en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
" ... የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ' ሸኔ ' ነው የገደለው ብሎ መግለጫ አውጥቷል ? እኔ አላውቅም ፤ እኔ እስከዛሬ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን መግለጫ አላወጣም፤ ከተሰጠም ስህተት ነው " - ግርማ ገላን ትላንት የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን መግለጫ ሰጥቶ ነበር። መግለጫው ትኩረቱ በታህሳስ ወር ላይ በምስራቅ ሸዋ ዞን በውሰት እና ፈንታሌ ወረዳዎች ስለተገደሉ ሰዎች ነው። ይህ መግለጫ የተሰጠው ኢሰመኮ መግለጫውን ባወጣ ከአንድ ቀን በኃላ ነው። የኦሮሚያ ፖሊስ በውሰት እና ፈንታሌ ወረዳዎች 14 ሰዎችን ጨምሮ 11 የፖሊስ አባላት ተገድለዋል ብሏል። ም/ኮሚሽነር እና የወንጀል ምርመራና ፍትህ ማስተባበሪያ ኃላፊ ግርማ ገላን ፥ "ማህበራዊ ሚዲያ ላይ እንደሚወራው ፖሊስ መመሪያ ሰጥቶ ሰዎችን ሊያስገድል አይችልም ህጉም የፓሊስ ስነምግባር አይፈቅድም። ተልዕኮ የተሰጠው የፖሊስ አባል ድርጊቱን ፈፅሞ ከሆነ በህግ ይጠየቃል " ሲሉ ተናግረዋል። ኢሰመኮ ያወጣውን ሪፖርት በተመለከተ ምክትል ኮሚሽነር ገርማ ፥ " ኢሰመኮ በራሱ መንገድ ማጣራት አድርጓል፤ መግለጫም አውጥቷል፣ ኢሰመኮ ካወጣው መግለጫ አኳያ ትንሽ ከኛ ተልዕኮ ጋር አብሮ አይሄድም፤ በግልፅ መታወቅ ያለበት። እኛ መርማሪ ፖሊሶች ነን በምርመራ መርህ አንድ ሰው በወንጀል ተጠርጥሯል ተብሎ ጥቆማ ፖሊስ ሲያገኝ ያን ያገኘውን ጥቆማ አጣርቶ በህግ ማስጠየቅ ሲችል ብቻ ነው በዛ ጉዳይ ማብራሪያ መስጠት የሚችለው " ብለዋል። አክለው ፥ " መግለጫው እጅግ የሚያበረታታ መቀጠልም ያለበት ፣ ከወገናዊነትም የፀዳ የህዝብ ወገንተኝነትን ማዕከል ባደረገ መልኩ ነው ተቋሙ መግለጫ ያወጣው በተለይ እንደክልላችን ስለዚህ ተቋሙ ያወጣው መግለጫ እንደውም እኛ ምንድነው በአካባቢው ላይ ያለው የሚለውን በደንብ እንድናይ አድርጎናል " ሲሉ ገልፀዋል። የኦሮሚያ ፖሊስ 14ቱ ሰዎች የከረዩ አባገዳዎችን ሸኔ ነው የገደለው የሚል መረጃ እንዳላወጣ ገልጾ ከወጣም ስህተት ነው ብሏል። ምክትል ኮሚሽነሩ ግርማ ፥ " የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ' ሸኔ ' ነው የገደለው ብሎ መግለጫ አውጥቷል እኔ አላውቅም ፤ እኔ እስከዛሬ እስከዚህች ሰዓት ድረስ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን መግለጫ አላወጣም፤ ከተሰጠም ስህተት ነው። ምክንያቱም የሆነ ነገር ሊባል ይችላል ነገር ግን ካጣራ እና ትንሽ እውነት የሚመስል ነገር ሲኖር ነው በአግባቡ ደረጃ በደረጃ መረጃ እየሰጠ መሄድ ያለበት " ነው ያሉት። የክልሉ ፖሊስ ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ምርመራው ሲጠናቀቅ ለህዝብ እንደማያሳውቅ ገልጿል። የከረዩ አባገዳዎች በተገደሉበት ወቅት የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን ግድያውን 'ሸኔ' እንደፈፀመ በመግለጭ የሀዘን መግለጫ ማውጣቱ / የምስራቅ ሸዋ ዞን አስተዳደር በተመሳሳይ ግድያውን ሸኔ እንደፈፀመ በመግለፅ መረጃ ማውጣቱ ፤ የተለያዩ የመንግስትና የግል ሚዲያዎች እንዲሁም አክቲቪስቶች " የከረዩ አባገዳ በአሸባሪው ሸኔ ተገደሉ " በሚል ዘገባዎችን ማውጣታቸው አይዘነጋም። በውቅቱ በተለይም የሟች ቤተሰብ እና የአካባቢው ነዋሪዎች አባ ከድር ሀዋስን ጨምሮ 14 ሰዎች የተገደሉት በፀጥታ አስከባሪ ኃይሎች መሆኑን አሳውቀው ነበር። በተለይም ደግሞ ወ/ሮ ወርቄ ሀዋስ የአባገዳ ከድር ሀዋስ እህት ወንድማቸው ከጊዳራ ቀበሌ ማህበር ተውስደው መገደላቸውን ፤ ይዘዋቸው የሄዱት ደግሞ የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች እንደሆኑ እንዲሁም ሰዎቹ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል እና የፖሊስ ዩኒፎርም አድርገው እንደነበር ተናግረው ነበር : በዚህ አንብቡ : https://t.me/tikvahethiopia/65365 @tikvahethiopia

