en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
#news ደቡብ ሱዳን የደህንነት ኃላፊዋን ከሥልጣን አነሳች። የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ደቡብ ሱዳን ነጻ ሃገር መሆኗን ካወጀችበት እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር 2011 አንስቶ የሃገሪ
#news ደቡብ ሱዳን የደህንነት ኃላፊዋን ከሥልጣን አነሳች። የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ደቡብ ሱዳን ነጻ ሃገር መሆኗን ካወጀችበት እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር 2011 አንስቶ የሃገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት ኃላፊ ሆነው ያገለገለገሉትን ጀነራል አኮል ኩር ኩክ’ን ከሥልጣን ማንሳታቸውን መንግሥታዊው የደቡብ ሱዳን ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘገበ። በብሔራዊ የደህንነት አገልግሎት ስር የሚገኘውን የሀገር ውስጥ ደህንነት ቢሮ ለዓመታት የመሩት ጀነራል አኮል ኩር ከሥልጣን የተነሱት የሽግግር መንግሥቱ በሀገሪቱ ሊደረግ የታቀደው ምርጫ በድጋሚ መዘግየቱን ካሳወቀ ሳምንታት በኃላ ነው። በምትካቸውም የፕሬዝዳንት ኪር ቅርብ ሰው መሆናቸው የተገለጸው አኬክ ቶንግ አልዩ፣ አዲሱ የደህንነት ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል። ባለፈው ወር የፕሬዝዳንት ኪር ፅህፈት ቤት የሽግግር መንግሥቱ ሥልጣን ለሁለት አመት መራዘሙን እና እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር 2022 መካሄድ የነበረበት ምርጫ በድጋሚ መራዘሙን በማስታወቁ ከዩናይትድ ስቴትስ እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት ትችቶች ቀርበውበት ነበር። ሮይተርስ የመንግሥቱን ቃል አቀባይ እና የፕሬዝዳንቱን ጽህፈት ቤት ቢሮ ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረት ያለማሳካቱን አስታውቋል። ሆኖም ‘የደህንነት ኃላፊው ከሥልጣን መባረራቸው፣ በመንግሥት ከፍተኛ የሥልጣን እርከኖች ውስጥ ያለውን የስልጣን ሽኩቻ ያሳያል’ ሲሉ ተንታኞች ተናግረዋል። @topmereja

#news በቅርቡ በጂቡቲ ባሕር ዳርቻ ሰጥመው የሞቱት ፍልሰተኞችን ጉዳይ በተመለከተ የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ለቪኦኤ በሰጠው ተጨማሪ መረጃ፣ ፍልሰተኞቹ ባሕር ውስጥ የሰጠሙት ጀልባ
+1
#news በቅርቡ በጂቡቲ ባሕር ዳርቻ ሰጥመው የሞቱት ፍልሰተኞችን ጉዳይ በተመለከተ የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ለቪኦኤ በሰጠው ተጨማሪ መረጃ፣ ፍልሰተኞቹ ባሕር ውስጥ የሰጠሙት ጀልባዎቹ ዳር ሳይደርሱ ሕገ ወጥ አስተላላፊዎቹ ፍልሰተኞቹን እንዲወርዱ በማስገደዳቸው ነው ብሏል። የአይኦኤም የአፍሪካ ቀንድ እና ደቡባዊ አፍሪካ ዲሬክተር የሆኑት ፍራንትዝ ሰለስቲን ለቪኦኤ እንዳስታወቁት፣ በሁለት ጀልባዎች ውስጥ ተሳፍረው ከነበሩት 310 ፍልሰተኞች ውስጥ 48 ሲሞቱ፣ 154 የሚሆኑት ደግሞ ከአደጋው ተርፈዋል። 108 ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም ወይም ሕይወታቸው አልፏል። በአንደኛው ጀልባ ላይ 100 ፍልሰተኞች ተሳፍረው የነበር ሲሆን በሁለተኛው ጀልባ ላይ ደግሞ 210 ፍልሰተኞች ተሳፍረው እንደነበር ዲሬክተሩ አስታውቀዋል። ፍልሰተኞቹ ከየመን ወደ ጂቡቲ በማቅናት ላይ የነበሩ ሲሆን፣ የጂቡቲን ባሕር ዳርቻን በመቃረብ ላይ ሳሉ ሕገወጥ አስተላላፊዎቹ ጀልባዎቹ ባሕሩ መሃል ላይ ሳሉ ፍልሰተኞቹን እንዲወርዱ ማስገደዳቸውን ሃላፊው ተናግረዋል። በርካታ ቁጥር ያላቸውና መዋኘት ያልቻሉት ፍልሰተኞች ሰጥመው መምታቸውንም ሃላፊው ለቪኦኤ አስታውቀዋል። ባለፈው ሰኞ በተፈጠረው በዚህ ክስተት እስከ አሁን ያልተገኙትን በተመለከተ ፍለጋው መቀጠሉን፣ ነገር ግን ከተቆጠሩት ቀናት አንጻር ሕይወታቸው ሊያልፍ ይችላል ብለው እንደሚሰጉ ፍራንትዝ ሰለስቲን ለቪኦኤ ተናግረዋል። በሕይወት የተረፉት ፍልሰተኞች ድርጅቱ በጂቡቲ መጠለያና የሕክምና ዕርዳታ እንደሰጣቸው የገለጹት ኃላፊው፣ በባሕር መሥመሩ የሚተላለፉት ኢትዮጵያያንና ሶማሊያውያን እንደሆኑ፣ በአብዛኛው ግን ኢትዮጵያውያን እንደሆኑ ገልፀዋል።

