cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

የቀድሞ አበው እና እመት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ጥበብ... 👇👇👇👇👇👇👇👇 👉 @behlateabew 👈 👆👆👆👆👆👆👆👆 https://t.me/+RICJUxY54uwNbPXe

Show more
Advertising posts
10 901Subscribers
-424 hours
-237 days
-7230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

"ቤተክርስትያንን መርዳት ከፈለክ ሌሎችን ለማረም ከማሰብ በፊት በቅድሚያ እራስን ማስተካከል ይበጃል። እራስህን ካስተካከልክ አንድ የቤተክርስትያን ክፍል ዳነ ወይም ተስተካከለ ማለት ነው። ሁሉም ሰው ይህን ማድረግ ከቻለ ቤተክርስትያን ጤናማ ትሆናለች። ስለዚህ ላስተዋለው ሰው ሌሎች ላይ መፍረድ እጅግ በጣም ቀላል ነው እራስን ማስተካከል ግን ጥረት ይጠይቃል።" #ቅዱስ_ፓሲዮስ
Show all...
👍 8
#ከአዲሱ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መጽሐፍ ትርጉም በጨረፍታ እናስቃኛችሁ። እውነትም አፈወርቅ ጥዑም ዘይጥዕም እም መዓር ወሦከር። #10_የነፍስ_ምግብ_ጉርሻዎች #የነፍስ_ምግብ አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ አዲሱ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ #የነፍስ_ምግብ የተሰኘው መጽሐፍ በገበያ ላይ መዋሉን ምክንያት በማድረግ 10 የነፍስ ምግብ ጉርሻዎችን ከነፍስ ምግብ መጽሐፍ ጋብዘናል፦ #1 "ቃላቶችህ ምንም ያህል ትክክል ቢሆኑም በቁጣ ስትናገር ሁሉንም ነገር ታበላሻለህ።" #2 "ብል ልብስን እንደሚበላው ሰውንም ቅናት ይበዋል።" #3 "እግዚአብሔር የሚጠይቀው ጥቂት፣ የሚሰጠው ብዙ ነው" #4 "እያንዳንዱ ሰው የህይወቱ ሠዓሊ እና ቀራፂ ነው።" #5 "ባለጠጋ ብዙ ያለው ሳይሆን ብዙ የሚሰጥ ነው።" #6 “ምሕረት አምላክን ይመስላል ሰይጣንንም ያሳዝነዋል።" #7 " ኃጢአት ስትሠራ እንጂ ንስሐ ስትገባ አትፈር" #8 "ለምን በትንንሽ ነገሮች መደሰትን አትማርም - በጣም ብዙ ናቸው።" #9 "ጸሎት የጭንቀት ሁሉ መሸሸጊያ፣የደስታ መሠረት፣ ከሐዘን መከለያ ናት። " #10 "ክርስቶስን በቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ላይ ባለው ነዳይ ውስጥ ማግኘት ካልቻላችሁ፣ በቤተመቅደስ ውስጥ አታገኙትም።" እውነትም #የነፍስ_ምግብ የሚያሰኘው ይህ ድንቅ መጽሐፍ ከእንጀራ በፊት አንድ አንድ ጉርሻ ጎረስ ጎረስ እያረጋችሁ እንድትመገቡ ጋብዘናችኋል። #የመጽሐፉ ርእስ #የነፍስ ምግብ የጀርባው ዋጋ=450 አርጋኖናዊ ቅናሽ እንደተጠበቀ ነው ይጎብኙን። ለበለጠ @dawitfikr ይዘዙን። https://t.me/BetMetsahfte #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ዋናው_በር_ፊትለፊት_ሽዋ_ዳቦ_መነጽር_ቤቶቹ_ውስጥ_ወይም_0912044752_0925421700_ይደውሉ
Show all...
👍 8
የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ
✍✝#"ሰላም ለእሌኒ ንግሥት ዘከሠተት መስቀለ በጎልጎታ:ለክርስቲያን ዘይከውን ወልታ፤እምኀበ ወጽአ ጢስ በሃይማኖታ፤ወዓዲ ረከበት ቅንዋተ መስቀሉ ለክርስቶስ፤ወአግበረት ልጓመ ፈረስ በከመ ይቤ ዘካርያስ" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
Show all...
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ዳዋ ጥሳ ፣ ተራራ ቧጣ ፣ ቋጥኝ ፈልፍላ ፣ የእምነት እና የታሪክ ቦታዎችን የመሥራት ብቃት ፣ ችሎታ ፣ መንፈሳዊነት እና መለኮታዊ ኃይል አላት ። መስቀል አደባባይ እንዲህ ዛሬ ያም እየተነሳ የእኔ ነው ያም እየተነሳ የእኔ ነው ከማለቱ በፊት ጉቶውን ነቅላ አረሙን አርማ ስትጠቀምበት የኖረችው ይኸችው መከረኛዋ እናታችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ናት ። አሁንም ቤተ ክርስቲያናችን የሆነ በረሃ ላይ ሄዳ እንደ መስቀል አደባባይ ዓይነት በዓላቶቿን የምታከብርበት ቦታ ብታዘጋጅ ይኸንኑ ያዘጋጀችውን ቦታ ሊቀራመቷት የሚመጡ አይጠፋም ። ዝንጀሮ እና ጦጣ ሁል ጊዜ ያልዘራውን ያጭዳል ያላበቀለውንም ያለ ይሉኝታ ይበላል ። ቅድስት እናታችን ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችንም ይኸ ነው የገጠማት ። ጊዜ የሚባል ፍትሐዊ ዳኛ አለ ! Zekaryas Kiros
Show all...
7👍 2
ጥያቄ ነበረኝ አንዱ ነው ቀረብ ብሎኝ "ጥያቄ ነበረኝ" አለኝ? ምንድነው አልኩት። አሳ በጾም ይበላል ወይ አለኝ። አይበላም ሳልለው  "ብላ" ብዬ መለስኩለት። መምህር አሳ በጾም አይበላም የሚልኮ ተምሬ ነበር አለኝ። ከተማርክ ለምን ጠየከኝ አልኩት። አይ ለማረጋገጥ ብዬ ነው አለኝ። ያኔ ስትማር እርግጠኛ አይደለም ብለውኽ ነበር? አልኩት። አላሉንም አለኝ።  በራሱ የሳቀ ይመስለኛል ሳቁ መጣ እኔ ጠንከር ባለ ቃል ነው የመለስኩለት። መንገዱን ቀጠለ። ኹለተኛ ሰው ይጠይቃል ብዬ አልገምትም።
Show all...
👍 20🤣 4
"በጾምና በጸሎት ኃጢአት ይሠረያል በደልም ኹሉ ይደመሰሳል።" ጾመ-ድጓ ዘወረደ
Show all...
9😢 6👍 3🙏 1
➦'' ከመብል ከመጠጥ ታቅቦ የሚጾም አንድ ሰው በሐሜት የሰዎችን ሥጋ መብላት ከቀጠለ ይህ ጾም የግብዝነት ነው።" ማር ይስሕቅ በመጽሐፍተ መነኮሳት ➦እስመ በጾም ኤልያስ ሰማያተ ዐርገ ዳንኤል ድኅነ እምአፈ አናብስት ወሶስና ድህነት እምእደ ረበናት ኤልያስ በጾም ወደ ሰማይ ዐረገ ዳንኤልም ከአናብስት አፍ ዳነ ሶስናም በጾም ከሐሰት ምስክሮቹ ከረበናት እጅ ዳነች (ቅዱስ ያሬድ) #ጾመኢየሱስ
Show all...
👍 8 1
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!