en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እስር ላይ ከነበሩ ጋዜጠኞች መካከል እስካሁን ስይፈታ የቆየው ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ ዛሬ ረቡዕ ከእስር መፈታቱ ተገልጿል። [ https://t.me/tikvahethiopia/65538 ] "
+1
#Update እስር ላይ ከነበሩ ጋዜጠኞች መካከል እስካሁን ስይፈታ የቆየው ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ ዛሬ ረቡዕ ከእስር መፈታቱ ተገልጿል። [ https://t.me/tikvahethiopia/65538 ] " ተራራ ኔትዎርክ " የተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ አቋቁሞ ሲሰራ በነበረበት ወቅት ታህሳስ 1 ቀን የታሰረው ጋዜጠኛ ታምራት ከ118 ቀናት እስር በኃላ መፈታቱን የሚሰራበት ሚዲያ አሳውቋል። ጋዜጠኛ ታምራት ከታሰረ በኃላ በተደጋጋሚ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን በ50 ሺህ ብር ዋስ ነው ከእስር የተፈታው። ከዚህ ቀደም ጋዜጠኛ መአዛ መሃመድ፣ ጋዜጠኛ እና አክቲቪስት ኢያስፔድ ተስፋዬ ፣ ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁ ፣ የአሶሴትድ ፕረስ (AP) ጋዜጠኛ አሚር አማን እና የካሜራ ባለሙያው ቶማስ እንግዳ ከእስር መፈታታቸው ይታወቃል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Qatar2022 " ለኳታሩ 2022 የዓለም ዋንጫ በዳኝነት እንዳጫውት በፊፋ መመረጤን አላውቅም " - ባምላክ ተሰማ (ለቢቢሲ) ዓለም አቀፍ ዳኛ ባምላክ ተሰማ "ለኳታሩ 2022 የዓለም ዋንጫ በዳኝነ
+1
#Qatar2022 " ለኳታሩ 2022 የዓለም ዋንጫ በዳኝነት እንዳጫውት በፊፋ መመረጤን አላውቅም " - ባምላክ ተሰማ (ለቢቢሲ) ዓለም አቀፍ ዳኛ ባምላክ ተሰማ "ለኳታሩ 2022 የዓለም ዋንጫ በዳኝነት እንዳጫውት በፊፋ መመረጤን አላውቅም" ሲል ተናግሯል። ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ለቢቢሲ በሰጠው ቃል ፥ " ምንም ነገር አላውቅም። በይፋ የደረሰኝ ነገር የለም " ብሏል። ባምላክ ተሰማ በኳታሩ የዓለም ዋንጫ እንዲዳኙ በFIFI ከተመረጡ 8 አፍሪካውያን ዳኞች መካከል አንዱ መሆኑን የምዕራብ አፍሪካ ድረ-ገጾች እና በሀገራችን የተለያዩ ሚዲያዎች ሲዘግቡ ነበር። " እንደዚህ ዓይነት መረጃ ከየት እንደሚመጣ አላውቅም" ያለው ኢንተርናሽናል አልቢትር ባምላክ ተሰማ ለኳታሩ የዓለም ዋንጫ በፊፋ ስለመመረጡ የወጡ ዘገባዎችን መመልከቱን ግን ተናግሯል። የተለያዩ ሚዲያዎች ባምላክ ለኳታሩ የዓለም ዋንጫ መመረጡን የዘገቡት ፊፋን ዋቢ አድርገው ሲሆን በፊፋ ይፋዊ ድረ-ገጽ ላይ የተባለ ነገር የለም። ባምላክ ፊፋ የዓለም ዋንጫን የሚመሩ ዳኞችን ማንነት ይፋ ለማድረግ ጊዜው የፈጠነ ነው ብሎ እንደሚያስብም ለቢቢሲ በሰጠው ቃል ገልጿል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#USA የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት በኢትዮጵያ ላይ ጠንካራ ማዕቀቦችን ይጭናል የተባለውን ረቂቅ ህግ ለማዘግየት መስማማታቸውን ዘ አፍሪካን ሪፖርት ዘግቧል። እንደ ዘ አፍሪካን ሪፖርት ዘገባ ይህ ውሳኔ
+1
#USA የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት በኢትዮጵያ ላይ ጠንካራ ማዕቀቦችን ይጭናል የተባለውን ረቂቅ ህግ ለማዘግየት መስማማታቸውን ዘ አፍሪካን ሪፖርት ዘግቧል። እንደ ዘ አፍሪካን ሪፖርት ዘገባ ይህ ውሳኔ የመጣው ከሳምንታት በፊት በሰብዓዊነት ላይ የተሰመሰረት ግጭት የማቆም ውሳኔ ላይ ተንተርሶ ሲሆን የተደረሰው ስምምነት ተግባር ላይ እስከዋለ ድረስ የኮንግረሱ አባላት ረቂቅ ህጎችን ለማዘግየት ተስማምተዋል። ጦርነቱ የሚያገረሽ ከሆነ ግን እንዲዘገዩ የተደረጉት ረቂቅ ሕጎች እንደገና እንደሚንቀሳቀሱ ተሰምቷል። አሁን ኮንግረሱ ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም የተወሰነውን ውሳኔ ተከትሎ ረቂቅ ህጉ እንዲዘገይ የተስማማውን ውሳኔ በተመለከተ የኮሚቴው ህግ አውጪዎች ጉዳዩ ለኢትዮጵያ መንግስት፣ ለኤርትራ መንግስት፣ እና ለትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) ግልፅ መልዕክት ያስተላለፈ ነው ፤ ረቂቅ ህጉ ለመጨረሻ ድምጽ አሰጣጥ ከቀረበ በፍጥነት ለማለፍ በቂ ድምጾች አሉ ብለዋል። የአሜሪካ ኮንግረስንና ሴኔትን እንዲሁም የረቂቅ ሕጎችን ሂደት የሚከታተለው የGovTrack.us H.R. 6600 እና S.3199 ረቂቅ ህጎችን ስለመዘግየታቸው የሚገልጽ መረጃ ይፋ አላደረገም። እ.