en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
#Afar በአፋር ክልል ዱለሳ ወረዳ በተከሰተ " የመሬት መንቀጥቀጥ " ምክንያት ከተፈጠረ የመሬት ስንጥቅ ውስጥ ፍል ውሃ መፍለቅ መጀመሩን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የወረዳው አስተዳደር ተናግረዋል።
+1
#Afar በአፋር ክልል ዱለሳ ወረዳ በተከሰተ " የመሬት መንቀጥቀጥ " ምክንያት ከተፈጠረ የመሬት ስንጥቅ ውስጥ ፍል ውሃ መፍለቅ መጀመሩን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የወረዳው አስተዳደር ተናግረዋል። ከትናንት ሌሊት ጀምሮ መፍለቅ የጀመረው ፍል ውሃ መጠኑ እየጨመረ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። አፋር ክልል ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እያስተናገደ ነው። በክልሉ ጋቢ ራሱ ዞን በሚገኘው ዱለሳ ወረዳ ሳንጋቶ ቀበሌ ፍል ውሃ መፍለቅ የጀመረው ትናንት ሰኞ መስከረም 27/2016 ዓ.ም. ምሽት " የመሬት መንቀጥቀጥ " ከተከሰተ በኋላ እንደሆነ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ ደስታ እና ሁለት የቀበሌው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ነዋሪዎች ምን አሉ ? - ትናንት ምሽት ሦስት ሰዓት ገደማ መከሰት የጀመረው የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ ሶስት ጊዜ ያህል ተደጋግሟል። - የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የሚናገሩት ካቆመ በኋላ ሌሊት 10 ሰዓት ገደማ ላይ ድምፅ ሰማን። ጠዋት ላይ  ድምፅ ወደተሰማበት ቦታ ስናመራ ከመሬት ስንጥቅ ውስጥ ፍል ውሃ እየፈለቀ ተመልክተናል። - ውሃው የወጣው የአካባቢው ማህበረሰብ በሚኖርበት ሰፈር ውስጥ ነው። ድምፅ ነበረው። ማታ ፈርተን ነው ያደርነው። በጠዋት ሄደን ሁሉንም ነገር ለማየት ችለናል። - ውሃው በሚወጣበት የመሬት ስንጥቅ ስር ድምፅ ይሰማል። ወደላይ የሚፈናጠረው ፍል ውሃ መጠን እና የሚፈልቅበት ስንጥቅ መጠን እየጨመረ ነው። ፍል ውሃው በወጣበት ሳንጋቶ ቀበሌ ውስጥ ፍል ውሃ ባለመኖሩ አዲሱ ክስተት ነዋሪዎች ድንጋጤ እና ስጋት ላይ ጥሏል። የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ አሊ ደስታ ምን አሉ ? ° ከትናንት በስቲያ ከተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አንጻር የትናንቱ ትንሽ ያነሰ ነው። ° ከዚህ በኃላ ነው ፍል ውሃ መፍለቅ የጀመረው።

#Attention🚨 በአዋሽ ፣ መተሀራ ፈንታሌ ተራራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ መድረሱን የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አሳውቋል። " በሬክተር ስኬል 4.9 ነው። 150 ኪሎሜትር አካባቢ ርቀት ላይ የተፈፀመ
#Attention🚨 በአዋሽ ፣ መተሀራ ፈንታሌ ተራራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ መድረሱን የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አሳውቋል። " በሬክተር ስኬል 4.9 ነው። 150 ኪሎሜትር አካባቢ ርቀት ላይ የተፈፀመ ነው። ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ ተሰምቷል " ብሏል። " በስምጥ ሸለቆች ውስጥ ንዝራቱ ከማሰማት  በሻገር የመሬት መንቀጥቀጥ ከፈንታሌ ተራሮች ውጭ የደረሰ ስለመኖሩ አልተረጋገጠም " ሲል አክሏል። " በደሴ መሾመር እስከ ኮምቦልቻ የተየውም ንዝራቱ ነው። ክስተቱ ከሰሞኑ ጀምሮ በፈንታሌ ተራራ እና አዋሽ አካባቢዎች የነበረ ስሜት ነው " ብሏል። @topmereja

