ምድርን ማሳመር
Open in Telegram
የተለያዩ የዳዕዋ እና ወቅታዊ ምስል , ፅሁፍ እና ቪዲዎች የሚለቀቁበት ቻናል መጪው ግዜ የኢስላም ነው!
Show more894
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1930 days
Posts Archive
894
وسنبقى على جبل الرّماة .. وخلفنا صوت النّبيّ يردد.. لا تبرحوا.. لا تبرحوا
كتائب القــ ــســ ــام في مشهد قنص جندي بحي الشجاعية: "لن نبرح جبل الرماة".
894
አስቸኳይ! አስቸኳይ! አስቸኳይ!
SHARE, SHARE, SHARE
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ በመጀመረው የኮሪደር ልማት ሳቢያ በርካታ መኖሪያና የንግድ ቤቶች በልማቱ ምክንያት ከቦታቸው እየተነሱ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በዛሬው ዕለት ሰኔ 15 ቀን 2016 ፒያሳ በሚገኘው ኑር መስጊድ ውስጥ ላለፉት አርባ ዓመታት ሕዝቡን በማስተማር ሲለፉ የኖሩት የሸይኽ ሙሐመድ ሶብዩ መኖሪያ ቤት የልማት ተነሺ እንዲሆን መደረጉ ታውቋል፡፡
ሸይኽ ሙሐመድ ሶብዩ ለሕዝበ ሙስሊሙ ለሚሰጡት የዘወትር አገልግሎት፣ መስጊዱ እንዲቀርባቸው በሚል ፒያሳ በተለምዶ "እሪ በከንቱ" በሚባለው ሰፈር ውስጥ በሚገኝ ኮንዶሚኒየም ውስጥ ላለፉት ዓመታት ሲኖሩ ነበር፡፡
በዛሬው ዕለት ሰኔ 15 ቀን 2016 ይኼ ሸይኹ የሚኖሩበት የኮንዶሚኒየም ሕንፃ በኮሪደር ልማቱ ሳቢያ እንዲፈርስ ተደርጎ፣ እርሳቸውን ጨምሮ የኮንዶሚኒየሙ ነዋሪዎች፣ ከኑር መስጊድ እጅግ በሚርቀው ቃሊቲ ወደሚባለው ሰፈር እንዲዘዋወሩ ታዘዋል፡፡
☞ሙስሊሙ ኅብረተሰብ በጠቅላላው የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ በከተማችን አስተዳደር የሚከናውንን ማንኛውንም ልማት እንደሚደግፍ ይታወቃል፡፡
☞ነገርግን ሸይኽ ሙሐመድ ዐብደላህ (ሶብዩ) ባለፉት አርባ ዓመታት በመማር ማስተማር ሕይወት ውስጥ ቆይተው ኅብረተሰቡን በመልካም ሥነ ምግባር ሲያንጹ የኖሩ የአገር ባለውለታ የሆኑ የሃይማኖት አባት መሆናቸውን መንግሥት ተገንዝቦ፣ የእርሳቸውን ጉዳይ በልዩ ሁኔታ በመመልከት በመስጊዱ አቅራቢያ የሚገኝ በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ይዞታ ሥር ያለ መኖሪያ ቤት እንዲመድብላቸው ስል በመላው የአዲስ አበባ ሕዝበ-ሙስሊም ስም እጠይቃለሁ፡፡
☞ ይኼ ካልተቻለ ደግሞ ማለትም በመስጊዱ አቅራቢያ የእርሳቸውን ክብርና የአገር ባለውለታነት የሚመጥን የመንግሥት ቤት ማግኘት ካልተቻ፣ በመስጊዱ ማለትም በኑር መስጊድ ፊትለፊት የሚገኝ በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አማካኝነት ተገንብቶ እየተጠናቀቀ ያለ የሚሸጥ መኖሪያ አፓርታማ ስላለ እርሱን ገዝተን ለሸይኹ ለማስረከብ አሁኑኑ የሶሻል ሚዲያ የጋራ ካምፔን ይጀመር፡፡
©Abubeker almu muhe
894
Repost from N/a
⌛3 ቀን ብቻ ቀረ!⌛
