en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#USA የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን አሜሪካ " ለችግር ጊዜ " በሚል ካከመቻችው ነዳጅ በገፍ እንዲቀዳ አዘዋል። ፕሬዝደንቱ ይህን ትዕዛዝ ያስተላለፉት እየናረ የመጣውን የነዳጅ ዋጋ ለመዋጋት መሆኑ
+1
#USA የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን አሜሪካ " ለችግር ጊዜ " በሚል ካከመቻችው ነዳጅ በገፍ እንዲቀዳ አዘዋል። ፕሬዝደንቱ ይህን ትዕዛዝ ያስተላለፉት እየናረ የመጣውን የነዳጅ ዋጋ ለመዋጋት መሆኑ ተገልጿል። ባይደን እንዲወጣ ያዘዙት 180 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ በማከማቻው ታሪክ ትልቁ ነው። ዩክሬን ባለው ጦርነት ምክንያት ጣራ እየነካ የነበረው የነዳጅ ዋጋ ከባይደን ትዕዛዝ በኋላ ትንሽ ረገብ ማለቱ ተነግሯል። በዘርፉ ላይ ያሉ ሰዎች ግን አሜሪካ በየቀኑ ለመከራ ጊዜ ካስቀመጠችው ነዳጅ አንድ ሚሊዮን በርሜል ብትቀዳም ችግሩን ሙሉ በሙሉ አይቀርፈውም ብለዋል። ጆ ባይደን፤ ከማከማቻው እንዲቀዳ የታዘዘው ነዳጅ አሜሪካ "የራሷን የነዳጅ ምርት እስክታሳልጥ ድረስ" እንዲያግዝ በሚል ነው ብለዋል። ፕሬዝደንቱ ኩባንያዎች ነዳጅን ከመንግሥት መውሰድ የመጨረሻ አማራጭ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። የአረንጓዴ የኃይል ምንጭ የሚከተሉ ኩባንያዎችንም እንዲበረታቱ መክረዋል። የዩክሬን እና ሩስያ ጦርነት ባመጣው መዘዘ አሜሪካን ጨምሮ የዓለም ሃገራት የኑሮ መወደድ እያማረራቸው ነው። ባይደን፤ " ስትራቴጂክ ፔትሮሊዬም ሪዘርቭ " ከተሰኘው የችግር ቀን ገንዳ ነዳጅ ለመቅዳት የወሰንነው " ያለዕቅዳችን " ነው ብለዋል። አሜሪካ ከሳዐዲ አረቢያ ቀጥሎ ሁለተኛዋ ግዙፍ የነዳጅ አምራች ከሆነችው ሩሲያ ነዳጅ አልገዛም ካለች ወዲህ የነዳጅ እጥረት እያንገላታት ይመስላል ሲል ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የ2013 የ12ኛ ክፍል ፈተና በሁለት ዙር ተሰጥቶ ውጤት እና የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ከሆነ ቀናት ተቆጥሯል። የፈተናው ውጤት እና የመቁረጫ ነጥቡ በተለያዩ ተማሪዎች/ወላጆች፣የትምህርት ቢ
#ETHIOPIA የ2013 የ12ኛ ክፍል ፈተና በሁለት ዙር ተሰጥቶ ውጤት እና የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ከሆነ ቀናት ተቆጥሯል። የፈተናው ውጤት እና የመቁረጫ ነጥቡ በተለያዩ ተማሪዎች/ወላጆች፣የትምህርት ቢሮና መምሪዎች ዘንድ ቅሬታ ፈጥሮ ትልቅ አጀንዳ መሆኑ ይታወቃል። መንግስት ለቅሬታዎች ምላሽ እንዲሰጥም ግፊት እየተደረገ ነው። የትምህርት ሚኒስቴር በበኩሉ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ምደባ ለማድረግ ተማሪዎች ማስተካከል ያለባቸውን መረጃዎች እንዲያስተካክሉ ያስቀመጠው ቀነ ገደብ መጋቢት 19 ላይ ተጠናቋል። ተማሪዎች ግን መቼ ተመድበው ትምህርት እንደሚጀምሩ እስካሁን አይታወቅም። በውጤት እና መቁረጫ ነጥብ ላይ ከተነሳው ቅሬታ ባለፈ ወደዩኒቨርሲቲ መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው ሳይገቡ ሌላው ቀርቶ የት እንደሚማሩ ሳያውቁ ለመቀመጥ ተገደዋል፤ ይህም ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል። መንግስት እየተነሱ ላሉ ቅሬታዎች ያለውን ምላሽ በፍጥነት እንዲሰጥና ሌሎች ውጤት የመጣላቸውና ወደ ዩኒቨርሲቲ መቀላቀል ያለባቸውን ተማሪዎች በፍጥነት ወደ ትምህርት እንዲያስገባ ከወላጆችና ተማሪዎች እየተጠየቀ ይገኛል። ይህ ዓመት ሊጠናቀቅ ጥቂት ወራት የቀረው ሲሆን እስካሁን ተማሪዎች አልተመደቡም፤ ዩኒቨሲቲዎችም መቼ ጥሪ እንደሚያደርጉ አይታወቅም። የኮቪድ19 ወረርሽኝ በሀገሪቱ ከተነሳ ጊዜ አንስቶ በኃላም በሰሜን ኢትዮጵያ የተነሳው ጦርነት የኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ላይ እያሳደረ ያለው ተፅእኖ ከባድ ሆኖ ቀጥሏል። በትግራይ ተማሪዎች የ2012ና የ2013 ፈተናን አልወሰዱም የ2014 ይወስዳሉ ተብሎ አይታሰብም። በሀገር ደረጃም የትምህርት መርሃግብሩ ቀድሞ ወደነበረበት ሊመለስ አልቻለም። ይህ ትውልዱ ላይ ትልቅ ተፅእኖ የሚያሳድር በመሆኑ መፍትሄ ያሻዋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ሞጆ 🛣 ሀዋሳ ! የባቱ - አርሲ ነጌሌ ግንባታ ፦ 👉 በእስራኤሉ SBI international holdings A.G /ኤስ ቢ አይ ኢንተርናሽናል ሆልዲንግስ ኤ.ጂ ነው/ የሚነናወነው። 👉 የማማከርና
+2
ሞጆ 🛣 ሀዋሳ ! የባቱ - አርሲ ነጌሌ ግንባታ ፦ 👉 በእስራኤሉ SBI international holdings A.G /ኤስ ቢ አይ ኢንተርናሽናል ሆልዲንግስ ኤ.ጂ ነው/ የሚነናወነው። 👉 የማማከርና ቁጥጥር ስራውን ኩንውሀ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ እያከናወኑ ነው። 👉 ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚሆነው ሶስት ቢሊየን ሶስት መቶ አምስት ሚሊየን ሁለት መቶ አርባ ሶስት ሺህ ብር እየተሸፈነ የሚገኘው ከአለምባንክ በተገኘ ፋይናንስ ነው፡፡ 👉 የአፈር ቆረጣ ስራ፣ ሰብ ቤዝ ስራዎች፣ የስትራክቸር ፣የውሀ ማፋሰሻ ፣ የአቃፊ ግንብ፣ ትላልቅ የድልድይ ግንባታ፣ ማሳለጫዎችና ማቋረጫዎች እና የክሬሸር ስራ በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ 👉 21 ኪ.ሜ የDBM/ ለመጨረሻ የአስፋልን ንጣፍ ስራ ዝግጁ የማድረግ ስራ ተጠናቋል/ ። አርሲ ነጌሌ - ሀዋሳ የሚዘልቀው የመንገድ ክፍል ፦ 👉 ሚገነባው የስራ ተቋራጭ cccc ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ነው። 👉 የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ቤጂንግ ኤክስፕረስ ዌይ ሱፐር ቪዥን ካምፓኒ ሊሚትድ ከውሀን ጄአይኦኬ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንሲ ሊሚትድ ጋር በጋራ በመሆን እየሰሩት ነው ፡፡ 👉 መንገዱን ለመገንባት የሚውለውን ወጪ አምስት ቢሊየን አንድ መቶ አርባ ዘጠኝ ሺህ ብር በቻይናው ኤግዚም ባንክ 85 በመቶ እና 15 በመቶ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ 👉 በአርሲ ነጌሌ - ሀዋሳ የመንገድ ፕሮጀክት የአፈር ቆረጣ እና ድልዳሎ ስራ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣የስትራክቸር ስራዎች፣ የሰብ ቤዝ ስራ፣ የውሀ ማፋሰሻ ቱቦዎች ቀበራ ፣ የድልድይ ግንባታ፣ የጠጠር ንጣፍ ስራዎች እየተሰሩ ናቸው፡፡ 👉 የ3 ነጥብ 4 ኪ.ሜ ለመጨረሻ የአስፋልት ንጣፍ ስራ ዝግጁ የማድረግ ስራ የDBM ተጀምሯል። #ERA @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሞጆ - ሀዋሳ ፈጣን የመንገድ ፕሮጀክት አካል የሆኑት ፦ 👉 በክፍል ሶስት ባቱ - አርሲ ነጌሌ 57 ኪ.ሜ 👉 በክፍል አራት የአርሲ ነጌሌ - ሀዋሳ 52 ኪ.ሜ የአስፓልት ኮንክሪት የ
+1
#Update የሞጆ - ሀዋሳ ፈጣን የመንገድ ፕሮጀክት አካል የሆኑት ፦ 👉 በክፍል ሶስት ባቱ - አርሲ ነጌሌ 57 ኪ.ሜ 👉 በክፍል አራት የአርሲ ነጌሌ - ሀዋሳ 52 ኪ.ሜ የአስፓልት ኮንክሪት የዲዛይን እና ግንባታ ፕሮጀክቶች በመስክ የስራ ቅኝት መጎብኘታቸው ተገልጿል። ቅኝቱ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ እና በሌሎች የተቋሙ ስራ ሀላፊዎችና በሚመለከታቸው አካላት ነው የተካሄደው። በዚህም ወቅት እየተከናወኑ የሚገኙ ወቅታዊ የግንባታ ስራ እንቅስቃሴዎች እና ቀጣይ ስራዎች የተገመገሙ ሲሆን ፕሮጀክቶቹ በተቀመጠላቸው ጊዜ ግንባታቸው እንዲጠናቀቅ ለማስቻል ከስራ ተቋራጮቹና ከአማካሪ ድርጅቶች ጋር ምክክር ተደርጓል፡፡ በቀጣይም የሚከናወኑ ስራዎችን በተመለከተም