን የያዘ ሲሆን ሁለቱ በእንጦጦ ፖርክ ዋና መግቢያ በር እንዱሁም ሶስተኛው በሱሉልታ መግቢያ በኩል የተገነቡ ናቸው፡፡ እነዚህ የመኪና ማቆሚያዎች 14,063 ሜትር ስኩዌር ስፋት ያላቸው ሲሆን በአንድ ጊዜ 450 መኪኖችን ማቆም የሚችሉ ናቸው፡፡ @tikvahethiopia

#DrTedrosAdhanom ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም ጤና ድርጅትን እንዲመሩ በድጋሚ እጩ ሆነው ቀረቡ፡፡ ዶ/ር ቴድሮስ በራሱ በዓለም ጤና ድርጅት ቦርድ ነው በድጋሚ እጩ ሆነው የቀረቡት፡፡ ይህ
#DrTedrosAdhanom ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም ጤና ድርጅትን እንዲመሩ በድጋሚ እጩ ሆነው ቀረቡ፡፡ ዶ/ር ቴድሮስ በራሱ በዓለም ጤና ድርጅት ቦርድ ነው በድጋሚ እጩ ሆነው የቀረቡት፡፡ ይህም በመጪው ወርሃ ግንቦት 2022 ለሚካሄደው የዋና ዳይሬከተርነት ምርጫ በብቸኛነት የቀረቡ እጩ ያደርጋቸዋል። ዶ/ር ቴድሮስ ምርጫውን አሸንፈው ድርጅቱን በድጋሚ በዋና ዳይሬክተርነት የመምራታቸው እድል ሰፊ ስለመሆኑ ይነገራል፡፡ #AlAIN @tikvahethiopia

#ይቅርታ " ባቀድነው ልክ ውጤታማ ባለመሆናችን የ ኢትዮጵያ ህዝብን ይቅርታ እጠይቃለሁ " - የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአፍሪካ ዋ
+1
#ይቅርታ " ባቀድነው ልክ ውጤታማ ባለመሆናችን የ ኢትዮጵያ ህዝብን ይቅርታ እጠይቃለሁ " - የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአፍሪካ ዋንጫው ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ ጠየቀ። ዛሬ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን የኢትዮጵያን የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ቆይታ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የፌዴሬሽኑ ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን " ባቀድነው ልክ ውጤታማ ባለመሆናችን የ ኢትዮጵያ ህዝብን ይቅርታ እጠይቃለሁ " ብለዋል። አክለውም ፥ " የአሰልጣኙን ኮንትራት እናከብራለን ፣ እስከ ኮንትራቱ መጨረሻ አብሮን ይቀጥላል ብለን እናምናለን " ሲሉ ተናግረዋል ። አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በበኩላቸው ፥ " ስንሄድም ስንመጣም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው አልተደበቅንም ፣ ብሄራዊ ቡድኑ ኩራት ነው ፣ በ ማህበራዊ ገፆች እንደተመለከትነው ድንጋይ ይዞ የተቀበለን ሰው የለም " ብለዋል። " እስከ መስከረም 30/2015 ከ ፌዴሬሽኑ ጋር ኮንትራት አለኝ " ያሉት አሰልጣኙ እስከዛው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ነኝ " ሲሉ ተናግረዋል። ብሄራዊ ቡድኑ ከ8 ዓመታት በኃላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ቢመለስም ምድቡን ማለፍ ሳይችል በመቅረቱ የመጀመሪያ ተሰናባች ሆኖ ከቀናት በፊት ወደ ሀገሩ መመለሱ ይታወቃል። More : @tikvahethsport

" በርታ " የብሄረሰቡን መጠሪያ ለምን መቀየር አስፈለገ ? ዛሬ በተካሄደ የበርታ ብሔረሰብ ም/ቤት ጉባኤ የብሔረሰቡ መጠሪያ ስያሜ "ቤኒሻንጉል" ተብሎ አንዲጠራ ወሳኔ አሳልፏል። በቤ/ጉ ክልል ኮሚኒ
" በርታ " የብሄረሰቡን መጠሪያ ለምን መቀየር አስፈለገ ? ዛሬ በተካሄደ የበርታ ብሔረሰብ ም/ቤት ጉባኤ የብሔረሰቡ መጠሪያ ስያሜ "ቤኒሻንጉል" ተብሎ አንዲጠራ ወሳኔ አሳልፏል። በቤ/ጉ ክልል ኮሚኒኬሽን ገፅ እንደሰፈረው ዛሬ እንዲቀየር የተደረገው መጠሪያ ብሔረሰቡ ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ በ ' ህወሃት ' አስገዳጅነት ይጠራበት እንደነበር ይገልጻል። ዛሬ ግን የብሔረሰቡ ስያሜ "ቤኒሻንጉል" ተብሎ እንዲጠራ ተወስኗል። በዚሁ መረጃ ላይ በዛሬው ጉበዔ ለምክር ቤቱ " የበርታ ብሔረሰብ ስያሜ ለመቀየር የቀረበ የህዝብ ዉሳኔ መነሻና ሳይንሳዊ ትንታኔ " በሚል ርዕሰ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን የተጠና ጥናት ቀርቦ ዉይይት ተደርጎበታል። ከዉይይት በኃላ ምክር ቤቱ የብሔረሰቡ መጠሪያ ስያሜ "ቤኒሻንጉል" ተብሎ እንዲጠራ ወሳኔ አሳልፏል። @tikvahethiopia