# አፍሪካ news በ90 አስገድዶ መድፈሮች ጥፋተኛ የተባለው ግለሰብ በ42 የዕድሜ ልክ እስራቶች ተቀጣ በደቡብ አፍሪካ በ90 አስገድዶ መድፈሮች ጥፋተኛ የተባለ ግለሰብ በ42 የዕድሜ ልክ እሥራቶች
# አፍሪካ news በ90 አስገድዶ መድፈሮች ጥፋተኛ የተባለው ግለሰብ በ42 የዕድሜ ልክ እስራቶች ተቀጣ በደቡብ አፍሪካ በ90 አስገድዶ መድፈሮች ጥፋተኛ የተባለ ግለሰብ በ42 የዕድሜ ልክ እሥራቶች ተቀጥቷል። የ40 ዓመት ዕድሜ ያለው ንኮሲናቲ ፋካቲ የዘጠኝ ዓመት ዕድሜ ያላቸው ልጆች ላይ ጭምር በፈፀመው አስገድዶ መድፈር፣ ሌሎች ልጆች ድርጊቱን እንዲመለከቱ ያስገድድ ነበር ተብሏል። ግለሰቡ ድርጊቱን የፈፀመው ከእ.አ.አ 2012 እስከ 2021 ባለ ጊዜ ውስጥ ከጆሃንስበርግ በስተ ምሥራቅ በምትገኝ መንደር ወዳለ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ልጆችን ዒላማ በማድረግ ነበር። ሃገሪቱና የተቀረውንም ዓለም ላስደነገጠው ድርጊት የጆሃንስበርግ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግለሰቡን በአስገድዶ መድፈር፣ በጠለፋ ዝርፊያና ጥቃት በመፈጸም ጥፋተኛ በማለት 42 የዕድሜ ልክ እስራቶች ፈርዶበታል። “ፍርድ ቤቱ፣ በተለይም እንዲህ ዓይነት ወንጀል በወጣቶች እና ራሳቸውን መከላልከል በማይችሉ ልጆች ላይ ሲፈጸም ቅጣት የመስጠት ግዴታ አለበት” ሲሉ ዳኛው ተናግረዋል። አንዳንዶቹ ሰለባዎቹ ዩኒፎርም እንደለበሱ ወደ ትምህርት ቤት ሲጓዙ ጥቃቱ እንደደረሰባቸው፣ ሌሎቹ ደግሞ በመኖሪያ ቤታቸው የቤተሰብ ዓባላት እየተመለከቱ ድርጊቱ እንደተፈፀማቸው ዳኛው አስታውቀዋል። በቁጥጥር ሥር በሚውልበት ጊዜ ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ እግሩ ላይ በጥይት የተመታው ተከሳሽ፣ በፍርድ አሰጣጡ ወቅት አንገቱን አቀርቅሮ ተስተውሏል። በደቡብ አፍሪካ ካለፈው ሚያዚያ እስከ ሰኔ ባለው ጊዜ ውስጥ 9ሺሕ 309 አስገድዶ መደፈሮች እንደተፈፀሙ የፖሊስ መረጃ ያሳያል።