ኢስላምን ለመተግበር ህግጋቱን ማወቅ አስፈላጊ ነው። የኢስላማዊ ህግጋት ጥናት ዘርፍ ፊቅህ ይባላል። ታዋቂ ከሆኑ የፊቅህ መዝሀቦች (አስተሳሰብ ትምህርት ቤቶች) መሀከል የሆነው ፊቅህ አሻፊዒያ የመጀመሪያ ኪታብ የሆነችውን ሰፊነቱ ነጃ መማር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ብዙ ምሁራን መስክረዋል።
ሰፊነቱ ነጃ ማለት የመዳኛይቱ መርከብ ማለት ሲሆን በአምልኮ ተግባራቶቻችን ስኬታማ ሆነን እንድን ዘንድ ሁነኛ ሚና ያላት ኪታብ ነች። በሀገራችንም የሀይማኖት ትምህርት ጀማሪዎች የሸሪዓ እውቀትን የሚጀምሩባት ኪታብ ነች።
በኪታቧ አንድ ሙስሊም ሊያከናውናቸው የሚገቡ መሰረታዊ አምልኳዊ ተግባራት ህግጋት በግሩም ሁኔታ ቀርበዋል።
እርስዎም ሀይማኖታዊ ግዴታዎትን በእውቀት ላይ ተመስርተው ያከናውኑ ዘንድ ለማገዝ አልገዛሊ አካዳሚ ይህን አድል አመቻችቶላችኋል።
የትምህርት አሰጣጡ ሙሉ በሙሉ በኦንላየን የቀጥታ ስርጭት (LIVE) ሲሆን በተጨማሪም ለትምህርት አሰጣጥ ሂደቱ ውጤታማነት አጋዥ የሆኑ የትምህርት ግብአቶችን ያገኛሉ።
ትምህርቱ የሚጀምረው ጁን 22/2024 ወይም ሰኔ 15/2016 ዓ ል ሲሆን ለተከታታይ 12 ሳምንታት ዘወትር ቀዳሜ ማታ 2:30–3:15 በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል። በትምህርቱ ማጠናቀቂያም ፈተና የሚኖር ይሆናል።
በስኬት የሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ሰርተፍኬት የሚያገኙ ሲሆን ወደቀጣይ ምዕራፍ በመሸጋገር የእውቀት አድማሳቸውን የሚያሰፉበት እድል ተመቻችቷል።
ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ዛሬውኑ ተመዝግበው ቦታዎትን ይያዙ።
ለመመዝገብ ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ
https://forms.gle/35MjjTBNxhkyiBH66
ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም @algazaliacademyadmin
ወይም በዋትስአፕ https://wa.me/251984109507 ያናግሩን
894
የኡድሒያ በሬ አስተራረድ ትምህርት
1/ መጀመሪያ ገበያ ወጥተን በሬውን search እናደርጋለን።
2/ ካገኘነው በኋላ: በተስማማነው መሰረት ዋጋውን ከፍለን በሬውን save ማድረግ ነው።
3/ ወደቤት እናመጣውና በ group በመሆን: መሬት ላይ በግራው download እናደርገዋለን።
4/ ከዛም የተቀደሰውን የጌታችንን የአላህን ስም በማውሳት shortcut እናደርገዋለን።
5/ ከዛም የበሬው ህይወት እስትንፋሱ swith off እስኪሆን እንጠብቀዋለን።
6/ ሲቀጥል ደግሞ ቆዳውን ከበሬው ሰውነት ላይ remove በማድረግ እናራቁተዋለን።
7/ በመቀጠል ወደ ሰውነቱ hack አድርገን እንገባለን።
8/ ከዚያም ከውስጡ ያሉትን applications አንድ በአንድ እናወጣቸዋለን።
8/ ያወጣናቸውን applications በፎልደር ላይ እንደረድራቸዋለን።
9/ ከዚያም ዘመድና ጎረቤት invite በማድረግ እንቃመሳቸዋለን።
10/ ምስኪኖችን ጠርተን ደግሞ share እናደርጋለን።
ትስማማላችሁ???
በአቡ ሀይደር
894
የሸህ ሚናስ ልጅ ሼህ ከረም በጠና ታመው ለማሳከሚያ ለተጠየቀው እርዳታ እስከአሁን የተባበራችሁ ወንድምና እህቶች አላህ ኸይር ጀዛ ይክፈላችሁ።
ሼህ ከረም በ ታዝማ ሜዲካል እና ሰርጂካል የሕክምና ማእከል ከግንቦት 21 ጀምሮ ተኝተው ከባድ ክትትል እየተደረገላቸው ነው። አሁን ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ አልጋ ይዘዉ እየታከሙ ያለ ቢሆንም ሃኪሞቹ “ICU Room ገብተዉ ህክምናዉን ካልተከታተሉ በስተከቀር በሽታው እየተባባሰባቸዉ ይሄዳል” ለዚህ ደግሞ በየግዜዉ ማሲያዢያ እየተባለ የሚከፈል በርከት ያለ ገንዘብ ያስፈልጋችኋል ስላሉና በገንዘብ እጥረት ምክንያት በሆስፒታሉ ዉስጥ የሚሰጠውን ህክምና ለማቋረጥ ጫፍ ላይ የደረሱበት ሁኔታ ዉስጥ ነዉ ያሉት ፡፡
በተጨማሪም በተጠየቀው አካውንት የገባላቸው ብር በጣም አነስተኛ ከመሆኑም በላይ ካሉበት ሁኔታ አንጻር በሳቸው ፊርማ አካውንቱን ማንቀሳቀስ አልተቻለም።
በመሆኑም በሶስት ቅርብ ዘመዶቻቸው በጋራ የሚንቀሳቀስ አዲስ አካውንት የተከፈተ በመሆኑ ለሚያስፈልገው ከፍተኛ ህክምና የቻላችሁትን ታበረክቱ ዘንድ በአላህ ስም እንጠይቃለን።
CBE Account
1000631136641
Hassen Tahir
Mahmoud Teyib
Mezid Abdella
:
:
بسم الله ، الحمدلله ، والصلاة والسلام على رسول الله
እኝህ አባታችን ሸይኽ ከረም ሸይኽ ዐብዱልባሲጥ ይባላሉ። ላፍቶ፣ ሀና ማርያምና ሰፈራ አካባቢ ባሉ መስጊዶች ለረዥም ዓመታት ነሕዉና ሌሎች ፈኖችን ሲያቀሩ የኖሩ ዓሊም ናቸው። ካለፉት አምስት ወራት ወዲህ ግን ሐኪሞች እንደሚሉት በልብ እና በኩላሊት ችግር የተነሳ በጽኑ ታመው የአልጋ ቁራኛ ሆነዋል። ከሚወዱት የዒልም ማእድ ከተነጠሉም ይህንኑ ያህል ጊዜያት ተቆጥረዋል። ሸይኽ ከረም ከአባታቸው የወረሱትን ሀይማኖታዊ ዕውቀት በማሠራጨት ሲባትሉ የኖሩ
894
የፍልስጤም ነቅባ (መከራ) ከተፈፀመ ከ76 ዓመታት በኋላም ፍልስጤም በፅናት መቆሟን ትቀጥላለች ወረራውም መክሸፉ አይቀርም 🇵🇸✌🏼
©Embassy of Palestine in Addis ababa
894
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢላይሂ ራጂዑን
በተለያዩ ከተሞች በመዘዋወር የጎዳና ላይ ዳዕዋ ያደርግ የነበረው ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ ወደ አኼራ ሄደ!
...
(ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 06/2016)
...
በተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወረ በተለይ በአሳሳ፣ሮቤ፣አዳማ ፣ አርሲ ፣ባሌ፣ሻሸመኔ ፣ሀረር፣ድሬዳዋ፣አዲስአበባን በመሳሰሉ ከተሞች በወዘዋወር የጎዳና ላይ ዳዕዋ ያደርግ የነበረው ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ በዛሬው ዕለት በሻሸመኔ ከተማ በድንገት ወደአኼራ መሻገሩ ተሰምቷል።
..
ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ ምንም የማይፈራ ሙጃሂድ ከልጅነት እስከ ወጣትነትና ጎልማሳነት ምናልባት እስካዛሬዋ እስከመጨረሻዋ የዱንያ ላይ ቀኑ ድረስ ሐያቱን በሙሉ በደዕዋ አሳልፏል፡፡ኢስላምን ለማድረስ ብዙ የለፋ የጎዳና ላይ ዳዕዋ የሚያደርግበት ስፒከሩ በተዳጋጋሚ ታስሮበት በተለያዩ የሀገሪቷ ከተሞች በሚገኙ የፖሊስ ጣቢያቢያዎች በመንከራተት ብዙ መስዋዕትነት ይከፍል እንደነበረ "ኑ ወደ አላህ"እያለ በሚያደርገው ጥሪ ብዙ ድብደባ እና እስርና እንግልት ይፈፀምበት እንደነበርም ወዳጆቹ ገልፀዋል።
...
ኡስታዝ ፈቂ ገለቶ እሁድ ዕለት ግንቦት 4/2016 ዓ.ል በሻሸመኔ ከተማ የተካሄደውን የቁርአን ውድድር ታድሞ የነበረ ሲሆን ዛሬ ሻሻመኔ ላይ ድንገት ወደአኼራ መሄዱ ተሰምቷል።
...
¤ሀሩን ሚዲያ አላህ ለእርሱ ጀነትን ለወዳጅዘመዶቹ ሰብርን እንድወፍቃቸው ይመኛል!
...
©ሀሩን ሚዲያ
894
+1
Tet abba cajji mucammad Nur Nacwi kee Tesfsiir berseenak sugee
. Usuk biyaakiteh yan widdir ina marin sara kalqisak orbissah tan dagiinat aqeeshuk sugen. Waysi alsaay sanat 2013 i.l.l qunxuk baaxok akah tewqem ken catta^gadik sugte. Dubayal sugtem takkay immay Awropa koo beenno axcuk dallaala dirab oyti teetil cayuk tet duquurussa heenih Etyopiya temeeteeh, akah temeete gexoh gita qimbisseek lakal liibiyal tet yibbixeenih uma weelot tan. Tet caboonuh 800 alfi esseran, ayroorah addat esseren lakqo gee weenik tet qideloonum warsan. Tet abba lakimi numuh yan, ken cattaamak tuh elle xayi malon, yablem faxa mari yablem xiqa karaakare Ansuar Masjidih dariifa kinni buxa keenik.
Ossotinah oyta
Cajji Mucammad Nur
Telefoon Ne 0913- 333659
Ina Lubaaba Ayalew
Telefoon Ne: 0964-046713
Tet catam faxa mari yenek tet ina Lubaaba Ayalew migaaqal yan Banki cisaabih ixxima: 1000413996493
894
Tet abba cajji mucammad Nur Nacwi kee Tesfsiir berseenak sugee
. Usuk biyaakiteh yan widdir ina marin sara kalqisak orbissah tan dagiinat aqeeshuk sugen. Waysi alsaay sanat 2013 i.l.l qunxuk baaxok akah tewqem ken catta^gadik sugte. Dubayal sugtem takkay immay Awropa koo beenno axcuk dallaala dirab oyti teetil cayuk tet duquurussa heenih Etyopiya temeeteeh, akah temeete gexoh gita qimbisseek lakal liibiyal tet yibbixeenih uma weelot tan. Tet caboonuh 800 alfi esseran, ayroorah addat esseren lakqo gee weenik tet qideloonum warsan. Tet abba lakimi numuh yan, ken cattaamak tuh elle xayi malon, yablem faxa mari yablem xiqa karaakare Ansuar Masjidih dariifa kinni buxa keenik.