ኤ.አ መጋቢት 29 የአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ባለፈው አመት ህዳር ወር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቀውን S.3199 ረቂቅ ህግ (በኢትዮጵያ ሰላም እና ዴሞክራሲ ለማበረታታ) እንዳሳለፈው ይታወሳል። NB : እንዲዘገይ ተደረገ ከተባለው ረቂቅ ህግ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ ሚዲያዎች " ተቋረጠ " ተብሎ እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን በኢትዮጵያ የመረጃ አጣሪው ድረገፅ ኢትዮጵያ ቼክ አሳውቋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ በ108 ዶላር እየተሸጠ ነው። ዛሬ የ1 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 108 ዶላር እየተሸጠ የሚገኝ ሲሆን በአሜሪካ ነዳጅ ገበያ እንደመለኪያ በሚታየው ዌስት ቴክሳስ
#Update የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ በ108 ዶላር እየተሸጠ ነው። ዛሬ የ1 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 108 ዶላር እየተሸጠ የሚገኝ ሲሆን በአሜሪካ ነዳጅ ገበያ እንደመለኪያ በሚታየው ዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዴት 1 በርሜል ነዳጅ 104.4 ዶላር በሆነ ዋጋ እየተሸጠ ነው። ሩስያና ዩክሬን የገቡበት ጦርነት መፍትሄ አለናግኘቱን ተከትሎ አሁንም በነዳጅ ዋጋ ላይ እያሳደረ የሚገኘው ተፅእኖ እጅጉን በርትቷል። #OilPrice @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የካማሺ ዞን የማረሚያ ቤት አዛዥ ተወካይን ጨምሮ 3 የጸጥታ አካላት እንደታገቱበት ገለፀ። እገታው በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን መፈፀሙን ገልጿል። የክልሉ ፖሊስ ፥ በአ
+1
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የካማሺ ዞን የማረሚያ ቤት አዛዥ ተወካይን ጨምሮ 3 የጸጥታ አካላት እንደታገቱበት ገለፀ። እገታው በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን መፈፀሙን ገልጿል። የክልሉ ፖሊስ ፥ በአሁን ሰዓት ታጋቾቹን ለማስለቀቅ የኦሮሚያና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ጥረት መጀመራቸውን አሳውቋል። ፖሊስ እንደሚለው በማረሚያ ቤት ኃላፊዎቹ ላይ እገታው የተፈጸመው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ መጋቢት 22/2014 ዓ.ም ከአሶሳ ከተማ ወደ ካማሺ ዞን እየሄዱ ባሉበት ወቅት መንገድ ላይ ነው። ታጋቾቹ የት እንዳሉ እና በምን ምክንያት እንደታገቱ ሙሉ መረጃ ባይኖርም እስከ ትላንት በስቲያ ድረስ በሕይወት እንዳሉ መረጃ እንዳለው ፖሊስ ገልጿል። የክልሉ ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ምስጋናው እንጅፈታ ፥ ታጋቾቹ " በሌላ ስልክ አስደውለው በሕይወት እንዳሉና "አታስቡ" የሚል መልዕክት ለቤተሰብ ማስተላለፋቸውን ገልፀዋል። ክልሉ፥ ከኦሮሚያ ክልል ጋር እየተነጋገረ ሲሆን የክልሉ አባ ገዳዎች፣ የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ግለሰቦቹን ለማስለቀቅ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተገልጿል። በካማሺ ዞን በኩል የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ወደ ስፍራው አምርተው ቀጥታ ግንኙነት በማድረግ በውይይት ሰዎቹ እንዲለቀቁ ለማድረግ እቅድ ያለ ሲሆን እኚሁ የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስፍራው ያመራሉ ተብሏል። የአጋቾቹ ማንነት በተመለከተ ም/ ኮሚሽነር ምስጋናው በሰጡ ቃል እስካሁን በግልፅ የተደረሰበት ነገር እንደሌለ ፤ ነገር ግን በመረጃ ደረጃ በአካባቢው የ " ኦነግ ሸኔ " ኃይል በስፋት እንደሚንቀሳቀስ ገልፀው እገታውን የፈፀመው " ኦነግ ሸኔ " ነው የሚል ጥርጣሬ አለን ማለታቸውን #ቢቢሲ ዘግቧል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz📍 በኢትዮጵያ በተለያየ አቅጣጫ በጦርነት እና በግጭት ምክንያት እጅግ በርካታ ወገኖቻችን ተፈናቅለው ይገኛሉ። በርካታ ተፈናቃይ ወገኖቻችን ከሚገኙባቸው አካባቢዎች አንዱ የ