ሩሲያ ታሊባንን ከአሸባሪ ቡድን ዝርዝር ለመሰረዝ መወሰኗን አስታወቀች ሩሲያ ትላንት እንዳስታወቀችው አፍጋኒስታንን እየመራ ያለው ታሊባን ከሞስኮ የአሸባሪ ድርጅቶች ዝርዝር ውስጥ እንዲሰረዝ "ዋናው ው
ሩሲያ ታሊባንን ከአሸባሪ ቡድን ዝርዝር ለመሰረዝ መወሰኗን አስታወቀች ሩሲያ ትላንት እንዳስታወቀችው አፍጋኒስታንን እየመራ ያለው ታሊባን ከሞስኮ የአሸባሪ ድርጅቶች ዝርዝር ውስጥ እንዲሰረዝ "ዋናው ውሳኔ" አስቀድሞ ተላልፏል ብላለች፡፡ የደቡብ እስያ ሃገራት የሩሲያ ፕሬዚዳንታዊ ልዑክ ዛሚር ካቡሎቭ በመንግስት የሚተዳደረው የዜና ወኪል ላይ እንደገለጡት “የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ ደህንነት ኤጀንሲዎች የታሊባን ከፌዴራል ህጎች ጋር በተጣጣመ መልኩ መሰረዙን በተመለከተ “ህጋዊ ስራዎችን እያጠናቀቁ ነው” ብለዋል ። የመጨረሻው ውሳኔም በቅርቡ ይፋ ይሆናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል፡፡ ይህ አስተያየት የተሰማው ሞስኮ በአፍጋኒስታን ጉዳይ ለመወያየት የአካባቢው ሀገራት ጉባኤን ባዘጋጀችበት ቀን ሲሆን ውይይቱንም የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭን መርተዋል። ከጉባኤው በኋላም ላቭሮቭ የአፍጋኒስታን የውይይቱ ተሳታፊ ልዑካናቸውን ከመሩት የታሊባን ተጠባባቂ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር ካን ሙታኪ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

እስራኤል ጋዛ ውስጥ በሚገኝ መስጂድ ላይ በፈጸመችው ጥቃት 19 ሰዎች ተገደሉ site logosite logo ቀጥታ ፈልግ Search ዜና እስራኤል ጋዛ ውስጥ በሚገኝ መስጂድ ላይ በፈጸመችው ጥቃት 19
+2
እስራኤል ጋዛ ውስጥ በሚገኝ መስጂድ ላይ በፈጸመችው ጥቃት 19 ሰዎች ተገደሉ site logosite logo ቀጥታ ፈልግ Search ዜና እስራኤል ጋዛ ውስጥ በሚገኝ መስጂድ ላይ በፈጸመችው ጥቃት 19 ሰዎች ተገደሉ ዲር አል-ባላህ፣ ጋዛ ሰርጥ — እስራኤል በጋዛ ሰርጥ በሚገኝ መስጂድ ላይ እሁድ ማለዳ በፈጸመችው ጥቃት በትንሹ 19 ሰዎች መሞታቸውን የፍልስጤም ባለስልጣናት ገለፁ ። ከኢራን- አጋር ታጣቂ ቡድኖች ጋር የምታደርገው ጦርነት እየተስፋፋ በሚገኝበት በአሁኑ ሰዓት፣ እስራኤል በሰሜን ጋዛ እና በደቡባዊ ቤይሩት ላይ የምታደርገውን የቦምብ ድብደባም አጠናክራለች ። በማዕከላዊ ዲር አል ባላህ ዋና ሆስፒታል አቅራቢያ በሚገኘው ጥቃት የተፈጸመበት መስጂድ ውስጥ የተፈናቀሉ ሰዎች ተጠልለው እንደነበር ተነግሯል ።በከተማዋ አቅራቢያ የተፈናቀሉ ሰዎች በተጠለሉባቸው ትምህርት ቤቶች ላይ በተፈፀመ ሌላ ጥቃት ተጨማሪ አራት ሰዎች ተገድለዋል። የእስራኤል ጦር ሁለቱም ጥቃቶች ታጣቂዎች ላይ ያነጣጠሩ ናቸው ቢልም ማስረጃ ግን አላቀረበም ። የአሶሼትድ ፕሬስ ጋዜጠኛ በአል-አቅሳ ሰማዕታት ሆስፒታል የሚገኙ አስከሬኖችን ቆጥሯል ። በመስጂዱ ላይ በደረሰው ጥቃት የሞቱት በሙሉ ወንዶች መሆናቸውን የሆስፒታሉ መረጃዎች ያሳያሉ።

