en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
#Update አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው፡፡
+1
#Update አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው፡፡ በዚህም የፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ የሥራ ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው መሾማቸው ተገልጿል። አምባሳደር ታዬ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ከመሾማቸው በፊት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ፡፡ @topmereja

#Update አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው፡፡ በዚህም የፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ የሥራ ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው መሾማቸው ተገልጿል። አምባሳደር ታዬ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ከመሾማቸው በፊት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ፡፡ @topmereja

በመዲናዋ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና ተቋማት እውቅና ተሰጠ በመርሐ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የከተማ አስተዳደሩ ት/ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር)፣ የትምህርት አ
+1
በመዲናዋ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና ተቋማት እውቅና ተሰጠ በመርሐ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የከተማ አስተዳደሩ ት/ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር)፣ የትምህርት አመራሮች፣ ተሸላሚ ተማሪዎችና ወላጆቻቸው ተገኝተዋል፡፡ በመድረኩ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ላፕቶፕና ታብሌቶችን ጨምሮ የተለያዩ ሽልማቶች የተበረከቱ ሲሆን ÷በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበችው ተማሪ ሲፈኔ ተክሉን ጨምሮ ለሶስት ተማሪዎች የውጭ ሀገር የትምህርት ዕድል ተሰጥቷል፡፡ ከዚህ ባለፈም ተማሪዎቻቸውን ሙሉ ለሙሉ ያሳለፉ የትምህርት ተቋማት ዕውቅና እንደተሰጣቸው የከተማ አስተዳደሩ ት/ቢሮ መረጃ ያመላክታል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ መንግስት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የተማሪዎች ውጤት መሻሻል እያሳየ እንደሚገኝ ገልፀው÷ከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክር አስገንዝበዋል፡፡ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው÷ በከተማ አስተዳደሩ በ2016 ዓ.ም 21ነጥብ 4 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን እና ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ5 በመቶ እድገት መመዝገቡን ጠቁመዋል፡፡ @topmereja

photo content

ተቃዋሚው ባይቶና በትግራይ ሁሉን አካታች ምክር ቤት እንዲቋቋም ጥሪ አቀረበ!! ባይቶና "ግዚያዊ አስተዳደሩ ሐላፊነቱን መተግበሩ አለመተግበሩን መከታተል የሚቻለው ምክርቤት ሲኖር ነው"ይላል።የትግራይ
+1
ተቃዋሚው ባይቶና በትግራይ ሁሉን አካታች ምክር ቤት እንዲቋቋም ጥሪ አቀረበ!! ባይቶና "ግዚያዊ አስተዳደሩ ሐላፊነቱን መተግበሩ አለመተግበሩን መከታተል የሚቻለው ምክርቤት ሲኖር ነው"ይላል።የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር የስራ አፈፃፀሙን፣ በጀት እና ዕቅድ የሚከታተል የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪል ማሕበራት እና ሌሎችን ያካተተ ምክርቤት ለማቋቋም ባለፈው ዓመት አዋጅ አጽድቋል። ምክርቤት ግን እስካሁን ወደ ስራ አልገባም። በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው እና በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር የካቢኔ አባላት የሚያሳትፈው የታላቋ ትግራይ ብሔራዊ ሸንጎ ባይቶና እንደሚለው በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መሰረት የተቋቋመው የክልሉ ግዚያዊ አስተዳደር የሚከታተል ምክርቤት እንዲቋቋም ጠይቋል። ግዚያዊ አስተዳደሩ በርካታ ሐላፊነቶቹne በሚገባ እየተወጣ አይደለም የሚለው ባይቶና፥ ይህን ለመፍታት እና ተጠያቂነት ለማረጋገጥ ሁሉን አካታች ምክርቤት እንዲቋቋም ጥሪ አቅርቧል። የባይቶና ሊቀመንበር አቶ ክብሮም በርሃ "ግዚያዊ አስተዳደሩ ሐላፊነቱን መተግበሩ አለመተግበሩ መከታተል የሚቻለው ምክርቤት ሲኖር ነው" ይላሉ። የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር የስራ አፈፃፀሙ፣ በጀት እና ዕቅድ የሚከታተል የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪል ማሕበራት እና ሌሎች ያካተተ ምክርቤት ለማቋቋም ባለፈው ዓመት አዋጅ ማፅደቁ ይታወሳል። ሕወሓት ብቻውን ትግራይን ወክሎ መደራደር የለበትም መባሉ ይህ ተከትሎ ከሰባት ወራት በፊት ማብራሪያ ሰጥተው የነበሩት በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር በምክትል ፕሬዝደንት ማዕርግ የዴሞክራታይዜሽን እና ያልተማከለ አስተዳደር ዘርፍ ሐላፊ ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ የሚቋቋመው ምክርቤት ሁሉ አካታች እና የመወሰን ስልጣን ያለው ብለውት ነበር። @topmereja

