cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የኖህ መርከብ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ

የ ኢ/ኦ/ተዋህዶ/ቤተክርስቲያን አስተምህሮ የጠበቁ የ አባቶች ምክር;ግጥም;ተከታታይ አምዶች;ልሳነ ግእዝ;ጥያቄናመልሶች የምናገኝበ ስለሆነ ቻናሉን ይቀላቀሉ። for any opinion @Abeln ይላኩ "ይህች ቤተክርስቲያን ክርስቶስን ከቶ አታውቀውም" በሉ ግድ የለም ለቃሉ ! ግን ድምጽ ቀንሱ ! የጌታን መከራ ሕማሙን አስባ ስግድት ላይ ናትና ልጆቿን ሰብስባ ግድ የለም አንቋሿት ግን አትረብሿት !!

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
1 646
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-57 أيام
-3830 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

"ድንግል ሆይ እኔ ግን ልጅሽን በማምለክ በባሕርይ አባቱም በአብ በባሕርይ ሕይወቱም በመንፈስ ቅዱስ አምኜ ደስ እሰኛለሁ ለሦስትነቱ አንድ ስግደት እየሰገድሁ እመካበታለሁ እንዲህ ስል፡፡  አምላኬ ነው አመሰግነዋለሁ ያባቶቼም አምላክ ነው አከብረዋለሁ አገነዋለሁ ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ፡፡ እግዚአብሔር ፀብ ክርክርን ይሰብራል፡፡ ስሙም እግዚአብሔር ነው፡፡ ደግሞ እንዲህእላለሁ (ዘፀአት ፲፭፣ ፪፣ ፫)  እንደ አምላካችን ያለ ታላቅ አምላክ ማነው፡፡ ይህንንም የመለኮት ሰይፍ ተቀብዬ የሰይጣንን ራሱን እቆርጠዋለሁ፡፡ ይህንንም የሃይማኖት በትር ተመርኩዤ የእባቡን (የዲያብሎስን) ራሱን እቀጠቅጠዋለሁ፡፡ የምስጋናውንም ጽዋ ከጽርሐ አርአያም ቀድቼ ከቤትሽ አፈሳለሁ፡፡ ከትንቢት ቃል ጋራ እንዲህ እላለሁ፡፡ ከሞት ደጅ ከፍ ከፍ የሚያደርገኝ በጽዮን ልጅ ደጅ ምስጋናውን ሁሉ እናገር ዘንድ፡፡ ዳግመኛም እንዲህ እላለሁ፡፡ በጽዮን ምስጋና ላንተ ይገባል በኢየሩሳሌም ጸሎት ላንተ ነው፡፡" (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ - አርጋኖን)
إظهار الكل...
የዘመናችን የእሾኽ አክሊል ከዛሬ 40 ዓመታት በፊት የሸዋ ክፍለ ሀገር ሊቀጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ (2ኛ) በዝዋይ ገዳም ለዲያቆናት እና ካህናት ሃይማኖት ከምግባር እየመረመሩ ክህነት ይሰጡ ነበር። ለሹመት ከቀረቡት መካከል አንደኛው በወጉ ያለተማረ በምግባርም ያልሰመረ አንድ እጩ አግኝተው "ዘንድሮ አልሾምህም። ለሚቀጥለው ዓመት በደምብ ተምረህ፣ በምግባርም ሰክነህ ስትመጣ ትሾማለህ" ብለው መለሱት። አብረውት የመጡት ወዳጅ ዘመዶቹ ተሰብስበው ብፁዕነታቸውን "እባክዎ ከነ ችግሩም ቢሆን ይሹሙልን። ወገኖቹም ይጣሉናል። እርሱ ካልተሾመ ቤተክርስቲያናችንም ትዘጋለች" ሲሉ በማስተዛዘን ልመና አቀረቡ። አቡነ ጎርጎርዮስ ግን "የወገኖቹን ቁጣ ፈርቼ በሃይማኖቱ ያለጸና በምግባሩ ያልቀናን ሰው ካህን እንዲሆን