#ዓለምአቀፍ news ቱርክ ለነዳጅ ፍለጋ አገልግሎት የሚውል መርከብ ወደ ሶማሊያ ላከች ቱርክ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ የተፈረመው የመከላከያ እና ምጣኔ ሀብት ስምምነት አካል የሆነ የነዳጅ እና የተ
#ዓለምአቀፍ news ቱርክ ለነዳጅ ፍለጋ አገልግሎት የሚውል መርከብ ወደ ሶማሊያ ላከች ቱርክ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ የተፈረመው የመከላከያ እና ምጣኔ ሀብት ስምምነት አካል የሆነ የነዳጅ እና የተፈጥሮ ሀብት ፍለጋ መርከብ ወደ ሶማሊያ ላከች። ኡሩች ሪስ በመባል የሚጠራው መርከብ በሶስት ሳምንታት ውስጥ የሶማሊያ የባህር ዳርቻ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።ከዚያም በሶማሊያ የባህር ዳርቻ ላይ (የድምጽ ንዝረትን በመጠቀም ነዳጅን ለማመላከት የሚደረግ) ሴይስሚክ ጥናት ያከናውናል ። የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ታይብ ኤርዶጋንን ፣ ጨምሮ የሁለቱ ሀገራት ባለስልጣናት በተገኙበት ቅዳሜ ዕለት በኢስታንቡል የሽኝት ስነ ስርዓት ተካሂዷል። መርከቧ በሶማሊያ ፍቃድ በተሰጣቸው ሶስት እያንዳንዳቸው 5 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ባላቸው አካባቢዎች ጥናቱን እንደምታከናውን ኤርዶጋን ገልጸዋል። በመርከቧ የሽኝት ሥነ-ሥርዓት ላይ የተሳተፉት የሶማሊያ ነዳጅ እና ማዕድን ሀብት ሚኒስትር አብዲሪዛክ ሞሐመድ በማዕከላዊ ሶማሊያ የባሕር ዳርቻ ላይ የሶስት አንጻር (3ዲ) ሴይስሚክ ሙከራ ጥናት እንደሚያካሂድ ተናግረዋል።ሞሐመድ ሶስቱ ስፍራዎች "ነዳጅ የመገኘት ዕድሉ ጥሩ በሆነበት " የጋሙደግ ባህር ዳርቻ ግዛት ውስጥ እንደሚገኙ አክለዋል ። ሞሐመድ ለቪኦኤ የአፍሪካ ቀንድ አገልግሎት እንደተናገሩት መርከቧ ወደ ምርምር ስፍራዎቹ ከማቅናቷ በፊት ፣የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ የሚገኙበት የአቀባበል ስነ ስርዓት በሚከናወንባት ሞቃዲሾ ትደርሳለች ።

የዋጋ ጭማሪ ላይ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ተደርቦ እንዴት እንዘልቀዋለን?? ለደንበኞችና ለሸማቾች ከሚሰጡ አገልግሎቶች ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች መልክና ቅርፃቸውን እያቀያየሩ ጫና ማሳደራቸውን ቀጥለዋል፡
+1
የዋጋ ጭማሪ ላይ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ተደርቦ እንዴት እንዘልቀዋለን?? ለደንበኞችና ለሸማቾች ከሚሰጡ አገልግሎቶች ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች መልክና ቅርፃቸውን እያቀያየሩ ጫና ማሳደራቸውን ቀጥለዋል፡፡ በሕግ ሽፋን የሚደረጉ የዋጋ ጭማሪዎችም እየበረከቱ ነው፡፡ ኢኮኖሚያዊ ወይም ምክንያታዊ ያልሆኑ የዋጋ ጭማሪዎችን የሚከላከል አሠራር የለም፡፡ ለአንድ አገልግሎት የሚጠየቀው ዋጋ በምን መሥፈርት ተሠልቶ እንደሚወጣ ማወቅ ከባድ ነው፡፡ ይህ በብዙ የአገልግሎት ተቋማት የምንታዘበው ነው፡፡ በተለይ በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ለሚሰጡ አገልግሎቶች የሚጠየቀው ዋጋ ለምን? የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ ይሆናል፡፡ ከግብይት ጋር በተያያዘ የንግድ ድርጅቶች ምርቶቻቸውን የሚሸጡበት ዋጋ አግባብነትም የግብይት ሥርዓታችን ችግር ነው፡፡ ለምሳሌ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ›› በሚል ማስታወቂያ የሚፈጸሙ ግብይቶችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በእርግጥ በትክክል ቅናሽ ተደርጎባቸው ለግብይት የቀረቡ መሆናቸውን ማወቅ በማይችልበት ሁኔታ በስመ የቅናሽ ማስታወቂያ ሸማቹ ይታለላል፡፡ ዋጋ ጨምሮ ጊዜ መጠበቅ በተመደበለት አገር ዋጋ ቀንሶ ለመሸጥ በማይቻልበት የአገራችን ገበያ በእውነተኛ የዋጋ ቅናሽ የሚሸጥ ይኖራል ብሎ ማመን ከባድ ነው፡፡ አንዳንድ የንግድ ድርጅት፣ ከባንያዎች ወይም መደብሮች የዋጋ ቅናሽ ሊያውጁ የሚችሉበት ምክንያት በትክክል የማይገልጽ ከሆነ በታላቅ ቅናሽ ስም የሚደረጉ ማጭበርበሮች አሉ ማለት ነው፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች ታላቅ ቅናሽ አድርገናል ወደሚሉ መደብሮች ጎራ ያሉ ሸማቾች አለ የተባለው የዋጋ ቅናሽ እውነት ያለመሆኑን ማረጋገጥ ችለዋል፡፡ ስለዚህ ታላቅ ቅናሽ በሚሉ ማስታወቂያዎች የሚሸጡ ምርቶችና አንዳንድ አገልግሎቶችን ለማመን ይከብዳል @topMereja