#ኢትዮጵያ «እየተተኮሰብን ነው አምልጠን የወጣነው » ሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የእሥራኤል ጦር ሰሞኑን ሊባኖስ ውስጥ የሚገኘውን የሂዝቦላህ ቡድን ለማጥቃት የከፈተውን መጠነ ሰፊ ውጊያ ሸሽተው ከ
+1
#ኢትዮጵያ «እየተተኮሰብን ነው አምልጠን የወጣነው » ሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የእሥራኤል ጦር ሰሞኑን ሊባኖስ ውስጥ የሚገኘውን የሂዝቦላህ ቡድን ለማጥቃት የከፈተውን መጠነ ሰፊ ውጊያ ሸሽተው ከ1 ,2 ሚሊዮን በላይ ሊባኖሳውያን መፈናቀላቸው ተሰምቷል። በቤት ሰራተኝነት ተቀጥረው ለመስራት ወደ ሊባኖስ የሄዱ እንደ የኢትዮጵያ፣ ፊሊፒንስ፣ ሲሪላንካ እና የሱዳን ሀገር ዜጎችም ከመፈናቀል እና መሰደድ አልዳኑም። የመካከለኛው ምሥራቅ ውጥረት በአሳሳቢ ደረጃ ተባብሶ ቀጥሏል። እስራኤል የሂዝቦላህ ቡድንን ለማጥቃት በምድር ጭምር ካለፈው ማክሰኞ አንስቶ ወደ ሊባኖስ ስትዘምት፤ የሂዝቦላህ ቡድንን የምትደግፈው ኢራን ሚሳኤሎቿን ወደ እስራኤል አስወንጭፋለች። የእሥራኤል ጦር ኢላማዎቹን ማጥቃት ቀጥሏል። ለደህንነታቸው ሲሉ የደቡባዊ ሊባኖስ ነዋሪዎች 20 ከተሞችን ለቀው እንዲወጡም ሰሞኑን ማስጠንቀቂያ አስተላልፋለች። ከ1,2 ሚሊዮን በላይ ሊባኖሳውያን እስካሁን ከቀያቸው መፈናቀላቸው ተሰምቷል። የፈረንሳይ ዜና ምንጭ እንደዘገበው እስራኤል ደቡባዊ ሊባኖስ ውስጥ የሂዝቦላህ ታጣቂዎች ላይ በከፈተችው ጥቃት ሳቢያ ሊባኖስ ዋና ከተማ ቤሩት የሚገኙ ​​ትምህርት ቤቶች፣ ሆቴሎች እና መኖሪያ ቤቶች በተፈናቃዮች ተጣበዋል። አንዳንዶች እንደውም ጎዳና ላይ ተጠልለው ይገኛሉ። በስልክ ያነጋገርናት ኢትዮጵያዊት ቅድስት ለአራት ቀናት ያህል ጎዳና ላይ ነበርን ብላለች። « ዳውራ ፤ዳውን ታውን የሚባል ቦታ ለአራት ቀናት ያህል ሜዳ ላይ ነበርን። አሁን ሀበሾች ብር አዋጥተው የቤት ኪራይ ከፍለውልን ጀበል የሚባል ቦታ ነው ያለነው።» @topmereja

በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ ቤቶችን ማፍረሱን ሰመራ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ!! በአዋሽ ፈንታሌ እና አካባቢው ትናንት ምሽት የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ መኖሪያ ቤቶ
በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ ቤቶችን ማፍረሱን ሰመራ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ!! በአዋሽ ፈንታሌ እና አካባቢው ትናንት ምሽት የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ መኖሪያ ቤቶችን ማፍረሱን ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው መረጃው አመልክቷል። በመሬት መንቀጥቀጡ መሬት መሰንጠቁንም ዩኒቨርቲው ዛሬ ሰኞ ማለዳ አስታውቋል። በፈንታሌ ተራራ ላይ ተከስቶ ንዝረቱ አዲስ አበባ ከተማ ድረስ የተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ከሁለት ሳምንታት በላይ በተለያየ አጋጣሚ መከሰቱን ባለሞያዎቹ ገልፀዋል። ትናንት መስከረም 26/2017 ምሽት 2፡10 ገደማ የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበበት ነበር። ከሰሞኑ የሚስተዋለው የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሽ ፈንታሌ እና አካባቢው ከፍተኛ ሥጋት ፈጥሯል ያለው ዩኒቨርሲቲው፣ አደጋው በተከሰተበት ሳቡሬ ቀበሌ ተገኝቶ መረጃ የመሰብሰብ እና ለማህበረሰቡ ጥንቃቄ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ መሥራቱንም ገልጿል። @topmereja

ቴለግራም የሃሳብ ነጻነት መድረክ ወይስ የወንጀለኞች መሸሸጊያ? አዲሱ የቴሌግራም የግላዊነት ማሻሻያ የተጠቃሚዎችን መረጃ ለባለስልጣናት አሳልፎ የሚሰጥ በመሆኑ እያከራከረ ነው። አንዳንዶች የተጠቃሚን
+1
ቴለግራም የሃሳብ ነጻነት መድረክ ወይስ የወንጀለኞች መሸሸጊያ? አዲሱ የቴሌግራም የግላዊነት ማሻሻያ የተጠቃሚዎችን መረጃ ለባለስልጣናት አሳልፎ የሚሰጥ በመሆኑ እያከራከረ ነው። አንዳንዶች የተጠቃሚን መረጃዎች ለመንግስታት ማጋራት ወንጀልን ለመዋጋት ይረዳል ሲሉ፤ በሌላ በኩል መንግስታት ዜጎቻቸውን እንዲሰልሉእና እንዲጨቁኑ ይረዳቸዋል።በማለት ይከራከራሉ ቴሌግራም በግላዊነት ፖሊሲው ላይ ትልቅ ማሻሻያ ማድረጉን በቅርቡ አስተውቋል። ነገር ግን አዲሱ የቴሌግራም የግላዊነት ማሻሻያ የተጠቃሚዎችን መረጃ ለባለስልጣናት አሳልፎ የሚሰጥ በመሆኑ እያከራከረ ነው። አንዳንዶች የተጠቃሚን መረጃዎች ለመንግስታት ማጋራት ወንጀልን ለመዋጋት ይረዳል ሲሉ፤ በሌላ በኩል መንግስታት ዜጎቻቸውን እንዲከታተሉ እና እንዲጨቁኑ ይረዳቸዋል።በማለት ይከራከራሉ።የዛሬው የሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዝግጅት፤ በአዲሱ የቴሌግራም የግላዊነት ፖሊሲ ላይ በማተኮር የተሰናዳ ነው። ቴሌግራም በግላዊነት ፖሊሲው ላይ ትልቅ ማሻሻያ ማድረጉን በቅርቡ አስተውቋል። የመልዕክት መላላኪያ መተግበሪያው አሁን ለህጋዊ ጥያቄዎች ምላሽ የተጠቃሚ ውሂብን ለባለስልጣኖች ያጋራል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ900 ሚሊዮን በላይ ንቁ ተጠቃሚዎች ያሉት ቴሌግራም፤ሁለት ዋና ዋና አገልግሎቶችን ለተጠቃሚዎቹ ይሰጣል፡ አንደኛው የመልዕክት መላላኪያ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የማህበራዊ ትስስር መድረክ ሆኖ ያገለግላል። ከታዋቂ የመረጃ መለዋወጫ መተግበሪያዎች አንዱ የሆነው ቴሌግራም፡ ሚስጥራዊ ውይይቶችን ለማድረግ የሚፈቅድ ልዩ ባህሪ አለው። ይህም ሁለቱም ተጠቃሚዎች ማለትም ለኪውም ሆነ ተቀባዩ የተለዋወጧቸውን መልዕክቶች መሰረዝ ይችላሉ። ዋትስ አፕ ተመሳሳይ ባህሪ የለውም። @topmereja