የአዲስ አበባ ከተማ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሽፋን 1. ካዛንቺስ ፣ መስቀል አደባባይ ፣ ሜክሲኮ ፣ ቸርችል ፣ አራት ኪሎ ፣ እስጢፋኖስ ኮሪደር እና መልሶ ማልማት 1000 ሄክታር ቦታ ስፋ
+1
የአዲስ አበባ ከተማ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሽፋን 1. ካዛንቺስ ፣ መስቀል አደባባይ ፣ ሜክሲኮ ፣ ቸርችል ፣ አራት ኪሎ ፣ እስጢፋኖስ ኮሪደር እና መልሶ ማልማት 1000 ሄክታር ቦታ ስፋት እና 40.4 ኪሎሜትር ርዝመት 2. ሳውዝጌት ፣መገናኛ ፣ሃያሁለት፣ መስቀል አደባባይ የኮሪደር ልማት 128.7 ሄክታር የቦታ ስፋት እና 7.1 ኪሎሜትር ርዝመት 3. ሲኤሜሲ ፣ ሰሚት ጎሮ ፣ ቦሌ አየር ማረፊያ ቪ አይ ፒ ተርሚናል ፣ አዲስ አፍሪካ አለም አቀፍ ኮንቬንሽንና ኤግዚብሽን ማዕከል የኮሪደር ልማት 146 ሄክታር የቦታ ስፋት እና 10.8 ኪሎሜትር ርዝመት 4. ሳር ቤት ፣ ካርል አደባባይ ፣ ብስራተ ገብርኤል ፣ አቦ ማዞሪያ ፣ ላፍቶ አደባባይ ፣ ፉሪ አደባባይ ኮሪደር ልማት 565 ሄክታር የቦታ ስፋት እና 15.9 ኪሎሜትር ርዝመት 5. አንበሳ ጋራዥ ፣ ጃክሮስ ጎሮ ኮሪደር ልማት 16.58 ሄክታር የቦታ ስፋት እና 3.1 ኪሎሜትር ርዝመት 6. አራት ኪሎ ፣ ሽሮ ሜዳ እንጦጦ ማርያም፣ ጉለሌ እጸዋት ማዕከል የኮሪደር ልማት 314 ሄክታር የቦታ ስፋት እና 13.19 ኪሎሜትር ርዝመት 7. የቀበና ወንዝ ዳርቻ ኮሪደር ልማት 372.5 ሄክታር የቦታ ስፋት እና 20 ኪሎሜትር ርዝመት 8. እንጦጦ ፣ፒኮክ ፓርክ የወንዝ ዳርቻ ልማት ኮሪደር ልማት 274 ሄክታር የቦታ ስፋት እና 21.5 ኪሎሜትር ርዝመት። በአጠቃላይ ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት 2817 ሄክታር የቦታ ስፋት እና 132 ኪሎሜትር ርዝመትን ይሸፍናል። @topmereja

#Gambellla በጋምቤላ ክልል 50 ብር ይሸጥ የነበረው ኮንዶም በ150 ብር ለሽያጭ እየቀረበ ይገኛል ተባለ !😂 በአሁኑ ወቅት የኤይ አይቪ ኤድስ የስርጭት ምጣኔ 3 ነጥብ 24 መድረሱን ገልፀው
+2
#Gambellla በጋምቤላ ክልል 50 ብር ይሸጥ የነበረው ኮንዶም በ150 ብር ለሽያጭ እየቀረበ ይገኛል ተባለ !😂 በአሁኑ ወቅት የኤይ አይቪ ኤድስ የስርጭት ምጣኔ 3 ነጥብ 24 መድረሱን ገልፀው በክልሉ እንደ ባህል ሆኖ የሚቆጠረው የውርስ ጋብቻ መበራከት እንዲሁም የተለያዮ ባህላዊ ጨዋታዎች ላይ የሚደረግ ጥንቃቄ የጎደለው የግብረ ስጋ ግንኙነት መኖር በሽታው እንዲስፋፋ ማድረጋቸውን ተናግረዋል:: በበሽታው ይበልጥ ተጋላጭ ከሆኑት የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል ሴቶችና በወጣትነት እድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሰዎች ናቸው።በክልሉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመከላከል የሚረዳው የኮንዶም ዋጋ መናር ሰዎች እራሳቸውን ከበሽታው ለመከላከል እንቅፋት እንደሆነባቸው ተገልጿል:: በክልሉ በአሁኑ ወቅት በነፃ በሚታደለው ሆነ በበርካታ የመሸጫ ቦታዎች በ50 ብር ለሽያጭ ሲቀርብ የነበረው ኮንዶም እስከ 150 ብር ድረስ እየተሸጠ እንደሚገኝ ታውቋል።

#Athletics የዓለም የማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤቷ በድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ ስሟ ስለመስፈሩ ምን አለች? አትሌት ትዕግሥት አሰፋ በሴቶች ማራቶን 2 ሰዓት ከ11 ደቂቃ ከ53 ሰከንድ በመግባት ባ
#Athletics የዓለም የማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤቷ በድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ ስሟ ስለመስፈሩ ምን አለች? አትሌት ትዕግሥት አሰፋ በሴቶች ማራቶን 2 ሰዓት ከ11 ደቂቃ ከ53 ሰከንድ በመግባት ባስመዘገበችው ክብረ ወሰን አማካኝነት ስሟ በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ (ጊነስ ቡክ ኦፍ ዎርልድ ሪከርድስ) ላይ ሰፍሯል። የዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ ከቢኤም ደብሊው ማራቶን ጋር በመተባባር በ2023 በበርሊን በተዘጋጁት ውድድሮቸ ላይ ክብረ ወሰን ላሻሻሉ ስፖርተኞች የምስክር ወረቀት ሽልማት ሰጥቷል። በአውሮፓውያኑ 2023 በጀርመን በርሊን በተካሄደው ማራቶን 11 ክብረ ወሰኖችን ለማሻሻል ታስቦ ስምንት መሳካቱን የዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ ያሳያል። አትሌት ትዕግሥት ከቢቢሲ ጋር በነበራት አጭር ቆይታ ወቅት “በሽልማቱ እና በዕውቅናው በጣም ደስተኛ ነኝ” ያለች ሲሆን፣ የሯሷን ክብረ ወሰን ማሻሻል እንደምትፈልግም ተናግራለች። “ከዚህም በኋላ ሪከርዱን ከዚህ በበለጠ ማሻሻል እፈልጋለሁ. . .ችሎታው አለኝ፤ አቅሙም አለኝ። ስለዚህ ችሎታዬን አዳብሬ ከዚህ የበለጠ ሰዓት መሮጥ እፈልጋለሁ።” የዓለም የሴቶች ማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤቷ አትሌት ትዕግሥት አሰፋ በፓሪስ ኦሊምፒክ 2 ሰዓት ከ22 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ለአገሯ የብር ሜዳሊያ ማስገኘቷ ይታወሳል። ከ14 ዓመት በፊት ወደ ሩጫ ዓለም የገባቸው ትዕግሥት አሰፋ መስከረም 13/2016 ዓ.ም. በጀርመን በርሊን በተካሄደው 48ኛው የማራቶን ውድድር የዓለም ክብረ ወሰንን ከሁለት ደቂቃ በላይ በማሻሻል 2 ሰዓት ከ11 ደቂቃ ከ53 ሰከንድ መግባቷ ይታወሳል።

