en
Feedback
የኖህ መርከብ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ

የኖህ መርከብ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ

Open in Telegram

የ ኢ/ኦ/ተዋህዶ/ቤተክርስቲያን አስተምህሮ የጠበቁ የ አባቶች ምክር;ግጥም;ተከታታይ አምዶች;ልሳነ ግእዝ;ጥያቄናመልሶች የምናገኝበ ስለሆነ ቻናሉን ይቀላቀሉ። for any opinion @Abeln ይላኩ "ይህች ቤተክርስቲያን ክርስቶስን ከቶ አታውቀውም" በሉ ግድ የለም ለቃሉ ! ግን ድምጽ ቀንሱ ! የጌታን መከራ ሕማሙን አስባ ስግድት ላይ ናትና ልጆቿን ሰብስባ ግድ የለም አንቋሿት ግን አትረብሿት !!

Show more
1 646
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+5
in 0 channels
November '24
+10
in 0 channels
Get PRO
October '24
+18
in 0 channels
Get PRO
September '24
+1
in 0 channels
Get PRO
August '240
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 0 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '240
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '230
in 0 channels
Get PRO
November '230
in 0 channels
Get PRO
October '230
in 0 channels
Get PRO
September '230
in 0 channels
Get PRO
August '23
+12
in 0 channels
Get PRO
July '23
+16
in 0 channels
Get PRO
June '23
+5
in 0 channels
Get PRO
May '23
+6
in 0 channels
Get PRO
April '23
+4
in 0 channels
Get PRO
March '23
+9
in 0 channels
Get PRO
February '23
+6
in 0 channels
Get PRO
January '23
+15
in 0 channels
Get PRO
December '22
+6
in 0 channels
Get PRO
November '22
+14
in 0 channels
Get PRO
October '22
+16
in 0 channels
Get PRO
September '22
+16
in 0 channels
Get PRO
August '22
+18
in 0 channels
Get PRO
July '22
+9
in 0 channels
Get PRO
June '22
+9
in 0 channels
Get PRO
May '22
+7
in 0 channels
Get PRO
April '22
+15
in 0 channels
Get PRO
March '22
+18
in 0 channels
Get PRO
February '22
+9
in 0 channels
Get PRO
January '22
+6
in 0 channels
Get PRO
December '21
+6
in 0 channels
Get PRO
November '21
+8
in 0 channels
Get PRO
October '21
+9
in 0 channels
Get PRO
September '21
+13
in 0 channels
Get PRO
August '21
+18
in 0 channels
Get PRO
July '21
+19
in 0 channels
Get PRO
June '21
+14
in 0 channels
Get PRO
May '21
+10
in 0 channels
Get PRO
April '21
+42
in 0 channels
Get PRO
March '21
+55
in 0 channels
Get PRO
February '21
+61
in 0 channels
Get PRO
January '21
+84
in 0 channels
Get PRO
December '20
+3 701
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
21 December+1
20 December+1
19 December+2
18 December0
Channel Posts
"ድንግል ሆይ እኔ ግን ልጅሽን በማምለክ በባሕርይ አባቱም በአብ በባሕርይ ሕይወቱም በመንፈስ ቅዱስ አምኜ ደስ እሰኛለሁ ለሦስትነቱ አንድ ስግደት እየሰገድሁ እመካበታለሁ እንዲህ ስል፡፡  አምላኬ ነው አመሰግነዋለሁ ያባቶቼም አምላክ ነው አከብረዋለሁ አገነዋለሁ ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ፡፡ እግዚአብሔር ፀብ ክርክርን ይሰብራል፡፡ ስሙም እግዚአብሔር ነው፡፡ ደግሞ እንዲህእላለሁ (ዘፀአት ፲፭፣ ፪፣ ፫)  እንደ አምላካችን ያለ ታላቅ አምላክ ማነው፡፡ ይህንንም የመለኮት ሰይፍ ተቀብዬ የሰይጣንን ራሱን እቆርጠዋለሁ፡፡ ይህንንም የሃይማኖት በትር ተመርኩዤ የእባቡን (የዲያብሎስን) ራሱን እቀጠቅጠዋለሁ፡፡ የምስጋናውንም ጽዋ ከጽርሐ አርአያም ቀድቼ ከቤትሽ አፈሳለሁ፡፡ ከትንቢት ቃል ጋራ እንዲህ እላለሁ፡፡ ከሞት ደጅ ከፍ ከፍ የሚያደርገኝ በጽዮን ልጅ ደጅ ምስጋናውን ሁሉ እናገር ዘንድ፡፡ ዳግመኛም እንዲህ እላለሁ፡፡ በጽዮን ምስጋና ላንተ ይገባል በኢየሩሳሌም ጸሎት ላንተ ነው፡፡" (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ - አርጋኖን)

2
የዘመናችን የእሾኽ አክሊል ከዛሬ 40 ዓመታት በፊት የሸዋ ክፍለ ሀገር ሊቀጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ (2ኛ) በዝዋይ ገዳም ለዲያቆናት እና ካህናት ሃይማኖት ከምግባር እየመረመሩ ክህነት ይሰጡ ነበር። ለሹመት ከቀረቡት መካከል አንደኛው በወጉ ያለተማረ በምግባርም ያልሰመረ አንድ እጩ አግኝተው "ዘንድሮ አልሾምህም። ለሚቀጥለው ዓመት በደምብ ተምረህ፣ በምግባርም ሰክነህ ስትመጣ ትሾማለህ" ብለው መለሱት። አብረውት የመጡት ወዳጅ ዘመዶቹ ተሰብስበው ብፁዕነታቸውን "እባክዎ ከነ ችግሩም ቢሆን ይሹሙልን። ወገኖቹም ይጣሉናል። እርሱ ካልተሾመ ቤተክርስቲያናችንም ትዘጋለች" ሲሉ በማስተዛዘን ልመና አቀረቡ። አቡነ ጎርጎርዮስ ግን "የወገኖቹን ቁጣ ፈርቼ በሃይማኖቱ ያለጸና በምግባሩ ያልቀናን ሰው ካህን እንዲሆን ሾሜ ቤተክርስቲያኒቱ ላይ የማይነቀል እሾኽ ከምተክልባት ለጊዜው ብትዘጋ ይሻላል። ወደፊት የተሻለ እና ለክህነት የተገባ ሰው አግኝተን ስንሾም ያኔ ይከፍታታል።" ብለው መለሷቸው። ዛሬ ላይ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ለሁለት ካልሰነጠቅናት ብለው ቁም ስቅሏን የሚያሳዩዋት ግለሰቦች በሃይማኖት ጽናታቸው፤ በምግባርም መቅናታቸው የተመሠከረላቸው መሆኑ ሳይረጋገጥ የሆነ ወገንን ለማስደሰት በይድረስ ይድረስ የተሾሙ እንደነበሩ  አሁን እሾኹ ደርሶ ሲወጋን ተረድተነዋል። ለቤተክርስቲያኒቱ የእሾኽ አክሊል ሆነው እየወጓትና እያደሟት ነውና! ያለፈ አልፏል! አሁንም ቢሆን ባለሥልጣናትን ለማስደሰት ወይንም የአጃቢዎቻቸውን ጩኸት በመፍራት እንኳንስ ጵጵስና ዲቁና ለማይገባቸው፤ ከእግዚአብ ልጅነታቸው ይልቅ የብሔረሰብ ልጅነታቸው ደርሶ ለሚንጣቸው ዘውገኞች የክህነት ሹመት መስጠት በክርስቶስ መቅደስ ጉልላት ላይ ሌላ ተጨማሪ መርዛማ እሾኽ አክሊል እንደመድፋት ይቆጠራል።
144
3