ሾሜ ቤተክርስቲያኒቱ ላይ የማይነቀል እሾኽ ከምተክልባት ለጊዜው ብትዘጋ ይሻላል። ወደፊት የተሻለ እና ለክህነት የተገባ ሰው አግኝተን ስንሾም ያኔ ይከፍታታል።" ብለው መለሷቸው። ዛሬ ላይ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ለሁለት ካልሰነጠቅናት ብለው ቁም ስቅሏን የሚያሳዩዋት ግለሰቦች በሃይማኖት ጽናታቸው፤ በምግባርም መቅናታቸው የተመሠከረላቸው መሆኑ ሳይረጋገጥ የሆነ ወገንን ለማስደሰት በይድረስ ይድረስ የተሾሙ እንደነበሩ  አሁን እሾኹ ደርሶ ሲወጋን ተረድተነዋል። ለቤተክርስቲያኒቱ የእሾኽ አክሊል ሆነው እየወጓትና እያደሟት ነውና! ያለፈ አልፏል! አሁንም ቢሆን ባለሥልጣናትን ለማስደሰት ወይንም የአጃቢዎቻቸውን ጩኸት በመፍራት እንኳንስ ጵጵስና ዲቁና ለማይገባቸው፤ ከእግዚአብ ልጅነታቸው ይልቅ የብሔረሰብ ልጅነታቸው ደርሶ ለሚንጣቸው ዘውገኞች የክህነት ሹመት መስጠት በክርስቶስ መቅደስ ጉልላት ላይ ሌላ ተጨማሪ መርዛማ እሾኽ አክሊል እንደመድፋት ይቆጠራል።
إظهار الكل...
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ፍቅርን እንደ ዓይን ብሌን ስንጠብቃት በእጅጉ የምትጠቅመንን ያህል ስንተዋት ደግሞ በእጅጉ ትጎዳናለች፡፡ በፍቅር እጦት የሚደርሰው ጉዳት በተወሰነ ነገር ብቻ ሳይሆን በነፍስም ሆነ በሥጋ፣ በምድርም ሆነ በሰማይ እጅግ በጣም የገዘፈና የሰፋ ነው፡፡  በሀገራችን የሆነውና እየሆነ ያለውም ይኸው ነው፡፡ ፍቅርን ባጣንባቸው ዓመታት ከየት ወዴት እንደደረስን ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚገነዘበው ነው፡፡ ያተረፍነው ነገርም ምን እንደሆነ የምናውቀው ነው፡፡  ይሁንና የፍቅር እጦት ምን ያህል እንደጎዳን ራሳችን ተገንዝበን ወደ ሰላሙ መንገድ መመለሳችን የተሻለ አማራጭ መሆኑን ሳንመሰክር አናልፍም፡፡ የተጀመረው የፍቅርና የሰላም ጉዞም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ልባዊ ምኞታችንና ጸሎታችን ነው፡፡ ይህንን ሰላም እንዲመጣ ያደረጉ ወገኖችም ሁሉንም ሳናመሰግን አናልፍም፡፡ ምክንያቱም በሰዎች መካከል ፍቅርንና ሰላምን የሚያደርጉ የእግዚአብሔር ልጆች  እንደሚባሉ ጌታ እንደ አስተማረን ብፅዕና ይገባቸዋልና ነው፡፡  (ማቴ.፭፥፱) የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! የፍጹም ፍቅር መገኛ የሆነው ቅዱስ ወንጌል የሚያስተምረው ፍቅር ራስን ማፍቀር ወይም መውደድ ሳይሆን ራስን መጥላት ባልንጀራን ግን መውደድ እንደሆነ ነው፡፡ “ወንጌላዊ-ፍቅር ፍጹም ነው” የሚያሰኘውም ቅሉ ይህ ነው፡፡  ለሁለት ሺህ ዘመናት ያህል በቅዱስ ወንጌል አስተምህሮ ላይ የተገነባው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ባህልም ይህን ፍቅር ጠብቆ የሚጓዝ ነው፡፡  ይህም በመሆኑ የኢትዮጵያ አበው መነኮሳት ከነበራቸው ፍቅርና ትሕትና የተነሣ፣ የሹመት ሽሚያ አያውቁም ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር ትልቁን ሥልጣን ይቅርና የአንድ ገዳም መሪ ለመሆንም በእግር ብረት ታስረው በግድ ካልሆነ በቀር እሺ ብለው በፈቃደኝነት ሹመትን አይቀበሉም ነበር፡፡ ራሱን በራሱ መሾም ወይም እኔን ሹሙኝ ብሎ መናገርና የሌላን ድጋፍ መጠየቅ ለኢትዮጵያውያን መነኮሳት ጭራሽ ነውርና ጸያፍም ነበር፡፡  ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ ለሦስት ሺህ ዘመናት የዘለቀው ሃይማኖታችን ምንም ዓይነት መለያየት ሳያጋጥመው አንድ ሆኖ ሊዘልቅ የቻለው ያም በመሆኑ ነው፡፡ ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ጠንካራ አንድነት ለሕዝቡም በመትረፉ የሀገሪቱን አንድነትና ነጻነት አስጠብቆ እስከ ዘመናችን ሊደርስ ችሎአል፡፡ በዚህም ቤተ ክርስቲያናችን የሕዝብንና የሀገርን አንድነትና ነጻነት ለማስጠበቅ ያደረገችውና የምታደርገው ጥረት ሊያስመሰግናት እንጂ ሊያስወቅሳት አይገባም፡፡  የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ከቅርብ ቀናት ወዲህ በቤተ ክርስቲያናችን ተከሥስቶ የነበረውን ሕጋዊ ያልሆነ ድርጊት የቤተ ክርስቲያናችንን ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና ባሕላዊ መርሕን የናደ፣ እንደዚሁም በኢትዮጵያ ይቅርና በዓለም ታሪክ ተደርጎ የማያውቅ ድርጊት እንደሆነ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ስትገልጽ ቆይታለች፡፡ ይህንን የቤተ ክርስቲያን ድምፅ በመስማትና በመቀበል ሕዝበ ክርስቲያንና ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለእግዚአብሔር ባቀረቡት ኀዘንና ጸሎት እንደዚሁም ባደረጉት መጠነ ሰፊና ዙርያ መለስ የሆነ የድጋፍ ርብርብ ስሕተቱ ሊታረም ችሏል፡፡  ለተገኘው መንፈሳዊ ውጤትም ጠቅላይ ሚንስትርና መንግሥታቸውን፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነትና ሉዓላዊነት እንዲከበር ከፍተኛ መሥዋዕትነት ለከፈለው መላው ሕዝበ ክርስቲያን እንዲሁም ይህ ስሕተት እንዲታረም ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን ተሰልፈው ድምፃቸውን ላሰሙ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በቤተ ክርስቲያናችን ስም ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርብላቸዋለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ግልጽ ማድረግ የምንፈልገው ከቤተ ክርስቲያናችን ዶግማ፣ ቀኖና እና ሥርዓት መከበር እንደዚሁም ከሉዓላዊ አንድነቷ መጠበቅ በመለስ ያለው ጥያቄ ለማስናገድ ቤተ ክርስቲያናችን ዝግጁ መሆኗን ነው፡፡  ቤተ ክርስቲያናችን ሕዝቦች በቋንቋቸው የመማር፣ የማስተማርና የማምለክ እንዲሁም የመተዳደር መብትን ካሁን በፊትም፣ አሁንም፣ ካሁን በኋላም የምትነፍግበት መሠረት እንደሌለም ሁሉም ሊያውቀው ይገባል፡፡  