+5
#BenishangulGumuz📍 በኢትዮጵያ በተለያየ አቅጣጫ በጦርነት እና በግጭት ምክንያት እጅግ በርካታ ወገኖቻችን ተፈናቅለው ይገኛሉ። በርካታ ተፈናቃይ ወገኖቻችን ከሚገኙባቸው አካባቢዎች አንዱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ነው። በክልሉ በተለያየ ጊዜ በተከሰተ የፀጥታ ችግር ከሞቀው ቄያቸው ተፈናቅለው እርዳታ የሚጠባበቁ ወገኖቻችን ቁጥር እየጨመረ ሲሆን ከክልሉ የአደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን እንደተገኘው መረጃ አሁን በክልሉ ከ400 ሺህ በላይ ተፈናቅይ ይገኛል። ከመኖሪያቸው ከተፈናቀሉ ጀምሮ በርካታ ችግር እየደረሰባቸው እንደሆነ የሚናገሩት ተፈናቃይ ወገኖቻችን ዝናብ እና ፀሃይ እየተፈራረቀባቸው መሆኑን እና የሚደረግላቸው ድጋፍ በቂ እንዳልሆነ አስረድተዋል። ከተፈናቃዮቹ ብዛት ያላቸው ሴቶች፣ ህፃናት ፣ ተማሪዎች የሚገኙ ሲሆን በእድሜ የገፉ አረጋዊያን በመጦሪያ እድሜያቸው ተፈናቅለው እየተንገላቱ ናቸው። እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሆነ የሚገልፁት ተፈናቃዮች ግን በቂ እንዳልሆነ ምግብ፣ የህክምና፣ አልባሳት ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀዋል። ክልሉን የሚያስተዳድሩት አቶ አሻድሊ ሀሰን ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል፤ በክልሉ ከደረሰው ጉዳት እና ካለው ተፈናቃይ ቁጥር አንፃር የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ገልፀው ለመንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፣ አጋር አካላት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል። እየቀረበ ካለው ጥሪ ጋር በተያያዘ ፤ Action for Social Development and Environmental Protection Organization (ASDEPO) የተባለ ድርጅት ከ100 ሺህ በላይ ሰዎችን ለመድረስ 40 ሚሊዮን ብር በጀት የተያዘለት ፕሮጀክት ይፋ ማድረጉን ከብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን እና በሲዳማ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ እሁድ ምሽት በተቀሰቀሰ ግጭት ቢያንስ 5 ሰዎች ተገደሉ። የሲዳማ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ፥
+1
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን እና በሲዳማ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ እሁድ ምሽት በተቀሰቀሰ ግጭት ቢያንስ 5 ሰዎች ተገደሉ። የሲዳማ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ፥ ግጭት የተቀሰቀሰው በሲዳማ ክልል፣ ጪሪ ወረዳ፣ ሀሌላ ቀበሌ ነዋሪዎች ዘንድ ታዋቂ የሆኑ የሀገር ሽማግሌ መገደላቸውን ተከትሎ ነው ብለዋል። አዴ ሎኬ ዮኔ የተባሉት እኚሁ አባት እሁድ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ የተገደሉት " ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ነው " ብለዋል።  ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ በሀሌላ ቀበሌ የተቀሰቀሰው ግጭት ወደ አጎራባች ቀበሌዎች ተስፋፍቶ በሲዳማ ክልል ጪሪ ወረዳ ሱጫ ቀበሌን እና በኦሮሚያ ክልል ሻምበልና ውሮ ቀበሌዎችን አዳርሷል። በግጭቱ እስካሁን ከሲዳማ በኩል የሀገር ሽማግሌውን ጨምሮ ቢያንስ 2 ሰዎች ሲገደሉ፤ በኦሮሚያ በኩል የ3 ሰዎች ህይወት እንዳለፈ ገልጸዋል። ከቦናና በዳዬ ሆስፒታል በተገኘው መረጃ 15 ሰዎች በጥይት ቆስለዋል። ቦና ከገቡ 7 ሰዎች 3ቱ በብርቱ የቆሰሉ ናቸው። በዳዬ ደግሞ 9 ሰዎች ቆስለው የገቡ ሲሆን አንዱ ህክምና እርዳታ ላይ እያለ ህይወቱ አልፏል። ሰው ላይ ከደረሰ ጉዳት ባለፈ በርካታ ቤቶች ወድመዋል። የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ግጭቱን ለማርገብ እርምጃዎች መውሰዳቸውን የተገለፀ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ የሁለቱ ክልል ኃላፊዎች፣ በአባ ገዳዎች እና በሲዳማ ሀገር ሽማግሌዎች የታገዘ ምክክር በማድረግ ግጭቱ እንዲቆም ማድረጋቸውን አቶ አለማየሁ ገልፀዋል። የጥቃቱን ፈጻሚዎች ማንነት በተመለከተ ታጣቂዎቹን ለመለየት ማጣራት እየተደረገ ነው ሆኖም ግን "በኦሮሚያ ክልል ታጥቀው የሚዞሩ ታጣቂዎች ሊሆኑ ይችላሉ" ብለዋል። ለጊዜው ከኦሮሚያ በኩል አስተያየት ሊገኝ እንዳልተቻለ ዘገባውን ያሰራጨው 👉ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ገልጿል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የህክምና፣ ምግብ እና የውሃ ማጣሪያ ግብዓቶችን ያካተተ ድጋፍ ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2014 ዓ.ም ትግራይ ክልል ደርሷል፡፡ ይህም እ.ኤ.አ ከመስከረም 2
+1
#Tigray የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የህክምና፣ ምግብ እና የውሃ ማጣሪያ ግብዓቶችን ያካተተ ድጋፍ ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2014 ዓ.ም ትግራይ ክልል ደርሷል፡፡ ይህም እ.ኤ.አ ከመስከረም 2021 በኋላ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ክልሉ የደረሰ የመጀመሪያው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ድጋፍ ነው፡፡ https://www.icrc.org/en/document/ethiopia-icrc-resumes-aid-convoys-tigray-after-six-months-0 @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray , #Mekelle 📍 የዓለም ምግብ ፕሮግራም ከ8 ወር በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ የነዳጅ ቦቴ ትግራይ መገባቱን አስታውቋል። ዛሬ 47,000 ሊትር ነዳጅ መቐለ የደረሰ ሲሆን ፤ ድርጅቱ
+1
#Tigray , #Mekelle 📍 የዓለም ምግብ ፕሮግራም ከ8 ወር በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ የነዳጅ ቦቴ ትግራይ መገባቱን አስታውቋል። ዛሬ 47,000 ሊትር ነዳጅ መቐለ የደረሰ ሲሆን ፤ ድርጅቱ በክልሉ ያለውን የሰብዓዊ ፍላጎት ለማሟላት በየሳምንቱ 200,000 ሊትር ነዳጅ ያስፈልጋል ብሏል። ከትላንት አርብ ጀምሮ ወደ ትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍ በየብስ እየገባ ይገኛል። የዓለም ምግብ ፕሮግራም ከዚህ ቀደም በክልሉ ያለውን የሰብዓዊ ፍላጎት ለማሟላት በየቀኑ 100 ሰብዓዊ ድጋፍ የጫኑ ተሽከርካሪዎች መግባት እንዳለባቸው መግለፁ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት ለሰብዓዊነት ግጭት የማቆም ውሳኔ ማሳለፉ ፤ ከትግራይ ክልል በኩልም በጎ የሆነ ምላሽ መሰጠቱን ተከትሎ በችግር ላይ ለሚገኙ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዜጎች ሰብዓዊ ድጋፍ መግባት መጀመሩን የተለያዩ ሀገራት፣ የተለያዩ ረድኤት ድርጅቶች እያበረታቱ ይገኛሉ። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#DireDawa 1443 ኛው የረመዳን ፆም ወር የአፍጢር መርሀ-ግብር በአሁን ሰአት በለገሀር አደባባይ እየተካሄደ ይገኛል። በዚሁ የአፍጢር መርሀ-ግብር ላይ በርካታ የእምነቱ ተከታዮች ፣ የሀይማኖት
+4