#Update በባህር ዳር ከተማ ሊካሄድ የነበረው 11ኛው የጣና ፎረም ለሶስተኛ ጊዜ ተራዘመ!! የአፍሪካ ሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ የሚመክረው እና በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ የሚካሄደው ዓመታ
#Update በባህር ዳር ከተማ ሊካሄድ የነበረው 11ኛው የጣና ፎረም ለሶስተኛ ጊዜ ተራዘመ!! የአፍሪካ ሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ የሚመክረው እና በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ የሚካሄደው ዓመታዊው የጣና ፎረም ጉባኤ ለሶስተኛ ጊዜ ተራዘመ። 11ኛው ጉባኤ መጀመሪያ ሊካሄድ ቀን ተቆርጦለት የነበረው ባለፈው ዓመት ከጥቅምት2-4 2016 ዓ.ም ነበር። ሆኖም ጉባኤው “ባልተጠበቁ ሁኔታዎች ምክንያት” እንደተራዘመ የፎረሙ ጽህፈት ቤት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰላም እና ደህንነት ጥናቶች ተቋም አስታውቆ ነበር። ጉባኤው ሚያዚያ ወር 2016 ዓ.ም. እንደሚካሄድ ጽህፈት ቤቱ በጊዜው አስታውቆ የነበረ ቢሆንም በተባለው ጊዜ ሳይካሄድ ለሁለተኛ ጊዜ ተራዝሟል። “አፍሪካ እየተሻሸለ በመጣው የዓለም ሥርዓት ውስጥ” የሚል መሪ ቃል የያዘው 11ኛው ጉባኤ ከጥቅምት 15-17 2017 ይካሄዳል ተብሎ ተጠብቆ ነበር። ነገር ግን ፎረሙ በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መግለጫ “11ኛው የጣና ከፍተኛ የጸጥታ ጉዳዮች ፎረም [እ.ኢ.አ] ወደ 2025 መተላለፉን የጣና ፎረም ሴክሬታሪያት ለማሳወቅ ይወዳል” ብሏል። ፎረሙ አክሎም የጣና ፎረም ሴክሬታሪያት ከጣና ፎረም ቦርድ ጋር በመሆን ፎረሙ የሚካሄድበትን ቀጣይ ቀን ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል። የጣና ፎረም ሲራዘም ይህ የመጀመሪያው አይደለም። ከሶስት ዓመት በፊት 10ኛው የጣና ፎረምም በተመሳሳይ ሁኔታ መራዘሙ ይታወሳል። ህዳር አጋማሽ 2014 ላይ ሊካሄድ ነበረው ይህ ፎረም ተካሄደው ከአንድ ዓመት በኋላ ጥቅምት 2015 ዓ.ም ነው። ከዚያ በፊትም በ2013 ዓ.ም የነበረው የጣና ፎረም በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ በአዲስ አበባ አናሳ ተሳታፊዎች ባሉበት እንዲካሄድ ሆኖ ነበር። @topmereja

#ኢትዮጵያ በዳውሮ ዞን ቶጫ ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተገለጸ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ በሚገኙ በ5ቱ ቀበሌዎች ላይ ትላትና
+1
#ኢትዮጵያ በዳውሮ ዞን ቶጫ ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተገለጸ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ በሚገኙ በ5ቱ ቀበሌዎች ላይ ትላትና ቀን በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ተከትሎ፤ የተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት ማስከተሉ ተገልጿል። በዚህም በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች፤ ቲማ፣ ደሊ፣ ሻንዳ፣ ኦክሊና ቦቶሪ ላይ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ በመዝነቡ እና የአካባቢው መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ ተጨምሮ የተስተዋለው የአፈር መንሸራተት አደጋ በአርሶ አደሮች ማሳ፣ በእንስሳት፣ በመኖሪያ ቤቶች እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ወረዳው አስታውቋል። በደረሰው ክስተት በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩ የተገለጸ ሲሆን፤ የተከሰተውን ከፍተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ተከትሎ ወረዳው ግብረ- ኃይል አቋቁሞ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል። አጠቃላይ የጉዳት መጠኑ በቀጣይ ከሚመለከተው ክፍል ጋር በመሆን እንደሚገለጽ የቶጫ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አስታውቋል። የወረዳው መንግሥት በቀጣይም ከመደበኛ በላይ መጠን ያለው ዝናብ የሚጠበቅ በመሆኑ ማኅበረሰቡ አስፈላጊውን ሁሉ ቅድመ ዝግጅት እና ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል። @topmereja

