cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

TIKVAH-ETHIOPIA

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Show more
Advertising posts
1 357 177
Subscribers
+66024 hours
+3 8857 days
+17 06330 days
Posts Archive
የሀገራችንን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ የሚቃኝ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሀገር አቀፍ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፣ የተከበሩ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንዲሁም የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በተገኙበት በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ተካሄደ! በመርሃ ግብሩ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ጉዞ፣ የተገኙ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጋር በተደረገ የመድረክ ላይ ወግ ፣ ዘርፉን ከሚመሩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገ የፖነል ውይይት ተዳሰዋል። በውይይቱ ወቅት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዲጂታል ኢትዮጵያ ግንባታ ረገድ ሀገራችን መልካም ጅማሮዎች እና ወሳኝ ምዕራፎች ላይ የምትገኝ መሆኗን አንስተው በመሰረተ ልማት፣ በኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሁም በዲጂታል ፋይናንስ የተሰሩት ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ አክለውም፣ መንግስት ለዲጂታል ጉዞ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆኑን በመግለጽ የግሉ ዘርፍ በበኩሉ በዲጂታል ሥነምህዳሩ የተፈጠረለትን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በዘርፉ ላይ የሚጠበቅበትን ሚና መጫወት እንደሚገባው አጽንዖት ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምናደርገውን ጉዞ በይበልጥ ለማፋጠን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የሚመራ ሃገራዊ ካውንስል እንዲቋቋም አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #DigitalEconomy #MINT #PMO #EthiopianCommunicationAuthority #GSMA #ITU #SmartAfrica #HOPR #HOF
Show all...
😡 254 152🤔 8🥰 7👏 5🕊 3😭 2
Photo unavailableShow in Telegram
#አቢሲንያ_ባንክ ቴሌብርን ጨምሮ ከተለያዩ ባንኮች ገንዘብ ወደ አፖሎ ማስተላለፍና ማስቀመጥ ይችላሉ። መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ። ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US ለአፕል ስልኮች  https://apps.apple.com/us/app/apollo-digital/id1601224628 #Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
Show all...
40😡 16🕊 1
#2 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት ከባንኩ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ወስደው እስካሁን ያለመለሱ የ565 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ከአካውንት ቁጥራቸው ጋር ይፋ አደርጓል። ባንኩ ግለሰቦቹ ገንዘቡን ካልመለሱ በቀጣይ በህግ እንደሚጠይቃቸው አስጠንቅቋል። @tikvahethiopia
Show all...
😡 701👏 383😱 173 153🙏 69😭 68🤔 50😢 46🕊 35🥰 30
#1 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት ከባንኩ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ወስደው እስካሁን ያለመለሱ ደንበኞቹን ስም ዝርዝር፣ የአካውንት ቁጥራቸውን ይፋ አደርጓል። @tikvahethiopia
Show all...