ሳምሶን ተክለሚካኤል እስካሁን ያለበት አልታወቀም፤ የት ነው ያለው ? ኢትዮጵያ የኬንያ ባለስልጣናትን ናይሮቢ ውስጥ መሀል መንገድ ላይ ስለታገተው ሳምሶን ተክለሚካኤል ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቃለች። በ
+3
ሳምሶን ተክለሚካኤል እስካሁን ያለበት አልታወቀም፤ የት ነው ያለው ? ኢትዮጵያ የኬንያ ባለስልጣናትን ናይሮቢ ውስጥ መሀል መንገድ ላይ ስለታገተው ሳምሶን ተክለሚካኤል ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቃለች። በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ አለም ኬንያ ለሚገኝ የሃገር ውስጥ ሚዲያ በሰጡት ቃለ ምልልስ የኬንያ የህግ አስከባሪ አካላት በንግድ ስራ ላይ የተሰማራው ሳምሶን ተክለሚካኤል የት እንዳለ እንዲሁም በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ እንዲያብራሩ መጠየቃቸውን ገልፀዋል። አምባሳደር መለስ ኢትዮጵያ የኬንያ ባለስልጣናት እና የህግ አስከባሪ አካላትን በማነጋገር ስለ ዜጋዋ ዝርዝር መረጃ እንዲሰጣት መጠየቋን አስረድተዋል። ሳምሶን በመጥፋቱ ቤተሰቦቹ አሁንም ድረስ ከፍተኛ ስቃይ ላይ እንደሆኑ የገለፁት አምባሳደሩ ክስተቱ የትውልድ ሀገሩን ኢትዮጵያንም እንደጎዳው ገልፀዋል። አምባሳደሩ፥ " በህዳር ወር የተከሰተው ክስተት ኢትዮጵያን አስደንግጧል። በኪሊሌሽዋ በጠራራ ፀሀይ፣ በህዝብ በፊትና ፖሊስ ባለበት ነው የተከሰተው፤ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሳምሶን ተክለሚካኤልን አላየንም" ብለዋል። " የኬንያ ባለስልጣናትን ቀርበን ስለ ዜጋችን ደህንነት መረጃ እንዲሰጡን ጠይቀን ምርመራዎች እስኪጠናቀቁ ድረስ እየጠበቅን ነው " ሲሉም ተናግረዋል። አምባሳደር መለስ አለም " ባለፉት 3 ወራት ቤተሰቦቹ እና ልጆቹ በጭንቀት ውስጥ ናቸው ሰፊው የኢትዮጵያ ማህበረሰብም እንዲሁ፤ ህዝባችን ከዚህ ሁኔታ እንዲወጣ እንፈልጋለን። በእኛ በኩል ዜጋችን ሳምሶን ያለበትን እስክናውቅ ድረስ አንመለስም " ሲሉ አስገንዝበዋል። ምርመራው ረዘም ያለ ጊዜ መውሰዱን የሚገልፁት አምባሳደሩ፤ " 3 ወር አጭር አይደለም፤ እኛ ጉዳዩ በእጅጉ ያሳስበናል፤ ይህንም የኤምባሲው ተልዕኮ ይጋራል" ሲሉ ገልፀዋል። ሳምሶን የት ነው ያለው ? @tikvahethiopia

#Tigray , #Mekelle📍 የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በዚህ ሳምንት 2 በረራዎችን ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ በማድረግ የህክምና ቁሳቁሶችን አድርሷል። ባለፈው ሳምንት በ5 በረራ
