en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
ሰበር ‼️ ቁልፍ የመከላከያ አዋጊ እና መሪ በወረታ አከባቢ እየተደረገ ባለው ዉጊያ ተገደሉ። አስከሬናቸው አዲስአበባ ደርሷል። ይሄን የሚያሳይ እና የሚያረጋግጥ ቪድዮ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/BTPUmTK8WO8?si=QKdgVH88Nua6ISvl

አቶ በቀለ የኦሮሞ ፌደራሊስት ፓርቲ ለሚታገልለት ሕዝብ ከፍተኛ ተቆርቋሪ ድርጅት መሆኑን እራሳቸው እስከ መስዋትነት አሳልፈው ከሚሰጡ የፓርቲ አመራሮች ጋር በርካታ መራር ጊዜያትን ማሳለፋቸውን አስታውሰው፤ “እንደ ከዚህ ቀደሙ ከእነርሱ ጋር አብሬ መታገል እና መሥራት አለመቻሌን ሳስብ ትልቅ ሐዘን ነው የሚሰማኝ” ብለዋል። አቶ በቀለ ገርባ እራሳቸው ከኦፌኮ ፓርቲ አግልያለሁ ይበሉ እንጂ “ፓርቲው እና የኦሮሞ ሕዝብ በሚያደርገው ትግል በምፈለግበት ጊዜ ሁሉ ለመገኘት ዝግጁ ነኝ” ብለዋል። “ፖለቲካ አቆምኩ ማለት አይደለም። ስለ ኦሮሞ ሕዝብ መናገር አቆማለሁ ማለት አይደለም። ኦሮሞ በሚፈልገኝ ወቅት የኦሮሞ ተቋም በሚፈልግበት ወቅት እና ጊዜ አቅሜ በፈቀደ ሁሉ ለመገኘት ዝግጁ ነኝ።” አቶ በቀለ ከፓርቲያቸው ምንም አይነት ጫና በየትኛውም መልኩ እንዳልደረሰባቸው እና ከፓርቲው አመራሮች ጋር ተከባብረው መሥራታቸውን እንዲሁም በይፋ ከፓርቲው ቢለያዩ ደስታቸው ይሆን እንደነበር ገልጸዋል። አቶ በቃለ ከፓርቲው መለየታቸው በፖለቲካ ፓርቲው ላይ ምንም አይነት አሉታዊ ተጽእኖ ሊፈጠር ይችላል የሚል እምነት እንደሌላቸውም ተናግረዋል። የአርቲስ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ በቀለ ገርባ፣ ጃዋር መሐመድ እና ሌሎች እስረኞችን ጨምሮ በርካቶች ለቀናት የረሃብ አድማ ማድረጋቸው ይታወሳል። እነ አቶ በቀለ ፖለቲከኞች ላይ የሚደርሰውን እንግልት እና እስር እንዲሁም በሌሎች ላይ የሚፈጸም እስር እና ወከባ እንዲቆም ለመጠየቅ ነበር የረሃብ አድማ ሲያደርጉ የቆዩት። አቶ በቀለን ጨምሮ ፖለቲከኞቹ በረሃብ አድማ ለረዥም ቀናት በመቆየታቸው ከፍተኛ የሆነ የጤና መቃወስ አጋጥሟቸው ነበር። አቶ በቀለ በአሁኑ ወቅት ጤናቸው በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ “አሁን ላይ ሙሉ ጤና አለኝ። ከዚህ ቀደም አደርገው የነበረውን ነገር በሙሉ እያደረግኩ ነው። ከየትኛውም ጊዜ በላይ ጤንነት እየተሰማኝ ነው” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። BBC @topMereja