😱 408👏 220😡 141 87🤔 33😭 25😢 20🥰 19🕊 15🙏 7
" ... ብዙዎቹ ወላጆቻቸው እንዲከፍሉ ተደርጓል " - ንግድ ባንክ ዓርብ መጋቢት 6/2016 ዓ/ም ለሊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የሲስተም ችግር አጋጥሞት በነበረበት ወቅት ገንዘብ ከኤቲኤሞች ሲያወጡ እንዲሁም ሲያዘዋውሩ (ግብይት ሲፈፅሙ) ከነበሩት መካከል 57 በመቶዎቹ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደሆኑ ተነግሯል። ባንኩ ፥ በ25,761 ደንበኞች ተወስዷል ካለው ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ 622 ሚሊዮን ያህሉን እስካሁን ተመላሽ መደረጉን ገልጿል። በቀጣይም የሚመለስም እንዳለ ጠቁሟል። ብር ከወሰዱት እና ካዘዋወሩ / ግብይት ከፈፀሙ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው። አሁንም በህገወጥ መንገድ ገንዘብ ከወሰዱት መካከል 567ቱ ብሩን እንዳልመለሱ እነዚህም የወሰዱት የገንዘብ መጠንም 9.8 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ተመላክቷል። በዕለቱ መጀመሪያ ገንዘብ #በኤቲኤም (ATM) አውጥተው የሄዱ ቡድኖች በመጠጥ ቤቶች እና ለሌሎች ጥፋቶች ላይ ማዋላቸው ተመላክቷል። በእንዲህ ያለ መልኩ የወጣ ገንዘብ ለመመለስ አስቸጋሪ ቢሆንም ብዙዎቹ ግን ወላጆቻቸው እንዲከፍሉ ተደርጓል። መረጃ ስላለ ለወላጆቻቸው እየተደወለ " ልጃችሁ እንዲህ አድርገዋል " እየተባሉ መክፈላቸው ተመላክቷል። እስከ ባለፈው ቅዳሜ ድረስ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ገንዘብ ያልመለሱ ደንበኞች የስም ዝርዝራቸው በየዲስትሪክቱ ከትላንት ምሽት ጀምሮ መለጠፍ ተጀምሯል ፣ ከዛሬ ጀምሮ ደግሞ በማህበራዊ ሚዲያ ስማቸው ይሰራጫል ተብሏል። እስካሁን በአንድ ሰው ተወስዶ ያልተመለሰው ከፍተኛ ገንዘብ 304 ሺህ ብር መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሳውቋል። @tikvahethiopia
Show all...
😡 831👏 197 121😢 39😱 35🕊 27😭 26🤔 25🥰 9🙏 8
" ሁለት አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል " - የአካባቢው ምዕመናን የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገ/ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሁለት አገልጋዮች #ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው መገደላቸውን የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለጸ። በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በዶዶላ የደብረ  ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው ጋር ለጊዜው " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት መገደላቸው ተነግሯል። የቴሌቪዥን ጣቢያው ፤ ግድያው የተፈፀመው ትናንት መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ገደማ መሆኑን የአካባቢው ምዕመናን እንደነገሩት ገልጿል። በተፈጸመው በዚግ ግድያ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን  አገልጋይ የሆኑት አንድ መሪጌታና ዲያቆንን ጨምሮ 5 የቤተሰብ አባሎቻቸው በጥይት ተደብድበው መገደላቸው ተገልጿል። የቴሌቪዥን ጣቢያው ፥ በዶዶላ ከተማ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም በርካታ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን አስታውሷል። @tikvahethiopia
Show all...
😭 3075😡 376😢 136 97🕊 43🙏 29😱 24👏 13🥰 11🤔 2