የእስራኤል ጦር የሄዝቦላህ ከፍተኛ አዛዥ የሆኑትን ሱሄል ሁሴኒ መግደሉን አስታወቀ ጦሩ በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫ የሄዝቦላህ የበጀት እና ሎጂስቲክ ክፍል ሃላፊ በቤሩት በተፈጸመ የአየር ጥቃት መገ
የእስራኤል ጦር የሄዝቦላህ ከፍተኛ አዛዥ የሆኑትን ሱሄል ሁሴኒ መግደሉን አስታወቀ ጦሩ በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫ የሄዝቦላህ የበጀት እና ሎጂስቲክ ክፍል ሃላፊ በቤሩት በተፈጸመ የአየር ጥቃት መገደላቸውን አመላክቷል። ሁሴኒ ከኢራን የሚላኩ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን ለሄዝቦላህ የተለያዩ ወታደራዊ ክፍሎች የማከፋፈል ሃላፊነት ነበራቸው ያለው ጦሩ የሄዝቦላህ ወታደራዊ ምክርቤት አባል እንደነበሩም ጠቁሟል። ሄዝቦላህ ሁሴኒ በቤሩት ተገድለዋል በሚል በእስራኤል ጦር የወጣውን መረጃ እስካሁን አላስተባበለም። የሊባኖሱ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ቡድን ትናንት ምሽት በእስራኤል የስለላ ድርጅት (ሞሳድ) ዋና ቢሮ አቅራቢያ ለተፈጸመው የሮኬት ጥቃት ሃላፊነቱን መውሰዱን ዩሮ ኒውስ አስነብቧል። ዋና መሪው ሀሰን ናስራላህ የተገደሉበት ሄዝቦላህ አዲስ መሪ መምረጡንና በጋዛ ተኩስ እስካልቆመ ድረስ ከእስራኤል ጋር የሚያደርገው ውጊያ እንደማይቆም ገልጿል። እስራኤል ወደ ደቡባዊ ሊባኖስ የእግረኛ ጦሯን በማስገባት ከሄዝቦላህ ጋር የምታደርገው ውጊያ መቀጠሉን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል። የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴርም እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ በፈጸመችው የአየር ድብደባ በጥቂቱ 10 የእሳት አደጋ ሰራተኞች መገደላቸውን አስታውቋል። ሄዝቦላህ ለፍልስጤማውያን አጋርነቱን በማሳየት ወደ እስራኤል መተኮስ ከጀመረ ዛሬ ጥቅምት 8 አንድ አመት ደፍኗል። እስራኤል በጦር ጄቶቿ በቤሩትና አካባቢው የምትፈጽመው ድብደባና በደቡባዊ ሊባኖስ እየተካሄደው ያለው ውጊያ ሊባኖስን እንደ ጋዛ እንዳያፈራርሳት ስጋት ደቅኗል። ኢትዮጵያን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሊባኖስ እያስወጡ ሲሆን፥ ቱርክም ዜጎቿን ከቤሩት ለማስወጣት 2 ሺህ ሰዎችን የሚይዙ መርከቦችን መላኳ ተሰምቷል። @topmereja

በመዲናዋ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ በዚህ ሳምንት ይጀመራል ከንቲባ አዳነች የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል። የኮሪደርና
+1
በመዲናዋ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ በዚህ ሳምንት ይጀመራል ከንቲባ አዳነች የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል። የኮሪደርና የመልሶ ማልማት ስራ ዋና ዓላማ አዲስ አበባን እንደስሟ ውብና ጽዱ፣ ለነዋሪዎቿ ምቹና ማራኪ እንዲሁም የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን ተወዳዳሪነት ማስቀጠል መሆኑን ገልጸዋል። በከተማው ብዙ አካባቢዎች እርጅና ተጭኗቸው ዜጎች ክብራቸውን በማይመጥን መልኩ እየኖሩ እንደነበር አስታውሰው፤ ይህም ገጽታዋን በእጅጉ መጉዳቱን ገልጸዋል። የኮሪደርና መልሶ ማልማት በመጀመሪያው ምዕራፍ ስራ መለወጥ እንደሚቻል የታየበት ጠንካራ ትብብርና የስራ ባህል የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል። የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ቅድመ ዝግጅትን በተመለከተ ከነዋሪው ጋር ውይይት መደረጉንና በዚህም ስምንት ኮሪደሮችን የማልማት ስራ በዚህ ሳምንት እንደሚጀመር ገልጸዋል። ለቀበሌ ቤት ተነሺዎች ምትክ ቤቶች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው፤ይህም ነዋሪዎች ከዚህ ቀደም ከሚኖሩበት በእጅጉ የተሻለ መሆኑንና ለግል ቤቶችም አስፈላጊው ካሳ መዘጋጀቱን ከንቲባዋ ተናግረዋል። @topmereja