የተቋሙ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ የስራ አቅጣጫዎችን አስቀምጠቄ። በሁለቱም የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክቶች ስራ ላይ የሚያጋጥሙ ውስንነቶችን በመፍታት ግንባታው ይበልጥ በፍጥነትና በሚገባ መልኩ እንዲከናወን ለማስቻልም የሚደረገውን ጥረት እንደሚቀጥልም አመላክተዋል፡፡ የሞጆ - ሀዋሳ የፈጣን መንገድ አካል የሆኑት ክፍል አንድ ሞጆ - መቂ እና ክፍል ሁለት መቂ - ባቱ ከዚህ ቀደም ግንባታቸው ተጠናቅቆ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት መደረጉ ይታወሳል። ምንጭ፦ ERA @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረችው ፅጌሬዳ ግርማይን በመግደል የተከሰሰው ተማሪ የመከላከያ ማስረጃ እንዲያቀርብ ለመጋቢት 28 ቀን 2014 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቶታል። በሕግ ጥላ ስር
+1
#Update የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረችው ፅጌሬዳ ግርማይን በመግደል የተከሰሰው ተማሪ የመከላከያ ማስረጃ እንዲያቀርብ ለመጋቢት 28 ቀን 2014 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቶታል። በሕግ ጥላ ስር የሚገኘው ተከሳሹ ብሩክ በላይነህ፤ በአርባ ምንጭ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩን እየተከታተለ ይገኛል። ማክሰኞ መጋቢት 20/2014 ዓ.ም ፍርድ ቤት የቀረበው ተከሳሹ፤ "የሚፈልጋቸው ምስክሮቹ በአካባቢው ባለመኖራቸው ምክንያት" የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ሳይችል ቀርቷል። በመሆኑም ፍ/ቤቱ ተለወጫ ቀጠሮ ለመጋቢት 28/2014 ዓ.ም እንደሰጠው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ አገልግሎት ዳይሬክተር መርኪያ መንገሻ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል። ጥር 23/2014 ዓ.ም የተገደለችው የ20 ዓመቷ ተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሆቴልና ቱሪዝም ማኔጅመንት የ2ኛ ዓመት ተማሪ ነበረች፡፡ More : @tikvahuniversity

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የነዳጅ ትራንስፖርት ባለንብረቶች ማኅበር የሥራ ማቆም አድማ ለማድረግ የጊዜ ገደብ ማስቀመጡ ተሰማ። የማህበሩ አባላት ዛሬ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ በተደጋጋሚ መን
+1
#NewsAlert የነዳጅ ትራንስፖርት ባለንብረቶች ማኅበር የሥራ ማቆም አድማ ለማድረግ የጊዜ ገደብ ማስቀመጡ ተሰማ። የማህበሩ አባላት ዛሬ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ በተደጋጋሚ መንግስት ቸልተኛ በመሆኑ የነዳጅ አመላላሽ ቦቴ ቁጥር ከ3500 በ20 እጅ ቀንሷል ብለዋል። ጅቡቲ ደርሶ መልስ 25,000 ብር እየከሰሩ መሆኑንና ይኸም የሆነውም የብር ዋጋ በመውረዱና መለዋወጫ በመወደዱ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም መንግስት በአስር ቀናት ውስጥ መፍትሄ የማይሰጣቸው ከሆነ የሥራ አድማ እንደሚጠሩ ማስታወቃቸውን #ሪፖርተር_ጋዜጣ ዘግቧል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🗣 የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ቦሰት ለቪኦኤ ፦ " አውራ ጎዳና የምትባለው የአሞራ ቤት ቀበሌ መንደር ነች። ሰው ከፊል አርሶ አደር የሆነ በንግድም ጭምር የሚተዳደር ነው። በዕለቱ ጥዋት አካባቢ አንዳንድ ምልክቶች ነበሩ 4 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ ከዛ በኃላ ወደ ቀን 7 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ መሳሪያ የጫኑ በልዩ ልዩ በአይሱዙ ፣ በመሳሰሉ መኪናዎች ጭነው የመጡ ሰዎች አልፍ ሲልም የመንግስት ተሽከርካሪ ጭምር የተጠቀሙ ሰዎች ናቸው የመጡት። የቡድን መሳሪያም አጥምደው ነው የመጡት መጀመሪያ ላይ በአውራ ጎዳና ከተማ ውስጥ አለፉ ከዛ መጨረሻ ላይ ዳር ላይ ሲደርሱ የፌዴራል ፖሊስ ምንድነው ሲላቸው መጀመሪያ እሱን ገደሉ ከዛ ተመልሰው ወደ ማህበረስቡ ገቡና ወደ 8 ሰዓት አካባቢ በጣም የጦፈ ጦርነት ውስጥ ነበር የተገባው። አመሻሽ 12 ሰዓት አካባቢ ነው ተኩስ እየቆመ የመጣው ፤ ድንገቴ ስለሆነ ሰውም ባላሰበበት ሰዓት ስለሆነ ከባድ ችግር ነበር የነበረው። እንደምንም ብሎ የአካባቢው ማህበረሰብ እራሱን ለማዳን ጥረት አድርጎ ሴቶች እና ህፃናትን አሽሽቶ ሌላውን አካል እዛው ባለበት ለማድረግ ተሞክሯል። የአካል ጉዳት ፣ የሞት ፣ የንብረት ጉዳት ና መፈናቀል ጭምር ነው የተፈጠረው። " 🗣 በኦሮሚያ ክልል የምሥራቅ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ ለቢቢሲ ፦ " ... ከአጎራባቹ የአማራ ክልል አካባቢ የመጣ ታጣቂ ቡድን በዞኑ የፀጥታ ኃይሎች ላይ ጥቃት ፈጽሞ ጉዳት አድርሷል። የብሔር ግጭት መፍጠር የሚፈልጉ በኦሮሚያ እና አማራ ድንበር ላይ የሚንቀሳቀስ የተደራጀ ጽንፈኛ ኃይል ሊሆን ይችላል። ጥቃት ፈጻሚው ቡድን ማንነቱ የማይታወቅ ነው። በጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው የፀጥታ አባላት ለሥራ ጉዳይ ተሰማርተው በቡድን እየተመለሱ ሳለ ነው በተፈጸመባቸው ድንገተኛ ጥቃት ከመካከላቸው 18ቱ የተገደሉት እና 15 ደግሞ የቆሰሉት። " 🗣 የምሥራቅ ሸዋ ፖሊስ አዛዥ ኤቢሳ አሰፋ ለኦቢኤን ፦ አዛዡ ፤ በጥቃቱ 26 ሰዎች ተገድለዋል ብለዋል ፤ ጥቃቱን ያደረሰውን ቡድን ማንነት አልገለፁም። ነገር ግን የተደራጀ እና ዘመናዊ ጦር መሳሪያ የታጠቀ ነው " ሲሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#CHINA #USA ቻይና ለአሜሪካ ባለስልጣት የቪዛ አገልግሎት ላለመስጠት ወሰነች። ይህ ውሳኔ አሜሪካ ለቻይና ባለሰልጣናት ቪዛ እንደማትሰጥ ከገለፀች በኃላ በቻይና የተሰጠ ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ ነ
#CHINA #USA ቻይና ለአሜሪካ ባለስልጣት የቪዛ አገልግሎት ላለመስጠት ወሰነች። ይህ ውሳኔ አሜሪካ ለቻይና ባለሰልጣናት ቪዛ እንደማትሰጥ ከገለፀች በኃላ በቻይና የተሰጠ ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ ነው። አሜሪካ ሰኞ ዕለት በሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ላይ እጃቸው አለበት ባለቻቸው የቻይና ባለስልጣናት ላይ ነው የቪዛ እገዳ ጥላ ነበር። መረጃው የአል ዓይን ኒውስ ነው። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአቶ ገለሳ ዲልቦ ስርዓተ ቀብር የፊታችን ቅዳሜ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈፀም የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ገለፀ። አቶ ገላሳ ከኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባልነታቸው ባለፈ
#Update የአቶ ገለሳ ዲልቦ ስርዓተ ቀብር የፊታችን ቅዳሜ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈፀም የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ገለፀ። አቶ ገላሳ ከኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባልነታቸው ባለፈ በምክር ቤቱ የኢንዱስትሪ እና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ም/ሰብሳቢም ነበሩ። በአቶ ገላሳ ዲልቦ ህልፈት ሀዘኑን የገለፀው ም/ቤቱ የቀብር ስነ-ስርዓታቸው የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 24/ 2014 ዓ.ም በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን አሳውቋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#DrAbiyAhmed የአቶ ገለሳ ዲልቦ ህልፈትን ተከትሎ የኢትዮጵያው ጠ/ሚ ሀዘናቸውን ገልፀዋል። " አቶ ገለሳ ከተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ ለኦሮሞ ሕዝብ ነጻነት እና እኩልነት ታግለዋል ያሉት " ዶ/ር