የሥልጣን ቆይታቸውን ያገባደዱት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሁለቱን ምክር ቤቶች የሥራ ዘመን ነገ ያስጀምራሉ። የስድስት ዓመት የሥልጣን ዘመናቸውን ያጠናቀቁት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የሕዝብ
+2
የሥልጣን ቆይታቸውን ያገባደዱት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሁለቱን ምክር ቤቶች የሥራ ዘመን ነገ ያስጀምራሉ። የስድስት ዓመት የሥልጣን ዘመናቸውን ያጠናቀቁት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶችን የ2017 የሥራ ዘመን ነገ ያስጀምራሉ። የሁለቱ ምክር ቤቶች የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በተገኙበት ሰኞ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ የላከው መረጃ ያመለክታል። ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ የመጀመርያ የሥልጣን ዘመናቸውን ያገባደዱ ቢሆንም፣ ሰኞ የሚጠበቀው የሁለቱ ምክር ቤቶች የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ከተካሄደ በኋላ ቀጣዩ የአገሪቱ ርዕሰ ብሔር ምርጫ የሚካሄድ ስለመሆኑ ግን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ ያለው ነገር የለም። የአገሪቱ ርዕሰ ብሔር የሥልጣን ዘመን ስድስት ዓመት እንደሆነ፣ ነገር ግን ርዕሰ ብሔሩ ለሁለተኛ ጊዜ ሊመረጥ እንደሚችል ሕገ መንግሥቱ ይደነግጋል። ሪፖርተር የሥልጣን ዘመናቸውን ባጠናቀቁት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ምትክ ሌላ ርዕሰ ብሔር ይመረጥ ይሆን? ወይም እሳቸው ለሁለተኛ ጊዜ በርዕሰ ብሔርነት የመመረጥ ዕድል ያገኙ ይሆን? የሚለውን ለማወቅ የተለያዩ የምክር ቤቱ አባላትን ያነጋገረ ቢሆንም ሁሉም ስለዚህ ጉዳይ የሰሙት ነገር እንደሌለና ከምክር ቤቱም ይህንን ጉዳይ የተመለከተ መረጃ እንዳልደረሳቸው ገልጸዋል። @topMereja

ዜናፖለቲካ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ ነዋሪዎች ምሬታቸውን ገለጹ ከመስከረም 23 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል በአንዳንድ የዞን ከተሞችና በገጠር
ዜናፖለቲካ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ ነዋሪዎች ምሬታቸውን ገለጹ ከመስከረም 23 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል በአንዳንድ የዞን ከተሞችና በገጠር አካባቢዎች የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ፣ አሽከርካሪዎችም ሆኑ የትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚዎች በእጅጉ መቸገራቸውን በምሬት ተናገሩ፡፡ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሲቆም የመንግሥት አካላት ለምን አገልግሎት አትሰጡም? ማን አቁሙ ብሏችሁ ነው? በማለት ጥያቄ እንደሚያቀርቡ፣ በሌላ በኩል የፋኖ ታጣቂዎች ከሐሙስ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ መንገድ እንዲዘጋና ምንም ዓይነት የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይኖር በጥብቅ መከልከላቸውን አገልግሎት ሰጪዎቹና ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ወልዲያ ከተማን ጨምሮ በዞኑ በሚገኙ የገጠር ከተሞች የትራንስፖርት አገልግሎት በከፊልና ሙሉ በሙሉ መቆሙን የተናገሩት ነዋሪዎቹ፣ በመንግሥት አካላት በአንድ በኩል በፋኖ ታጣቂዎች በሌላ በኩል ጫና እየደረሰባቸው መሆኑን አክለው ተናግረዋል፡፡ አንድ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የወልዲያ ከተማ ነዋሪ በሰጡት አስተያየት፣ ‹‹በሁለት መንግሥት የምንተዳደር እስኪመስለን ድረስ አንዱ ውጡና ሥራ ሥሩ ሲል፣ ሌላው ከወጣችሁ በሕይወታችሁና በንብረታችሁ ላይ ፈርዳችሁ መሆን አለበት፤›› በማለት እንደሚያስጨንቋቸው ተናግረዋል፡፡ በከተማዋ የነዳጅ ማደያዎችን ጨምሮ ሌሎች እንቅስቃሴዎች መቆማቸውን፣ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ከመፍታት ባሻገር በእግራቸው የሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎችን ስልካቸውን እንደሚፈተሽ፣ የሽለላ ሙዚቃና የተፈላጊ ሰዎች ፎቶግራፍ ከተገኘባቸው ድብደባና እስራት እንደሚደርሱባቸው ነው ነዋሪው ያስረዳሉ፡፡