ስለ አዋሽ ፈንታሌ የመሬት መንቀጥቀጥ የሰመራ ዩኒቨርስቲ ባለሙያዎች እና የወረዳው አስተዳዳሪ ምን አሉ? እሁድ ምሽት እስከ አዲስ አበባ ድረስ ንዝረቱ የተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተበት የአፋር
+2
ስለ አዋሽ ፈንታሌ የመሬት መንቀጥቀጥ የሰመራ ዩኒቨርስቲ ባለሙያዎች እና የወረዳው አስተዳዳሪ ምን አሉ? እሁድ ምሽት እስከ አዲስ አበባ ድረስ ንዝረቱ የተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተበት የአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ፤ ከ700 በላይ በከሰም ግድብ እና ፈንታሌ ተራራ አካባቢ የነበሩ ነዋሪዎችን አስቀድሞ ወደ ሌላ ቦታ ማዘዋወሩን አስታወቀ። የትናንቱን ጨምሮ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በአካባቢው በተከሰቱ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጦች ትምህርት ቤት እና መስኪድን ጨምሮ በአራት ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን የወረዳው አስተዳደር ለቢቢሲ በሬክተር ስኬል 4.9 ሆኖ የተመዘገበው ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ 10 ኪሎ ሜትር ጥልቀት ያለው እንደነበር “ኧርዝ ክዌክ ትራክ” የተሰኘው የመሬት መንቀጥቀጥ መከታተያ ድረ ገፅ ዘግቧል። የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባህ አባህ ሁሴን፤ የትናንቱ የመሬት ነውጥ “መጠኑ ሰፋ ያለ እና አስደንጋጭ” እንደነበር ለቢቢሲ ተናግረዋል። የመሬት መንቀጥቀጡ በተከሰተበት ሰዓትም በወረዳው በሚገኘው ፈንታሌ ተራራ አካባቢ ላይ “ከፍተኛ ድምፅ እና ፍንዳታ” ተሰምቶ እንደነበር የወረዳ አስተዳዳሪው ገልጸዋል። እስካሁን ድረስ [ሰኞ ረፋድ] ፍንዳታው ወደ ተከሰተበት አካባቢ ተጉዘው አለመመልከታቸውን አክለዋል። “ተራራው መፈንዳት የጀመረው የመሬት መንቀጥቀጡ ሲያጋጥም ነው። ፍንዳታው ካጋጠመ በኋላ ትንሽ ሻል የማለት ሁኔታ ተከስቷል” ሲሉ በሰዓቱ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል። በወረዳው በተከሰቱት የመሬት መንቀጥጦች የተፈጠሩ የመሬት ስንጥቆች ርዝመት "በጣም ረጅም" መሆኑ ተገልጿል። @topmereja

#ኢትዮጵያ #Tigray " ለሚፈጠረው ማንኛውም ዓይነት ጥፋት ብቸኛ ተጠያቂ ቡድኑና አመራሩ መሆናቸውን ለህዝባችን መግለፅ እንወዳለን " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ስ
+1
#ኢትዮጵያ #Tigray " ለሚፈጠረው ማንኛውም ዓይነት ጥፋት ብቸኛ ተጠያቂ ቡድኑና አመራሩ መሆናቸውን ለህዝባችን መግለፅ እንወዳለን " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ስርዓት አልበኝነት ለመቆጣጠር " የጥፋት ሃይል " ሲል በስም  ባልገለፀው አካል ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚጀምር አስታወቀ። " ህግና ስርዓት ለማስክበር የተጀመሩ ጥረቶች በማጠናክር የህዝቡ ስጋት ከግምት ያስገባ እንቅስቃሴ አደርጋለሁ " ብሏል ጊዚያዊ አስተዳደሩ። በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት መስከረም 27/2017 ዓ.ም ያወጣውን የመንግስታዊ ስልጣን ሹም ሽር የነቀፈው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፤ " ቡድኑ ወደ ስርዓት አልበኝነት ለመሸጋገር የሚያስችለው ግልፅ  መንግስታዊ ግልበጣ ማካሄዱን አውጇል " ሲል ከሰዋል።   " ቡድኑ የመንግስት ስልጣን እንዴትና በምን ሁኔታ እንደሚያዝ ተደብቆት ሳይሆን ከዛሬ መስከረም 27/2017 ዓ.ም ጀምሮ ስርዓት አልበኝነት ለማስፈን ያለው ከፍተኛ ፍላጎት ለማሳካት ሆን ብሎ ያደረገው ነው " ብሏል የጊዚያዊ አስተዳደሩ።  " ጊዚያዊ አስተዳደሩ ይህንን ስርዓት አልበኝነት በትእግስት አያልፈውም " ብሎ " የጥፋት ሃይል " ሲል በገለፀው áŠ áŠŤáˆ ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ ይጀምራል ብሏል። " በሂደቱ ለሚፈጠር ማንኛውም ዓይነት ጥፋት ብቸኛ ተጠያቂ ቡድኑና አመራሩ መሆናቸውን ለህዝባችን መግለፅ እንወዳለን " ሲል አስጠንቅቋል። #topmereja @topmereja

#ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ የሚገኘው የህንድ ኤምባሲ ለኢትዮጵያዊያን የህክምና ቪዛ መስጠት አቆመ፡፡ ኤምባሲው እንደገለፀው ይህንን እርምጃ ለመውሰድ የተገደደው የሚቀርቡለት ሀሰተኛ ዶክመንቶች እየጨመሩ በመምጣታቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያን በህንድ ለመታከም በሚል ቪዛ ከወሰዱ በኋላ ወደአገራቸው ከመመለስ ይልቅ በዚያው ሌላ አገር እንደሚሄዱ የጠቀሰው ኤምባሲው ሀሰተኛ ዶክመንት የሚያቀርቡለትም እነዚህኞቹ መሆናቸውን አስረድቷል፡፡ ቀደም ሲል ኢትዮጵያዊያንን ወደህንድ ለህክምና ለመውሰድ ሁኔታዎችን የሚያመቻቹ በርካታ ኤጀንሲዎች የነበሩ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህንድ ኤምባሲ ለአንድ ኤጀንሲ ብቻ እውቅና ሰጥቶ የቪዛ ስራው ይከናወን ነበር፡፡ ይሁንና ይህ በቦሌ ሚካኤል አካባቢ የሚገኘው ኤጀንሲ በዚህ ሳምንት በመንግስት እንዲዘጋ ተደርጓል፡፡ ኤጀንሲው በምን ምክንያት እንደተዘጋ ለማወቅ ያልተቻለ ሲሆን የህን ኤምባሲም የህክምና ቪዛ ለምን መስጠት እንዳቆመ ያለው ነገር የለም፡፡ የኤምባሲው ምንጮች ግን ሀሰተኛ ሰነድ በብዛት መቅረቡን ተከትሎ ይህ እርምጃ ሊወሰድ እንደቻለ ለካፒታል ጋዜጣ ገልፀዋል፡፡ @topmereja

የሐዘን መግለጫ የብዙዎች አባት እና አለኝታ የነበሩት አቶ ኃይለኢየሱስ በላይነህ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም. በተወለዱ በ 78 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በ
የሐዘን መግለጫ የብዙዎች አባት እና አለኝታ የነበሩት አቶ ኃይለኢየሱስ በላይነህ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም. በተወለዱ በ 78 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተውናል ። መስከረም 28 ቀን 2017ዓ.ም በናዝሬት ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን ከቀኑ 8:00 ሰዓት በሚፈፀመው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ በመገኘት ሐዘናችንን እንዲጋሩን ጥሪ እናቀርባለን ። ባለቤታቸው ወይዘሮ ወጋየሁ ባህሩ እና ልጆቻቸው @topmereja

#ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን አስመልክቶ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ @topmereja
#ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን አስመልክቶ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ @topmereja

#Update እግር ኳስ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በታች ተጨዋቾች በሚፎካከሩበት የሴካፋ እግር ኳስ ግጥሚያ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ከዩጋንዳ ጋር አቻው ጋር ተጋጥሞ 3 ለ0 ተሸንፏል ። ሦስተኛው ግብ የተቆጠረው ቡድኑ ዛሬ በአዛም ኮምፕሌክስ ስታዲየም ውስጥ ያደረገው የመጀመርያ የምድብ ጨዋታውን ነው ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በበኩሉ ለ2025 የአፍሪቃ ዋንጫ ማጣርያ ከጊኒ ጋር ለሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ዝግጅቱን ከወዲሁ መጀመሩ ታውቋል ። ብሔራዊ ቡድኑ እሁድ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሜዳ የሁለተኛ ቀን ልምምዱን አከናውኗል ። በትናንት ልምምድ ላይም ከአሜሪካ ቡድኑን ከሚቀላቀለው ሱራፌል ዳኛቸው በስተቀር 22 ተጫዋቾች መገኘታቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዐሳውቋል ። ከጊኒ ጋር ሁለት የማጣርያ ጨዋታዎች ጥቅምት 2 እና 5 ኮትዲቯር አቢጃን ውስጥ እንደሚከናወኑም ታውቋል ።

የስፖርት ዘገባ በሊዝበን የግማሽ ማራቶን ብርቱ ፉክክር ኢትዮጵያዊው አትሌት ሞስነት ገረመው ለድል በቅቷል ። በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ ሊቨርፑል መሪነቱን እንዳስጠበቀ ነው ። ማንቸስተር ሲቲ እና አር
የስፖርት ዘገባ በሊዝበን የግማሽ ማራቶን ብርቱ ፉክክር ኢትዮጵያዊው አትሌት ሞስነት ገረመው ለድል በቅቷል ። በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ ሊቨርፑል መሪነቱን እንዳስጠበቀ ነው ። ማንቸስተር ሲቲ እና አርሰናልም እግር በእግር ይከተላሉ ። በጀርመን ቡንደስሊጋ መሪው ባየር ሙይንሽን በሁለት ነጥብ ከሚበልጠው አይንትራኅት ፍራንክፉርት ጋር ነጥብ ለመጋራት ተገድዷል ። ለአይንትራኅት ፍራንክፉርት ዖማር ማርሙሽ ድንቅ ብቃቱን ዐሳይቷል ። ሮበርት ሌቫንዶቭስኪ በስፔን ላሊጋ ሔትትሪክ ሠርቶ ባርሴሎናን ለድል አብቅቷል ። በዩናይትድ ስቴትስ ዝነኛው የቅርጫት ኳስ ግጥሚያ አባት እና ልጅ አንድ ላይ በመሰለፍ ታሪክ አስመዝግበዋል። ፖርቹጋል ውስጥ ትናንት በተከናወነው የሊዝበን የግማሽ ማራቶን ብርቱ ፉክክር ኢትዮጵያዊው አትሌት ሞስነት ገረመው ኬንያውያን እና የዩጋንዳ ሯጮችን አስከትሎ በአሸናፊነት አጠናቋል ። አትሌት ሞስነት ገረመው ውድድሩን በአንደኛነት ያጠናቀቀው 1:03.09 በሆነ ጊዜሮጦ በመግባት ነው ። በዚህ ውድድር፦ የኬንያው አትሌት ፔተር ክዋሊ ሰባት ሰከንድ ከሞስነት በመዘግየት ሁለተኛ ወጥቷል ። ሦስተኛ ደረጃ ያገኘው የዩጋንዳው ሯጭ ቪክቶር ክዌምቦይ በሞስነት በ14 ሰከንዶች ተቀድሟል ። ኬንያውያት አሸናፊ በሆኑበት በሴቶች ተመሳሳይ ርቀት ፉክክር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዓለም ንጉሥ የሦስተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች ። ኬንያዊቷ ሯጭ ፌይዝ ቼፕቺር ኪፕሮች ርቀቱን በ01:10:33 በማጠናቀቅ አንደኛ ወጥታለች ። ሌላኛዋ ፌይዝ ቼፕኮዬች በአራት ሰከንዶች ተቀድማ ሁለተኛ ደረጃ አግኝታለች ። ዓለም ያጠናቀቀችው 01:10:46 በመሮጥ ነው ። @topmereja