+1
#DrAbiyAhmed የአቶ ገለሳ ዲልቦ ህልፈትን ተከትሎ የኢትዮጵያው ጠ/ሚ ሀዘናቸውን ገልፀዋል። " አቶ ገለሳ ከተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ ለኦሮሞ ሕዝብ ነጻነት እና እኩልነት ታግለዋል ያሉት " ዶ/ር ዐቢይ ፤ " በተለይ ሶማሌ በነበራቸው የትግል ቆይታ ብዙ መከራ እና ችግር እንዳሳለፉ አጫውተውኝ ነበር " ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ " በቅርቡ በለውጡ አመራር በተደረገላቸው ግብዣ የሰላማዊ ትግል ጉዞ መርጠው ወደ ሀገራቸው ተመልሰው በሰላማዊ መንገድ መታገል ከመጀመራቸውም ባሻገር በ2013 ምርጫ በግል ተወዳድረው የፓርላማ አባል ለመሆንም ችለዋል " ሲሉ ገልፀዋል። " በትግል ውጣ ውረድ ውስጥ የገጠማቸውን በጎ እና ክፉ ለማሄስ እና ወጣቶች ከሁለቱም እንዲማሩ ለማድረግ ይተጉ ነበር " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ፤ " አቶ ገላሳ ዝምተኛ፤ አስተዋይ፤ ምክንያታዊ እና ለሰላማዊ ንግግር እጅግ የሚያመች ሰብእና የተላበሱ ግለሰብ ነበሩ ፤ ያጣናቸው ይበልጥ በሚያስፈልጉን ጊዜ ነው። " ሲሉ ገልፀዋቸዋልም @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#AtoGelesaDilbo በኢህአዴግ የሽግግር ወቅት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀ መንበር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የፓርላማ አባሉ አቶ ገላሳ ዲልቦ በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት መለያ
+1
#AtoGelesaDilbo በኢህአዴግ የሽግግር ወቅት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀ መንበር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የፓርላማ አባሉ አቶ ገላሳ ዲልቦ በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት መለያታቸውን ቤተሰቦቻቸው ገልፀዋል። የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አንዱ መስራች የሆኑት አቶ ገላሳ ዲልቦ ባለፈው ዓመት በነበረው ምርጫ የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ጎላኦዳ ቁምቢ መልካ በሎ ወረዳዎችን በመወከል በግል ተወዳድረው በማሸነፍ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ። አቶ ገላሳ ዲልቦ ፤ ለረጅም ዓመታት በስደት ኑሯቸውን በለንደን አድርገው የነበሩ ሲሆን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በውጭ አገራት የነበሩ ተቃዋሚ ኃይሎች ጥሪ ማድረጋቸውን ተከትሎ ወደ አገር ቤት ከተመለሱ አንጋፋ ፖለቲከኞች መካከል አንዱ ነበሩ። አቶ ገላሳ ፤ የተወለዱት ምሥራቅ ወለጋ ነቀምቴ ከተማ ሲሆን አንደኛ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እዚያው ነበር የተከታሉት። በአውሮፓውያኑ 1974 አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የገቡ ቢሆንም የመጀመሪያ ዓመት ትምህርታቸውን ሳይጨርሱ ደርግ ሥልጣን መቆጣጠሩን ተከትሎ ለትግል ወደ ሶማሊያ መሄዳቸውን በወቅቱ ተናግረው ነበር። ሆኖም የሶማሊያ መንግስት ወደ ሀገር ስለመለሳቸው በአገር ቤት የነበረውን የትጥቅ ትግል