#ኢትዮጵያ ደብረ ማርቆስ ከተማ ዳሽን ባንክ በአብይ ሰራዊት ተዘረፈ!!!!! ደብረ ማርቆስ ከተማ ዳሽን ባንክ ሸዋበር ቅርንጫፍ በ”መከላከያ ሠራዊት” ተዘርፎ ማደሩ ታውቋል። ከጥበቃዎች መካከል አንዱ እዛው አፍነው እንዳሰሩት የተገኘ ሲሆን፣ ሌላኛው የደረሰበት አልታወቀም ተብሏል። ከባንኩ ፊትለፊት የአድማ ብተና አባላት ካምፕ እያለ ነው ዘረፋው የተፈጸመው! ስለጉዳዩ ባንኩ እስካሁን ያለው ነገር የለም!! @topmereja

#አፍሪካ News ቱኒዚያ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አከናወነች !!! በቱኒዚያ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ፣ መራጮች ድምጻቸውን ሲሰጡ ውለዋል ። ሁነኛ ተችዎቻቸው ወህኒ መወረዳቸውን ተከትሎ ፣ የአሁኑ የሀገሪቱ ፕሬ
#አፍሪካ News ቱኒዚያ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አከናወነች !!! በቱኒዚያ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ፣ መራጮች ድምጻቸውን ሲሰጡ ውለዋል ። ሁነኛ ተችዎቻቸው ወህኒ መወረዳቸውን ተከትሎ ፣ የአሁኑ የሀገሪቱ ፕሬዚደንት ካይስ ሰዒድ ለተጨማሪ አምስት ዓመታት በስልጣን መቆያታቸውን ያረጋግጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ። ሰኢድ መጠነ ሰፊ ስልጣን ነጠቃ ከአካሄዱ ከሶስት አመታት በኋላ ምርጫው የቱኒዚያ የዲሞክራሲ ሙከራ የመጨረሻ ምዕራፍ ሆኖ ታይቷል። ለሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር በአምባገነን ስርዓት ላይ የተነሳው የአረብ አብዮት ህዝባዊ አመጽ መፍለቂያ መሆኗ ከአስር አመታት በላይ የኩራት ምንጭ ሆኖ ቆይቷል። የ ሀገሪቱ ምርጫ ቦርድ 9.7 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በምርጫው ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል ብሏል። ከእነዚህ ውስጥ 47 በመቶ የሚሆኑት ዕድሜያቸው በ36 እና 60 መካከል የሚገኙ መሆናቸውንም አክሏል። ሰኢድ ዛሬ ማለዳ ከቱኒስ በስተሰሜን በምትገኘው በኤንናስር ከተማ በሚገኝ ጣቢያ ከባለቤታቸው ጋር በመሆን ድምጽ ሰጥተዋል። እ.ኤ.አ. በ2019 በከፍተኛ ድምፅ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ፣ ሰኢድ ህገ መንግስቱን እንደገና ለመጻፍ ያበቃቸው የስልጣን ነጣቃ ፈጽመዋል ። በተቃዋሚዎች ላይ እየበረታ ያለው የአፈና እርምጃ እና በሁሉም የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ትችት የሚሰነዝሩ ሰዎች እስር ቁጥር መጨመሩ ፣ በሀገር ውስጥ እና ውጪ ትችት ቀስቅሷል ። @topmereja