አቶ በቀለ ገርባ ከኦፌኮ መልቀቃቸውን እና በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ተናገሩ ለረዥም ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበሩት አቶ በቀለ ገርባ ከፓርቲያቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) በመልቀቅ በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ። አቶ በቀለ ለቢቢሲ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ “በሰላማዊ መንገድ ለመታገልም ሆነ በግል በነጻነት መኖር” አሳሳቢ በመሆኑ በሄዱበት በአሜሪካ ለመኖር ጥገኝነት መጠየቃቸውን ገልጸዋል። የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል የሆኑት አቶ በቀለ፣ በውጭ አገር ሆነው ሥልጣኑን ይዘው መቀጠለቸው ጠቃሚ ስላልሆነ እራሳቸውን ከፓርቲው ለማግለል መወሰናቸውንም ተናግረዋል። አቶ በቀለ ገርባ ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ተፈጥሮ የነበረውን ሁከት ተከትሎ በቁጥጥር ሥር ውለው ለ18 ወራት በእስር ላይ ቆይተው ከተለቀቁ በኋላ ወደ አሜሪካ ተጉዘዋል። አቶ በቀለ ከእስር ከወጡ በኋላ ወደ አሜሪካ ሲጓዙ ዓላማቸው የእርሳቸውን ከእስር መለቀቅ ሲጠይቅ ለነበረው የዳያስፖራ ማኅብረሰብ ምስጋና ለማቅረብ እንጂ በዚያው የመቅረት ዕቅድ እንዳልነበራቸው ጨምረው ተናግረዋል። “ወደዚህ አገር ከመጣሁ አንድ ዓመት ከሦስት ወር ሆኖኛል። መጀመሪያ ስንመጣ የነበረኝ ዕቅድ በውጭ ከሚኖረው ሕዝባችን ጋር ተገናኝተን፣ አንደኛ ከእስር እንድንለቀቅ ላደረጉት ትግል ለማመስገን ሁለተኛ ደግሞ ወደፊት ምን ማድረግ አለብን የሚለው ላይ ለመወያየት ነበር” ብለዋል። አቶ በቀለ አሜሪካ በቆዩባቸው 15 ወራት በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ በመቀየሩ “ወደዚያ አገር መመለሱ አስፈላጊ መስሎ አልታየኝም” ብለዋል። ወደ አገር እንዳይመለሱ ያደረገቸው በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታን ሲያስረዱም “በኢትዮጵያ የፖለቲካ ለውጥ ከመጣበት ወዲህ በተለይ ደግሞ ያለፈው ዓመት እጅግ አደገኛ ነው” ብለዋል። “ከአንድ ዓመት ወዲህ ያለው በጣም የሚያሳዝን ነው። ሰዎች ከእስር ቤት እየተወሰዱ ይገደላሉ፣ የፈለገ አካል ሰው ይዞ ያስራል፣ የሰዎች አድራሻ ይጠፋል፣ ሰው ከመሬቱ ይፈናቀላል፣ ኦሮሞ ድንበሩ ተሰብሮ ቤቱ ይቃጠላል፣ በሕይወት እያለ በቁሙ በእሳት ይቃጠላል፣ እራሱ በቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ ተገድሎ እንዲቀበር የሚደረግም አለ።” የፖለቲካ ፓርቲዎች ጽሕፈት ቤት ሙሉ ለሙሉ ማለት በሚባልበት መልኩ ተዘግተዋል የሚሉት አቶ በቀለ፤ በዚህ ምክንያት በአገሪቱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ አይቻልም ብለዋል። “በዚህ ሁኔታ ውስጥ በሕይወት እንኳ መቆየት አሳሳቢ የሆነ ደረጃ ላይ ተደርሷል። ሁለተኛ ደግሞ ወደዚያ አገር በመመለስ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ስለማይቻል እና የማመጣው ውጤት ስለማይኖር እዚሁ ለመቆየት ወስኛለሁ።” አቶ በቀለ ከዚህ ቀደም ወደ አገር ቤት በተመለሱበት ጊዜ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ወደነበራቸው የመምህርነት ሥራ መመለስ እንዳልቻሉ ሲያስረዱ፣ “ከእስር ቤት እንደወጣሁ ዩኒቨርሲቲው እድሜህ 60 ዓመት ሞልቷል በማለት ጡረታ አስወጥቶኛል” ብለዋል። “ከእስር ቤት እንደወጣሁ ደብዳቤ ላኩልኝ። 