#ኢትዮጵያ በዶክተር ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት አቶ ጌታቸው ረዳ ጨምሮ 13 የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ባለስልጣናትን ከስልጣናቸው እንዲወርዱ መወሰኑን አስታወቀ። በቅርቡ ጉባኤ ያደረ
+1
#ኢትዮጵያ በዶክተር ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት አቶ ጌታቸው ረዳ ጨምሮ 13 የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ባለስልጣናትን ከስልጣናቸው እንዲወርዱ መወሰኑን አስታወቀ። በቅርቡ ጉባኤ ያደረገው ይህ የህወሓት ቡድን በምትካቸው የሚሰሩ ያላቸውን አዳዲስ ሹመቶችንም ሰጥቷል። ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በሊቀመንበርነት የሚመሩት የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ቡድን ዛሬ እንዳስታወቀው መስከረም 24 ቀን 2017 ዓ/ም ባደረገው የማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ህወሓትን ወክለው በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ያሉ ባለስልጣናት ከሓላፊነታቸው እንዲወርዱ መወሰኑ ይፋ አድርጓል። በጊዚያዊ አስተዳደሩ ሃምሳ ሲደመር አንድ ድርሻ እንዳለው የገለፀው የህወሓት ቡድኑ፥ ህወሓትን ወክለው በግዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ፣ የዞን አስተዳደር እና ኤጀንሲዎችና ኮሚሽኖች ያሉ ባለስልጣናት መቀየሩን አስታውቋል።በዚህ መሰረት የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ እንዴት እና በማን ይተካሉ የሚለው ከፌደራል መንግስቱ እና ከሚመለከታቸው አካላት በመግባባት ይፈፀማል ሲል ህወሓት ዛሬ ባወጣው መግለጫው ይፋ አድርጓልከዚህ በተጨማሪ አቶ በየነ ምክሩ፣ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት፣ ዶክተር ሓጎስ ጎደፋይ ጨምሮ ሌሎች በህወሓት ውክልና ወደ ግዚያዊ አስተዳደሩ የገቡ ባለስልጣናት ማውረዱን የገለፀው የፓርቲው መግለጫ በምትካቸው ደግሞ እነ ዶክተር አብርሃም፣ አቶ አማኑኤል አሰፋ፣ ዶክተር ፍስሃ ሃፍተፅዮን እና ሌሎችን ለተለያዩ ሐላፋነቶች መሾሙ ያትታል። @topmereja

#Update የሐማሱ ምክትል መሪ ከቢቢሲ ጋር ያደረጉት ሞጋች ቃለ-ምልልስ ከሐማስ ነባር መሪዎች መካከል አንዱ የሆነት ኻሊል አል-ሀያ ለቢቢሲ ቃለ ምልልስ ሰጥተዋል። ባለፈው ዓመት የተቀሰቀሰው እና
+1
#Update የሐማሱ ምክትል መሪ ከቢቢሲ ጋር ያደረጉት ሞጋች ቃለ-ምልልስ ከሐማስ ነባር መሪዎች መካከል አንዱ የሆነት ኻሊል አል-ሀያ ለቢቢሲ ቃለ ምልልስ ሰጥተዋል። ባለፈው ዓመት የተቀሰቀሰው እና ቡድናቸው ያስጀመረው ጦርነት ምክንያታዊ ነው ሲሉ ይሞግታሉ። ከቢቢሲው ጄሬሚ ቦዌን ጋር ቆይታ ያደረጉት የሐማስ ምክትል መሪ ኻሊል አል-ሀያ ከአንድ ዓመት በፊት ቡድናቸው እስራኤላውያን ሰላማዊ ዜጎችን አልገደለም ሲሉ ያስተባብላሉ። ነገር ግን መረጃዎች የሚጠቁሙት ሌላ ነው። ባለፈው ዓመት መስከረም 26 (ጥቅምት 7/2023) ሐማስ በእስራኤል ምድር ላይ በፈጸመው ጥቃት አብዛኞቹ ሲቪል የሆኑ 1200 ሰዎች ተገድለዋል። ቡድኑ ከ250 በላይ ሰዎች አግቶ ወደ ጋዛ ወስዷል። ሐማስ በዩናይትድ ኪንግደም እና በሌሎች አገራት ሽብርተኛ ቡድን ተብሎ ተፈርጇል። ቃለ-ምልልሱ የተካሄደው አብዛኞቹ የሐማስ ፖለቲካዊ አመራሮች በሚኖሩባት የኳታሯ መዲና ዶሃ ነው። እስራኤል ባለፈው ሐምሌ ኢስማኢል ሃኒያህን መግደሏን ተከትሎ ኻሊል አል-ሀያ ከጋዛ ውጪ ካሉ የሐማስ መሪዎች ነባሩ ሆነዋል። @topmereja