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ፍቅርን እንደ ዓይን ብሌን ስንጠብቃት በእጅጉ የምትጠቅመንን ያህል ስንተዋት ደግሞ በእጅጉ ትጎዳናለች፡፡ በፍቅር እጦት የሚደርሰው ጉዳት በተወሰነ ነገር ብቻ ሳይሆን በነፍስም ሆነ በሥጋ፣ በምድርም ሆነ በሰማይ እጅግ በጣም የገዘፈና የሰፋ ነው፡፡  በሀገራችን የሆነውና እየሆነ ያለውም ይኸው ነው፡፡ ፍቅርን ባጣንባቸው ዓመታት ከየት ወዴት እንደደረስን ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚገነዘበው ነው፡፡ ያተረፍነው ነገርም ምን እንደሆነ የምናውቀው ነው፡፡  ይሁንና የፍቅር እጦት ምን ያህል እንደጎዳን ራሳችን ተገንዝበን ወደ ሰላሙ መንገድ መመለሳችን የተሻለ አማራጭ መሆኑን ሳንመሰክር አናልፍም፡፡ የተጀመረው የፍቅርና የሰላም ጉዞም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ልባዊ ምኞታችንና ጸሎታችን ነው፡፡ ይህንን ሰላም እንዲመጣ ያደረጉ ወገኖችም ሁሉንም ሳናመሰግን አናልፍም፡፡ ምክንያቱም በሰዎች መካከል ፍቅርንና ሰላምን የሚያደርጉ የእግዚአብሔር ልጆች  እንደሚባሉ ጌታ እንደ አስተማረን ብፅዕና ይገባቸዋልና ነው፡፡  (ማቴ.፭፥፱) የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! የፍጹም ፍቅር መገኛ የሆነው ቅዱስ ወንጌል የሚያስተምረው ፍቅር ራስን ማፍቀር ወይም መውደድ ሳይሆን ራስን መጥላት ባልንጀራን ግን መውደድ እንደሆነ ነው፡፡ “ወንጌላዊ-ፍቅር ፍጹም ነው” የሚያሰኘውም ቅሉ ይህ ነው፡፡  ለሁለት ሺህ ዘመናት ያህል በቅዱስ ወንጌል አስተምህሮ ላይ የተገነባው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ባህልም ይህን ፍቅር ጠብቆ የሚጓዝ ነው፡፡  ይህም በመሆኑ የኢትዮጵያ አበው መነኮሳት ከነበራቸው ፍቅርና ትሕትና የተነሣ፣ የሹመት ሽሚያ አያውቁም ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር ትልቁን ሥልጣን ይቅርና የአንድ ገዳም መሪ ለመሆንም በእግር ብረት ታስረው በግድ ካልሆነ በቀር እሺ ብለው በፈቃደኝነት ሹመትን አይቀበሉም ነበር፡፡ ራሱን በራሱ መሾም ወይም እኔን ሹሙኝ ብሎ መናገርና የሌላን ድጋፍ መጠየቅ ለኢትዮጵያውያን መነኮሳት ጭራሽ ነውርና ጸያፍም ነበር፡፡  ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ ለሦስት ሺህ ዘመናት የዘለቀው ሃይማኖታችን ምንም ዓይነት መለያየት ሳያጋጥመው አንድ ሆኖ ሊዘልቅ የቻለው ያም በመሆኑ ነው፡፡ ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ጠንካራ አንድነት ለሕዝቡም በመትረፉ የሀገሪቱን አንድነትና ነጻነት አስጠብቆ እስከ ዘመናችን ሊደርስ ችሎአል፡፡ በዚህም ቤተ ክርስቲያናችን የሕዝብንና የሀገርን አንድነትና ነጻነት ለማስጠበቅ ያደረገችውና የምታደርገው ጥረት ሊያስመሰግናት እንጂ ሊያስወቅሳት አይገባም፡፡  የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ከቅርብ ቀናት ወዲህ በቤተ ክርስቲያናችን ተከሥስቶ የነበረውን ሕጋዊ ያልሆነ ድርጊት የቤተ ክርስቲያናችንን ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና ባሕላዊ መርሕን የናደ፣ እንደዚሁም በኢትዮጵያ ይቅርና በዓለም ታሪክ ተደርጎ የማያውቅ ድርጊት እንደሆነ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ስትገልጽ ቆይታለች፡፡ ይህንን የቤተ ክርስቲያን ድምፅ በመስማትና በመቀበል ሕዝበ ክርስቲያንና ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለእግዚአብሔር ባቀረቡት ኀዘንና ጸሎት እንደዚሁም ባደረጉት መጠነ ሰፊና ዙርያ መለስ የሆነ የድጋፍ ርብርብ ስሕተቱ ሊታረም ችሏል፡፡  ለተገኘው መንፈሳዊ ውጤትም ጠቅላይ ሚንስትርና መንግሥታቸውን፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነትና ሉዓላዊነት እንዲከበር ከፍተኛ መሥዋዕትነት ለከፈለው መላው ሕዝበ ክርስቲያን እንዲሁም ይህ ስሕተት እንዲታረም ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን ተሰልፈው ድምፃቸውን ላሰሙ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በቤተ ክርስቲያናችን ስም ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርብላቸዋለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ግልጽ ማድረግ የምንፈልገው ከቤተ ክርስቲያናችን ዶግማ፣ ቀኖና እና ሥርዓት መከበር እንደዚሁም ከሉዓላዊ አንድነቷ መጠበቅ በመለስ ያለው ጥያቄ ለማስናገድ ቤተ ክርስቲያናችን ዝግጁ መሆኗን ነው፡፡  ቤተ ክርስቲያናችን ሕዝቦች በቋንቋቸው የመማር፣ የማስተማርና የማምለክ እንዲሁም የመተዳደር መብትን ካሁን በፊትም፣ አሁንም፣ ካሁን በኋላም የምትነፍግበት መሠረት እንደሌለም ሁሉም ሊያውቀው ይገባል፡፡  ይህም በመሆኑ በቋንቋ የመጠቀም መብት በሕገ ቤተ ክርስቲያናችን ምዕራፍ ፪ አንቀጽ ፭ ከቁጥር ፩ እስከ ፫ ባለው አንቀጽ በሚገባ ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ስለሆነም በቋንቋ የመጠቀም ጥያቄ በሕግ ደረጃ ተመልሶ በተግባር እየተሠራበት የሚገኝ መሆኑን ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡  የተወዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ዛሬ ታላቁን ጾም በፍቅር ሆነን የምንጾምበት ወቅት ነው፡፡ ሁላችንም እንደምናውቀው ጾም ማለት ሥጋዊ ፈቃድን በመግታት ከእግዚአብሔር ጋር ጥብቅ ግንኙነት ለማድረግ የሚካሄድ መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው፡፡  በጌታችን ጾም በተግባር እንዳየነው ጾም ማለት ዲያብሎስ የሚሸነፍበት በአንጻሩ ደግሞ የእግዚአብሔር ሕዝብ አሸናፊዎች የሚሆኑበት ኃይል ነው፡፡  ስለሆነም ጾም የተጋድሎና የሙዓት ሜዳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ የምንታገለውም ልብሰ ሥጋ ሰውን ሳይሆን ረቂቅ ፍጡር የሆነው ሰይጣን በሰው አድሮ የሚነዛውን አጥፊ ሐሳቡንና ድርጊቱን ነው፡፡ ከዚህም ጋር ሰውነታችን ለዚህ ክፉ መንፈስ ታዛዥ እንዲሆን የሚገፋፉ ጥሉላት መባልዕትን መተው፣ ኃይለ ሥጋን መቈጣጠር፣ ኃይለ መንፈስን ደግሞ ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡ በጾም ወቅት የተራቡትን ማጉረስ፣ የታረዙትን ማልበስ፣ የተበደሉትን መካስ፣ ፍትሕና ርትዕ በማኅበረ ሰብ ውስጥ ማንገሥ ያስፈልጋል፡፡ በጾም ወቅት ኅሊናችን ማሰላሰል ያለበት ሰው ምን አለ? ወይም ምን አደረገ? በሚለው ሳይሆን እግዚአብሔር በፊቱ ምን ዓይነት ሰው እንድንሆንለት ይፈልጋል? በሚለው ላይ ነው፡፡ ስለዚህ ጾማችን በዚህ መንፈስ የተቃኘ ፍቅረ፣ እግዚአብሔርንና ፍቅረ ቢጽን ማእከል ያደረገ፣ መጠራጠርንና አለመተመማንን ያስቀረ፣ የተለያዩትን ያቀራረበ፣ የተሳሳቱትን ያረመ በአንጻሩ ደግሞ ሁላችንን በሰላምና በፍቅር አንድ አድርጎ ያስተሳሰረ ይሆን ዘንድ በዚህ መንፈስ ተነቃቅተን እንድንጾመው አባታዊ ጥሪያችንን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናስተላልፋለን፡፡  በመጨረሻም በሀገራችን እየታየ ያለው የሰላም ጭላንጭልና ችግሮችን በውይይት የመፍታት ዝንባሌ ለሁለንተና ልማታችንና ለዕድገታችን እንደዚሁም ለተሟላ አንድነታችን ጠቃሚነቱ የጎላ ስለሆነ እግዚአብሔር ለዘለቄታው እንዲያሳካልን ከልብ እንድናዝንና ወደ አምላካችን በተመሥጦ እንድንጸልይ በአጽንዖት በማሳሰብ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡  መልካም የጾም ወራት ያድርግልን! እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር! አሜን አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
132
4
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ የዐቢይ ጾምን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት መልእክት! • በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት እንዲሁም ኢትዮጵውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ! እንደ ስሑትና ደካማ ሰብአዊ ባሕርያችን ሳይሆን እንደ አባታዊ ቸርነቱ ሁል ጊዜ በምሕረቱ የሚጐበኘን አምላካችን እግዚአብሔር እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዐቢይ ጾም አደረሰን፤ አደረሳችሁ! • “ንጹም ጾመ፣ ወናፍቅር ቢጸነ፣ እስመ ከማሁ አዘዘነ፤ ጾምን እንጹም፤ ባልንጀራችንንም እንውደድ፣ እንዲህ አዞናልና” (ቅዱስ ያሬድ) እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ስንኖር እንድናደርገው ያዘዘን ዐቢይ ነገር ቢኖር ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ እየመገበ የሚገኘው በፍቅር ነው፡፡ እኛንም ከፍዳ ኃጢአት ያዳነን በፍቅር ነው፤ ሕይወታችንና ንብረታችን ተጠብቆ የሚኖረው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡  ግላዊና ማኅበራዊ ኑሮአችን እንዲሁም ሃይማኖታዊ አምልኮአችንና የተግባር እንቅስቃሴአችን በሙሉ ውጤታማ ሊሆን የሚችለው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡  በፍቅር ውስጥ በረከት እንጂ ጉድለት የለም፤ በፍቅር ውስጥ ጤና እንጂ በሽታ የለም፤ በፍቅር ውስጥ ጽድቅ እንጂ ኃጢአት የለም፤ በፍቅር ውስጥ እግዚአብሔር እንጂ ዲያብሎስ የለም፡፡ ይህም በመሆኑ ቅዱስ መጸሐፍ ፍቅርን ‹‹የሁሉም ነገር ማሰሪያ ነች›› በማለት ይገልጻታል፡፡ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከሁሉም የምትበልጠው ታላቋ ትእዛዝ ‹‹ፍቅር›› እንደሆነች ከመግለጹም በላይ ኦሪትና ነቢያት ሁሉ በእርሷ እንደሚጠቃለሉ አስተምሮናል፡፡
127
5
አጫጭር መልሶች ለአንዳንድ የቤተክርስቲያን ጥያቄዎች 1 / ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ምን ማለት ነው? ለምንስ እንዲህ ሆነ ወይም ለምን ይባላል? 👇👇👇 ይህ ማለት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ እና ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት የሆነው አባት በተደራቢነት የአክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የደብረሊባኖስ ገዳም እጨጌ (አበ ምኔት) ነው ማለት ነው። ይህ የሆነበትን ዝርዝር ምክንያት በየተወሰነበት ጊዜ ሒዶ ዝርዝር ጉዳዩን ማጥናት ይቻላል። በአጭሩ ግን ለኢትዮጵያ ከእስክንድርያ መጀመሪያ ተሹሞ የመጣው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሰላማ በወቅቱ የሀገሪቱ መናገሻ በነበረችው በአክሱም ሆኖ መላ ኢትዮጵያን ስላገለገለ በኢትዮጵያ ፓትርያርክ የሚሆነው አባት የአክሱም ሊቀ ጳጳስነት ወንበሩን እንዲይዝ ስለተፈለገ ነው ። አቡነ ተክለ ሃይማኖትም እርሳቸው ደብረ ሊባኖስን መሥርተው ከነበሩበት ጊዜ አንሥተው የእርሳቸው ልጆች (እጨጌዎች) ቤተ ክርስቲያንን ወክለው ከየዘምኑ ነገሥታት ጋር ይገናኙ ስለነበረ እና ርእሰ ሊቃነ ጵጵስናው ለኢትዮጵያ ሲፈቀድ እስከዚያ ድረስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ቤተ ክህነት ወክሎ ከመንግሥት ጋር ይሠራ የነበረው እጨጌው በርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ እንዲተካ እና እጨጌው ራሳቸው ይህን አዲስ ሐላፊነት እንዲረከቡ ስለተደረገ ነው ።  2 / የኢትዮጵያ ፓትርያርክ መንበሩ መንበረ ተክለ ሃይማኖት ለምን ተባለ? 👇👇👇 ከላይ ለማብራራት እንደሞከርኩት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የፕትርክና መንበሩ መነሻአ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ እንጂ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አይደሉም። የእርሳቸው ሊሆን ይችል የነበረው እርሳቸው በፓትርያርክነት አገልግለው አሁን እንደሚደረገው ጳጳሳትን ሾመው ቢያልፉ እና እርሳቸው ሲያልፉ የነበሩት ሊቃነ ጳጳሳት በእርሳቸው ፋንታ አንዱን ከመካከላቸው ፓትርያርክ አድርገው ቢመርጡ እና እንዲህ እያለ ሳይቋረጥ እስካሁን ደርሶ ቢሆን ኖሮ ፓትርያርክ ዘመንበረ ተከለ ሃይማኖት ይባል ነበር ። አሁን እየተባለ ያለው ግን “ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፣ ... ወእጨጌ ዘመነበረ ተከለ ሃይማኖት” ነው። ይህም ማለት መንበረ ተክለ ሃይማኖት የእጨጌነት እንጂ የፓትርያርክነት አይደለም ማለት ነው። ለፕትርክናችን ስም መጠቀስ ቢችል ኖሮ ሊባል ይሚችለው “ዘመንበረ ማርቆስ” ነበረ። ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ስድስት ኪሎ ግቢ ውስጥ ያለውን ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እንዱ ያስተከሉበት ምክንያቱም ይህንን ሀሳብ በመያዝም ጭምር እንደነበር ይነገራል ። ነገር ግን የግብጽ ቤተ ክርስቲያን “ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ” የሚለውን ስትፈቅድ ዘመንበረ ማርቆስ የሚለውን መጠቀም ግብፅን የተቀማች ያስመስላል ብለው ነው መሰል ይህንን ሀሳብ ስለተቃወሙ እና የእኛም አባቶች ዋናው ስሙ ሳይሆን ተግባሩ ነው ብለው ይህ እንዳይጠቀስ በሰነድ በተፈረመ መንገድ ስለተስማሙ ያን አክብረን በስያሜ አንጠቀመውም እንጂ የፕትርክና መንበራችን የቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ነው ። 3 / መንበረ ሰላማ የሚባል አለ ወይ? 👇👇👇 መንበረ ሰላማ የሚባል መንበር የለም ። ሊኖርም አይችልም ። ከላይ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት እንዳስረዳሁት ይህም ተመሳሳይ ነው ። መንበረ ሰላማ ሊባል ይችል የነበረው አባ ሰላማ ጳጳሳትን ሾመው እርሳቸው ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሆነው ቢሆን ኖሮ እና እርሳቸው ካለፉ በኋላ እርሳቸው የሾሟቸው በእርሳቸው ምትክ ሌላ ርእሰ ሊቀ ጳጳስ መርጠው ቀጥለው ቢሆንና ያ መተካካትም በዚያው መንገድ ሳይቋረጥ እስካሁን ቀጥሎ ቢሆን ኖሮ መንበረ ሰላማ ማለት ይቻል ነበር ። ነገር ግን እርሳቸው ማንንም አልሾሙም፣ እርሳቸውም ካለፉ በኋላ እንደገና ከግብጽ ተሾሞ መጣ እንጂ ከእርሳቸው የቀጠለ እንኳን የፕትርክና የጵጵስናም ሠንሠለት ስለሌለ መንበረ ሰላማ የሚባል የለም ፤ ሊኖርም አይችልም ።
582
6
ይህ ክፉ ነገር እንዴት አገኘን!!! “ከነነዌ ሰዎች በላይ የከፉ ማን ነበር? ከነነዌ ሰዎች በላይ ግራውንና ቀኙን የማያውቅ ማን ነበር? ምንም እንኳን ድንጋይ ጠርበው ዕንጨት ቈርጠው የሚያመልኩ አሕዛብ ቢኾኑም፣ ምንም እንኳን ስለ ሀልወተ እግዚአብሔር ምንም  ባያውቁም ምንም እንኳን ስለ ፈሪሐ እግዚአብሔር ከማንም ነቢይ ባይማሩም ዮናስ መጥቶ አንዲት አረፍተ ነገር ስለ ነገራቸው ብቻ በሦስት ቀን ውስጥ ኹሉንም ተዉት፡፡ ዘማዊው ንጹሕ ኾነ፡፡ ስግብግቡ ለጋሽ ኾነ፡፡ ቁጡውና ተሳዳቢው መራቂ ኾነ፡፡ ሰነፉ ሰው ለጦም ለጸሎት ብርቱ ኾነ፡፡ ከክፋታቸውም አንዱን ወይም ኹለቱን ብቻ የተዉት አይደሉም ኹሉንም ተዉት እንጂ፡፡ ምንም እንኳን የበደላቸው ጽዋ ሞልቶ መንበረ ጸባዖትን ለቁጣ የቀሰቀሰ የነበረ ቢኾንም ተመለሱ፡፡ ሲመለሱም እግዚአብሔር በቁጣ ሳይኾን በምሕረት ዓይን አያቸው፡፡ ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጸተ፡፡ ተወዳጆች ሆይ! የነነዌ ሰዎች ምንም አሕዛብ ቢኾኑም በሦስት ቀን ውስጥ ብቻ እንዲኽ ማራኪየኾነ ንስሐን ከገቡ፥ እጅግ ብዙ ዘመናትን ተምረን ያልተለወጥን እኛው ክርስቲያኖች እንደምን ይፈረድብን ይኾን?”