60 ዓመት ስለሞላህ ጡረታ ወጥተሃል አሉኝ። ጡረታዬን ለማስከበር ያደረኩት ጥረትም ሳይሳካ ቀርቷል። ዕድሜ ልኬን ስለፋበት የነበረውን ሳላገኝ ቀርቻለሁ። በዚህም ባዶ እጄን በሰው አገር ለመቅረት ተገድጃለሁ።” አቶ በቀለ ገርባ ወደ ኢትዮጵያ ቢመለሱ ለሕይወታቸው አስጊ መሆኑን አሁን ባሉበት አገር ማሳወቃቸውን እና የጥገኝነት ማመልከቻቸውን ማስገባታቸውንም ገልጸዋል። ተስፋ መቁረጥ አቶ በቀለ ገርባ ከዚህ ቀደም ከአንድም ሁለት ጊዜ ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱት ሰላማዊ የፖለቲካ ተሳትፎን ተስፋ በማድረግ መሆኑን አስታውሰው፣ “አሁን ግን ምንም አይነት ተስፋ የለም” ብለዋል። እውቁ ፖለቲከኛ እአአ 2015 ላይ ለጉብኝት ወደ አሜሪካ በሄዱበት ወቅት ወደ አገራቸው ቢመሰሉ ሕይወታቸው አደጋ ላይ ሊወድቅ ይችላል ለሚባሉ ምሁራን ድጋፍ የሚሰጠው ‘ስኮላርስ አት ሪስክ’ የተባለ ተቋም፣ በአሜሪካ በቋሚነት የሚኖሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ያቀረበላቸውን ጥያቄ ውድቅ አድርገው ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ተናግረዋል። አቶ በቀለ ከዚህ ጉብኝታቸው መልስ በኢትዮጵያ ለእስር መዳረጋቸውን በመግለጽ፣ እአአ 2018 ላይም ከእስር ወጥተው ወደ አሜሪካ በተጓዙበት ወቅት የተጠቀሰው ድርጅት በአሜሪካ በቋሚነት የሚኖሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በድጋሚ ቢጠይቃቸውም፣ በፓርቲያቸው በኩል የጀመሩትን ትግል ለማስቀጠል ዳግም ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ይገልጻሉ። አቶ በቀለ የቀረበላቸውን ዳግም ጥያቄ ውድቅ አድርገው ኢትዮጵያ ከገቡ በኋላ ለሦስተኛ ጊዜ ለእስር ተዳርገዋል። ከእስር በኋላም ባለፈው ዓመት ወደ አሜሪካ ተጉዘው ሁለት ጊዜ የመኖሪያ ፈቃድ ለማመቻቸት ጥያቄ አቀርቦላቸው የነበረውን ድርጅት ጠይቀው ሦስተኛ ዕድል አልሰጠም የሚል ምላሽ እንዳገኙ ገልጸዋል። “ማሸነፍ የምንችል ከሆነ ሕዝብ ሊጠቅም የሚችል ፖሊሲ ቀርጸን አገር የማስተዳደር ተስፋ አለን ብለን ነበር ለሁለተኛ ጊዜ የቀረበልኝን ዕድል ትቼ ወደ አገር ቤት የተመለስኩት። አሁን ግን በጭራሽ ምንም አይነት ተስፋ የለም” ብለዋል። “እንደ ኦፌኮ አመራር የመጨረሻ ቃሌ ነው” አቶ በቀለ ረዥም የፖለቲካ ሕይወት ካሳለፉባት የትውልድ አገራቸው ተሰደው በውጭ አገር በስደት ለመኖር የወሰኑት ከእስር ለመውጣት ከመንግሥት ጋር የደረሱት አንዳች የስምምነት አካል ይኖር ይሆን? ተብለው የቀረበላቸውን ጥያቄ አስተባብለዋል። አቶ በቀለ ከበርካታ ፖለቲከኞች ጋር ለእስር ከተዳረጉ በኋላ “ከእስር ለመውጣት የቀረበልኝ አንዳችም ቅድመ ሁኔታ የለም ብለዋል፤ ከአገር እስከወጣሁበት ጊዜ ድረስ የደረሰኝ አንዳችም ማስጠንቀቂያ የለም” በማለት የተለቀቁበትን ሁኔታ ገልጸዋል። ከ2001 ዓ.ም. ጀምሮ በፖለቲካ ቀጥተኛ ተሳትፎ ውስጥ የቆዩት አቶ በቀለ ገርባ “ይህ ቃለ መጠይቅ እንደ የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ መንበር ሆኜ የምሰጠው ቃሌ ነው” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። አቶ በቀለ የፖለቲካ ፓርቲ አስፈላጊ የሚሆነው ሕዝብን የሚጠቅም ፖሊሲ ሲያወጣ፣ ዕድሉን ካገኘ ደግሞ መንግሥት መመሥረት፣ ካልሆነም ለመንግሥት ምክረ ሃሳቦችን መለገስ ነው የሚሉት አቶ በቀለ “አሁን ባለው ሁኔታ ግን እነዚህ አማራጮች ሙሉ በሙሉ ዝግ ናቸው” ይላሉ። “ስለዚህ እኔ አሁን ላይ የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ መቆየቱ አያስፈልገኝም። ለፖለቲካዊ ሥልጣን እየተንቀሳቀስኩም አይደለም፤ በፖለቲካ ፓርቲ ስም በዚያ አገር ሕዝብ እያንቀሳቀስኩ አይደለም፤ ለዚያ ሕዝብ እየሠራሁ አይደለም፤ ይህን ለማድረግ ዕድሉ የለኝም።” በዚህም የተነሳ አቶ በቀለ አሁን ካሉበት ሁኔታ አንጻር በኦፌኮ ፓርቲ ውስጥ ባላቸው ተሳትፎ መቀጠሉ አስፈላጊ ሆኖ ስላልታያቸው ፓርቲውን መልቀቃቸውን ተናግረዋል። “ይህ ቃለ መጠይቅ ምናልባት እንደ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ተቀዳሚ ሊቀ-መንበር ሆኜ የምሰጠው ቃሌ ነው። ከአሁን በኋላ እንደማንኛውም ለኦሮሞ ሕዝብ እንደሚቆረቆር ሰው፣ እንደ አንድ ኦሮሞ እንጂ እንደ ፓርቲ አመራር የምቀጥል አይሆንም።” አቶ በቀለ እራሳቸውን ከኦሮሞ ፌደራሊስት ፓርቲ የማግለላቸውን ውሳኔ እስካሁን ድረስ ለፓርቲያቸውም ሆነ ለየትኛውም ሰው አለመናገራቸውን ገልጸዋል። “በዚህ ጉዳይ ብዙ ሳስብ ቆይቻለሁ። ጥቅሙ [ፓርቲው ውስጥ መቆየቴ] ስላልታየኝ በቅርቡ ከውሳኔ ላይ ደርሻለሁ” በማለት በኦፌኮ ውስጥ የነበራቸው ኃላፊነት እና ተሳትፎ ማብቃቱን ተናግረዋል።