#DireDawa 1443 ኛው የረመዳን ፆም ወር የአፍጢር መርሀ-ግብር በአሁን ሰአት በለገሀር አደባባይ እየተካሄደ ይገኛል። በዚሁ የአፍጢር መርሀ-ግብር ላይ በርካታ የእምነቱ ተከታዮች ፣ የሀይማኖት አባቶች እና ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል። ፎቶ ፦ የድሬዳዋ ኮሚኒኬሽን @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert የጤና ሚኒስቴር የትዊተር አካውንት ተጠለፈ። ከ204 ሺ በላይ ተከታዮች ያሉት የሚኒስቴሩ የትዊተር አካውንት ተጠልፏል። የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጤና ሚኒስቴር ይፋዊ የትዊተር አካውንቱ #FMoHeal
+1
#Alert የጤና ሚኒስቴር የትዊተር አካውንት ተጠለፈ። ከ204 ሺ በላይ ተከታዮች ያሉት የሚኒስቴሩ የትዊተር አካውንት ተጠልፏል። የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጤና ሚኒስቴር ይፋዊ የትዊተር አካውንቱ #FMoHealth ዛሬ መጋቢት 24 መጠለፉን (ሃክ መደረጉን) አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ በትዊተር ገጹ ላይ የሚለቀቁ ማንኛውም መረጃዎች እንደማይወክሉት ገልጿል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ተፈርዶባቸዋል ከቀናት በፊት መጋቢት 19 ላይ በብቸና ከተማ 2 ታዳጊዎችን አግተው ከቤተሰቦቻቸው 400 ሺ ብር የጠየቁ ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውንና የምርመራ ስራ እየተሰራ መሆኑን
#ተፈርዶባቸዋል ከቀናት በፊት መጋቢት 19 ላይ በብቸና ከተማ 2 ታዳጊዎችን አግተው ከቤተሰቦቻቸው 400 ሺ ብር የጠየቁ ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውንና የምርመራ ስራ እየተሰራ መሆኑን መረጃ መለዋወጣችን አይዘነጋም። [ https://t.me/tikvahethiopia/69002?single ] ከከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ በተገኘው መረጀ በተጠርጣሪዎቹ ላይ በፍርድ ቤት የቅጣት ውሳኔ ተላልፏል። የእነማይ ወረዳ ፍርድ ቤት በተጠርጣሪዎች ላይ የተጣራውን ምርመራ መዝገብ የተመለከተ ሲሆን 2ቱ ተከሳሾች ጥፋተኛ መሆናቸውን በቀረቡ ማስረጃዎች አረጋግጧል። መጋቢት 23 ቀን 2014 ዓ/ም በዋለው ችሎትም 1ኛ ተከሳሽ ተሾመ ሀብቴ በ7 ዓመት ከ6 ወር ፤ 2ኛ ተከሳሽ በሀይሉ ይዘንጋው በ7 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል። መረጃው የብቸና ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ነው። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
🤲 ረመዳን 🤲 ነገ ቅድሜ ታላቁ የረመዳን ፆም አንድ ብሎ ይጀምራል። ቤተሰቦቻችን እንኳን ለታላቁ የረመዳን ፆም አደረሳችሁ። ረመዳን የፍቅር ፣ የአንድነት ፣ የሰላም ፣ የመተሳሰብ እና የአብሮነት
+4
🤲 ረመዳን 🤲 ነገ ቅድሜ ታላቁ የረመዳን ፆም አንድ ብሎ ይጀምራል። ቤተሰቦቻችን እንኳን ለታላቁ የረመዳን ፆም አደረሳችሁ። ረመዳን የፍቅር ፣ የአንድነት ፣ የሰላም ፣ የመተሳሰብ እና የአብሮነት ወር ነው። በዚህ ታላቁ ወራችን በስቃይና መከራ ፣ በሰላም እጦት ፣ በግጭት እና በጦርነት ከሞቀው ቤታቸው ተፈናቅለው ሜዳ ወድቀው የሚገኙ፣ በረሃብ እና ጥማት የሚሰቃዩ፣ በድርቅ የተጎዱ ፣ በህመም እና በጭንቀት፣ በተለያየ የኑሮ ፈተና ላይ ያሉትን ወገኖቻችን ሁሉ እድናስብ አደራ እንላለን። እንዲሁም ለዓለም፣ ለሰው ልጅ ሁሉ ሰላም እና ደህንነት ፈጣሪያችንን አጥብቀን የምንማፀንበት ፤ ፈጣሪያችንም ተማጽኗችንን የሚሰማበት እንዲሆንልን እንመኛለን። رمضان مبارك #TikvahFamily❤️ @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#KonssoZone📍 በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን ሰገን ዙሪያ ወረዳ ባለፈው ቅዳሜ የወረዳው የገቢዎች ኃላፊ ምግብ ቤት ውስጥ በጥይት መገደሉ ከተገለጸ በኋላ በተከታታይ 4 ሰዎች መሞታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰው መረጃ ያሳያል። ህይወታቸው ያለፈው የ ' ሰገን ገነት ቀበሌ ' ሊቀመንበር አቶ ኩሴ ጦኔ እንዲሁም አንድ የሚሊሻ አባል እና 2 ነዋሪዎች ናቸው። የወረዳው የመንግስት ተጠሪ አቶ ገመይዳ ጉዴኖ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት መጋቢት 18 ቀን 2014 የአከባቢው ሚሊሻ ከደራሼ ልዩ ወረዳ ሀይቤና ቀበሌ በኩል የመጡ ታጣቂዎች ጥቃት ፈጽመውበት መገደሉን ገልጸዋል። አቶ ገመይዳ ፥ " ጥቃቱ ሲፈጸምም ሽፋን የሰጠ አካል የለም " ሲሉ ነው የገለጹት። በመቀጠልም ፤ መጋቢት 22 በግምት ከቀኑ 8:30 አከባቢ የሰገን ገነት ቀበሌ ሊቀመንበር ኩሴ ጦኔ በታጣቂዎቹ ታፍኖ መሳሪያውን ተቀምቶ ተገድሏል ብለዋል። ''ትላንት ማታ ነው ሬሳ ያወጣነው'' ሲሉም ተናግረዋል። በዚያው ቀን 5:30 አከባቢም በመጓዝ ላይ በነበሩ 3 ሰዎች ላይ በተከፈተ ጥቃት ሁለቱ ህይወታቸው ሲያልፍ አንደኛው በከፍተኛ ሁኔታ ተጎድቶ የህክምና ክትትል እየተደረገለት እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት መረጃ ይድረስንልን ያሉ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ግለሰብ ፤ ጥቃቱን የሚፈጽሙት " በትጥቅ የተደራጁና መሳሪያ የታጠቁ አካላት " መሆናቸውን ተናግረዋል። ከአካካቢው የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ያሰባሰብነው መረጃ እንደሚያሳየው ደግሞ የክልሉ ልዩ ኃይል ከነበረበት ካንፕ ለቆ በወጣበት ቅጽበት የቀበሌው ሊቀመንበር አቶ ኮሴ ጡኔ በታጣቂዎቹ መገደላቸውን ይጠቁማል። አቶ ገመይዳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳሉት የጸጥታ መዋቅሩ ከየቀጠናው ተሰብስቦ በመውጣቱ ጥቃቱን ሚሊሻ ብቻውን መከላከል እንዳልቻለ ጠቁመዋል። የወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በርሻ ኦላታ ፤ " ፅንፈኛው " ሲሉ የጠሩት ኃይል እየፈጠረ ባለው ሁከትና ብጥብጥ ህዝቡ ዳግም መፈናቀሉንና ለእንግልት መዳረጉን ገልፀዋል። አቶ በርሻ ፤ የመለጋ እና ዱጋያ ቀበሌ ህብረተሰብ መንግስት የሰጣቸውን ጊዜያዊ መጠለያ ሸራ ቤት በመወጠር ቤት ንብረቱ በተቃጠለበት ቦታ ቀልሰው መኖር በጀመሩበት ወቅት ጥቃት መፈጸሙን አንስተዋል። በዱጋያ ትም/ት ቤት እና ለሰራዊት ማረፊያ የተገነባው ሁለት ካምፕ ላይም ጥቃት ደርሷል ሲሉ ነው የገለፁት። በተመሳሳይ ከትላንትና መጋቢት 22 ቀን 2014 ማታ ጀምሮ " ጋርጨ " በሚባል ቀበሌ ከዚህ ቀደም በነበሩ ግጭቶች ተፈናቅለው ሸራ ወጥረው በሚገኙ ነዋሪዎች ላይ ጥቃት መከፈቱን የቲክቫህ ቤተሰቦቻችን መልዕክት ጠቁመዋል። ጥቃት አድራሾቹ ሸራውን ሙሉ ለሙሉ ማቃጠላቸውን እና ለመቋቋሚያ የተሰጣቸውን ቆርቆሮም መዘረፉ ተጠቅሷል። በአጠቃላይ በወረዳው ውስጥ ከሚገኙ ዘጠኝ ቀበሌዎች በ7ቱ ላይ ጥቃት የተፈጸመ ሲሆን አምስቱ ሙሉ ለሙሉ መቃጠላቸውን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡ ከፍተኛ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ እንደሚገኝ የገለጹት የአካባቢው ቤተሰቦቻችን ሶስት አመት ሙሉ በተመሳሳይ ችግር ውስጥ መሰቃየታቸውን ይናገራሉ። ችግሩ እንዲፈታ በተደጋጋሚ የክልልና የፌደራል መንግስት አካላት እንዲያውቁት ቢደረግም እዚህ ግባ የሚባል ምላሽ እንዳላገኙና ይበልጡኑ ይህ ችግር ባለበት ሁኔታ ያሉትን የጸጥታ ኃይሎች ማንቀሳቀስ ለችግሩ መስፋፋት አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የረመዳን ፆም ነገ ይጀምራል። 1443ኛው የረመዳን ፆም ነገ መጋቢት 24 ይጀምራል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ ቤት ጨረቃ ዛሬ ማምሻውን በመታየቷ ፆሙ ነገ ቅዳሜ እንደሚጀምር አረጋግጧል
+2
የረመዳን ፆም ነገ ይጀምራል። 1443ኛው የረመዳን ፆም ነገ መጋቢት 24  ይጀምራል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ ቤት ጨረቃ ዛሬ ማምሻውን በመታየቷ ፆሙ ነገ ቅዳሜ እንደሚጀምር አረጋግጧል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #Afar #WFP ወደ ትግራይ ጉዞ እንደጀመሩ የተገለፀላቸው የሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ወደ ክልሉ መግባት መጀመራቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) አስታውቋል፡፡ ተሽከር
+2