ይህም በመሆኑ በቋንቋ የመጠቀም መብት በሕገ ቤተ ክርስቲያናችን ምዕራፍ ፪ አንቀጽ ፭ ከቁጥር ፩ እስከ ፫ ባለው አንቀጽ በሚገባ ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ስለሆነም በቋንቋ የመጠቀም ጥያቄ በሕግ ደረጃ ተመልሶ በተግባር እየተሠራበት የሚገኝ መሆኑን ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡  የተወዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ዛሬ ታላቁን ጾም በፍቅር ሆነን የምንጾምበት ወቅት ነው፡፡ ሁላችንም እንደምናውቀው ጾም ማለት ሥጋዊ ፈቃድን በመግታት ከእግዚአብሔር ጋር ጥብቅ ግንኙነት ለማድረግ የሚካሄድ መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው፡፡  በጌታችን ጾም በተግባር እንዳየነው ጾም ማለት ዲያብሎስ የሚሸነፍበት በአንጻሩ ደግሞ የእግዚአብሔር ሕዝብ አሸናፊዎች የሚሆኑበት ኃይል ነው፡፡  ስለሆነም ጾም የተጋድሎና የሙዓት ሜዳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ የምንታገለውም ልብሰ ሥጋ ሰውን ሳይሆን ረቂቅ ፍጡር የሆነው ሰይጣን በሰው አድሮ የሚነዛውን አጥፊ ሐሳቡንና ድርጊቱን ነው፡፡ ከዚህም ጋር ሰውነታችን ለዚህ ክፉ መንፈስ ታዛዥ እንዲሆን የሚገፋፉ ጥሉላት መባልዕትን መተው፣ ኃይለ ሥጋን መቈጣጠር፣ ኃይለ መንፈስን ደግሞ ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡ በጾም ወቅት የተራቡትን ማጉረስ፣ የታረዙትን ማልበስ፣ የተበደሉትን መካስ፣ ፍትሕና ርትዕ በማኅበረ ሰብ ውስጥ ማንገሥ ያስፈልጋል፡፡ በጾም ወቅት ኅሊናችን ማሰላሰል ያለበት ሰው ምን አለ? ወይም ምን አደረገ? በሚለው ሳይሆን እግዚአብሔር በፊቱ ምን ዓይነት ሰው እንድንሆንለት ይፈልጋል? በሚለው ላይ ነው፡፡ ስለዚህ ጾማችን በዚህ መንፈስ የተቃኘ ፍቅረ፣ እግዚአብሔርንና ፍቅረ ቢጽን ማእከል ያደረገ፣ መጠራጠርንና አለመተመማንን ያስቀረ፣ የተለያዩትን ያቀራረበ፣ የተሳሳቱትን ያረመ በአንጻሩ ደግሞ ሁላችንን በሰላምና በፍቅር አንድ አድርጎ ያስተሳሰረ ይሆን ዘንድ በዚህ መንፈስ ተነቃቅተን እንድንጾመው አባታዊ ጥሪያችንን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናስተላልፋለን፡፡  በመጨረሻም በሀገራችን እየታየ ያለው የሰላም ጭላንጭልና ችግሮችን በውይይት የመፍታት ዝንባሌ ለሁለንተና ልማታችንና ለዕድገታችን እንደዚሁም ለተሟላ አንድነታችን ጠቃሚነቱ የጎላ ስለሆነ እግዚአብሔር ለዘለቄታው እንዲያሳካልን ከልብ እንድናዝንና ወደ አምላካችን በተመሥጦ እንድንጸልይ በአጽንዖት በማሳሰብ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡  መልካም የጾም ወራት ያድርግልን! እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር! አሜን አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
إظهار الكل...