# news update ሩሲያዊው የፑቲን ተቃዋሚ ለዩክሬን ሲዋጋ ተገደለ!!! አንድ ዝነኛ የፖለቲካ መብት ተቆርቋሪና የፑቲን ተቃዋሚ ሩሲያዊ ለዩክሬን ተሰልፎ ሲዋጋ በአውደ ውጊያ ተገደለ። ኢልዳር ዳዲ
# news update ሩሲያዊው የፑቲን ተቃዋሚ ለዩክሬን ሲዋጋ ተገደለ!!! አንድ ዝነኛ የፖለቲካ መብት ተቆርቋሪና የፑቲን ተቃዋሚ ሩሲያዊ ለዩክሬን ተሰልፎ ሲዋጋ በአውደ ውጊያ ተገደለ። ኢልዳር ዳዲን በሚል ስም የሚታወቀው ሥመ ጥሩ ተቃዋሚ የተገደለው ከሰሞኑ በነበረ ፍልሚያ ነው። የርሱን ሞት ይፋ ያደረገው ሲቪክ ካውንስል ለቢቢሲ እንደገለጸው ''የዳዲን ሞት የጀግና ሞት ነው፤ ጀግንነቱ ሲዘከር ይኖራል'' ብሏል። የመብት ተቆርቋሪው ተዋጊ በበጎ ፈቃደኛ ታጋዮች ባታሊዮን ሥር ሆኖ የገዛ አገሩን ሩሲያን ሲዋጋ ነበር። ዳዲን በካርኪቭ ክልል፣ ሰሜን ምሥራቅ ዩክሬን ግንባር በአውደ ውጊያ ላይ ሳለ ከሩሲያ ኃይሎች በተተኮሰ መድፍ እንደተገደለ ነው የተዘገበው። አንዲት በስደት የምትኖር የፖለቲካ ተቃዋሚ ሩሲያዊት የዳዲንን መሞት ለቢቢሲ አረጋግጣለች። ኢልዳር ዳዲን በሩሲያ ሰላማዊ ተቃውሞዎችን በመምራት የሚታወቅ ሰው ነበር። እርሱን ለማጥቃት እንደወጣ የሚነገር አንቀጽ 212.1 ለመታሰር የመጀመርያው ሲሆን ዛሬም ድረስ ይህ አንቀጽ በተለምዶ “የዳዲን አንቀጽ’ ተብሎ ይጠራል። @topmereja

# International News እስራኤል የሐማስን ጥቃት 1ኛ ዓመት በምትዘክርበት ቀን በጋዛ እና በቤይሩት ጥቃት ፈጸመች የእስራኤል መከላከያ ኃይል እሑድ ዕለት ቤይሩት የሚገኙ በርካታ የሄዝቦላህ
# International News እስራኤል የሐማስን ጥቃት 1ኛ ዓመት በምትዘክርበት ቀን በጋዛ እና በቤይሩት ጥቃት ፈጸመች የእስራኤል መከላከያ ኃይል እሑድ ዕለት ቤይሩት የሚገኙ በርካታ የሄዝቦላህ የደኅንነት ቀጣናዎች እና የመሣሪያ ማከማቻዎችን መምታቱን ገለጸ። በሊባኖስ ዋና ከተማ ቤይሩት ከፍተኛ ድምፅ ያለው ፍንዳታ ተሰምቷል። ይህ የሆነው የእስራኤል ጦር በአካባቢው ያሉ ሰዎች ለቀው እንዲወጡ ማሳሳቢያ ከሰጠ ከሰዓታት በኋላ ነው። እስራኤል በሊባኖስ የምታደርገውን ጥቃት አጠናክራ የቀጠለች ሲሆን፣ እሑድ ምሽት በተፈጸመው ጥቃት የቤይሩት ሰማይ በቃጠሎ እና በጭስ ታፍኖ ታይቷል። የሊባኖስ ፓርላማ አባል የሆኑት ሜልሔም ኻላፍ “ሊባኖስ ላይ ከፍተኛ ጥቃት እየተፈጸመ ነው” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ሜልሔም እንደሚሉት እስራኤል ቤይሩት ላይ እያደረሰች ያለው ጥቃት “ተመጣጣኝ” አይደለም። “ሰላማዊ ዜጎች ላይ ቦምብ መጣል፤ መንደሮችን ማውደም፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሕንፃዎችን ማፈራረስ፤ ንፁሐንን መግደል፤ ይሄ ሁሉ እስራኤል ሽብርተኛ ያለችውን ለመግደል የምታደርገው ጥረት ነው።” በተያያዘ ዜና የሊባኖሱ ሄዝቦላህ በሰሜናዊ እስራኤል በፈጸመው ጥቃት 10 ሰዎች መቁሰላቸው ተሰምቷል። የእስራኤል የአምቡላንስ አገልግሎት እንደገለፀው በሐይፋ እና ሪቤሪያስ ከተሞች ሄዝቦላህ በሰነዘረው የሚሳዔል ጥቃት 10 ሰዎች ቆስለዋል። # @topmereja