#Tigray , #Mekelle📍 የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በዚህ ሳምንት 2 በረራዎችን ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ በማድረግ የህክምና ቁሳቁሶችን አድርሷል። ባለፈው ሳምንት በ5 በረራዎች እጅግ አስፈላጊ የህክምና ቁሳቁሶችን ወደ ትግራይ ክልል መቐለ ማጓጓዙና ማከፋፈል መጀመሩን መግለፁ ይታወሳል። በዚህ ሳምንት ከኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና ከቀይ መስቀል የቀረቡ መድሃኒቶችና ሌሎች የህክምና አቅርቦቶችን በመያዝ 2 ተጨማሪ በረራዎች ወደ ትግራይ ክልል ተደርገዋል። በዚህ ሳምንት በቀሩት ቀናት እና በሚቀጥሉት ሳምንታት ተመሳሳይ በረራዎች እንደሚደረጉ እና ይህም ቀጣይነት ያለው እርዳታ እንደሚሆን የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታውቋል። የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ላለፉት ወራት የህክምና አቅርቦት ማድረግ እንዳልቻለ ገልፆ አሁን እየተደረጉ ያሉት እጅግ በጣም አስቸኳይ ለሰዎች ህይወት አድን የሚሆኑ አቅርቦቶች ናቸው ብሏል። ከዚህ በተሻለ በርካታ የህክምና ቁሳቁሶች እና መድሃኒቶችን ለማድረስ ከአየር ላይ በረራ በተጨማሪ በየብስ ለማጓጓዝ መታሰቡን ይህን ተግባራዊ ለማድረግም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል። የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) ከትግራይ ክልል በተጨማሪ በአፋር ክልል እና አማራ ክልል ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ገልጿል። ፎቶ ፦ ፋይል @tikvahethiopia

#GamoZone በጋሞ ዞን የሰዓት እላፊ ማሻሻያ ተደረገበት። የጋሞ ዞን ኮማንድ ፖስት #ለተሽከርካሪዎች የሠዓት ማሻሻያ ማድረጉን ትላንት ምሽት አሳውቋል። ኮማንድ ፖስቱ የዞኑ ሠላም እንዲጠበቅ ለማድ
#GamoZone በጋሞ ዞን የሰዓት እላፊ ማሻሻያ ተደረገበት። የጋሞ ዞን ኮማንድ ፖስት #ለተሽከርካሪዎች የሠዓት ማሻሻያ ማድረጉን ትላንት ምሽት አሳውቋል። ኮማንድ ፖስቱ የዞኑ ሠላም እንዲጠበቅ ለማድረግ በቂ የሆነ የሕዝባዊ ሠራዊት በመሠልጠኑ እንዲሁም የህብረተሰቡ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዳይገደብ የሠዓት ማሻሻያ ማድረጉ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልጿል። በዚሁ መሠረት፦ - ለባለሁለት እግር ሞተር ሳይክል እስከ ምሽቱ 3:00 ሠዓት - ለባለሦስት እግር ባጃጅ እስከ ምሽቱ 4:00 ሠዓት ማሻሻያ ማድረጉን የዞኑ ኮማንድ ፖስት ገልጿል። @tikvahethiopia

#Borana የኢትዮጵያጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከፍተኛ ባለስጣናት በቦረና ዞን ያቤሎ ወረዳ ጉብኝት እያደረጉ ነው። የጠ/ሚ ፅ/ቤት ጉብኝቱ ፥ " በድርቅ የተጎዱ ማህበረሰቦችን ተ
+2
#Borana የኢትዮጵያጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከፍተኛ ባለስጣናት በቦረና ዞን ያቤሎ ወረዳ ጉብኝት እያደረጉ ነው። የጠ/ሚ ፅ/ቤት ጉብኝቱ ፥ " በድርቅ የተጎዱ ማህበረሰቦችን ተግዳሮቶች በጥልቀት ለመገምገም " እንደሆነው ገልጿል። ፅ/ቤቱ የዝናብ ውሀ እጥረት መከሰቱ የእንስሳት መኖ እጥረት እና የውሃ አቅርቦት ውስንነትን ጨምሮ በርካታ ፈታኝ ሁኔታዎችን ማስከተሉን አሳውቋል። በሌላ መረጃ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ያቤሎ ኢፋ ቦሩ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤትን መጎብኘታቸው ተገልጿል። @tikvahethiopia

#Update 40ኛው የአፍሪካ ሕብረት የአስፈጻሚዎች ምክር ቤት ጉባኤ ጀምሯል። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የሚሳተፉበት 40ኛው የአፍሪካ ሕብረት