መቀላቀላቸውንና የትግል ሕይወታቸውም በዚያው እንደተጠነሰሰ በአንድ ወቅት ለቢቢሲ ተናግረዋል። በሽግግሩ ወቅት የኦነግ ሊቀ መንበር የነበሩት አቶ ገለሳ ፤ ከኦነግ ፓርቲ የወጡት በአውሮፓውያኑ 1998 የኦነግ መከፋፈልን ተከትሎ ሲሆን፣ "አባኦ ቃማ ጨኡምሳ" የሚባል ሌላኛውን የኦነግ ፓርቲን መስርተው በሊቀ መንበርነት ለረጅም ዓመታት ማገልግለላቸውን ቢቢሲ አስታውሷል። አቶ ገለሳ ትላንት ለሊት በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" አፋር ውስጥ ጦርነቱ ቀጥሎ በሌላው የኢትዮጵያ ክፍል ሰላም ሊኖር አይችልም " - አቶ ሰዒድ ሙሳ ኢብራሒም (የኤሬብቲ ጎሣ መሪ) አፋር ክልል ውስጥ የቀጠለው ጦርነት " ለሰብዓዊነት ሲባል በታወጀው
+3
" አፋር ውስጥ ጦርነቱ ቀጥሎ በሌላው የኢትዮጵያ ክፍል ሰላም ሊኖር አይችልም " - አቶ ሰዒድ ሙሳ ኢብራሒም (የኤሬብቲ ጎሣ መሪ) አፋር ክልል ውስጥ የቀጠለው ጦርነት " ለሰብዓዊነት ሲባል በታወጀው ግጭት ማቆም ውሳኔ " ላይ አደጋ መደቀኑን ዲፕሎማቶች ተናግረዋል። ሮይተርስ ፤ አፋር ውስጥ ጦርነቱ መቀጠሉን 2 የሰብአዊ ርዳታ ሠራተኞች እንዳረጋገጡለት አስነብቧል። በአፋር 6 ወረዳዎች በትግራይ ኃይሎች መያዛቸውን ዘገባው ገልጿል። የአፋር ኤሬብቲ ጎሣ መሪ አቶ ሰዒድ ሙሳ ኢብራሒም ለሮይተርስ በሰጡት ቃል፥ " አፋር ውስጥ ጦርነቱ ቀጥሎ በሌላው የኢትዮጵያ ክፍል ሰላም ሊኖር አይችልም " ሲሉ ተናግረዋል። የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አህመድ ሃሪፍ ፤ በትግራይ ኃይሎች ተይዘዋል ካሉት 6 ወረዳዎች 2ቱ ውስጥ ጦርነቱ መቀጠሉን፤ በክልሉ መዳረሻ ላይም በከፍተኛ ሁኔታ የትግራይ ኃይሎች እየተበራከቱ መሆናቸውን ተናግረዋል። የህወሓት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ በሰጡት ቃል በተጠቀሱት አካባቢዎች ውጊያ የለም ሲሉ አስተባብለዋል። በአፋር ክልል አቅራቢያ ተዋጊዎቻቸውን እያሰፈሩ ነው ስለመባሉ ግን ማስተባበያ አልሰጡም ሲል ሮይተርስ ገልጿል። (Reuters.com / Deutsche Welle) በሌላ መረጃ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ አስፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ አን ጃኮብሰን ከአፋር ክልል ፕሬዜዳንት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ታውቋል። አምባሳደር ጃኮብሰን ፤ አሜሪካ በጦርነት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል የገለፁ ሲሆን አቶ አወል አርባ ህወሓት እያደረሰ ነው ያሉትን ስቃይ የዓለም ህብረተሰብ በፅኑ ሊያወግዘው ይገባል ብለዋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ከሳኡዲ አረቢያ በሁለተኛ ዙር 438 ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ዛሬ ከሰዓት በሁለተኛው ዙር በረራ 438 ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረ
+1
#Update ከሳኡዲ አረቢያ በሁለተኛ ዙር 438 ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ዛሬ ከሰዓት በሁለተኛው ዙር በረራ 438 ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ዛሬ ማለዳ በመጀመሪያ ዙር 498 ወገኖቻችን ወደሀገር መግባታቸው ይታወሳል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA #KENYA ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገር ኬንያ ጋር በሰላምና የደህንነት ጉዳዮች ለመተባበር ተስማምታለች። ዛሬ የኢፌዲሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና
+1