191
7
“ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት” ያዕ 1፥2-3። "…ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ። ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል። 1ኛ ቆሮ 10፥ 12-13። "…በዘራችሁና በሃይማኖታችሁ ምክንያት እስር መንገላታት ቢገጥማችሁ ጽኑ። ምክንያቱም “በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።” ያዕ 1፥12 ደግሞም “ማንም ሲፈተን፦ በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል፤ እግዚአብሔር በክፉ አይፈተንምና፤ እርሱ ራሱስ ማንንም አይፈትንም።” ያዕ 1፥13። "…ሁሉ ነገር በትእግስት ይሁን “በለሱን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል፥ ጌታውንም የሚጠብቅ ይከብራል።” ምሳ 27፥18።
207
8
ምንተ ንግበር!!! ከሁሉ በላይ በምትሆነው አንዲት እና ኩላዊት ቤተክርስቲያን አምናለሁ!!!!. 1.ነገር ግን ለዚህ ሁሉ መሆነ ምክንያት ምንድነው? 2.በዘመናት የ ፖለቲካ ለውጥ ውስጥ ሁልጊዜ  ቤተክርስቲያንን ለምን ያናውጣሉ? 3.ለምንስ ይህ ሆነ በእሑኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ሚዛናዊ እና ቤተክርስቲያንን ከመከፋፈል የታደገ ውሳኔ ነው የወሰነው? 4.የተወሰኑት ውሳኔዎችን ማን ይሆን የሚያስፈጽመው? 5.እነዚህ 3ሊቃነ ጳጳሳት ለምን ይሆን ይህን ተግባር የፈጸሙት? ቤተክርስቲያንን አሸናፊ የሚያደርግ ተመሳሳይ መሰል ችግሮች እዳይፈጠሩ ዘላቂ እና ዘመኑን የሚዋጅ ጠንካራ የሆነ ሁሉን የሚያስማማ ውሳኔ የውሰን ዘንድ ይህም እንዲሆነ እመኛለሁ። እስከዛው ግን እንደ ታናሽነቴ ሁሉንም አባቶች በእኩል እናይ ዘንድ አለምናለው ይልቁንም ሐዋርያት በሰሯት ርትዕት ቅድስት እና ንጽሕት በሆነች የ ሊቃነ ጳጳሳት,ኤጲስ ቆጶሳት,ቀሳውት ወዲያቆናት...መፍለቂያ እናም የክርስቶስ ሙሽራ በሆነች ቤተክርስቲያን አምነን ጸንተ እንኑር። ባለቤቱ ያቃለለው...ነውና ተረቱ ይህ ግዜ አልፎ ቤተክርስቲያን ስታሸንፍ እዳናፍር አባቶቻችን አንሳደብ,አንሳለቅባቸው። የቤተክርስቲያን ምርጥ አገልጋይ መሆን ባንችል እንኳን ችግር ግን አንሑንባት። ከቻልን ይህ ነገር ለምን ሆነ,እንዴት ሆነ ለቀጣይስ እንዳይሆን ምን መደረግ አለበት ብለን እናጥና,እንማከር,እንወያይ,እናንብብ,እንጻፍ የመፍትሔ ሰው እንሁን። "ንበሩ በኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ጽድቅ ዘአርያም"
163
9
⁉️ #ፓትርያርኩን_የደፈራቸው_ማን_ነው?⁉️ የኣባ ሳዊሮስን ስድነት ተቃውመህ "ከቅዱስ ኣባታችን ጋር እቆማለሁ" ያልከው ወዳጄ፣ ፓትርያርኩን የደፈራቸው አባ ሳዊሮስ ሳይሆኑ የአሁኖቹ "ተደፈርን" ባይ ጳጳሳት እንደሆኑ አታይምን? ትናንትና ቅዱስ ኣባታችንን የቁም እሥረኛ አድርገው ሲያበቁ፣ የቅዱስ አባታችንን ሥልጣን በመጋፋት እሳቸው ሳያውቁት ስንት ዝውውርና ስንት ሹመት ኣልተፈፀመም ወይ? በተለይም ስለ ትግራይ ሕዝብ መከራ እንዳይተነፍሱ፣ በራሳቸው ሚድያ በEOTC Tv እንኳን እንዳይነገሩ ድምፃቸው ያፈኑ እነዚህ ጳጳዳት አይደሉም ወይ? ታድያ ቤ/ክ የተሰደበችው፣ ፓትርያርካችን የተደፈሩት አሁን ነው? ቅዱስ ኣባታችን "አቡነ ጁንታ" ሲባሉ፣ ፓትርያርኩ ድምፃቸው ሲያሰሙ እንኳን "የግላቸው እንጂ ሲኖዶስን ኣይወክልን" ሲባሉ ሲኖዶሱ ቀኖና ቤ/ክ ለመጠበቅ፣ ክብራቸውን ለማስከበር ምን አደረገ? መዋቅር ላይ ያሉ ሰዎች ቅዱስ ኣባታችንን "ይሄ ሰውዬ አቡነ ወያኔ ናቸው" ብለው በግልፅ ሲሳደቡ ቤተ ክህነቱ ዝምታ ኣልመረጠምን? ታድያ የፓትርያርኩን ክብር የተነካው ዛሬ ይመስል "ከፓትርያርኩ ጎን እቆማለሁ" የምትለው በየትኛው ሞራልህ ነው? አስተውል:- "አባታችን ሲበደሉ ዝም ብለሃልና ዛሬም ሲበደሉ ዝም በል" እያልኩህ ኣይደለም። ስህተት በስህተት ኣይታረምምና። ነገር ግን ዛሬ የተወለደው የነ አባ ሳዊሮስ ሥርዓት-አልበኝነት፣ እነ አባ ዮሴፍ የጠነሰሱት፣ እነ ኣባ ፋኑኤል የወጠኑት አይደለም ወይ? የያኔው የአባታችን ግፍ፣ የእኛም ዝምታ ለዚህ ኣብቅቶናል። ትናንትና ቅዱስ አባታችንን አውርደህ ሌላ እንደራሴ ልትሾም ስትዶልት የነበርክ ሰው፣ ዛሬ ላይ ፕትርክናቸው የሚጋፋ ነገር ሲመጣ ከጎናቸው ለመቆም እንዴት ሞራል አገኘህ? ቅዱስ ፓትርያርኩ "ታቦት ሰርቀው ሲወጡ ተያዙ" ብለህ ያልክ ሰው፣ አሁን አባ ሳዊሮስን ለመቃወም እንዴት ቻልክ? የቅዱስ አባታችን መከራ፣ ግፍና ዕንባ የሚቀበል ጌታ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያን ቤ/ክ ላይ የቁጣ በትሩን የሚያነሳበት ጊዜ ደርሷል! እኛ ግን ትናንትም፣ ዛሬም ነገም ከፓትርያርኩ ጎን እንቆማለን‼️
1
10
ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ አምላክን!!!