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ የዐቢይ ጾምን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት መልእክት! • በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት እንዲሁም ኢትዮጵውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ! እንደ ስሑትና ደካማ ሰብአዊ ባሕርያችን ሳይሆን እንደ አባታዊ ቸርነቱ ሁል ጊዜ በምሕረቱ የሚጐበኘን አምላካችን እግዚአብሔር እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዐቢይ ጾም አደረሰን፤ አደረሳችሁ! • “ንጹም ጾመ፣ ወናፍቅር ቢጸነ፣ እስመ ከማሁ አዘዘነ፤ ጾምን እንጹም፤ ባልንጀራችንንም እንውደድ፣ እንዲህ አዞናልና” (ቅዱስ ያሬድ) እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ስንኖር እንድናደርገው ያዘዘን ዐቢይ ነገር ቢኖር ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ እየመገበ የሚገኘው በፍቅር ነው፡፡ እኛንም ከፍዳ ኃጢአት ያዳነን በፍቅር ነው፤ ሕይወታችንና ንብረታችን ተጠብቆ የሚኖረው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡  ግላዊና ማኅበራዊ ኑሮአችን እንዲሁም ሃይማኖታዊ አምልኮአችንና የተግባር እንቅስቃሴአችን በሙሉ ውጤታማ ሊሆን የሚችለው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡  በፍቅር ውስጥ በረከት እንጂ ጉድለት የለም፤ በፍቅር ውስጥ ጤና እንጂ በሽታ የለም፤ በፍቅር ውስጥ ጽድቅ እንጂ ኃጢአት የለም፤ በፍቅር ውስጥ እግዚአብሔር እንጂ ዲያብሎስ የለም፡፡ ይህም በመሆኑ ቅዱስ መጸሐፍ ፍቅርን ‹‹የሁሉም ነገር ማሰሪያ ነች›› በማለት ይገልጻታል፡፡ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከሁሉም የምትበልጠው ታላቋ ትእዛዝ ‹‹ፍቅር›› እንደሆነች ከመግለጹም በላይ ኦሪትና ነቢያት ሁሉ በእርሷ እንደሚጠቃለሉ አስተምሮናል፡፡
إظهار الكل...
አጫጭር መልሶች ለአንዳንድ የቤተክርስቲያን ጥያቄዎች 1 / ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ምን ማለት ነው? ለምንስ እንዲህ ሆነ ወይም ለምን ይባላል? 👇👇👇 ይህ ማለት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ እና ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት የሆነው አባት በተደራቢነት የአክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የደብረሊባኖስ ገዳም እጨጌ (አበ ምኔት) ነው ማለት ነው። ይህ የሆነበትን ዝርዝር ምክንያት በየተወሰነበት ጊዜ ሒዶ ዝርዝር ጉዳዩን ማጥናት ይቻላል። በአጭሩ ግን ለኢትዮጵያ ከእስክንድርያ መጀመሪያ ተሹሞ የመጣው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሰላማ በወቅቱ የሀገሪቱ መናገሻ በነበረችው በአክሱም ሆኖ መላ ኢትዮጵያን ስላገለገለ በኢትዮጵያ ፓትርያርክ የሚሆነው አባት የአክሱም ሊቀ ጳጳስነት ወንበሩን እንዲይዝ ስለተፈለገ ነው ። አቡነ ተክለ ሃይማኖትም እርሳቸው ደብረ ሊባኖስን መሥርተው ከነበሩበት ጊዜ አንሥተው የእርሳቸው ልጆች (እጨጌዎች) ቤተ ክርስቲያንን ወክለው ከየዘምኑ ነገሥታት ጋር ይገናኙ ስለነበረ እና ርእሰ ሊቃነ ጵጵስናው ለኢትዮጵያ ሲፈቀድ እስከዚያ ድረስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ቤተ ክህነት ወክሎ ከመንግሥት ጋር ይሠራ የነበረው እጨጌው በርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ እንዲተካ እና እጨጌው ራሳቸው ይህን አዲስ ሐላፊነት እንዲረከቡ ስለተደረገ ነው ።  2 / የኢትዮጵያ ፓትርያርክ መንበሩ መንበረ ተክለ ሃይማኖት ለምን ተባለ? 