Ossotinah oyta
Cajji Mucammad Nur
Telefoon Ne 0913- 333659
Ina Lubaaba Ayalew
Telefoon Ne: 0964-046713
Tet catam faxa mari yenek tet ina Lubaaba Ayalew migaaqal yan Banki cisaabih ixxima: 1000413996493
894
የሱና ዩኒቨርስቲ ተመራቂዎች የቢላሉል ሐበሺን ማእከል ጎበኙ
=============================
የሱና ዩኒቨርስቲ አሰተምሮ ያስመረቃቸዉን እና ተመርቀዉ በስራ ላይ ያሰማራቸዉን ኢማሞች ፣ ዳእዮች፣ አስተማሪዎች፣ መሻይኸች እና የዩኒቨርስቲዉ ስታፎች በትናትናዉ እለት ሳር ቤት በሚገኘዉ የቢላሉል ሐበሺ ማእከል በመገኘት ቢላሉል ሓበሺ እየሰራቸዉ ያሉትን ስራዎች ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የዩኒቨርስቲዉ መስራች እና ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ሸይኸ መሐመድ ሓሚዲን የተገኙ ሲሆን በጉብኝታቸዉም ቢላሉል ሐበሺን ከበርካታ አመታት በፊት እንደሚያዉቁት እና ለትዉልድ የሚተላለፍ ስራን እየሰራ ያለ ፋና ወጊ ሃገር በቀል ተቋም እንደሆነ አስተያታቸዉን ሰጥተዋል፡፡
በጉብኝቱ በአጠቃላይ 45 የሚሆኑ ኢማሞች ፣ ዳእዮች፣ አስተማሪዎች እና መሻይኸች የተገኙ ሲሆን ኡስታዝ መሓመድ ጀማል ጎናፍር እነዚህን ጎብኝዎች በመቀበል የቢላልን ስራዎች በማስጎብኝት ሁሉም ጎብኝዎች በተሰማሩበት ቦታ እና ስራ ለሃገር እና ለወገን የሚጠቅም ስራ እንዲሰሩ በማሳሰብ ዝግጅቱን በዱአ አጠናቀዋል፡፡
894
“አንድነት የሚገለጸው በአንድ ተቋም ዉስጥ በመሰብሰብ ብቻ አይደለም!”
”وليس بصحيح أن يكون معنى الوحدة هو الاجتماع تحت سقف مؤسسة واحدة"
በሱና ኢኒስቲትዩት ስር የሚገኘው ሱና ዩኒቨርስቲ በሰሞኑ ያዘጋጀዉ ምሩቃን ኮንፈረንስ የመዝጊያ ፕሮግራም ከኢብን መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ጋር የልምድ ልዉዉጥ ያደረጉ ሲሆን አብረዉ መሰራት የሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ዉይይት አድርገዋል።
የሱና ኢኒስቲትዩት መስራች እና ዋና ፕሬዝደንት ሸይኽ ሙሀመድ ሓሚዲን (ዶ/ር) እዉቀትን በማስፋፋት ዘርፍ ኢስለምን ለማገልገል እየሰራን እንደመሆኑ ይህን አላማችንን ከግብ ለማድረስ ከመሰል ተቋማት ጋር ህብረት እንደሚያሻ እናምናለን ብለዋል።
ሸይኽ ኢልያስ አህመድ በበኩላቸው የአንድነት መገለጫ በአንድ ተቋም ዉስጥ በመሰብሰብ ብቻ አለመሆኑን ገልፀው ከዚህ በፊት ኢስላምን በማገልገል ረገድ ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ እንደ ነበረዉ ሁሉ ወደፊት እንደ ተቋም ተጋግዘን የሰለፎችን ጎዳና ህያዉ እንደምናደርግ ተስፋ አለኝ ሲሉ ገልፀዋል።
ሚያዚያ 15/2016
©ደዕዋ ቲቪ