#ኢትዮጵያ አንዳንድ እናቶች ልጅ ከወለዱ በኋላ ለመንፈስ ጭንቀት የሚጋለጡበት ሁኔታ ይከሰታል። ለድህረ ወሊድ የድብታ ሕመም የተጋለጡ እናቶች ከፍተኛ የስሜት መዋዠቅ፣ ጥልቅ ሃዘን፣ የበረታ ድካም፣ የ
#ኢትዮጵያ አንዳንድ እናቶች ልጅ ከወለዱ በኋላ ለመንፈስ ጭንቀት የሚጋለጡበት ሁኔታ ይከሰታል። ለድህረ ወሊድ የድብታ ሕመም የተጋለጡ እናቶች ከፍተኛ የስሜት መዋዠቅ፣ ጥልቅ ሃዘን፣ የበረታ ድካም፣ የጥፋተኝነት ስሜት፣ ጭንቀት እና ልጃቸውን በወጉ የመንከባከብ ችግር ጭምር ሊገጥማቸው ይችላል። ሳምንታዊው ‘ሃኪምዎን ይጠይቁ’ ይህን ድሕረ ወሊድ የሚከሰት ሕመም ለማከም የሚረዳ አዲስ መድሃኒት ምንነት ይመለከታል። ሞያዊ ትንታኔውን የሚሰጡን በዩናይትድ ስቴትሱ የምግብ እና የመድሃኒቶች ቁጥጥር ባለ ሥልጣን በምርምር ባለሞያነት በማገልገል ላይ የሚገኙት ዶ/ር አሌክስ አካሉ ናቸው።

"የከተማችን ነዋሪዎች ሳይደናገጡ በባለሙያው የተገለጹ መደረግ የሚገባቸው ጥንቃቄዎችን እንዲያደርጉ ይህን መረጃ አጋርቻለሁ‼️" ከንቲባ #አዳነች #አቤቤ "ማምሻዉን በመዲናዋ የተለያዩ አከባቢዎች የተሰ
"የከተማችን ነዋሪዎች ሳይደናገጡ በባለሙያው የተገለጹ መደረግ የሚገባቸው ጥንቃቄዎችን እንዲያደርጉ ይህን መረጃ አጋርቻለሁ‼️" ከንቲባ #አዳነች #አቤቤ "ማምሻዉን በመዲናዋ የተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የመሬት ንዝረት ፈንታሌ ላይ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተ ነው ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ እንዳገለጹት ዛሬ ማምሻውን በከተማችን አዲስ አበባ የተከሰተው የመሬት ንዝረት በስምጥ ሸለቆ በተለይም ፈንታሌ አካባቢ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ላለፉት 10 ቀናት ዉስጥም እየተከሰተ የነበረ የመሬት መንቀጥቀጥ መሆኑን እና በአዲስ አበባም የተከሰተዉ የመሬት ንዝረት በዚሁ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል ። የከተማችን ነዋሪዎች ሳይደናገጡ በባለሙያው የተገለጹ መደረግ የሚገባቸው ጥንቃቄዎችን እንዲያደርጉ ይህን መረጃ አጋርቻለሁ።" https://www.facebook.com/share/v/MkzD36advTvpyfvh/?mibextid=WC7FNe