205
11
በወላይታ ዞን በቀበሌያቸው ውስጥ ብቻቸውን ኦርቶዶክስ ሆነው ለጸኑት እናት የታነጸው ህንጻ መቅደስ ነገ ህዳር 04 ይመረቃል። በወላይታ ሀገረስብከት ዳሞት ወይዴ ወረዳ አንካ ሻሻራ ቀበሌ ብቸኛ የኦርቶ+2
በወላይታ ዞን በቀበሌያቸው ውስጥ ብቻቸውን ኦርቶዶክስ ሆነው ለጸኑት እናት የታነጸው ህንጻ መቅደስ ነገ ህዳር 04 ይመረቃል። በወላይታ ሀገረስብከት ዳሞት ወይዴ ወረዳ አንካ ሻሻራ ቀበሌ ብቸኛ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ሆነው ለዘመናት ብቻቸውን በቀበሌው ውስጥ ኖረዋል። በማሳቸው ውስጥ ሣር ጎጆ ቀልሰው ዘውትር ሰንበት በእዚያ እልፍኝ የቅድስት አርሴማን ሥዕለ አድኖ ይዘው ስርዓተ አምልኮ ይፈጽሙ ነበር። በአሁኑ ወቅት 60 ተጨማሪ አባወራ እና እማወራ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ በአካባቢው አግኝተዋል። እኚህ እናት በማሳቸው ላይ በሰጡት ስፍራ የቅድስት አርሴማ ህንጻ መቅደስ ሙሉ በሙሉ ታንጾ ነገ ህዳር 04 ይመረቃል ሲል ወላይታ ዲቻ ታይምስ ዘግበዋል።
254
12
በወላይታ ዞን በቀበሌያቸው ውስጥ ብቻቸውን ኦርቶዶክስ ሆነው ለጸኑት እናት የታነጸው ህንጻ መቅደስ ነገ ህዳር 04 ይመረቃል። በወላይታ ሀገረስብከት ዳሞት ወይዴ ወረዳ አንካ ሻሻራ ቀበሌ ብቸኛ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ሆነው ለዘመናት ብቻቸውን በቀበሌው ውስጥ ኖረዋል። በማሳቸው ውስጥ ሣር ጎጆ ቀልሰው ዘውትር ሰንበት በእዚያ እልፍኝ የቅድስት አርሴማን ሥዕለ አድኖ ይዘው ስርዓተ አምልኮ ይፈጽሙ ነበር። በአሁኑ ወቅት 60 ተጨማሪ አባወራ እና እማወራ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ በአካባቢው አግኝተዋል። እኚህ እናት በማሳቸው ላይ በሰጡት ስፍራ የቅድስት አርሴማ ህንጻ መቅደስ ሙሉ በሙሉ ታንጾ ነገ ህዳር 04 ይመረቃል ሲል ወላይታ ዲቻ  ታይምስ ዘግበዋል።
1
13
+++ "እኔ" ብቻ +++ ዕውቁ ሩስያዊው የልብ ወለድ ደራሲ ዶስቶየቩስኪ "Brothers Karamazov" በተሰኘው ድርሰቱ ስለ አንዲት ምናባዊት ንፉግ ሴት ታሪክ እንዲህ ይተርካል። በአንድ ዘመን በግብርና ሥራ እየተዳደረች የምትኖር ክፉ ሴት ነበረች። ታዲያ በሕይወት እያለች አንድ በጎ ነገር እንኳ ሳትሠራ ይህን ዓለም በሞት ተሰናበተች። ነፍሷም በወጣች ጊዜ ወዲያው አጋንንት እየተናጠቁ ይዘዋት ሄደው ወደ እሳት ባሕር ወረወሯት። ጠባቂ መልአኳም ይህን ባየ ጊዜ ከፈጣሪ ፊት ቆሞ የሚያዘክርላት ጥቂት በጎ ሥራ ሠርታ እንደ ሆነ ለማስታወስ ሞከረ። ወዲያውም "አንድ ጊዜ ከማሳዋ ላይ አንድ ራስ ሽንኩርት ነቅላ ለአንዲት ነዳይ መስጠቷን" ለአምላኩ አሳሰበላት። እግዚአብሔርም "በል ያን ሽኝኩርት ውሰድና ወደ እርሷ ሂድ። እርሱን ይዛ መውጣት ከቻለች ወደ ገነት ታስገባታለህ። ካልሆነ ግን እዚያው ሲኦል ትቀራለች" አለው። መልአኩም እንደ ተባለው ሴቲቱ የሽንኩርቱን ራስ እንድትይዝ አድርጎ በጥንቃቄ ወደ ውጭ ይስባት ጀመር። ነገር ግን ሌሎች በዚያ የእሳት ባሕር ውስጥ የነበሩ ኃጥአን ስትወጣ ሲመለከቱ አብረዋት ለመውጣት እርሷ ላይ ተንጠላጠሉ። ያቺ ጨካኝ ሴት ግን ክፉኛ በመወራጨት ከላይዋ ላይ እያራገፈቻቸው "እኔ ነው እየሳበኝ ያለው እናንተን አይደለም። ይህ ሽንኩርት የእኔ ነው። የእናንተ አይደለም።" አለች። ይህን እየተናገረች ሳለም የያዘችው የሽንኩርቱ ጫፍ ተበጥሶ  ወደ እሳቱ ተመልሳ ገባች። መልአኩም በሁኔታው እያዘነ ከእርሷ ተለይቶ ሄደ። ያን የሽንኩርት ጫፍ የበጠሰው ምን ይመስላችኋል? እርሷ ላይ የተንጠለጠሉት ነፍሳት ወይስ የእርሷ ጭካኔ እና ንፋግነት? ይህ የዶስቶቩስኪ ምናባዊ ትርክት በዚህ ዘመን ያለነውን የእያንዳንዳችንን ማንነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ይመስለኛል። ከመጠን በላይ ለራስ በመጨነቅና የራስን ምቾት ብቻ መፈለግ የእኛ ጊዜ መለያ ጠባይ ሆኗል። በንግግራችን ውስጥ "እኔ" "ለእኔ" "የእኔ" የሚሉት ቃላት እየረቡ "እኛ" የሚለው ቃል እየሳሳ መጥቷል። በብዙዎች የሚመለክ በየቤቱ የቆመ  የዘመኑ አዲስ ጣዖት ቢኖር "እኔ"ነት (ራስ) ነው። ጥቂት የማይባሉ ሰዎች የትኩረት ማዕከል ለመሆን የማይቆፍሩት ጉድጓድ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም። በተገኙበት ሁሉ ስለ እነርሱ እንዲወራ ይፈልጋሉ። ለቀብር እንኳን ሄደው ለሞተው ሰው ከሚሰጠው ትኩረት አንጻር በዚያች ቅጽበት ያን አስከሬን ቢሆኑ አይጠሉም። ስማቸውን በየሰው አፍ ለማስገባትና መነጋገሪያ ለመሆን የትኛውንም ዓይነት ዋጋ ይከፍላሉ። ይህን ጊዜ "ራስን መውደድ" በሽታ ይሆናል። በራስ ዓለም ውስጥ እንደ መጥፋት፣ ራስን በራስ እንደመዋጥ ያለ ሊታከም የሚገባው ጽኑ ደዌ! ሁልጊዜ በስግብግብነት እና ለእኔ ብቻ በማለት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች መንፈሳቸው የተሰበረ ይሆናል። የገዙት አያስደስታቸውም፣ የሰበሰቡት አያረካቸውም። በሕይወታቸው ውስጥ ያስወጡት መልካም ነገር ስላለ መቼም የውስጥ ዕረፍት አያገኙም። ያ ከሕይወታቸው ያስወጡት መልካም ነገር ምንድር ነው? "ብቻ ያለ መሆን" መልካምነት ነዋ! "ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም" ዘፍ 2፥18 በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ግለኝነትና "ለእኔ ብቻ" ማለት ፈጽሞ የተወገዘ ነው። ምድር ላይ ባለችው ቤተ ክርስቲያን በኅብረት መንፈስ ካልኖርህ "በሰማያት ወደ ተጻፉት የበኩራት ማኅበር" ልትገባ አትችልም።(ዕብ 12፥23) በእግዚአብሔር ዙፋን ዙሪያ ቆመው የሚያመሰግኑት ሱራፌል ክንፎቻቸው እርስ በርስ የተያያዘ ነው። ይህንንም አንድ ሊቅ ሲተረጉም በአምላክ ዙፋን ፊት ለመቆምና ከእነዚህ አመስጋኝ  መላእክት ጋር አብሮ ለመቆጠር ሰዎች በአንዲት ኅብረት ሊኖሩ እንደሚገባቸው ያሳያል ሲል ተርጉሞታል። ክርስትና ራስን ማዕከል የማድረግ ሳይሆን ሌሎችን የማገልገልና ስለ ብዙዎችም በፍቅር መሥዋዕት የመሆን ሕይወት ነው።
220
14
እሾህ #የሌለባት_ጽጌ_ሬዳ    🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷 ጊዜው  የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን  የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች። እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ  ናቸው  ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን  አልጋይ እና ፈንጋይ  እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::  #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች  መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1  (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ። የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር  ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው  በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው  በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ    በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን  ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ   አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ። #እርሷ_እመቤታችን እንኳን  ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ  አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ  ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት:: እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ  የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።  #አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1 #አበባ መድኃኒትን ያስገኛል  እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች  ሉቃ 2÷10-11 አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2 "ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11 አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ  ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26 "በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ  " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም። እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ  የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች። አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ  እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4 አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም  የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች። አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው  ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል  ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ።  ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ  ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ። አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ  ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን። "ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ  #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ .......ይቆየን ............