#Update 40ኛው የአፍሪካ ሕብረት የአስፈጻሚዎች ምክር ቤት ጉባኤ ጀምሯል። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የሚሳተፉበት 40ኛው የአፍሪካ ሕብረት የአስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ “የአፍሪካ አህጉርን የስርዓተ ምግብ አቅም መገንባት፣ የሰው ሃብት ልማት፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማትን ማፋጠን” በሚል መሪ ቃል ይመክራል። የአስፈጻሚ ም/ቤቱ የፊታችን ቅዳሜና እሁድ በሚካሔደው 35ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ላይ በሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይም ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ሕብረት የአስፈጻሚ ምክር ቤት በሕብረቱ አባል አገራት የጋራ ፍላጎት የሆኑ የፖሊሲ ጉዳዮችን የሚያስተባብርና ውሳኔ የሚሰጥ ነው። ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር @tikvahethiopia

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፦ " ... በከረዩ የሚችሌ ገዳ አባላት ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸሙና ያስፈጸሙ ሰዎችን እንዲሁም በፖሊስ አባላት ላይ የግድያና የአካል ጉዳት ማድረስ ወን
+1
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፦ " ... በከረዩ የሚችሌ ገዳ አባላት ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸሙና ያስፈጸሙ ሰዎችን እንዲሁም በፖሊስ አባላት ላይ የግድያና የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል የፈጸሙትን ሰዎች በሕግ ተጠያቂነት ለማረጋገጥ ተገቢው የወንጀል ምርመራ በአፋጣኝ ሊደረግ እንደሚገባ ኮሚሽኑ ምክረ ሃሳብ አቅርቦ ነበር። ሾለ ጠቅላላው የነገሩ ሁኔታ እውነቱን በመግለጽ ፍትሕ በማረጋገጥና የተጎዱ ሰዎችን በመካስ ላይ የተመሰረተ አስፈላጊ ተግባራትን በማከናወን የማኅበረሰቡን ሰላም እና ደኅንነት áŠĽáŠ•á‹˛áˆ˜áˆˆáˆľ ማድረግ ይጠበቃል " @tikvahethiopia

ከኢሰመኮ ሪፖርት ፦ ህዳር 21 ቀን 2014 ዓ.ም ለስራ ወደፈንታሌ ወረዳ የተለያዩ ቀበሌዎች ሄደው ከቀኑ 8፡00 ሰዓት አከባቢ ወደመተሃራ በመመለስ ላይ የነበሩ የፀጥታ አባላት ላይ በወረዳው ሀሮ ቀ
ከኢሰመኮ ሪፖርት ፦ ህዳር 21 ቀን 2014 ዓ.ም ለሾል ወደፈንታሌ ወረዳ የተለያዩ ቀበሌዎች ሄደው ከቀኑ 8፡00 ሰዓት አከባቢ ወደመተሃራ በመመለስ ላይ የነበሩ የፀጥታ አባላት ላይ በወረዳው ሀሮ ቀርሳ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኢፍቱ በተባለ ቦታ ላይ ማንነታቸው ባልታወቀ የታጠቁ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት የ11 ፖሊስ አባላት ሕይወት ማለፉና ቢያንስ 17 ሌሎች የፖሊስ አባላት መቁሳለቸው ታውቋል። ይህንን ተከትሎ ህዳር 22 ቀን 2014 በግምት ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጥቃቱን ያደረሱ ተጠርጣሪዎችን ለመፈለግ በፈንታሌ ወረዳ ጡጢቲ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዴዲቲ ካራ ከሚባል የከረዩ ሚችሌ አባገዳዎችና የጅላ አባላት የመኖሪያ ሰፈር የደረሱ የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች 39 የጅላ አባላትን በቁጥጥር ሾር አውለዋል። በእነዚህ ፀጥታ አባላት ቁጥጥር ሾር ከዋሉ á‹¨áŠ¨áˆ¨á‹Š የሚችሌ ገዳ አባላት መካከል 16 áˆ°á‹Žá‰˝ ወደ ጨቢ አኖሌ ጫካ ተወስደው14ቱ ሰዎች በጥይት ተመተው ተገድለዋል። በዚህም፦ -የከረዩ አባገዳ #ከዲር_ሀዋስ -ኦዳ ጫርጨር -ቦሩ ፈንታሌ -ፈንታሌ ቦሩ -ቁምቢ ጉራቻ (ቃሉ ናቸው) -ቦሩ ፈንታሌ -ቡላ ፈንታሌ -ሮባ ሀዋስ -ቦሩ ጎዳና -ጂሎ ደዲኦ -ቡላ ፈንታሌ -ቡልጋ ቦረኡ -ጂሎ ዲዶ እና ቦሩ ጂሎን ጨምሮ 14 የከረዩ የሚችሌ ገዳ የጅላ አባላት መሬት ላይ እንዲተኙ ተደርገው በጥይት ተመተው ተገድለዋል። የሟቾችን አስከሬን ለማንሳት ግድያው ወደ ተፈጸመበት ቦታ የሄዱ ሰዎች በቦታው በነበሩ ፖሊሶች እንዳያነሱ በመከልከላቸው ፤ አስከሬኖቹ ለበርካታ ሰዓታት ሳይነሱ መቆየታቸውንና የፈነዱና በከፊል በዱር እንስሳ የተበሉ እንደነበሩ አስከሬኖቹን ያነሱና የቀበሩ ሰዎች ገልጸዋል። አስከሬኖቹ ከጀርባ በኩል ወገባቸውና ጭንቅላታቸው ላይ በጥይት ተመተው መገደላቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች ነበሩባቸው። @tikvahethiopia

#Oromia, #WestGuji 📍 በምዕራብ ጉጂ ዞን ገላና ወረዳ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በሸኔ በመከበቡ ውሎ መግባት አስቸጋሪ መሆኑን አመለከቱ። ነዋሪዎች የታጣቂ ቡዱን በርካታ የወረዳውን ቀበሌዎችን መቆጣጠሩን በመግለፅ ሰዎች እንደሚገደሉ፣ ንብረትም እንደሚወድም እና እንደሚዘረፍ ገልፀዋል። ወረዳው ነዋሪ ፦ " ያለንበት ሁኔታ አሰቃቂ እና ተስፋ የሌለው ነው። በአሁን ጊዜ አስከፊ ሁኔታ ውስጥ ነን። ታጣቂዎች ቤት አይሉ ማህበረሰቡ የሚገለገልባቸው የመንግስት ተቋማንት እያቃጠሉ እና እያወደሙ ነው።  በየቀኑ የ4 እና 5 ሰዎች መገደል ይሰማል። አርሶ አደር በከብቶቹ መሃል ይገደላል። ተሽከርካሪ እንደልብ አይንቀሳቀስም ይዘረፋል። ለማን አቤት እንደምንል አናውቅም እያለቅን እየተሰቃየን ነው። "  ሌላ ነዋሪ ፦ " ከወረዳው ከታጣቂዎች ንፁህ የሚባለው ሁለት ቀበሌ ብቻ ናቸው። እዚህ ደረጃ ከደረሰ ቆይቷል። የወረዳ የፀጥታ ኃላፊን ጨምሮ ልዩ ኃይሎች፣ ሚሊሻዎች፣ የቀበሌ ሊቀመንበሮች በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አልቀዋል " የገላና ወረዳ አስተዳደሪ አቶ ሞርከታ ሴሎ ፦ " እነዚህ ታጣቂዎች የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው። እንቅስቃሴያቸውን መግታት አልቻልንም ስለዚህ ችግሩ በጣም እየከፋ በመምጣቱ እኛም ለመንግስት አካል አመልክተናል። በተለይ የወታደር ኃይል ገብቶ ይህን ኃይል እንዲመታው እና ህብረተሰቡ በነፃነት ወጥቶ እንዲገባ የሚደረግበትን ሁኔታ እየፈጠርን ነው። ሁኔታው ትንሽ ከበድ ይላል። እውነቱን ለመናገር የወረዳው ብዙ ቀበሌዎች ላይ ገብተዋል። የመከላከያ ሰራዊት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይገባሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ከሚመለከተው አካል ጋር እየተነጋገርን ነው። " ያንብቡ : https://telegra.ph/Gelana-Woreda-02-01