#ATTENTION🚨 ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ? መደረግ ያለበት ጥንቃቄስ ምንድነው ? በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ምን አሉ ? " ድጋሚ ሊከሰ
+5
#ATTENTION🚨 ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ? መደረግ ያለበት ጥንቃቄስ ምንድነው ? በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ምን አሉ ? " ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ወይ ? የሚባለው ሰሞኑን በሙሉ ይሄን አይነት ንዝረቶች ነበሩ። መሬት መንቀጥቀጥ መተንበይ የሚባል ነገር የለም ፤ የት አካባቢ እንደሆነ እንጂ መቼ ይከሰታል የሚባለውን መተንበይ አይቻልም። ስለዚህ ሊከሰት ይችላል ሊመጣ ይችላል። ይሄ ሁል ጊዜ በተለይ አዲስ አበባ የምንኖር ሰዎች ነቅተን የምንጠብቀው ነገር መሆን አለበት። ስምጥ ሸለቆና የስምጥ ሸለቆ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ነቅተን የምንጠብቀው ነገር ነው መሆን ያለበት። ለጊዜው መናገር የምችለው ከበድ ያለ ነገር ከመጣ አይመጣም ብለን ነው የምንገምተው ከመጣ ግን ምን መደረግ ስለለበት ጥንቃቄ ነው። ➡️ የቤት ቋሚዎች በተለይ ኮንዶሚኒየም ህንጻ ላይ ያሉ ሰዎች ኮለኖች አካባቢ መጠጋት ለምን መውረድ ሊከብድ ይችላል ቁልፍ ማክፈትም ሊከብድ ይችላል። ስለዚህ ኮለኖች አካባቢ መጠጋት። ➡️ ከተቻለ ጠረጴዛ ስር መግባት። ➡️ ሊፍት አትጠቀሙ። ማንም ሰው በሊፍት ለመውረድ እንዳይሞክር። ያን እንዳትጠቀሙ። ይሄን ይሄን ጥንቃቄ ማደርግ ያስፈልጋል። ነገር ግን አሁን ባለው እዚህ ደረጃ የሚያደርስ ከባድ ነገር አለ ብለን አንገምትም። " #Ethiopia #AddisAbaba @topmereja

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ስለ መሬት መንቀጥቀጡ እና ከዚህ በሁዋላ ከተከሰተም መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች የሰጡትን መግለጫ ከላይ ባለው ድምፅ ቅጂ መከታተል ትችላላችሁ ! © ABD

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ስለ መሬት መንቀጥቀጡ እና ከዚህ በሁዋላ ከተከሰተም መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች የሰጡትን መግለጫ ከላይ ባለው ድምፅ ቅጂ መከታተል ትችላላችሁ ! @topmereja

በመዲናዋ የተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የመሬት ንዝረት ፈንታሌ ላይ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተ መሆኑ ተገለፀ በአዲስ አበበ ከተማ የተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የመሬት ንዝረት ፈንታሌ ላይ
+2
በመዲናዋ የተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የመሬት ንዝረት ፈንታሌ ላይ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተ መሆኑ ተገለፀ በአዲስ አበበ ከተማ የተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የመሬት ንዝረት ፈንታሌ ላይ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተ መሆኑ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጂዮፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ ለኢቲቪ ገልፀዋል፡፡

#Update " እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የለም፤ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ ነው ፤ አዋሽ አካባቢ ነው የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4.9 ነው " - ዶክተር ኤልያስ ሌዊ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን የሰጡት ቃል ምን አሉ ? " እስካሁን ባለው መረጃ እዚህ የመሬት መንቀጥቀጡ እዚህ አዲስ አባባ የተከሰተ ሳይሆን አዋሽ አካባቢ የተከሰተ ነው። ግን በመሬት ውስጥ አልፎ እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ ልዩ ልዩ ቦታዎች ተሰምቷል። ይሄን ግልጽ ማድረግ እንፈልጋለን እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ አይደለም። ግን በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ እዚህ ያሉ ህንጻዎችን አንቀጥቅጧል። በሪክተር ስኬል 4.9 ነው ያገኘነው። ይሄም ከፈንታሌ የሚባል ተራራ አለ ወደ መተሃራ አካባቢ ነው የተከሰተው። እስካሁን ያለው መረጃ ይሄ ነው። ሰውም ይረጋጋ እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይሆን ከሩቅ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ በተለይ እዚህ ሰሜን እና ሰሜን ምስራቅ ያሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በጣም ተረብሸዋል። ልክ ነው ከዛም ሊሰማ ይችላል። በሬክተር ስኬል 4.9 ነው ይሄ ነው ያለው መረጃ። ተጨማሪ መረጃ እንዳገኘን በግልጽ እንነግራለን። " ብለዋል። ዛሬ ምሽት በአዲስ አበባ በነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ምክንያት በተለይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚኖሩ ነዋሪዎች ህንጻቸው ሲንቀጠቀጥ እንደነበር ገልጸውልናል። በዚህ ምክንያት ከቤታቸው ወጥተው መሬት ላይ ወርደው ተሰባስበዋል። @topmereja