#DigitalEthiopia ዛሬ " የዲጂታል ኢትዮጵያ " የግምገማ መድረክ በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል። ጠ/ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ የፌደራል እንዲሁም የክልል ከፍተኛ አመራሮች እና የዘርፉ ተዋናዮች በመድረኩ ተሳታፊ ነበሩ። የ " ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 " ስትራቴጂ በዋናነት የዲጂታል መሰረተ ልማት በመገንባት እና በማስፋት የአገሪቱን ምጣኔ ኃብታዊ እድገት ማፋጠንን ዓላማ ያደረገ ሲሆን በአምስት ዓመታት ውስጥ ለመተግበር የታቀደ ነው። ዛሬ ላይ የስትራቴጂውን የ4 አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል። - ዲጂታል ሊትረሲን ለማስፋት፤ - የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎቱን የማሳደግ - የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፤ - የዲጂታል ክፍያ ሥርዓትና የሳይበር ጥበቃ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ገለጻ ተደርጎባቸዋል። በዚህ መድረክ በቅርቡ በንግድ ባንክ ላይ ያጋጠመው ጉዳይ በስፋት እንደማሳያ ሲቀርብ ነበር። ይህን ተከትሎ ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) የብሔራዊ ባንክ ገዢው አቶ ማሞ ምህረቱ አስተያየት ሰጥተው ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ? ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ፥ " በሳይበር ጥቃት በ2022 በዓለም ላይ 9 ትሪሊዮን ዶላር በጠላፊዎች ተመዝብሯል" ብለዋል። " ይህ ያጋጠመው ችግር ሰዎች አቅደው አምሯቸውን ተጠቅመው ለማለት ያስቸግራል፤ ከውስጥ ያሉ ሰዎች የፈጠሩት ችግር ነው " ሲሉ ገልጸዋል። " ይሄ ማለት [የሳይበር ጥቃት] አይከሰትም ግን ማለት አይደለም። በሺዎች የሚቆጠሩ አታኮች በየቀኑ ተቋሞቻችን ላይ ይፈጸማሉ፤ ኢንሳ ብትመጡ ይሄንን ትመለከታላችሁ " ብለዋል። የብሔራዊ ባንክ ገዢው ምን አሉ? አቶ ማሞ ምህረቱ " የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ችግር በውስጥ ሰዎች የተፈጠረ ነው [ Human Error] ነው " ብለዋል። " በዚሁ አጋጣሚ የፋይናንስ ሥርዓቱ ግልጽ ነው። ምን አይነት ገንዘብ የት እንደተላከ ከየት እንደወጣ የት እንደገባ ይታወቃል። በእንደዚህ አይነት ስህተቶች የሚጠፋ ገንዘብ አይኖርም " ሲሉ ተደምጠዋል። " አሁን ላይ 80 በመቶ የወጣው ገንዘብ ተመላሽ ተደርጋል " ብለዋል። ብሔራዊ ባንክ የዚህን ክስተት ሙሉ የምርመራ ውጤት በሳምንት ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ገልጸዋል። #AddisAbabaTikvahFamily @tikvahethiopia
Show all...
😡 455 223👏 22🙏 19😭 12🥰 9🕊 5😱 4🤔 2😢 2
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምን አለ ? " ... አንድ ሰው ያወጣው ትልቁ ገንዘብ 324 ሺህ ብር ነው ፤ 567 ደንበኞች ጠፍተዋል፤ የጠፉት ደንበኞች 9.8 ሚሊዮን ብር ነው ያወጡት " - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህም መግለጫቸው ባንኩ አጋጥሞት ከነበረው ችግር ጋር በተያያዘ እስካሁን ስለደረሰበት ደረጃ አብራርተዋል። ምን አሉ ? - ችግሩ የት ጋር ነው  ያጋጠመው ? የሚለው ላይ በባለሙያ ጥናት እየተደረገ ነው ገና አላለቀም። - አርብ መጋቢት 6 በተፈጠረው የሲስተም ችግር ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ተወስዶበት እንደነበርና 622 ሚሊዮን ያህሉን ወደ ባንኩ ተመላሽ ተደርጓል። - ቀሪ 567 ግለሰቦች የወሰዱትን 9.8 ሚሊዮን ብር ማግኘት አልተቻለም። - መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ምሽት ላይ ከ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ 8: 45 ድረስ ባለዉ ጊዜ ነው 25 ሺህ 761 ደንበኞች ብር 801.4 ሚሊዮን ነው የወሰዱት። - ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በሂደቱ ዉስጥ የተሳተፉ 15 ሺህ ያህል የሂሳብ ቁጥሮች ተገኝተዋል።   - የሲስተም ችግር በነበረበት በወቅት 25 ሺህ 761 ደንበኞች ግብይት ፈጽመዋል። በዚሁ ሰዓት ችግር ያለበት 238 ሺ 293 ጊዜ ግብይት ተፈጽሟል። አንድ ደንበኛ በአማካይ ከ9 ጊዜ በላይ ግብይት ፈፅሟል። - በእለቱ አንድ ወይም ሁለት ግብይት የፈጸሙ ደንበኞች ጥርጣሬ ውስጥ አልገቡም። ያለ አግባብ የተወሰደ ገንዘብ ከሂሳባቸው ተቀናሽ ተደርጎ እንደሚመለስ ተደርጓል።  በአካውንታቸው ላይ በቂ ገንዘብ ከነበራቸው 10 ሺህ ደንበኞች ላይ 44 ሚሊየን ብር ተመላሽ ተደርጓል። - ቀሪዶቹ 15 ሺህ 8 ደንበኞች 207 ሺህ ግብይት ፈጽመዋል። እያንዳንዱ በዚያ ሌሊት በአማካይ 14 ጊዜ ግብይት ፈፅሟል። - ሂሳባቸው ላይ ካለው ብር ወስደው ከነበሩ 15 ሺህ 8 ደንበኞች መካከል እስከ ትናንት ማታ ድረስ 372 ሚሊየን ብር ድረስ ተመላሽ ተደርጓል። ከእነዚህ ውስጥ 9 ሺህ 281 ሰዎች ሙሉ በሙሉ ያለባቸውን መክፈላቸውን 5 ሸህ 160 በከፊል መልሰው ቀሪውን ለመክፈል ቃል ገብተዋል። - እስካሁን በድምሩ ሊጠፋ ከነበረው 800 ሚሊየን ብር ውስጥ 623 ሚሊየን ብር ተሰብስቧል። ቀሪውን የማስመለስ እና የማፈላለግ ስራ እየተከናወነ ነው። - በህገ ወጥ መንገድ ገንዘብ ከወሰዱት መካከል 567 ደንበኞች ጠፍተዋል። ሙሉ አድራሻውን አለን፤ እየፈለግናቸው ነው። እነዚህ የጠፉት ደንበኞች የወሰዱት አጠቃላይ ገንዘብ 9.8 ሚሊየን ብር  ነው። ከዚህም ውስጥ አንድ ሰው ያወጣው ትልቁ ገንዘብ 324 ሺህ ብር ነው። - ገንዘብ ያልመለሱ ደንበኞች በባንኩ ቅርንጫፎች በያሉበት ስም ዝርዝራቸው ይለጠፋል። በባንኩ የማበራዊ ትስስር ገጾች ስማቸውን ይወጣል። ከዚህ ባልፉ ስማቸው ከነፎቶዋቸው ጭምር ይወጣል። በዚህም መመለስ ካልቻሉ በህግ ይጠየቃሉ። - ያለአግባብ የተወሰደ አንድ ብር እንኳ ሳይቀር እናስመልሳለን። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህን መረጃ የአል አይን ኒውስ እንዲሁም ከካፒታል ጋዜጣ መውሰዱን ይገላጻል። @tikvahethiopia
Show all...
😡 958 359👏 238😭 84🤔 78🙏 44🕊 35😢 33😱 29🥰 21
Photo unavailableShow in Telegram
#ራትዝብራንድ ራታዝBrand ጥራት ያላቸው ጫማዎች፤ ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በፈለጉት መጠን እኛ ጋር ያገኛሉ፤ እንዲሁም በየግዜው እቃ ስናስገባ እንዲደርሶ በቴሌግራም ገጻችን ቤተሰብ ሆነው ይከታተለሉ🔽 https://t.me/+OpJ4wNqSEqZhNTA8 አድራሻ ፦ አ.አ ቦሌ መ/ም አደባባይ ራክሲም ፕላዛ 3ኛ ፎቅ ሱ.ቁ 03። Free delivery 📱0911799616 ✉️@properties6 RATAZ:-thrive with us you will get greater value!
Show all...
23🕊 6🙏 5😭 3🥰 1👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
#SamiTech አዳዲስ ላፕቶፕች  ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!! @samcomptech በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ እና  በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ  ደንበኞቻችን ምስክሮቻችን ናቸው። ዛሬም ብዛትንም ጥራትንም ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለን። ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች  ወ.ዘ.ተ አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ። የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን። የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ። @sww2844 0928442662 / 0940141114 https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
Show all...