#UN የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UNOCHA) ፦ • በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለው ግጭት በህብረተሰቡ ህይወት እና ኑሮ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እያሳደረ እና የሰብአዊ ፍላጎቶችን እያሳደገው ይገኛል። • በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ፣ ምዕራብ እና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች ያለው ያልተረጋጋ የጸጥታ ችግር (የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አጎራባች አካባቢዎችን ጨምሮ) በርካቶችን ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው። • በኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች ከ250,000 በላይ ሰዎች የእህል ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። እስካሁን ያለው ምላሽ በቂ አይደለም፤ ሽፋኑም ውስን ነው። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የ2ኛው ዘር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ነገ ይጀመራል። በፀጥታ ምክንያት በመጀመሪያው ዙር ፈተና መውሰድ ያልቻሉ ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ፈተናቸውን መውሰድ ይጀምራሉ። #AmharaRegio
+1
#Update የ2ኛው ዘር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ነገ ይጀመራል። በፀጥታ ምክንያት በመጀመሪያው ዙር ፈተና መውሰድ ያልቻሉ ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ፈተናቸውን መውሰድ ይጀምራሉ። #AmharaRegionEB • 37 ሺህ 55 ተማሪዎችን ለፈተና ይቀመጣሉ። • ፈተናው በሰሜንና ደቡብ ወሎ ዞኖች፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደርና በደሴ ከተማ አስተዳደር ሙሉ በሙሉ ይሰጣል። • በዋግ ኽምራ ከአበርገሌ ወረዳ በስተቀር በሁሉም ወረዳዎች፣ በሰሜን ሸዋ ዞን 3 ወረዳዎች እና በሰሜን ጎንደር ዞን በአንድ ጣቢያ ፈተናው ይሰጣል። • በኦሮሚያ ክልል ከምስራቅ እና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች ተፈናቅለው ለመጡ 220 የክልሉ ተወላጅ ተማሪዎች በቡሬ ከተማ በተዘጋጀ የፈተና ጣቢያ ፈተናው ይሰጣል። • ለብሔራዊ ፈተና ከሚቀመጡት ተማሪዎች መካከል 34 ሺህ 970 የሚሆኑት መደበኛ ተማሪዎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ የግል ተፈታኞች ናቸው። • ፈተናው በአጠቃላይ በ129 ጣቢያዎች ይሰጣል። • ለፈተናው የሚያስፈልጉ ቁሶችና የመፈተኛ ወረቀቶች ወደተዘጋጁ የመፈተኛ ጣቢያዎች ተጓጉዘው አስፈላጊው ጥበቃ እየተደረገ ነው። #OromiaRegionEB • በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ አራት ዞኖች በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይካሄድ የቀረው የ2013 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል። • በቄሌም ወለጋ፣ ምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋና ምዕራብ ሸዋ ዞኖች በ17 ወረዳዎች 55 ትምህርት ቤቶች ከ21 ሺ በላይ ተማሪዎች ከዚህ ቀደም የተሰጠውን ፈተና በጸጥታ ምክንያት አልወሰዱም። • ፈተና ተፈትነው ውጤት በመጠባበቅ ላይ ላሉና እስካሁን በትዕግሥት ፈተናውን ለመውሰድ የተጠባበቁ ተማሪዎች ምስጋና ቀርቧል። • በሁለተኛው ዙር የተፈታኞች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ ውጤት ለመግለጽ ብዙ እንደማይቆይ ተገልጿል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ጡረታ እንደሚወጡ ማሳወቃቸውን ተከትሎ አሜሪካ በአዲስ አበባ ለሚገኘው ኤምባሲ አዲስ ሰው በተወካይነት በኃላፊነት ቦታ ላይ መድባለች። አሜሪካ