ከምሽቱ 2:10 ሰዓት ላይ በዓደይ አበባ ኖህ ረሪል ስቴት አራብሳ መንገድ ላይ ፣ ሃያት፣ ሲኤሚሲ በንዝረቱ ሰዎች ከቤታቸው ወጥተዋል‼️ በበነገራችን ላይ በያዝነው መስከረም ወር - በአፋር ክልል በሬ
+3
ከምሽቱ 2:10 ሰዓት ላይ በዓደይ አበባ ኖህ ረሪል ስቴት አራብሳ መንገድ ላይ ፣ ሃያት፣ ሲኤሚሲ በንዝረቱ ሰዎች ከቤታቸው ወጥተዋል‼️ በበነገራችን ላይ በያዝነው መስከረም ወር - በአፋር ክልል በሬክተር ስኬል 4.5 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጂዮ ፊዝክስ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም የመሬት መንቀጥቀጥ ተማራማሪ እና መምህር ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ገልፀው ነበር፡፡ በደቡባዊ አፋር ክልል ባለፉት 3 ሳምንታት ውስጥ የተለያየ መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ገልፀዋል፡፡ ባለፉት 20 ቀናት ውስጥ ከተከሰተው የመሬት መቀጥቀጥ ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.5 (ሪድ መሬት) የተመዘገበው ባለፈው ሀሙስ እኩለ ሌሊት 6፡36 ላይ መሆኑን አንተስዋል፡፡ የመሬት መንቀጥቀጡ እስከ አዲስ አበባ ከተማ ድረስም መሰማቱን ተናግረዋል፡፡ የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተበት ቦታ በአፋር ክልል ፈንታሌና ዶፈን እሳት ገሞራ በተራራውና በቆላማ መጋጠሚያ አከባቢ ሲሆን ይህም የሚጠበቅ ነው ብለዋል፤ ጉዳት ስለማድረሱ ግን መረጃ የለም ነው ያሉት፡፡ ይሁንና አንድ ደቂቃ ያልሞላ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱ ክስተቱ አስደንጋጭ አድርጎታል። @topmereja