photo content

ሰበር ‼️ አራት ኦራል የመከላከያ ሰራዊት ( 2 ሪፐብሊካን ጋርድ የጫነ ) ሙሉ በሙሉ ተደመሰሰ። ይህን የሚያሳይ እና የሚያረጋግጥ ቪድዮ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/d6RQKtQhkDc?si=N62-5zslCGQTijcj https://youtu.be/d6RQKtQhkDc?si=N62-5zslCGQTijcj

"የአማራ ህዝባዊ ሀይሎች የጠየቁኝ ድጋፍ የለም። ህዝቡ በራሱ የታጠቀ ነው። የታጠቁት የጦር መሳሪያ ብቻ ሳይሆን ቁርጠኝነትና አልሸነፍ ባይነትን ጭምር ነው።እንዲህ አይነቱን ሀይል ማሸነፍ አይቻልም።"
"የአማራ ህዝባዊ ሀይሎች የጠየቁኝ ድጋፍ የለም። ህዝቡ በራሱ የታጠቀ ነው። የታጠቁት የጦር መሳሪያ ብቻ ሳይሆን ቁርጠኝነትና አልሸነፍ ባይነትን ጭምር ነው።እንዲህ አይነቱን ሀይል ማሸነፍ አይቻልም።" ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ሰሞኑን የተናገሩት @topMereja

ሰበር ዜና ‼️ የአማራ ክልል ምክር ቤት አሁን እያደረገ በሚገኘው አስቸኳይ ጉባኤ የክልሉን አዲስ ፕረዝዳንት ሾመ። ይህን የሚያሳይ እና የሚያረጋግጥ የምክር ቤቱ ቪድዮ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/Ec-izrQG_nE?si=SbLlxXPa70dvMSCx

የአማራ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ይሰበሰባል።የወቅቱ የክልሉ ፕሬዝደንት ዶ/ር ይልቃል ከፈለን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች ትናንት ከሰዓት በኋላ ባህርዳር መግባታቸው ታውቋል።በዛሬው የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብ
የአማራ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ይሰበሰባል።የወቅቱ የክልሉ ፕሬዝደንት ዶ/ር ይልቃል ከፈለን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች ትናንት ከሰዓት በኋላ ባህርዳር መግባታቸው ታውቋል።በዛሬው የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ ሹም ሽር እንደሚካሄድ ይጠበቃል። የምክር ቤቱ ሂደት እና ውሎ በተከታዩ ቻናል ወደ እናንተ ይደርሳል። Subscribe በማድረግ ተቀላቀሉ።

በሃንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለፍጻሜ አለፉ፡፡ በ5ሺህ ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ ሀ
በሃንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለፍጻሜ አለፉ፡፡ በ5ሺህ ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ ሀጐስ ገ/ሕይወት እና በሪሁን አረጋዊ ለፍፃሜ አልፈዋል፡፡

ሰበር ዜና ጀነራል አበባዉ ላይ ግድያ! እና ሌሎች መረጃዎች 👇👇 https://youtu.be/rKb_nBawRqA

ሰበር መረጃ ‼️ በልዩ ሁኔታ ሰልጥነዋል የተባሉት የሪፓብሊካን ጋርድ ኮማንዶዎች ተማረኩ። ይህን የሚያሳይ እና የሚያረጋግጥ ቪድዮ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/BDshmPceaH4 https://youtu.be/BDshmPceaH4

የታሰሩት የምክር ቤት አባላት የት ናቸው ? በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተያዙ የም/ቤት አባላት ታስረውበት ከነበረው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የማቆያ ቦታ እንደሌሉ እና ያሉበትን ቦታ ማወቅ እንዳልቻሉ ከጠ
+1
የታሰሩት የምክር ቤት አባላት የት ናቸው ? በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተያዙ የም/ቤት አባላት ታስረውበት ከነበረው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የማቆያ ቦታ እንደሌሉ እና ያሉበትን ቦታ ማወቅ እንዳልቻሉ ከጠበቆቻቸው አንዱ ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት በሰጡት ቃል ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እንዲሁም በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ እና የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ካሳ ተሻገር ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ለቤተሰቦቻቸው ቢገለጽም፣ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀርተዋል። በተጨማሪ እስካሁን ድረስ ቤተሰቦቻቸውም ይሁን ጠበቆቻቸው ሁለቱ ታሳሪዎች ያሉበትን ቦታ እንዳላወቁ ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ ተናግረዋል። ጠበቃ ሔኖክ ምን አሉ ? " ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሚያቀርቧቸው ከቤተሰቦቻቸው ሰምተን ፍርድ ቤት ተገኝተን ነበር፤ አልቀረቡም። በኋላ ላይ ስናጣራ ይገኙበት በነበረው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ውስጥ እንደሌሉ እና ለጊዜው ያላረገገጥነው ቦታ እንደተወሰዱ ሰምተናል። ቤተሰቦቻቸውም ወደ እስር ቤቱ አስገብተውላቸው የነበሩ ንብረቶችን መውሰድ እንደሚችሉ ተነግሯቸዋል። በሐዘን እና በከፍተኛ የስሜት መሰበር ላይ ይገኛሉ። አንዳንድ ቤተሰቦቻቸውም ሌላ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይችላል በሚል የመረበሽ ስሜት ውስጥ ናቸው። 11፡00 ሰዓት ላይ ሊነጋጋ ሲል ነው የወጡት'፣ 'ወደ አዋሽ ተወስደዋል'  ከሚል ያልተረጋገጠ ወሬ በስተቀር የት እንዳሉ አናውቅም ብለዋል። @topMereja

ሰበር መረጃ ‼️ በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህርዳር ከባድ ፍንዳታ ተከሰተ። የቦንብ ጥቃት። ይህን የሚያሳይ እና የሚያረጋግጥ ቪድዮ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/a-cd0e9KLQA https://youtu.be/a-cd0e9KLQA

የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ በሰሜኑ ጦርነት በአገሪቱ ላይ ለደረሰው ውድመት መልሶ ግንባታ ኢትዮጵያ የዓለማቀፍ ተቋማትን ድጋፍ በጽኑ ትፈልጋለች በማለት መናገራቸውን ፋይናንሻል ታይምስ ዘ
የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ በሰሜኑ ጦርነት በአገሪቱ ላይ ለደረሰው ውድመት መልሶ ግንባታ ኢትዮጵያ የዓለማቀፍ ተቋማትን ድጋፍ በጽኑ ትፈልጋለች በማለት መናገራቸውን ፋይናንሻል ታይምስ ዘግቧል። ዜና ምንጩ፣ አገሪቱ ለመልሶ ግንባታ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ሚንስትሩ ነግረውኛል ብሏል። የፌደራሉና ክልል መንግሥታት ከበጀታቸው ከፊሉን ለመልሶ ግንባታ እንደሚመድቡ የገለጡት አሕመድ፣ ከኹሉም በላይ ግን የዓለም ባንክ ድጋፍ ያስፈልገናል ማለታቸውን ጠቅሷል። አሕመድ፣ መንግሥት ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት ጋር የጀመረው የብድር ድርድር ከፍተኛ ደረጃ መድረሱንም ተናግረዋል ተብሏል።(ዋዜማ) @topMereja