👇👇👇 ከላይ ለማብራራት እንደሞከርኩት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የፕትርክና መንበሩ መነሻአ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ እንጂ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አይደሉም። የእርሳቸው ሊሆን ይችል የነበረው እርሳቸው በፓትርያርክነት አገልግለው አሁን እንደሚደረገው ጳጳሳትን ሾመው ቢያልፉ እና እርሳቸው ሲያልፉ የነበሩት ሊቃነ ጳጳሳት በእርሳቸው ፋንታ አንዱን ከመካከላቸው ፓትርያርክ አድርገው ቢመርጡ እና እንዲህ እያለ ሳይቋረጥ እስካሁን ደርሶ ቢሆን ኖሮ ፓትርያርክ ዘመንበረ ተከለ ሃይማኖት ይባል ነበር ። አሁን እየተባለ ያለው ግን “ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፣ ... ወእጨጌ ዘመነበረ ተከለ ሃይማኖት” ነው። ይህም ማለት መንበረ ተክለ ሃይማኖት የእጨጌነት እንጂ የፓትርያርክነት አይደለም ማለት ነው። ለፕትርክናችን ስም መጠቀስ ቢችል ኖሮ ሊባል ይሚችለው “ዘመንበረ ማርቆስ” ነበረ። ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ስድስት ኪሎ ግቢ ውስጥ ያለውን ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እንዱ ያስተከሉበት ምክንያቱም ይህንን ሀሳብ በመያዝም ጭምር እንደነበር ይነገራል ። ነገር ግን የግብጽ ቤተ ክርስቲያን “ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ” የሚለውን ስትፈቅድ ዘመንበረ ማርቆስ የሚለውን መጠቀም ግብፅን የተቀማች ያስመስላል ብለው ነው መሰል ይህንን ሀሳብ ስለተቃወሙ እና የእኛም አባቶች ዋናው ስሙ ሳይሆን ተግባሩ ነው ብለው ይህ እንዳይጠቀስ በሰነድ በተፈረመ መንገድ ስለተስማሙ ያን አክብረን በስያሜ አንጠቀመውም እንጂ የፕትርክና መንበራችን የቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ነው ። 3 / መንበረ ሰላማ የሚባል አለ ወይ? 👇👇👇 መንበረ ሰላማ የሚባል መንበር የለም ። ሊኖርም አይችልም ። ከላይ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት እንዳስረዳሁት ይህም ተመሳሳይ ነው ። መንበረ ሰላማ ሊባል ይችል የነበረው አባ ሰላማ ጳጳሳትን ሾመው እርሳቸው ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሆነው ቢሆን ኖሮ እና እርሳቸው ካለፉ በኋላ እርሳቸው የሾሟቸው በእርሳቸው ምትክ ሌላ ርእሰ ሊቀ ጳጳስ መርጠው ቀጥለው ቢሆንና ያ መተካካትም በዚያው መንገድ ሳይቋረጥ እስካሁን ቀጥሎ ቢሆን ኖሮ መንበረ ሰላማ ማለት ይቻል ነበር ። ነገር ግን እርሳቸው ማንንም አልሾሙም፣ እርሳቸውም ካለፉ በኋላ እንደገና ከግብጽ ተሾሞ መጣ እንጂ ከእርሳቸው የቀጠለ እንኳን የፕትርክና የጵጵስናም ሠንሠለት ስለሌለ መንበረ ሰላማ የሚባል የለም ፤ ሊኖርም አይችልም ።
إظهار الكل...
ይህ ክፉ ነገር እንዴት አገኘን!!! “ከነነዌ ሰዎች በላይ የከፉ ማን ነበር? ከነነዌ ሰዎች በላይ ግራውንና ቀኙን የማያውቅ ማን ነበር? ምንም እንኳን ድንጋይ ጠርበው ዕንጨት ቈርጠው የሚያመልኩ አሕዛብ ቢኾኑም፣ ምንም እንኳን ስለ ሀልወተ እግዚአብሔር ምንም  ባያውቁም ምንም እንኳን ስለ ፈሪሐ እግዚአብሔር ከማንም ነቢይ ባይማሩም ዮናስ መጥቶ አንዲት አረፍተ ነገር ስለ ነገራቸው ብቻ በሦስት ቀን ውስጥ ኹሉንም ተዉት፡፡ ዘማዊው ንጹሕ ኾነ፡፡ ስግብግቡ ለጋሽ ኾነ፡፡ ቁጡውና ተሳዳቢው መራቂ ኾነ፡፡ ሰነፉ ሰው ለጦም ለጸሎት ብርቱ ኾነ፡፡ ከክፋታቸውም አንዱን ወይም ኹለቱን ብቻ የተዉት አይደሉም ኹሉንም ተዉት እንጂ፡፡ ምንም እንኳን የበደላቸው ጽዋ ሞልቶ መንበረ ጸባዖትን ለቁጣ የቀሰቀሰ የነበረ ቢኾንም ተመለሱ፡፡ ሲመለሱም እግዚአብሔር በቁጣ ሳይኾን በምሕረት ዓይን አያቸው፡፡ ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጸተ፡፡ ተወዳጆች ሆይ! የነነዌ ሰዎች ምንም አሕዛብ ቢኾኑም በሦስት ቀን ውስጥ ብቻ እንዲኽ ማራኪየኾነ ንስሐን ከገቡ፥ እጅግ ብዙ ዘመናትን ተምረን ያልተለወጥን እኛው ክርስቲያኖች እንደምን ይፈረድብን ይኾን?”