ማንኛውም ማስታወቂያ ለማሰራት በዚህ ያሳውቁን ! 💥 @ @Naolben💥

እስራኤል በሌባኖስ በጀመረቸው ዘመቻ ከ440 በላይ የሂዝቦላህ ታጣቂዎችን መግደሏን አስታወቀች‼️ የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዲየር ጄኔራል ዳንኤል ሃጋሪ እንደገለፁት ÷ በአየር እና በመሬት ላይ
+2
እስራኤል በሌባኖስ በጀመረቸው ዘመቻ ከ440 በላይ የሂዝቦላህ ታጣቂዎችን መግደሏን አስታወቀች‼️ የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዲየር ጄኔራል ዳንኤል ሃጋሪ እንደገለፁት ÷ በአየር እና በመሬት ላይ በተደረገው ዘመቻ የፍልስጤም ተሟጋችና የሌባኖስ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ቡድን መሪ የሆኑትን ሀሳን ናስራለህ ጨምሮ በርካታ የቡድኑ አመራሮችን ተገድለዋል፡፡ በዘመቻው ሂዝቦላህን ወደ ሰሜናዊ ሌባኖስ እንዲያፈገፍግ አድርገነዋል ያሉት ቃል አቀባዩ ÷ እስካሁን በተደረገው ዘመቻ ከ30 በላይ የቡድኑ የጦር አዛዦችን ጨምሮ 440 የሂዝቦላህ አባላትን ገድለናል ብለዋል፡፡ ሂዝቦላህ በትላንትናው እለት ብቻ 130 በላይ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል መተኮሱን ገልፀው ፥ የእስራኤል የአየር መከላከያ ጥቃቱን መመከት መቻሉን እና በሌባኖስ የሚያደርገውን ዘመቻ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡ ሂዝቦላህ በበኩሉ ÷እስራኤል በድንበር አካባቢ የምትገኘውን ኦዳይሴህ ከተማን ለመቆጣጠር ያደረገችውን ሙከራ ማክሸፉን ገልፆ ፤ እስራኤል የምታደርገውን መጠነ ሰፊ ዘመቻ እየመከተ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ከሂዝቦላህ በተጨማሪ የእስራኤል መከላከያ ኃይል ለኢራን የባላስቲክ ሚሳኤል ጥቃት የአፀፋ ምላሽ ለመስጠት ወታደራዊ እቅድ ማውጣቱ ተገልጿል፡፡ የእስራኤል ወታደራዊ ሀይል እንዳስታወቀው ÷ ኢራን ከ200 በላይ ሚሳኤሎችን ወደ ቴል አቪቭ በመተኮስ በእስራኤል የአየር ማረፊያዎች ላይ ጉዳት አድርሳለች፡፡ ለኢራን ጥቃትም የእስራኤል ጦር ከበድ ያለ ሲል የገለጸውን የአፀፋ ጥቃት በሣምንቱ መጀምሪያ አካባቢ ለመፈጸም እቅድ ማውጣቱን አስታውቋል፡፡