149
15
#መቁጠርያ_በቤተክርስቲያን (Prayer Ropes) በተለያዩ መናፍቃን ዘንድ እንደ ባዕድ ነገር ነው የሚታየው የሚገርመው ለዚህ ንግግራቸው ምክንያት እንኳ ማስቀመጥ አይችሉም። አባቶቻችን መቁጠርያን የሚጠቀሙት በፀሎት ጊዜያት ነው። አብዝተው ለመፀለይ ይጠቀሙበታል። መቁጠርያን ለፀሎት ስለተጠቀሙ መክሰስ አይገባም። ቅዱስ ጳውሎስ በ 1ኛ ተሰ 5፥18 ላይ "ሳታቋርጡ ፀልዩ በሁሉ አመስግኑ..." በማለት እንዳስተማረን አብዝቶ መጸለይ ያስፈልጋል። የጸሎት ተቃዋሚም ጠላት ሰይጣን ነው፡፡ ጌታም "ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ፀልዩ" ማቴ 26:41 ብሏል፡፡ በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይም ፀሎትን አብዝተን እንድናደርግ መፅሀፍ ቅዱስ ይመክራልና #እኛ_ኦርቶዶክሳውያን_መቁጠርያን_የምንጠቀመው #1ኛ በትኩረትና በተመስጦ ሆነን ለመፀለይ #2ኛ ይዘነው በመጓዝ ፀሎትን መፀለይ እንድናስታውስ #3ኛ እንዳንፀልይ ከሚያግዱን ክፉ መንፈሶች ለማሸነፍ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አብዛኛውን ጊዜ የሚጠቀሙባቸው መቁጠርያዎች ባለ 41 መቁጠርያ (Beads) (በውስጡ 41 ድብልብሎችን) እና ባለ 64 መቁጠርያ (በውስጡ 64 ድብልብሎችን) ናቸው 41_የመሆኑ_ምስጢር_የጌታችንና_የመድሃኒታችን_የኢየሱስ_ክርስቶስን_41_ግርፋት_ቁስል_ለማሰብ_ሲሆን #64_የመሆኑ_ምስጢር_ደግሞ_የእናታችን_የእመቤታችን_በምድር_ላይ_የኖረችበት_እድሜ_ለማሰብ_ነው አንዳንድ ቀሳውስትና መነኮሳት 150,300 ወይም ከዛም በላይ ድብልብሎች በመቁጠርያ ውስጥ ይጠቀማሉ። ባለ 41 መቁጠርያ ላይ በመደጋገም የሚፀለዩ ፀሎቶች አሉ።እነርሱም፦ 👉 1ኛ ጌታ በመዋዕለ ስጋው እንድንፀልይ ያስተማረን ፀሎትን እና የቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ። ይህም፦ አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር ስምህ ይቀደስ መንግስትህ ትምጣ... እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ በመልዓኩ በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም እልሻለሁ...(12 ጊዜ) 👉 2ኛ አቤቱ ማረን! (41 ጊዜ) 👉 3ኛ ስለ ድንግል ማርያም ብለህ ማረን! (41 ጊዜ) 👉 4ኛ ኪርያላይሶን(41 ጊዜ) 👉 5ኛ ሳዶር፣አላዶር፣ዳናት ፣አዴራ፣ ሮዳስ (41 ጊዜ) 👉 6ኛ. ኦ! አምላክ(41 ጊዜ) 👉 7ኛ .ኦ! ክርስቶስ (41 ጊዜ) 👉 8ኛ ስለ እናትህ ስለ ድንግል ማርያም ብለህ ከመአቱ አድነን፣ሰውረን ምህረትንም ላክልን (ማረን)41 ጊዜ) 👉 9ኛ አቤቱ አምላካችን መድሃኒታችን ሆይ ስማን! (41 ጊዜ) 👉 10. ኤሎሄ (አምላኬ) (41 ጊዜ) 👉 11. ወዮልኝ! ወዮልኝ!ወዮልኝ!አምላኬ ሆይ እየኝ (ተመልከተኝ) 👉 12.አቤቱ እንደ ምህረትህ እንጂ እንጂ እንደ በደላችን አይሁን! (12 ጊዜ) 👉 13. አቤቱ በመንግስትህ አስበን! (12 ጊዜ) 👉 14. እመቤቴ ሆይ (7 ጊዜ) ከዚህ በላይ የተጠቀሱት 14ቱ በፀሎት ጊዜ በመቁጠርያው በመደጋገም የሚፀለዩ ናቸው። እኚህ የተለመዱ ስርዓት ወጥቶላቸው በመደጋገም የሚፀለዩ ፀሎቶች ሲሆኑ ከዚህ በላይም የራስን የግል መሻት(ጨምሮ) ጨምሮ መፀለይ ይቻላል።ባለ ስልሳ አራቱን ( 64) መቁጠርያ ስንጠቀም ደግሞ 41 ጊዜ ተደጋግመው የሚፀለዩትን 64 ጊዜ ማድረግ ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ 12 እና 7 የነበሩት እንደዛው ሆነው ይቀራሉ።
216
16
ክርስቶስ በከበረ ደሙ የዋጃችሁ ሃይማኖታችሁ የቀና የተወደዳችሁ ምእመናን ሆይ ልዑል እግዚአብሔርን ልናመሰግነው ይገባናል። በይቅርታው ገናናነት በጎ የሆኑትን ሁሉ ስለሰጠን የልዕልናውን ምስጋና ጨምረን እጅግ ልናበዛ ይገባናል። እስከዚህች ዕለትና ሰዓት  አድርሶናልና። ዳግመኛም ከበደላችንና ከክፉ ሥራዎቻችን ወደ ንስሐ እስከምንመለስ በእኛ ላይ ይታገሥ ዘንድ ከእኛ አስቀድሞ ብዙዎች አሕዛብን እንዳጠፋቸው ስለ ክፉ ሥራችን እንዳያጠፋን እግዚአብሔርን እንለምነው። እንግዲህም ከታካችነታችን ነቅተን ከወደቅንበት እንነሣ ስለ አለፈው በደላችንና ስለ ብዙ ኃጢአታችን በፊቱ ልናለቅስ ወደርሱም ልንጮህ ይገባናል። በሕይወታችን ዘመን ሁሉ ከጠላችን ሰይጣን ወጥመድ ጠብቆ በቀናች ሃይማኖት ያጸናን ዘንድ በነፍስ በሥጋም ጤነኞች እንደሆን በቀናች ሃይማኖትና በበጎ ሥራ ሁሉ ጸንተን ደስ እንዳለን እንደ ዛሬው ለመጪው ዓመት ያደርሰን ዘንድ እንለምነው። ከእኛም በሞት የተለዩትን በበጎ ዕረፍት እንዲያሳርፍልን፣ በሀገራችንም ጽጋን በረከትን ይሰጥ ዘንድ፣ የተራቡም እንዲጠግቡ የምድራችንን ፍሬ ይባርክ ዘንድ፣ በሽተኞች ይፈወሱ ዘንድ፣ ሽማግሎዎችና አሮጊቶች፣ የሙት ልጆችም ይጠበቁ ዘንድ ለሀገራችንና ለዓለሙ ሁሉ ሰላም ይሁን አሜን! መጽሐፈ ስንክሳር
159
17
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ በረከት ጷጉሜን ፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፬ ዓ.ም """""""""""""""""""""""""" አዲስአበባ -ኢትዮጵያ """""""""""""""""""" በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ -በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ -ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ -የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣ -በሕመም ምክንት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ -እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵውያት በሙሉ! የዓመታትና የአዝማናት ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ለአዲሱ ዓመት ለሁለት ሺሕ ዐሥራ አምስት ዓመተ ምሕረት ዘመነ ሉቃስ በሰላም አደረሳችሁ !! “ወዓመቲከኒ ለትውልደ ትውልድ፤ ዓመቶችህ ለልጅ ልጅ ናቸው” (መዝ. ፻፩፥፳፬)፡፡ ይህንን ቃለ እግዚአብሔር የተናገረው እግዚአብሔር በቅብዕ ቅዱስ አማካኝነት ሀብተ ትንቢት ወመዝሙር ያሳደረበት ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው፤ የቃሉ መሠረተ ሐሳብም ዓመታት የእግዚአብሔር ስጦታ መሆናቸውን፣ እንደዚሁም የተሰጡት ለሰው ልጆች መሆናቸውን ይገልፃል፡፡ በእርግጥም ዓመታት ከእግዚአብሔር ለሰው ልጆች የተሰጡ ሀብቶች ናቸው፤ ዓመታት፣ ወራት፣ ዕለታት፣ ቀናት፣ ሰዓታት የሚያስፈልጉት ለሰው ልጅ እንጂ ለእግዚአብሔርና በመንፈሳዊ ዓለም ለሚገኙ ፍጡራን አይደለም፤ ምክንያቱም ሰው በደካማው ዓለም የሚኖር ደካማ ፍጡር ስለሆነ ለኑሮው ጊዜያት የግድ ያስፈልጉታል፤ በመንፈሳዊ ዓለም የሚገኙ ፍጡራን ግን፣ ድካም የሌለባቸው ትጉሃን ስለሆኑ፣ ዓመትም ቀንም ሰዓትም ወዘተ አያስፈልጋቸውም፤ የሰዓት መለኪያ ብርሃንም የላቸውም፤ ምክንያቱም ያሉበት ዓለም ሁሌም ብርሃን እንጂ ጨለማ ስለማይፈራረቀው፣ እንደዚሁም ተለዋዋጭ አየርም ሆነ ዕድሜ ስለሌላቸው ማለት ነው፤ ለሰው ግን የጊዜ መለኪያ የሚሆኑ ብርሃናትና አዝማናት ወዘተ የተመደቡለት ስለሆነ፣ በእነሱ እየተመራ ጊዜያትን ይለካል፤ ዓመታትን ወራትንና ቀናትን ወዘተ ይቈጥራል፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፡- ዓመታት ከእግዚአብሔር ለእኛ የተሰጡን ያለምክንያት አይደለም፤ የእግዚአብሔር ስጦታ ሁሉ ክብርም ጥቅምም አለውና ልናከብረውና ልንጠቀምበት እንጂ፤ ሁላችንም እንደምንገነዘበው ጊዜ ትልቁና ቀዳሚው የሥራ መሣሪያ ነው፡፡ እህልን ዘርተን የዓመት ምግባችንን የምናገኘው ወርኃ ክረምት ስለተሰጠን ነው፤ ይህ ወቅት ባይኖር ኖሮ የእርሻ ሥራ ሠርተን ራሳችንን መመገብ እንደማንችል የምንስተው አይሆንም፡፡ ከዚህ አንጻር ዓመታትንና ወቅቶችን እንደ አመቺነታቸው እየተጠቀምን ልንሠራባቸው እግዚአብሔር አመቻችቶ ሰጥቶናል ማለት ነው፤ ስለዚህ በብሂለ አበው “ጊዜ ሳለ ሩጥ ….” እንደሚባለው ሁሉንም በጊዜው ጊዜ መሥራትና ተጠቃሚ መሆን ያስፈልጋል፡፡ ሰውም ሆነ ጊዜ ለሥራ የተፈጠሩበት ምክንያት መክበርም መዳንም ማግኘትም ማደግም መልማትም በሥራና በሥራ ብቻ የሚገኝ ከመሆኑ የተነሣ እንደሆነ ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም፤ “ብላዕ በሐፈ ገጽከ፤ በፊትህ ላብ እንጀራህን ብላ” የሚለው አምላካዊ ትእዛዝም ይህንን ይገልጻል፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፡- እግዚአብሔር አምላክ ያለመታከት ሠርተን ራሳችንን በራሳችን የምናስተዳድርባት በሀብትና በጊዜ የተዋበች ምድር አስረክቦናል፤ ምድሪቱንም ለእኛ በሚመች አኳኋን አበጅተን እንድንጠቀምባት የሚያስችል አእምሮና ጉልበትም ከጤና ጋር ሰጥቶናል፤ ሐቁ ይህ ከሆነ ታድያ ለምንድን ነው በምድራችን ስጋትና ጭንቀት፤ ረኃብና እርዛት፣ የሀብት እጥረትና የእርስ በርስ ግጭት በስፋት የሚታየው የሚለውን ጥያቄ ሰው ሁሉ በጥልቀት ሊያጤነው ይገባል፡፡ እግዚአብሔር የሰጠን ምድር አሁንም ለፍጡራን የሚበቃ የተትረፈረፈ ሀብት ያለጥርጥር አላት፣ የአጠቃቀም ጉዳይ ካልሆነ በቀር ሀብት የሌለው የምድር አካባቢ ፈጽሞ የለም፡፡ ይህም ከሆነ ሁሉም ወደ ሥራና ሥራ ብቻ ተሠማርቶ ጥረቱን ከቀጠለ የሚያጣው ነገር የለም ማለት ነው፣ ሰው ጤና ዕውቀትና ሰላም ካለው ሀብታም ነው፤ ምክንያቱም እነዚህ ከተሟሉለት ሌላው ሁሉ እግዚአብሔር ከሰጠው ምድር ሠርቶ የሚያገኘው ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ግን ነገሩ ሁሉ ጨለማ ይሆንበታል፤ አካላዊና አእምሮአዊ ጤናውም ይደፈርስና ሳያጣ ያጣ ወደ መሆን ይቀየራል፡፡ ዛሬ በሀገራችንም ሆነ በዓለማችን እየተከሠተ ያለው ሐቅ ይኸው ነው፡፡ ይህ የሰላም እጦት በሀገራችን በኢትዮጵያ በርከት ላሉ ዓመታት እየተደጋገመ በመከሠቱ፣ በዚህ ጠንቅ ሕዝባችን ሳያጣ ያጣ ሆኖአል፤ ኢትዮጵያን በመሰለች ለምና ምድራዊት ገነት ተቀምጠን፣ በዓለም ውስጥ የድህነት ተምሳሌት ሆነን መገኘታችን፣ የሁላችንም ኅሊና ሊኰረኲረው ይገባል፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በአዲሱ ዓመት ለኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን ሁሉ በአጽንዖት የምንመክረው ዓቢይ ምክር በግጭት ችግሮቻችንን መፍታት በፍጹም አንችልም፤ በመራራቅም ማደግ አንችልም፤ በተለያየን ቊጥር ድህነታችንን ከማስቀጠልና ደካሞች ከመሆን በቀር የምናገኘው አንዳች ፋይዳ የለም፤ እውነቱ ይህ ከሆነ ከገባንበት ያላስፈላጊ ግጭት በፍጥነት ወጥተን ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት ወደሚያስችል ወደ ምክክርና ውይይት እንግባ፤ አዲሱ ዓመት እውነተኛ አዲስ ዓመት ሊሆን የሚችለው ይህንን ያደረግን እንደሆነ ነው፡፡ አሮጌውን አስተሳሰብ እንዳለ ተሸክመን ለመቀጠል እየዳዳን ከሆነ አዲስ ዓመት ማለቱ የአፍና የጆሮ ቀለብ ከመሆን በቀር የሚሰጠን አንዳች ትርጉም የለም፡፡ ስለሆነም አዲሱን ዓመት አዲስ የሆነ የሰላምና የዕርቅ የስምምነትና የአንድነት የይቅርታና የምሕረት የፍትሕና የእኩልነት መርሕ አንግበን ፍጹም ሰላምን ለማንገሥ በቊርጥ ማሰብና መነሣሣት አለብን፣ ይህንንም ለማሳካት በአንድ አዳራሽ፣ በአንድ ጠረጴዛ ተገናኝተን ችግሮቻችንን በውይይትና በምክክር እንድንፈታ በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ በመጨረሻም አዲሱ ዓመት የሰላም የፍቅር የበረከት የዕድገት የሃይማኖትና የልማት ዓመት እንዲሆንልን ወደ እግዚአብሔር በመጸለይና በብሩህ ተስፋ እንድንቀበለው መልእክታችንን በድጋሚ በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡ እግዚአብሔር መልካም አዲስ ዓመት ያድርግልን ! እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ !! ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን !!! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ  ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መስከረም ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓመተ ምሕረት አዲስ አበባ  ኢትዮጵያ፡፡
125
18
✝መዝሙር የሚወድ ✝
155
19