#ETHIOPIA #KENYA ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገር ኬንያ ጋር በሰላምና የደህንነት ጉዳዮች ለመተባበር ተስማምታለች። ዛሬ የኢፌዲሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የኬንያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሮበርት ኪቢቹ ኬንያ፣ ናይሮቢ ውስጥ ተወያይተዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከኬንያ አቻቸው ጄኔራል ሮበርት ኪቢቹ ጋር ባደረጉት ምክክር ሁለቱ አገሮች በሁለትዮሽና በአካባቢያዊ የፀጥታ ጉዳይ ለመተባበር ተስማምተዋል፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ኢትዮጵያና ኬንያ በሠላም እና ደህንነት እንዲተባበሩ የተመቻቸ ሁኔታ እና ዕድል እንዳለ ገልፀዋል፡፡ ጄኔራል ኪቢቹ ፤ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ በኬንያ ቆይታ በማድረጋቸው መደሰታቸውን ጠቅሰው '' አገሮቻችን የረⶵም ጊዜ ወዳጅ ናቸው ይህንን የበለጠ ማጠናከር ይገባናል '' ብለዋል፡፡ የጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹምቹ ፦ 👉 በስልጠና፣ 👉 በሠላምና ደህንነት ማስከበር ዘርፎች ለመደጋገፍ ከመግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡ ኢትዮጵያና ኬንያ አባል የሆኑበትንን የምስራቅ አፍሪካ የተጠንቀቅ ኃይልን ለማጠናከር በግንባር ቀደምትነት ለመስራት ተስማምተዋል። መረጃው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘ ነው። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ከፍተኛ የተባለ የዋጋ ግሽበት በጀርመን እና ቤልጂየም ተመዘገበ። በጀርመን በመጋቢት ወር 7.3% የሆነ የዋጋ ግሽበት የተመዘገበ ሲሆን ይህም ከ30 ዓመት በኃላ (ከጀርመን ውህደት በኃላ) የተመዘገበ
+1
ከፍተኛ የተባለ የዋጋ ግሽበት በጀርመን እና ቤልጂየም ተመዘገበ። በጀርመን በመጋቢት ወር 7.3% የሆነ የዋጋ ግሽበት የተመዘገበ ሲሆን ይህም ከ30 ዓመት በኃላ (ከጀርመን ውህደት በኃላ) የተመዘገበ ከፍተኛው የዋጋ ግሽበት ነው። በቤልጂየም ደግሞ 8.31% የዋጋ ግሽበት የተመዘገበ ሲሆን ይህም ከ39 ዓመታት በኃላ የተመዘገበ ከፍተኛው የዋጋ ግሽበት ነው። እስካሁን ይህ ነው የሚባል ተጨባጭ መፍትሄ ያላገኘው የዩክሬን እና ሩስያ ጦርነት በዓለም ሀገራት ላይ እያሳደረ ያለው ተፅእኖ እየከፋ ነው፤ ጦርነቱ መቋጫ ካላገኘ ተፅእኖው አሁን ካለውም እጅግ ሊከፋ ይችላል ተብሎ ይገመታል። በታዳጊ ሀገራት ላይ ይዞት እየመጣው ያለው መዘዝም ከባድ ነው። @tikvahethiopia

#የምስራች🎉 አባይ ኃይል መስጠት ጀመረ። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዛሬ ኃይል መስጠት ጀምሯል። ግድቡ ዛሬ ኃይል ማመንጨት የጀመረው ካሉት 13 ተርባይኖች ውስጥ በአንዱ ተርባይን አማካኝነት ነ
+3
#የምስራች🎉 አባይ ኃይል መስጠት ጀመረ። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዛሬ ኃይል መስጠት ጀምሯል። ግድቡ ዛሬ ኃይል ማመንጨት የጀመረው ካሉት 13 ተርባይኖች ውስጥ በአንዱ ተርባይን አማካኝነት ነው። አንዱን ተርንባይን በመጠቀም ወደ ስራ የገባው ግድቡ 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሙከራ ሂደት ሲያደርግ የነበረ ሲሆን የሙከራ ሂደቱ ተጠናቆ የኤሌክትሪክ ኃይል መስጠት ጀምሯል። ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ የግድቡን የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ሂደቱን በይፋ አስጀምረዋል፡፡ ፎቶ ፦ አሚኮ & TK.SS @tikvahethiopia

#TimeSportAccessories በ 0904144672 ይደውሉልን ። በሰውነት ክፍሎቻችን ያለውን ስብ በመቀነስ የሰውነትን ክብደት በኣግባቡ ለመቀነስ የሚረዱ፣ ለአራስ እናቶች የሚረዳ፣ ለስፖርተኞች