#NewsAlert በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ጡረታ እንደሚወጡ ማሳወቃቸውን ተከትሎ አሜሪካ በአዲስ አበባ ለሚገኘው ኤምባሲ አዲስ ሰው በተወካይነት በኃላፊነት ቦታ ላይ መድባለች። አሜሪካ በአዲስ አበባ ላለው ኤምባሲዋ ትሬሲ አን ጃኮብሰንን ነው በጊዜያዊነት በኃላፊነት ቦታ ላይ ያስቀመጠችው። አሜሪካዊቷ ዲፕሎማት ትሬሲ አን ጃኮብሰን በቱርክሜኒስታን፣ ታጂኪስታንና ኮሶቮ የአሜሪካ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል፤ በተጨማሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለዓለም አቀፍ ድርጅት ጉዳዮች ተጠባባቂ ረዳት ፀሀፊ ሆነውም አገልግለዋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የሳንካራ ስም ዛሬም ድረስ ለምን ተደጋግሞ ይነሳል ? ቶማስ ሳንካራ ምድር ላይ ለ37 ዓመታት ብቻ የተራመደ ነገር ግን በማእበል የማይጠፋ ዱካ አሳርፎ ያለፈ የዘመናችን አፍሪካዊ አብዮተኛ ነው። በቅኝ
የሳንካራ ስም ዛሬም ድረስ ለምን ተደጋግሞ ይነሳል ? ቶማስ ሳንካራ ምድር ላይ ለ37 ዓመታት ብቻ የተራመደ ነገር ግን በማእበል የማይጠፋ ዱካ አሳርፎ ያለፈ የዘመናችን አፍሪካዊ አብዮተኛ ነው። በቅኝ ግዛት ወቅት "አፐር ቮልታ" ትባል የነበረችውን በርሀማ ደሀ ሀገሩን "ቡርኪና ፋሶ" ወደሚል ይፋዊ መጠሪያ የቀየረ፣ ተበታትነው ይኖሩ የነበሩትን ህዝቦቿን "ቡርኪናቤ" የተሰኘ የጋራ ማንነት እንዲጋሩ ያደረገ፣ ለዜጎቹ ህይወት የሚገደው ባለራዕይ መሪ ነበር። ለምዕራባውያን ኃያላን ሀገራት ጫና ፍፁም ሳይንበረከክ በታደመባቸው ዓለምአቀፋዊና አፍሪካዊ ስብሰባዎች ላይ ሁሉ ዓለምን በማናለብኝነት ሲመዘብሩ ከነበሩ ሀገራት መሪዎች ጋር ጎሮሮ ለጎሮሮ ሲተናነቅ ያሳለፈ፣ ለጥቁር ህዝቦች እና በደል ላጎበጣቸው ምንዱባን ልሳን ሆኖ ያለፈ፣ ዓለም ከማይረሳቸው አብዮተኞች መካከል ጎልቶ የሚታወስ አፍሪካዊ እንቁ ነው። "የራስን የተፈጥሮ ሀብት በራስ ጉልበት ማልማት" በሚለው የሀገሩን ህዝብ ባነቃነቀ ዘመቻ ያስመዘገባቸው አስደናቂ ድሎች አፍሪካ የራሷን ተፈጥሯዊ እድገት እንድታድግ ለማይፈልጉት ምእራባውያን ሀገራት እንደ ስጋት እንዲቆጠር አድርጎት ነበር። ድሎት የማያሸንፈው ቆፍጣናው ወጣት ወደ ፕሬዝዳንትነት ከመጣ ጊዜ አንስቶ የቅንጦት ኑሮን ኖሮ አያውቅም። ከህዝብ ጋር የዩኒፎርሙን እጅጌ ከፍ አድርጎ ስሚንቶ የሚያቦካ፣ አካፋና ዶማ አንስቶ ጥቁር ላብ በግንባሩ እስኪንዠቀዠቅ ድረስ ሰርቶ የሚያሰራ፣ ድሆች ያለ ልኬት የሚሳሱለት መሪ ነበር። አካሄዱ ባስፈራቸው ምዕራባውያን መሪዎች እና ስልጣን ባናወዛቸው የቅርብ ጓዶቹ በአጭር ቢቀጭም ተራማጅ ሀሳቦቹና ያስመዘገባቸው ተጨባጭ ለውጦች ዛሬም ድረስ ስሙ ተደጋግሞ እንዲነሳ አስችሎታል። (ከሰለሞን ዳኜ - ቶማስ ሳንካራ ጥቁሩ አብዮተኛ) @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ThomasSankar የቶማስ ሳንካራ የፍርድ ሂደት ዛሬ ይቀጥላል። የወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በተካሄደባት ቡርኪና ፋሶ ለሳምንት ተቋርጦ የነበረው የቶማስ ሳንካራ ግድያ የፍርድ ሂድት ዛሬ እንደሚ
+2