إظهار الكل...
“ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት” ያዕ 1፥2-3። "…ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ። ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል። 1ኛ ቆሮ 10፥ 12-13። "…በዘራችሁና በሃይማኖታችሁ ምክንያት እስር መንገላታት ቢገጥማችሁ ጽኑ። ምክንያቱም “በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።” ያዕ 1፥12 ደግሞም “ማንም ሲፈተን፦ በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል፤ እግዚአብሔር በክፉ አይፈተንምና፤ እርሱ ራሱስ ማንንም አይፈትንም።” ያዕ 1፥13። "…ሁሉ ነገር በትእግስት ይሁን “በለሱን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል፥ ጌታውንም የሚጠብቅ ይከብራል።” ምሳ 27፥18።
إظهار الكل...
ምንተ ንግበር!!! ከሁሉ በላይ በምትሆነው አንዲት እና ኩላዊት ቤተክርስቲያን አምናለሁ!!!!. 1.ነገር ግን ለዚህ ሁሉ መሆነ ምክንያት ምንድነው? 2.በዘመናት የ ፖለቲካ ለውጥ ውስጥ ሁልጊዜ  ቤተክርስቲያንን ለምን ያናውጣሉ? 3.ለምንስ ይህ ሆነ በእሑኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ሚዛናዊ እና ቤተክርስቲያንን ከመከፋፈል የታደገ ውሳኔ ነው የወሰነው? 4.የተወሰኑት ውሳኔዎችን ማን ይሆን የሚያስፈጽመው? 5.እነዚህ 3ሊቃነ ጳጳሳት ለምን ይሆን ይህን ተግባር የፈጸሙት? ቤተክርስቲያንን አሸናፊ የሚያደርግ ተመሳሳይ መሰል ችግሮች እዳይፈጠሩ ዘላቂ እና ዘመኑን የሚዋጅ ጠንካራ የሆነ ሁሉን የሚያስማማ ውሳኔ የውሰን ዘንድ ይህም እንዲሆነ እመኛለሁ። እስከዛው ግን እንደ ታናሽነቴ ሁሉንም አባቶች በእኩል እናይ ዘንድ አለምናለው ይልቁንም ሐዋርያት በሰሯት ርትዕት ቅድስት እና ንጽሕት በሆነች የ ሊቃነ ጳጳሳት,ኤጲስ ቆጶሳት,ቀሳውት ወዲያቆናት...መፍለቂያ እናም የክርስቶስ ሙሽራ በሆነች ቤተክርስቲያን አምነን ጸንተ እንኑር። ባለቤቱ ያቃለለው...ነውና ተረቱ ይህ ግዜ አልፎ ቤተክርስቲያን ስታሸንፍ እዳናፍር አባቶቻችን አንሳደብ,አንሳለቅባቸው። የቤተክርስቲያን ምርጥ አገልጋይ መሆን ባንችል እንኳን ችግር ግን አንሑንባት። ከቻልን ይህ ነገር ለምን ሆነ,እንዴት ሆነ ለቀጣይስ እንዳይሆን ምን መደረግ አለበት ብለን እናጥና,እንማከር,እንወያይ,እናንብብ,እንጻፍ የመፍትሔ ሰው እንሁን። "ንበሩ በኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ጽድቅ ዘአርያም"
إظهار الكل...