#TimeSportAccessories በ 0904144672 ይደውሉልን ። በሰውነት ክፍሎቻችን ያለውን ስብ በመቀነስ የሰውነትን ክብደት በኣግባቡ ለመቀነስ የሚረዱ፣ ለአራስ እናቶች የሚረዳ፣ ለስፖርተኞች ተመራጭ እናም ለጊዜያዊ እና ለዘላቂ ሰዉነት ማስተካከያ አስመጥተናል። Telegram : https://t.me/timesportaccessories

#GERD የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ክፍሌ ሆሮ ፦ "... ማመንጨት ተጀመረ እንጂ ፕሮጀክቱ ተጠናቀቀ ማለት አይደለም። ፕሮጀክቱን ለመጠናቀቅ አሁን ብለው ሁኔታ ከሁለት ዓመት
#GERD የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ክፍሌ ሆሮ ፦ "... ማመንጨት ተጀመረ እንጂ ፕሮጀክቱ ተጠናቀቀ ማለት አይደለም። ፕሮጀክቱን ለመጠናቀቅ አሁን ብለው ሁኔታ ከሁለት ዓመት ተኩል እስከ ሶስት ዓመት ሊፈጅብን ይችላል። ስለዚህ ህዝቡ ከመጀመሪያውም ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያውያን ፕሮጀክት ነው። ፋይናንስ ሚደረገው በመንግስትና በኢትዮጵያ ነው ስለዚህ ይሄን ተገንዝበን ፕሮጀክቱን እስከመጨረሻው ፋይናንስ ማድረግ አለብን። የኢትዮጵያን እውነታ አሁን ተርባይኑን መቶ ነው ውሃ እየፈሰሰ ያለው ስለዚህ ኢትዮጵያ ከዚህ ውሃ ምንም የምትቀንሰው ነገር ስለሌለ ዓለምም ይህን እንዲረዳ እያንዳንዳችን ተረባርበን ለፕሮጀክቱ ዲፕሎማት ሆነን መንቀሳቀስ አለብን። " @tikvahethiopia

#GERD የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አንደኛው ሁኒት [ ዩኒት 10 ] ኃይል ማመንጨት መጀመሩን የግድቡ ሰራተኞች ለብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል። @tikvahethiopia
+3
#GERD የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አንደኛው ሁኒት [ ዩኒት 10 ] ኃይል ማመንጨት መጀመሩን የግድቡ ሰራተኞች ለብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል። @tikvahethiopia

#GERD የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ነገ እሁድ የካቲት 13 ቀን 2014 ዓ.ም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር አጀንስ ፍራንስ ፕሬስ (AFP) ሁለት ስማቸው ያልተገለፀ የኢትዮጵያ ከፍተ
+4
#GERD የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ነገ እሁድ የካቲት 13 ቀን 2014 ዓ.ም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር አጀንስ ፍራንስ ፕሬስ (AFP) ሁለት ስማቸው ያልተገለፀ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ዋቢ አድርጎ በዛሬው ዕለት ዘግቧል። ዛሬ አንድ ከፍተኛ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣን [ስማቸው ያልተገለፀ] " ነገ የግድቡ የመጀመሪያው የሃይል ማመንጫ ይሆናል" ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል። አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ (AFP) ሌላ ሁለተኛ ከፍተኛ ባለስልጣን መረጃውን ማረጋገጣቸውን ገልጿል። ሁለቱም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉት ጉዳዩ በይፋ ስላልተገለፀ ነው ተብሏል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በቅርቡ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር የገለፀ ሲሆን መቼ ? ለሚለው ግን መረጃ አልሰጠም ነበር። ይኸው ጉዳይ ባለፉት ቀናት በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሲዘዋወር ነበር፤ ነገር ግን በመንግስት በኩል ይፋዊ መረጃ አልተሰጠም። @tikvahethiopia