#ኢትዮጵያ ትናንት በኢትዮጵያ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ትልቅ መነጋገሪያ የሆነው በፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ X ኦፊሻል ገጽ ላይ የሰፈረው ፅሁፍ ነው። ፅሁፉ ላይ የማህሙድን ዘፈን ' ዝምታ ነው መልሴ 'ን በማንሳት " የሰው ልጅ ሆዱ ሲከፋው ጊዜም እንደ ሰው ሲገፋው: መሄጃ መውጫ ሲጠፋው ዝምታ ብቻ ነው ተስፋው " የሚለው ግጥም ተጋርቷል። መጨረሻ ላይ " ለአንድ አመት ሞከርኩ " የሚልም ሰፍሯል። ፅሁፉ ስለምን ጉዳይ እንደሆነ ፤ ለምንስ ይህንን ግጥም ነጥሎ እንደተጻፈ በግልጽ የሚያብራራው ነገር የለም። ያም ሆኖ ግን ፅሁፉን ላይ በርካቶች የየራሳቸውን አስተያየት እየሰጡ ይገኛሉ። አንዳንዶች ፤ " አሁን ባለው ስርዓት በከፍተኛ ጫና ውስጥ ወድቀው ነው እየሰሩ ያሉት ፤ በተለያዩ ጉዳዮች አለመግባባት ውስጥም እንደነበሩ ብዙ ጊዜ በሚዲያ ይሰማ ነበር ፤ ለመናገር እንኳን እድል የላቸውም ፤ ባገኙት አጋጣሚ ግን በገደምዳሜው ስሜታቸውን ስለ ሀገራቸው ይናገሩ ነበር ፤ አሁንም ቦታውን ሲለቁ ስለዚህ ስርዓት ብዙ የሚናገሩት ይኖር ይሆናል " የሚል አስተያየት ሰጥተዋል። አንዳንዶች፤ " በዚህ ልክ ትልቅ የስልጣን እርከን ይዘው ህዝብን ግራ የሚያጋባ ድፍንፍን ያለ ፅሁፍ በገጻቸው መጋራቱ ሳያንስ እውነትም እሳቸው መሆናቸውን በግልጽ አለማብራራታቸው ትክክል አይደለም ፤ ችግር ካለም እውነታውን ለህዝብ ማሳወቅ አለባቸው እንዲህ የዘፈን ግጥም ከሚያስቀምጡ " ብለዋል። ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ " የ6 ዓመት የስልጣን ዘመናቸው ሲያበቃ ይህን አይነት ነገር በገጻቸው መፃፋቸው የህዝብ ተቀባይነት ለማግኘት ነው እስከዛሬ በሀገሪቱ ብዙ ነገር ብዙ ግፍ ሲፈጠር ባላየ ሲያልፉ ነበር ፤ አንዳንዱን ደግሞ እየመረጡ ሲናገሩ ነበር ፤ ለምን አሁን ? በዚህ ስልጣን እንደማይቀጥሉ ስለሚያውቁ ነው ፤ ስልጣንም መልቀቅ ከነበረባቸው ቀድሞ ተናግሮ እንጂ አሁን ላይ ይህን አጀንዳ ለህዝብ መስጠት ትክክል አይደለም ፤ ጊዜያቸው አብቅቷል ይሰናበታሉ ፤ እሱንም ስለሚያውቁ ነው " ሲሉ ፅፈዋል። በኢትዮጵያ የፕሬዜዳንት ስልጣን ዘመን 6 ዓመት ሲሆን ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ወደ ስልጣን የመጡት ጥቅምት 15 ቀን 2011 ዓ/ም ላይ ነበር። ሌሎች ደግሞ " እንዲያው በደፈናው ድምዳሜ ላይ ከመድረስ የእሳቸውን ሙሉ ሀሳብ በትዕግስት ጠብቆ መስማት ይገባል " ብለዋል። ከዚህ ባለፈ ግን ለመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ የፕሬዝዳንትነት የስልጣን ድርሻው ምንድነው ? ፕሬዝዳንት የሚኮነው እንዴት ነው ? ምን ምን ይሰራል በዝርዝር ? ሲሉ የጠየቁ አሉ። ለዚህ ምላሽ ይሆን ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ህገ መንግስቱ ስለ ፕሬዜዳንቱ የሚለውን ከዚህ በታች አቅርቧል። የኢፌዲሪ ህገ መንግስት ስለ ሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ስልጣንና ተግባር ምን ይላል ? (የኢፌዴሪ ህገ መንግስት) ምዕራፍ ሰባት ስለ ሪፐብሊኩ ኘሬዚዳንት አንቀጽ 69 ስለ ኘሬዚዳንቱ ኘሬዚዳንቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ርዕሰ ብሔር ነው፡፡ አንቀጽ 70 የፕሬዜዳንቱ አሰያየም 1. ለፕሬዜዳንትነት ዕጩ የማቅረብ ሥልጣን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው። 2. የቀረበው ዕጩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ከተደገፈ ፕሬዜዳንት ይሆናል። 3. የምክር ቤት አባል ፕሬዜዳንት ሆኖ ከተመረጠ የተወከለበትን ምክር ቤት ወንበር ይለቃል። 4. የፕሬዜዳንቱ የሥራ ዘመን 6 ዓመት ነው። አንድ ሰው ከሁለት ጊዜ በላይ ለፕሬዜዳንትነት ሊመረጥ አይችልም። አንቀጽ 71 የኘሬዚዳንቱ ሥልጣንና ተግባር 1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽኑን ምክር ቤት ዓመታዊ የጋራ ስብሰበባ ይከፍታል፡፡ 2. በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያጸደቃቸው ሕጐችና ዓለምአቀፍ ስምምነቶች በነጋሪት ጋዜጣ ያውጀል፡፡ 3. ሀገሪቷን በውጭ ሀገሮች የሚወክሉትን አምባሳደሮችና ሌሎች መልክተኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት ይሾማል፡፡ 4. የውጭ ሀገር አምሳደሮችንና የልዩ መልዕክተኞችን የሹመት ደብዳቤ ይቀበላል፡፡ 5. በሕግ መሰረት ኒሻኖች እና ሽልማቶችን ይሰጣል፡፡ 6. በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት በሕግ በተወሰነው መሰረት ከፍተኛ የውትድርና ማዕረጐችን ይሰጣል፡፡ 7. በሕግ መሰረት ይቅርታ ያደርጋል፡፡ @topmereja