ሰበር መረጃ ‼️ ፋኖ በድጋሜ ዋና ከተማዋን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ ። ነገሮች ተቀያየሩ። ይህን የሚያሳይ እና የሚያረጋግጥ ቪድዮ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/k9k7Tt9NvFg https://youtu.be/k9k7Tt9NvFg

በአዲስ አበባ የሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ ተነሳ‼️ በአዲስ አበባ የሚገኙ የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች በሙሉ ከነገ ነሐሴ 15/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:
በአዲስ አበባ የሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ ተነሳ‼️ በአዲስ አበባ የሚገኙ የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች በሙሉ ከነገ ነሐሴ 15/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ ከአሽከርካሪው ውጪ ሌላ ተጨማሪ ተሳፋሪ ሳይጨምሩ የሞተር ብስክሌት ማሽከርከር እንደሚቻል የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል፡፡ ከተፈቀደው የሰው መጫን አቅም በላይ በሚጭኑ ማህበራትና አሽከርካሪዎች ላይ ቢሮው ጥብቅ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ገልጿል። አሽከርካሪዎችም ለትራፊክ አደጋ መንስኤ ከሆኑ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር፣ የራስ ቆብ መከለያ (ሄልሜት) አለመጠቀም፣ ከወንጀል ድርጊት በመራቅና ወንጀል የሚፈጽሙ ሲያጋጥሙም ለጸጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡ ቢሮው አሳስቧል። @topMereja

ሰበር ‼️ አምስት ኦራል የመከላከያ ሰራዊት ( 2 ሪፐብሊካን ጋርድ ) ሙሉ በሙሉ ተደመሰሱ። ይህን የሚያሳይ እና የሚያረጋግጥ ቪድዮ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/vSMlZKJTpYM https://youtu.be/vSMlZKJTpYM

የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ከሃላፊነታቸው መነሳታቸውን የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ 👉🏼 የቀድሞው ከንቲባ በህግ ይጠየቃሉም ተብሏል የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማር
የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ከሃላፊነታቸው መነሳታቸውን የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ 👉🏼 የቀድሞው ከንቲባ በህግ ይጠየቃሉም ተብሏል የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ በትናንትናው እለት በክልሉ ሲካሄድ የቆየዉን የግምገማ እና የ 2015 ዓ.ም አፈጸጸም ዉይይት መጠናቀቁን በማስመልከት የተላለፉ ዉሳኔዎችን አሳዉቀዋል። በዚህም መሰረት የህዝብን ተጠቃሚነት የሚጎዱ ብልሹ አሰራሮች መስተዋሉን ሀላፊዉ አንስተው ጠንካራ ፓርቲ እና የአመራር ውጤታማነት ከመገንባት አንፃር ብልሹ አሰራር ፣ ከሌብነት ጋር በተያያዘ የአፈር ማዳበሪያ ስርቆት ፣ የሀዋሳ ከተማ ኮንትራት አስተዳደር እንዲሁም ሌሎች ጉዳዮች መስተዋሉን በመግለጽ እኚህን መሰል ብልሹ አሰራሮችን የሚያርም ጠንካራ የግምገማ መድረክ መካሄዱን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ የነበሩት ረ/ፕ/ር ጸጋዬ ቱኬ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ መደረጉን ተናግረዋል። ከዚህ በዘለለም የህግ ተጠያቂነት እንደሚረጋገጥባቸዉ አቶ አብርሃም ማርሻሎ መናገራቸውን ብስራት ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ሰምቷል። የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ፕረስ ሰክረታሪ የከንቲባዉ ለሀላፊነት መነሳት የተሳሳተ መረጃ እና ሴራ ነዉ ሲል ገልጾት ነበር። @topMereja

ሰበር ዜና!! የመከላከያ መኪና ነደደ። ፋኖ ከተማ ያዘ ሙሉ መረጃ https://youtu.be/PTkWoV00DAA

ሰበር መረጃ ‼️ በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ከባድ ፍንዳታ ተከሰተ። ያልተጠበቀ ጥቃት ተፈፀመ።  ይህን የሚያሳይ እና የሚያረጋግጥ ቪድዮ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/oZEiI0_oPUw https://youtu.be/oZEiI0_oPUw