#Tigray #Afar #WFP ወደ ትግራይ ጉዞ እንደጀመሩ የተገለፀላቸው የሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ወደ ክልሉ መግባት መጀመራቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) አስታውቋል፡፡ ተሽከርካሪዎቹ ኢሬብቲ ደርሰው ወደ ትግራይ ማቋረጥ መጀመራቸውን የገለጸው ድርጅቱ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ መቐለ ይገባሉ ብሏል፡፡ ከ500 ሜትሪክ ቶን በላይ የተመጣጠነ ምግብ በርሃብ አፋፍ ላይ ለሚገኙ የእርዳታው ፈላጊዎች ይከፋፈላል ተብሏል። በተጨማሪ ፤ ከ1000 ሜትሪክ ቶን በላይ የተመጣጠነ ምግብ የጫኑ ሌሎች የእርዳታ ተሽከርካሪዎች ዛሬ ከሰዓት ሰሜናዊ አፋር መድረሳቸውንም የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታውቋል፡፡ የሰብዓዊ እርዳታው ፦ 👉 ዳሎል፣ 👉 በራህሌ 👉 ኮነባ አካባቢዎች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚደርስ ገልጿል። የዓለም ምግብ ፕሮግራም ተሽከርካሪዎቹ ደህንነታቸው ተጠብቆ በሰላም እንዲያልፉ የአፋር ክልላዊ መንግስት እና ህዝብ ትልቅ ድጋፍ እንዳደረገ ገልጿል። መረጃው የዓለም ምግብ ፕሮግራም የትዊተር ገፅ ነው። ፎቶ ፦ ወደ ትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ ጭነው እየተጓዙ የነበሩት ተሽከርካሪዎች (ከአፋር ክልል ቲክቫህ አባላት) @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR #MoE የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በ2013 ዓ.ም አገር ዐቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር
+2
#HoPR #MoE የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በ2013 ዓ.ም አገር ዐቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አቅም መገንባት እና ተዓማኒነትን ማሳደግ ላይ ቅድሚያ ተሰጥቶት ሊሰራ እንደሚገባ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ተናግረዋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) በበኩላቸው የትምህርት ተቋማትን ተዓማኒነት ለመሸርሸር የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ተገቢ አለመሆናቸውን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ አባላት የፈተና አሰጣጥ እና እርማት ሂደት እንዲሁም በፈተናዎች ደህንነት ዙሪያ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አቅርበዋል። በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እርማትና ውጤት አሰጣጥ ላይ ቅሬታ ያለበት ማንኛውም አካል ሂደቱን ለመፈተሽና ለማረጋገጥ ከፈለገ ማስተናገድና ግልጽነት መፍጠር እንደሚቻል የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፋንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በመጀመሪያው ዙር ከተሰጡት የትምህርት አይነቶች የሲቪክስ ትምህርት ፈተና እንደተሰረቀ የሚያሳዩ አሳማኝ መረጃዎች መቅረባቸውን ተከትሎ የሲቪክስ ውጤት ከዩኒቨርሲቲ መቁረጫ ነጥብ እንዲሰረዝ መወሰኑን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ሳሙዔል ክፍሌ (ዶ/ር) አስታውሰዋል። ከክልሎች የተውጣጡ የፖለቲካ አመራሮች እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በተገኙበት የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ትንተና እና የአስተራረም ሂደት ታይቶ የተፈጠረ ምንም አይነት ችግር እንዳልነበር የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር ተፈሪ ፈይሳ ጠቁመዋል። ምንጭ፦ የህ/ተ/ም/ቤት More @tikvahuniversity

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Ukraine #Russia የሩስያን ድንበር ጥሰው ገቡ የተባሉ ሁለት የዩክሬን ሂሊኮፕተሮች የነዳጅ ማከማቻ ላይ ጥቃት መፈፀማቸው ተሰማ። ሁለት የዩክሬን ሄሊኮፕተሮች የሩሲያን ስንበር ጥሰው በሀገሪቱ