#Update በደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ካምፓስ እንዲሁም የሐኪም ግዛው ማስተማሪያ ሆስፒታል ምረቃ ፕሮግራም ተካሂዷል። በምርቃት ስነስርአቱ የአማራ ክልል
+3
#Update በደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ካምፓስ እንዲሁም የሐኪም ግዛው ማስተማሪያ ሆስፒታል ምረቃ ፕሮግራም ተካሂዷል። በምርቃት ስነስርአቱ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶክተር ይልቃል ከፋለን ጨምሮ የክልልና የፌደራል ከፍተኛ ስራ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር። ፎቶ : የደብረ ብርሃን ኮሚኒኬሽን @tikvahethiopia

#Benishangul በዛሬው ዕለት የበርታ ብሔረሰብ ምክር ቤት 8ኛ መደበኛ ጉበዔውን በኩርሙክ ወረዳ አካሂዶ ነበር። በዚህ ጉባዔው የብሔረሰቡ መጠሪያ ሥያሜ 👉ቤኒሻንጉል እንዲሆን መወሰኑ ተሰምቷል።
#Benishangul በዛሬው ዕለት የበርታ ብሔረሰብ ምክር ቤት 8ኛ መደበኛ ጉበዔውን በኩርሙክ ወረዳ አካሂዶ ነበር። በዚህ ጉባዔው የብሔረሰቡ መጠሪያ ሥያሜ 👉ቤኒሻንጉል እንዲሆን መወሰኑ ተሰምቷል። ሥያሜውን ለመቀየር የተጠናዉ ጥናት በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ቀርቦ ውይይት እንደተደረገበት ተገልጿል። በጥናቱ ዙሪያ ከተደረገው ሰፊ ዉይይት በኃላ ምክር ቤቱ የብሔረሰቡን መጠሪያ ሥያሜ ቤኒሻንጉል እንዲሆን ወስኗል ነው የተባለው። @tikvahethiopia

#ProfessorAsratWeldeyes በደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ " ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ " በዛሬው ዕለት ይመረቃል፡፡ የምረቃ ስነስርዓቱ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተ
+2
#ProfessorAsratWeldeyes በደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ " ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ " በዛሬው ዕለት ይመረቃል፡፡ የምረቃ ስነስርዓቱ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት እንደሚካሄድ ከዩኒቨርስቲው የተገኘው መረጃ ይመለክታል፡፡ Credit : የደብረ ብርሃን ኮሚኒኬሽን @tikvahethiopia

#AliBira #NuhoGobena የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አንጋፋውን የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራን በመኖሪያ ቤታቸው ተገኝተው መጠየቃቸ
+2
#AliBira #NuhoGobena የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አንጋፋውን የኢትዮጵያ የሙዚቃ ሰው ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራን በመኖሪያ ቤታቸው ተገኝተው መጠየቃቸውን ገልፀዋል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፣ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የጉሙሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ህክምና ሲከታተሉበት በነበረው ሆስፒታል ተገኝተው መጠየቃቸው ይታወሳል። በሌላ መረጃ በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የኦፌኮ ከፍተኛ አመራሮቹ አቶ ጃዋር መሐመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ እንዲሁም ሀምዛ ቦረና በአዳማ ተገኝተው በቅርቡ ከዚህ ዓለም ሞት የተለዩት አርቲስት ኑሆ ጎበና ቤተሰቦችን አጽናንተዋል። በተጨማሪ በክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ መኖሪያ ቤት በመገኘት አርቲስቱን ጠይቀዋል። Photo Credit : AA Mayor Adanech Abiebie & Meseret Daba @tikvahethiopia