⁉️ #ፓትርያርኩን_የደፈራቸው_ማን_ነው?⁉️ የኣባ ሳዊሮስን ስድነት ተቃውመህ "ከቅዱስ ኣባታችን ጋር እቆማለሁ" ያልከው ወዳጄ፣ ፓትርያርኩን የደፈራቸው አባ ሳዊሮስ ሳይሆኑ የአሁኖቹ "ተደፈርን" ባይ ጳጳሳት እንደሆኑ አታይምን? ትናንትና ቅዱስ ኣባታችንን የቁም እሥረኛ አድርገው ሲያበቁ፣ የቅዱስ አባታችንን ሥልጣን በመጋፋት እሳቸው ሳያውቁት ስንት ዝውውርና ስንት ሹመት ኣልተፈፀመም ወይ? በተለይም ስለ ትግራይ ሕዝብ መከራ እንዳይተነፍሱ፣ በራሳቸው ሚድያ በEOTC Tv እንኳን እንዳይነገሩ ድምፃቸው ያፈኑ እነዚህ ጳጳዳት አይደሉም ወይ? ታድያ ቤ/ክ የተሰደበችው፣ ፓትርያርካችን የተደፈሩት አሁን ነው? ቅዱስ ኣባታችን "አቡነ ጁንታ" ሲባሉ፣ ፓትርያርኩ ድምፃቸው ሲያሰሙ እንኳን "የግላቸው እንጂ ሲኖዶስን ኣይወክልን" ሲባሉ ሲኖዶሱ ቀኖና ቤ/ክ ለመጠበቅ፣ ክብራቸውን ለማስከበር ምን አደረገ? መዋቅር ላይ ያሉ ሰዎች ቅዱስ ኣባታችንን "ይሄ ሰውዬ አቡነ ወያኔ ናቸው" ብለው በግልፅ ሲሳደቡ ቤተ ክህነቱ ዝምታ ኣልመረጠምን? ታድያ የፓትርያርኩን ክብር የተነካው ዛሬ ይመስል "ከፓትርያርኩ ጎን እቆማለሁ" የምትለው በየትኛው ሞራልህ ነው? አስተውል:- "አባታችን ሲበደሉ ዝም ብለሃልና ዛሬም ሲበደሉ ዝም በል" እያልኩህ ኣይደለም። ስህተት በስህተት ኣይታረምምና። ነገር ግን ዛሬ የተወለደው የነ አባ ሳዊሮስ ሥርዓት-አልበኝነት፣ እነ አባ ዮሴፍ የጠነሰሱት፣ እነ ኣባ ፋኑኤል የወጠኑት አይደለም ወይ? የያኔው የአባታችን ግፍ፣ የእኛም ዝምታ ለዚህ ኣብቅቶናል። ትናንትና ቅዱስ አባታችንን አውርደህ ሌላ እንደራሴ ልትሾም ስትዶልት የነበርክ ሰው፣ ዛሬ ላይ ፕትርክናቸው የሚጋፋ ነገር ሲመጣ ከጎናቸው ለመቆም እንዴት ሞራል አገኘህ? ቅዱስ ፓትርያርኩ "ታቦት ሰርቀው ሲወጡ ተያዙ" ብለህ ያልክ ሰው፣ አሁን አባ ሳዊሮስን ለመቃወም እንዴት ቻልክ? የቅዱስ አባታችን መከራ፣ ግፍና ዕንባ የሚቀበል ጌታ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያን ቤ/ክ ላይ የቁጣ በትሩን የሚያነሳበት ጊዜ ደርሷል! እኛ ግን ትናንትም፣ ዛሬም ነገም ከፓትርያርኩ ጎን እንቆማለን‼️
إظهار الكل...
ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ አምላክን!!!
إظهار الكل...