+1
#Ukraine #Russia የሩስያን ድንበር ጥሰው ገቡ የተባሉ ሁለት የዩክሬን ሂሊኮፕተሮች የነዳጅ ማከማቻ ላይ ጥቃት መፈፀማቸው ተሰማ። ሁለት የዩክሬን ሄሊኮፕተሮች የሩሲያን ስንበር ጥሰው በሀገሪቱ ምዕራባዊ ከተማ ቤልጎሮድ የነዳጅ ማከማቻ ቦታ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን የአከባቢው አስተዳዳር ዛሬ አስታውቋል። የአካባቢው አስተዳዳሪ የሆኑት ቫያቼስላቭ ግላድኮቭ በቴሌግራም ቻናላቸው ላይ ሁለት የዩክሬን ጦር ሄሊኮፕተሮች በፈፀሙት የአየር ጥቃት በሚያስተዳድሩት አካባቢ ባለ የነዳጅ ማከማቻ ላይ የእሳት ቃጠሎ መነሳቱን ጽፈዋል። በቃጠሎው ምክንያት በነዳጅ ማከማቻው ውስጥ የነበሩ ሁለት ሰራተኞች መቁሰላቸው ተገልጿል። የዩክሬን እና ሩስያ ጦርነት ከተጀመረበት ጊዜ አብስቶ ሩስያ ፤ ዩክሬን ድንበሯን አልፋ ጥቃት ፈፀመችብኝ ብላ ሪፖርት ስታደርግ ይህ የመጀመሪያ ነው። የ2ቱ ሀገራት ጦርነት እስካሁን ድረስ ይህን ነው የሚባል መፍትሄ ሳይገኝለት ከወር በላይ ተቆጥሯል። አሁንም ጦርነቱ እንዲቆም ለማድረግ ንግግሮች ቢኖሩም ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ ግጭት እንዲቀጥል የሚያደርጉ ወታደራዊ ሁኔታዎች እንደሚስተዋሉ እየተነገረ ነው። በሀገራቱ ጦርነት ምክንያት ከሚጠፋው የሰው ህይወት ፣ ከሚሰደደው ሰው ባለፈ በዓለም ኢኮኖሚ እና በሀገራት የኑሮ ውድነት ላይ በየዕለቱ እያሳደረ ያለው ግልፅ ተፅእኖ እየከፋ ነው። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#እገዳው_ተነስቷል ! ለትንሳኤ በዓል ወደ እስራኤል በሚሄዱ ኢትዮጵያዊያን ላይ ተጥሎ የነበረው የቡድን ጉዞ እገዳ መነሳቱ ተገልጿል። የእስራኤል የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ለሚመጡ ጎብኚ
+1
#እገዳው_ተነስቷል ! ለትንሳኤ በዓል ወደ እስራኤል በሚሄዱ ኢትዮጵያዊያን ላይ ተጥሎ የነበረው የቡድን ጉዞ እገዳ መነሳቱ ተገልጿል። የእስራኤል የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ለሚመጡ ጎብኚዎች የቡድን ቪዛ እገዳ ጥሎ ነበር። ሚኒስቴሩ ውሳኔውን አሳልፎ የነበረው በኢትዮጵያ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት ተጓዦች ወደ እስራኤል ከመጡ አይመለሱም በሚል ስጋት ነበር። በተላለፈው ውሳኔው ላይ ቅሬታ የተሰማቸው የተለያዩ አካላት በተለይ በእየሩሳሌም የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ገዳም አባቶች ባቀረቡት አቤቱታ መሠረት፣ በእስራኤል የኢፌዴሪ ኤምባሲ ከእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ከእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፣ ከሕዝብና ኢሚግሬሽን ጉዳይ የሥራ ኃላፊዎች እና ከሌሎችም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ከተለያዩ አካላት ጋር በተደረገው ተደጋጋሚ ምክክር ውሳኔው የሁለቱን አገራት ወዳጅነት አንጻር ተገቢ አለመሆኑን አሳውቋል። በመቀጠልም ፤ የእስራኤል የፓርላማ አባል የሆኑት ጋዲ ይባርከን ጋር በመሆን ከእስራኤል ከሕዝብና ኢሚግሬሽን ባለስልጣን ኃላፊዎች ጋር በተደረገው ውይይት ተጥሎ የነበረው የጉዞ ገደብ የተነሳ መሆኑን በእስራኤል ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘው መረጃ ያሳያል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ከማለዳው ጀምሮ በተደረጉ 3 በረራዎች በጠቅላላው 1173 ወገኖቻችን አዲስ አበባ ገብተዋል። ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደተገኘው መረጃ ከሆነ ከረቡዕ ጀምሮ 2,111 ወገኖቻችን ከሳዑዲ
#ETHIOPIA ከማለዳው ጀምሮ በተደረጉ 3 በረራዎች በጠቅላላው 1173 ወገኖቻችን አዲስ አበባ ገብተዋል። ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደተገኘው መረጃ ከሆነ ከረቡዕ ጀምሮ 2,111 ወገኖቻችን ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። @tikvahethiopia