#ThomasSankar የቶማስ ሳንካራ የፍርድ ሂደት ዛሬ ይቀጥላል። የወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በተካሄደባት ቡርኪና ፋሶ ለሳምንት ተቋርጦ የነበረው የቶማስ ሳንካራ ግድያ የፍርድ ሂድት ዛሬ እንደሚቀጥል ተነግሯል። የቡርኪና ፋሶ ወታደራዊው ፍርድ ቤት ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ጄነራል ጊልበት ዲንዴሬ ነፃ መውጣቱን የሚገልጹ ወሬዎች መሰራጨታቸውን ተከትሎ ሀሰተኛ ናቸው ሲል ወድቅ በማድረግ አሁንም በማካ እስር ላይ እንደሆኑ አረጋግጧል። #Update የሳንካራ ግድያ ክስ በዋና ከተማዋ ዋጋዱጉ በሚገኘው ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዛሬ ሰኞ ይቀጥላል ተብሎ ነበር። ፍርድ ቤቱ የፍርድ ሂደቱ መታገዱን አሳውቋል። " ህገ መንግስቱ ወደ ቦታው ከተመለሰ በኋላ የፍርድ ሂደቱ ይቀጥላል ተብሏል። @tikvahethiopia

#ColonelBezabihPetros ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ህዳር 21 ቀን 1972 ዓ/ም ለንባብ ለበቃው “ታጠቅ” ለተሰኘ የሰራዊቱ ጋዜጣ በሰጡት ቃለምልልስ የተናገሩት ፦ “… እኛ ብንሞት ሌላ ሰው
#ColonelBezabihPetros ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ህዳር 21 ቀን 1972 ዓ/ም ለንባብ ለበቃው “ታጠቅ” ለተሰኘ የሰራዊቱ ጋዜጣ በሰጡት ቃለምልልስ የተናገሩት ፦ “… እኛ ብንሞት ሌላ ሰው ይተካናል ፤ መተኪያ የሌላት ኢትዮጵያ ከሞተች ግን ተተኪው ትውልድ ስለሚሞት ዋጋ አይኖረውም፡፡ የሀገርን ሉአላዊነት በአስተማማኝነት መጠበቅ ቆራጥነት እና ልበ ሙሉነት ይጠይቃል፡፡ እኛ በሕይወት ቆመን እያየን ጠላት አንዲት ስንዝር መሬት ቆርሶ መሄድ ቀርቶ በአንድ እግሩ እንኳ ሊቆምባት አይችልም፡፡ ከሀገር ወዲያ ሌላ መኖሪያ ዋሻ ስለሌለ በሃገርና በነፃነት ጉዳይ ምንም ቀልድ ሊኖር አይችልም፡፡ ” @tikvahethiopia

#ShabelleBank የሸቤሌ ባንክ ምስረታ ስነ- ስርአት ተካሔደ። የሸቤሌ ባንክ መመስረቻ ስነ ስርአት ዛሬ በጅግጅጋ ከተማ ተካሒዷል። በ2011 የሶማሊ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም " ሄሎው ካሽ " በሚ
+3
#ShabelleBank የሸቤሌ ባንክ ምስረታ ስነ- ስርአት ተካሔደ። የሸቤሌ ባንክ መመስረቻ ስነ ስርአት ዛሬ በጅግጅጋ ከተማ ተካሒዷል። በ2011 የሶማሊ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም " ሄሎው ካሽ " በሚል የገንዘብ ግብይትና ዝውውር አገልግሎት መስጠት የጀመረው ተቋሙ ለመቶ ሺህ ለሚሆኑ የአካባቢው ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሮ እያገለገለ ይገኛል። በማይክሮ ፋይናንስነት አገልግሎቱ እስከ አሁን 1 ሚሊየን 3 መቶ ሺህ በላይ የሚደርሱ ደንበኞችን እንዳሉት ይገለፃል። ተቋሙ በእስከ አሁን ሒደቱ በ43 የተለያዩ የአገልግሎት ማዕከላት ሲኖረው 500 ቋሚ ሰራተኞችን ይዞ በ 3.7 ቢሊየን የኢትዮጵያ ብር ጠቅላላ የሐብት መጠን በማስመዝገብ በ2013 አመተ ምህረት ከብሔራዊ ባንክ ባገኘው እውቅና ወደ እስላሚክ ሸቤሌ ባንክነት ማደግ ችሏል። በዛሬው የባንክ በምስረታ የሐገር ሽማግሌዎች ፣ የሶማሊ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን ፣ አምባሳደር ዶ/ር መሐሙድ ድሪር ፣ የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሐሰን መሐመድ፣ የተለያዪ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። #SRTV @tikvahethiopia