#ኢትዮጵያ news የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች አሳለፈ‼️ ውሳኔዎቹ አንደሚከተለው ቀርበዋል÷ 39ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 39ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን 2017-2020 የገቢ ስትራቴጂ ላይ ነው፡፡ ስትራቴጂው የታክስ ሥርዓቱን ለማዘመን እና ለግል ኢንቨስትመንቱ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የታለመ ሲሆን አጠቃላይ የታክስ ፖሊሲዎችን እና አስተዳደራዊ ሪፎርሞችን እንዲሁም ማሻሻያዎችን ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡ ሰትራቴጂው ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ተደርጎ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በስትራቴጂው ላይ በዝርዝር ከተወያየበት በኋላ በምክር ቤቱ ውሳኔ ካገኘበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ከማልታ ሪፐብሊክ መንግስት እና ከቻድ ሪፐብሊክ መንግስት ጋር የተፈረማቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነቶችን ለማጽደቅ የቀረቡ 2 ረቂቅ አዋጆች ላይ ነው፡፡ ስምምነቶቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ማንኛውም የማልታ ከተማ እና ወደ እንጃሜና ከተማ በ3ኛና 4ኛ ትራፊክ መብት የመንገደኛ እና የጭነት የበረራ ምልልስ ለማድረግ፣ ተወካይ አየር መንገዶችን በሽርክና ለማሰራት፣ በ5ኛ ትራፊክ መብት ወደ ተመረጡ መዳረሻዎች በረራ ለማድረግ የሚያስችል እና አገራችን ከሁለቱ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር፣ ለንግድና ኢንቨስትመንት፣ ለወጪ ንግድ፣ ለቱሪዝም፣ ለስራ እድል ፈጠራ እና ለውጭ ምንዛሪ ግኝት ትልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ስምምነቶች ናቸው፡፡ ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጆቹ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ወስኗል፡፡ 3. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የፓሪስ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት ኮንቬንሽን ለማጽደቅ በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የፓሪስ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት ኮንቬንሽን በአባል አገራት መካከል ሕብረት በመፍጠር የኢንዱስትሪ ንብረትን ለመጠበቅ፣ የፈጠራ ባለቤትነት፣ የግልጋሎት ሞዴሎች፣ የኢንዱስትሪ ንድፎች፣ የንግድ ምልክቶች፣ የአገልግሎት ምልክቶች፣ የንግድ ስሞች፣ የምርቶች ምንጭ አመልካች ምልክቶች ለመጠበቅ እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ውድድር ለመከላከል እና ለግብርና እና ሁሉንም የተመረቱ ወይም ተፈጥሯዊ ምርቶች የሚያካትት ነው፡፡ የኮንቬንሽኑ መጽደቅ ሀገራችን ለምታደርገው የአለም ንግድ ድርጅት አባልነት ጥያቄ ድጋፍ የሚሆን ሲሆን ከአባል ሀገራቱ ለሚነሱ የኢንዱስትሪያዊ ንብረት ጥበቃን ለሚመለከቱ ጥያቄዎች አዎንታዊ መልስ ለመስጠት ያስችላል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የዓለም አቀፍ ምልክቶችን ከሚመለከተው የማድሪድ ስምምነት ጋር የተዛመደውን ፕሮቶኮል ለማጽደቅ በወጣ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ፕሮቶኮሉ የንግድ እና የአገልግሎት ምልክቶች በአገር ውስጥ ሕግ ከሚደረግላቸው ጥበቃ አልፈው በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥበቃ እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል ከመሆኑም በተጨማሪ ምርቶች እና አገልግሎቶች ያላግባብ ለሌሎች ጥቅም እንዳይውሉ በቂ ጥበቃ የሚደረግበትን ሁኔታ የሚፈጥር፣ ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና አገልግሎቶች እንዲኖሩና የሀብት ምንጭ እንዲሆኑ ትልቅ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ምክር ቤቱ በፕሮቶኮሉ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡ 5. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ደንብ እና የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ደንብ ላይ ነው፡፡ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር እና ሀላፊነት ለመወጣት፤ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለደንበኞች ለመስጠት እንዲሁም ከፓስፖርት የቆይታ ጊዜ ጋር በተያያዘ ያሉ ጥቄዎችን መፍታት እንዲችል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ በተጨማሪም የጀመረውን ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ፣ ሪፎርሙ በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ለማስቻል የአገልግሎቱን ልዩ ባህሪይ ከግምት ውስጥ ያስገባ ሰራተኞች መተዳደሪያ ደንብ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቦቹ ላይ በዝርዝር ከተወያየባቸው በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ @topmereja

#ኢትዮጵያ News የትግራይ እና የዓፋር ክልሎች ፕሬዝዳንቶች ውይይት ተስፋ እንዳሳደረባቸው ተፈናቃዮች ገለፁ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ባለፈው ረቡዕ መስከረም 22 ቀ
#ኢትዮጵያ News የትግራይ እና የዓፋር ክልሎች ፕሬዝዳንቶች ውይይት ተስፋ እንዳሳደረባቸው ተፈናቃዮች ገለፁ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ባለፈው ረቡዕ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ/ም በዓፋር ክልል ያደረጉት ጉብኝትና ተደረሰባቸው የተባሉ ስምምነቶች ተስፋ እንዳሳደሩባቸው በመቀሌ አካባቢ የተጠለሉ የአብዓላ ተፈናቃዮች ተናግረዋል። ችግር ውስጥ እንደሚገኙ የገለፁት ተፈናቃዮቹ ስምምነቱ ቶሎ እንዲተገበርም ጠይቀዋል። የትግራይ ክልል ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ፣ ባለፈው ረቡዕ በአፋር ያደረጉት ጉብኝት ከሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በኋላ የመጀመሪያ ነው። አቶ ጌታቸው በፌስቡክ ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት ከዓፋር ክልል ፕሬዝዳንት አወል አርባ ጋራ ባደረጉት ውይይት ፣ በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉትን በመመለስ፣ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማስጀመር እንዲሁም ሰላም፣ ፀጥታና ልማትን በጋራ በማረጋገጥ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል፡፡ @topmereja