#ሥርዓተ_ማኅሌት_ዘነሐሴ_ኪዳነ_ምሕረት ፩/ ነግሥ ( ለኲልያቲክሙ ) ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ ለሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኀኒት መስቀል፡፡ ዚቅ፦ ወታስተሥርዪ ኃጢአተ ሕዝብኪ ተበውሐ ለኪ ፨ እም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፨ ከመ ትኵኒ ተንከተመ ለዉሉደ ሰብእ፨ ለሕይወት ዘለዓለም ፨ ለኪ ይደሉ ከመ ትኵኒ መድኀኒቶሙ ለመሐይምናን ሕዝብኪ ፨ ኦ መድኀኒተ ኵሉ ዓለም ወልድኪ ሣህሎ ይክፍለነ ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡ ፪/ ነግሥ ( እምጌቴሴማኒ ፈለሰት ) እምጌቴሴማኒ ፈለሰት ኀበ ዘሉዓሌ መካን፤ ውስተ ቤተ መቅደስ ረባቢ ዘመሳክዊሁ ብርሃን፤ አንቀጸ አድኅኖ ማርያም ጽላተ ኪዳን፤ ኵሉ ይብልዋ በአኅብሮ ዘበዕብራይስጢ ልሳን፤ ዕፀ ጳጦስ ይእቲ እንተ በአማን ቅድስተ ቅዱሳን፤ እመቅድሀ ከርሣ ተቀድሐ አስራባተ ወይን፤ ወበውስቴታ ተሠርዓ ቊርባን፡፡ ዚቅ፦ ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን መዝገቡ ለቃል ፨ ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን አንቀጸ ብርሃን፨ ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን ጽጌ ደንጐላት ፨ ሐረገ ወይን ዘእምነገደ ይሁዳ፨ እንተ ሠረፀት ለሕይወት፡፡ ፫/ ለፍልሰተ ሥጋኪ ( መልክአ ኪዳነ ምሕረት ) ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ኀበ ሕንጻ ሕይወት ተሐደሰ፤ እምቅድመ ዝኒ ኀቤሁ ሥጋ ወልድኪ ፈለሰ፤ ቤዛዊተ ዓለም ማርያም አስተበቊዓኪ አንሰ፤ ትቤዝዊ በኪዳንኪ ዘዚአየ ነፍሰ፤ እስመ በሥራይኪ ለቊስልየ ቀባዕክኒ ፈውሰ፡፡ ዚቅ፦ ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ፨ ወማኅደሩ በጽድቅ ዘገብራ ከሃሊ፨ ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ ፨ በመሰንቆሁ እንዘ የኃሊ፨ ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ። ወረብ፦ ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ፤ በመሰንቆሁ እንዘ የሐሊ ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ። ፬/ ለዝክረ ስምኪ ( መልክአ ማርያም ) ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤ እምነ ከልበኒ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ ማርያም ድንግል ለባሲተ ዐቢይ ትእዛዝ፤ ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤ ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ፡፡ ዚቅ፦ ሰላም ለኪ ማርያም እመ አምላክ፨ ወልድኪ ይጼውዓኪ፨ ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር፡፡ ወረብ፦ ሰላም ለኪ ማርያም እመ አምላክ ማኅደረ መለኮት፤ ወልድኪ ወልድኪ ይጼውዓኪ ውስተ ሕይወት ወምንግሥተ ክብር። ፭/ ለእስትንፋስኪ ( መልክአ ማርያም ) ሰላም እስትንፋስኪ ዘመዐዛሁ ሕይወት፤ ከመ መዐዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት፤ ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት፥ ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት፤ በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት፡፡ ዚቅ፦ ንዒ ኀቤየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ፨ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል፨ ወኵሉ ነገራ በሰላም፡፡ ወረብ፦ ንዒ ኀቤየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ ፤ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል መዓዛ አፉሃ ታንሶሱ፡፡ ፮/ ለፍልሰተ ሥጋኪ ( መልክአ ፍልሰታ ) ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ዘኢይቀብል ሞገሱ፤ ወዘኢይነጽፍ ባሕርየ ተውዳሱ፤ ማርያም ታዕካ ለእግዚአብሔር ጽርሐ መቅደሱ፤ ተበሃሉ በሰማያት እለ ኪያኪ አፍለሱ፤ ማርያምሰ እንተ በምድር ታንሶሱ ፡፡ ዚቅ፦ ማርያም ጽርሕ ንጽሕት ማኅደረ መለኮት ፨እኅቶሙ ለመላእክት ሰመያ ሰማያዊት ፨ እንተ በምድር ታንሶሱ፡፡ ወረብ፦ ማርያም ጽርሕ ንጽሕት ፤ ማኅደረ መለኮት ጽርሕ ንጽሕት። +++++ አንገርጋሪ +++++ ትርሢተ ወልድ መለኮት ወፍቅር ኀደረ ላዕሌሃ፤ ይቤላ ርግብየ ወይቤላ ሠናይትየ፥ ፀቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍሪሃ ፡፡ ወረብ ዘአመላለስ፦ ትርሢተ ወልድ መለኮት ወፍቅር ኀደረ ላዕሌሃ፤ ይቤላ ርግብየ ወይቤላ ወይቤላ ሠዓለም፡፡ +++++ ዘሰንበት +++++ በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት፤ እኅትየ መርዓት አዳም አጥባትኪ እምወይን፤ መዓዛ ዕፍረትኪ እምኩሉ አፈው፤ እትፌሳህ ወእትኃሰይ ብኪ ነፍቅር አጥባተኪ እምወይን፤ ርቱዕ አፍቅሮትኪ ኩለንታኪ ሰናይት አንተ እምንሴየ፤ አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ በላዕሌኪ ፃዒ እምሊባኖስ እኅትየ መርዓት፡፡ 💠💠💠 መልካም በዓል💠💠💠
185
20
"መንፈሳዊ ጥበብን የምትወድ ነፍስ ዘወትር እግዚአብሔርን ታመሰግናለች፡፡ ሰው ሆይ! ሰዎች ክፉ ነገር ሲያደርሱብህ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያን ጊዜም ክፉው መልካም ይኾንልሃል፡፡ "እንዴት?" ብለህ የጠየቅኸኝ እንደኾነም፦ "በደል የሚፈፅመው ክፉ ነገር የሚቀበለው ሳይኾን ክፉ ነገር የሚያደርሰው ሰው ነውና" ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እመልስልሃለሁ፡፡ ስለዚህ ዘወትር እግዚአብሔርን አመስግን፡፡ ብትታመምም እግዚአብሔርን አመስግን፤ ሀብት ንብረት ብታጣም አመስግን፤ በሐሰት ቢከሱህም አመስግን፡፡ እንደ ነገርኩህ ተጎጂዎቹ ክፉ ተቀባዮች ሳይኾኑ ክፉ አድራሾች ናቸውና፡፡"
87