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ወታደሮች እያስመረቀ ነው .... የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ወታደሮች በዛሬው እለት እያስመረቀ ነው።
+2
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ወታደሮች እያስመረቀ ነው .... የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ወታደሮች በዛሬው እለት እያስመረቀ ነው። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም አማካሪ እና የተኩስ አመራር ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አለምሸት ደግፌ ብላቴ በሚገኘው የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ሲደርሱ ወታደራዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለውትድርና ሙያ ተመልምለው ስልጠና የወሰዱ መሰረታዊ ወታደሮችም ብቃታቸውን የሚያመላክቱ ወታደራዊ ትርኢቶችን ለክብር እንግዳው አሳይተዋል። በምረቃ መርሀ-ግብሩ ላይ ጀኔራል መኮንኖች ፣ ከፍተኛ የሠራዊቱ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸውን የሀገር መከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ200 ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ራስገዝ ዪንቨርስቲ የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በራሱ መስፈርት አውዳድሮ የተቀበላቸውን 5ሺህ 30
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ200 ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ራስገዝ ዪንቨርስቲ የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በራሱ መስፈርት አውዳድሮ የተቀበላቸውን 5ሺህ 300 የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች በመያዝ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ትምህርት እንደሚጀምር አስታወቀ ዩኒቨርሲቲው ከመዘገባቸው ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል ለ 200 ተማሪዎች ነፃ የትምህር እድል መስጠቱን አስታውቋል።

የሆረ አርሰዴ የኢሬቻ በዓል በድምቀት ተከብሮ ተጠናቋል-የፌደራል ፖሊስ አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በቢሾፍቱ ከተማ የተከበረው የሆረ አርሰዴ የኢሬቻ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብ
+3
የሆረ አርሰዴ የኢሬቻ በዓል በድምቀት ተከብሮ ተጠናቋል-የፌደራል ፖሊስ አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በቢሾፍቱ ከተማ የተከበረው የሆረ አርሰዴ የኢሬቻ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ መጠናቀቁን የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የፌደራል ፖሊስ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ከኦሮሚያ ፖሊስ፣ ከሌሎች የፀጥታና ደኅንነት አካላት፣ ከቢሾፍቱ ከተማ ነዋሪዎች፣ ከበዓሉ አዘጋጅ ኮሚቴ እና ከወጣቶች ጋር ተባብሮ በመሥራት በዓሉ በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል ነው የተባለው፡፡ በዚህም ለአባገዳዎች፣ ለሀደሲንቄዎች፣ ለበዓሉ ታዳሚዎች፣ ለቢሾፍቱ ከተማ ነዋሪ፣ ለበዓሉ አዘጋጅ ኮሚቴ እና ለወጣቶች እንዲሁም ለፀጥታና ደኅንነት አካላት የፌደራል ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል፡፡

በአርሲ ዞን ሙኔሳ ወረዳ ቀርሳ ከተማ ጦርነት ይቁም መኖር አልቻልንም ችግሮች በመነጋገር እና በእርቅ ይፈቱ በማለት የእርቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ። በሰልፉ ላይ ወጣቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ሃዳ ሲንቄዎች፣
+6
በአርሲ ዞን ሙኔሳ ወረዳ ቀርሳ ከተማ ጦርነት ይቁም መኖር አልቻልንም ችግሮች በመነጋገር እና በእርቅ ይፈቱ በማለት የእርቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ። በሰልፉ ላይ ወጣቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ሃዳ ሲንቄዎች፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ ህፃናት ተሳታፊ ሆኗል። @topMereja

https://t.me/hamster_Kombat_bot/start?startapp=kentId332377790 Play with me, become cryptoexchange CEO and get a token AirDrop! 💸 2k Coins as a first-time gift 🔥 25k Coins if you have Telegram Premium

https://t.me/hamsTer_kombat_bot/start?startapp=kentId736234445 Play with me, become cryptoexchange CEO and get a token AirDrop! 💸 +2k Coins as a first-time gift 🔥 +25k Coins if you have Telegram Premium

https://t.me/Binance_Moonbix_bot/start?startapp=ref_332377790&startApp=ref_332377790 Join the Moonbix Journey! Get 1000 Coins as a new player and stay tuned for exciting airdrops and special rewards from Binance!

https://t.me/hamster_Kombat_bot/start?startapp=kentId5668051797 Play with me, become cryptoexchange CEO and get a token AirDrop! 💸 2k Coins as a first-time gift 🔥 25k Coins if you have Telegram Premium