40🥰 3😱 2😭 2🕊 1
#ሩስያ ከዚህ ቀደም ማንኛውም #የግብረሰዶም እንቀስቃሴን #ሕገወጥ እና #ጽንፈኛ በማለት ፈረጃ የነበረችው ሩስያ አሁን ደግሞ የግብረ ሰዶም እንቅስቃሴን #የአክራሪነት እና #የሽብር ድርጊት ዝርዝር ውስጥ አካታዋለች። በዚህም ማንኛውም ዓለም አቀፍ የግብረሰዶም እንቅስቃሴ በሩስያ በአሸባሪነት እና በአክራሪነት ዝርዝር ውስጥ ተካቷል። ውሳኔው የተደረሰው የፍትህ ሚኒስቴር የቀረበለትን አቤቱታ ተከትሎ የግብረሰዶም ተከራካሪዎች #አክራሪ እና #አሸባሪ ተብለው እንዲጠሩ በህዳር ወር ላይ የሩሲያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከወሰነ በኋላ ነው። በቅርቡ የሩስያ ፍርድ ቤት በ " አክራሪ ድርጅት " ውስጥ ሚና አላቸው በሚል በመወንጀል ሁለት የመጠጥ ቤት / ባር ሰራተኞችን በእስር ቤት እንዲቆዩ እና እዛው እስር ቤት ሆነው ፍርዳቸውን እንዲከታተሉ ወሷል። የሩሲያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ከዚህ በፊት ዓለም አቀፍ የግብረሰዶም የአደባባይ እንቅስቃሴን " #ጽንፈኛ " በማለት ማንኛውንም እንቅስቃሴዎችን አግዶ ነበር። በወቅቱም የሩስያ ፀጥታ ኃይሎች በሞስኮ ከተማ በሚገኙ ፦ ° የተመሳሳይ ጾታ የምሽት ክበቦች (ክለቦች) ° የተመሳሳይ ፆታ ፓርቲዎችን ያዘጋጃሉ በተባሉ ባሮች ° የወንዶች ሳውና ቤቶች ላይ ዘመቻ አካሂደው ተጠርጣሪዎችን አስረው እንደነበር ይታወሳል። በሩሲያ የተመሳሳይ ጾታ ጥምረት እውቅና #የለውም። በሩሲያ #ትዳር ማለት የወንድ እና የሴት ጥምረት ማለት ስለመሆኑ ትርጉም ለመስጠት የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ከ3 ዓመታት በፊት ተቀይሮ ነበር። @tikvahethmagazine @tikvahethiopia
Show all...
👏 12146 1614🙏 389🥰 197🕊 105😡 52😱 29😭 18🤔 16😢 11
#ናይጄሪያ ናይጄሪያ ውስጥ አንድ ባለሃብት ገንዘብ ለማደል በጠራበት ዝግጅት ላይ በተፈጠረ ግርግር አንዲት የ8 ዓመት ሕፃንን ጨምሮ 7 ሰዎች ተረጋግጠው እንደ #ሞቱ ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል። ትላንትና እሁድ አልሃጂ ያኩቡ የተባለ ባለሀብት በሰሜን ምሥራቅ የባውቺ ግዛት ነዋሪዎች ወደ ቢሮእ ከመጡ ለእያንዳንዳቸው 5 ሺህ ናይራ [የናይጄሪያ ገንዘብ] ለመስጠት ቃል ይገባል። 5 ሺህ ናይራ ወደ ዶላር ሲመነዘር 3 ዶላር ከ70 ሳንቲም ሲሆን፣ ወደ ብር ሲቀየር 210 ነው። የባለሀብቱን የገንዘብ እደላ ጥሪ ተከተሎ በርካታ ሰዎች ይወጣሉ በዚህ ወቅት በተፈጠረ ግርግር ዕድሜያቸው ከ8 እስከ 55 የሚሆን 7 ሰዎች መሞታቸውን ፖሊስ አረጋግጧል። ነዋሪዎች ግን የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከተጠቀሰው ይበልጣል ብለዋል። ብዙ ጊዜ እንዲህ ያለ እደላ/እርዳታ ላይ ወንዶች የእርዳታ ገንዘብ ሲቀበሉ መታየት  ስለማይፈልጉ ሴቶችን እንደሚልኩ ተነግሯል። የሀገሪቱ ባለሥልጣናት የተፈጠረውን ነገር ለማጣራት ምርመራ መጀመራቸውን ተናግረዋል። ቢሮው አካባቢ ጥሬ ገንዘብ ልገሳ ያሰናዳው ባለሀብቱ አልሃጂ ያኩቡ ማይሻኑ እስካሁን ያለው ነገር የለም። የናይጄሪያ ምጣኔ ሀብት መላሸቁን ተከትሎ በርካቶች እርዳታ ጠባቂ ሆነዋል። 5 ሺህ ናይራ አንድን ቤተሰብ ለአንድ ቀን መመገብ ይችላል። ባለፈው ሳምንት በማዕከላዊ ናይጄሪያ የናሳራዋ ግዛት ዩኒቨርሲቲ ሩዝ ሲታደል ለመቀበል የወጡ የተወሰኑ ተማሪዎች ተረጋግጠው ሞተዋል። ባለፈው ወር የናይጄሪያ ገቢዎች አገልግሎት ሩዝ በቅናሽ ዋጋ ሲሸጥ በተፈጠረ ግርግር የተወሰኑ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው አሳውቆ ነበር። ናይጄሪያ ውስጥ ባለው የኑሮ ውድነት ምክንያት በርካቶች የሚቀበሉት ደመወዝ ከወር ወር ሊያደርሳቸው እንዳልቻለ ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል። Via https://t.me/thiqahEth @tikvahethiopia
Show all...
😭 1160 128😢 66😱 65😡 41🕊 32🤔 23🙏 15👏 10🥰 7
#አጣዬ “ የሰው ሕይወት በእነርሱም በእኛም ጠፍቷል። የሟቾች ቁጥር እንደ አጣዬ ከተማ ወደ 10 ደርሷል። በጣም በርካታ ቁስለኞች አሉ ” - የአጣዬ ከተማ ከንቲባ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አጣዬ ከተማና በኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን በታጣቂዎች መካከል ተከፈተ የተባለው የተኩስ ልውውጥ ከሰሞኑ ይልቅ ዛሬ (ሰኞ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም) አንፃራዊ #ሰላም እንዳሳዬ፣ በነበረው የተኩስ ልውውጥ ግን በሁለቱም ወገኖች የንጹሐን ሕይወት እንዳለፈ የአጣዬ ከተማ ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። Q. ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰላሙ ሁኔታ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ፣ የተኩሱ ሂደት ምን ይመስል እንደነበር፣ የጉዳት መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ ለከንቲባው ጥያቄ አቅርቧል። አቶ ተመስገን ተስፋ፦ “ ተኩሱ ሁለት ቀናት በዙሪያው ሲካሄድ ቆይቷል። ወደ ከተማው ከገባ በኋላ ደግሞ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ውጊያው ተካሂዷል። መከላከያ ገብቶ ከቆመ በኋላም ተራራ ላይ በመሆን በመተኮሱ የተገደሉ ንጹሐን አሉ። የሰው ሕይወት በእነርሱም በእኛም ጠፍቷል። በጠቅል የሟቾች ቁጥር እንደ አጣዬ ከተማ ወደ 10 አካባቢ ደርሷል። ቁጥራቸው ባይታወቅም እጅግ በጣም በርካታ ቁስለኞች ናቸው ያሉት። Q. ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን በኩል “ ፋኖ ታጣቂዎች ጥቃት አደረሱብን ” በአማራ ክልል በኩል ደግሞ “ የሸኔ ታጣቂዎች ጥቃት አደረሱብን ” የሚሉ ሀሳቦችን ነዋሪዎቹ በየፊናቸው እየገለጹ ይገኛሉ። እንደተባለው “ የፋኖ ታጣቂዎች ” ም ሆኑ የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው ጥቃት አድራሿቹ ? እውነታው ምንድን ነው? ሲል ጠይቋል። አቶ ተመስገን ተስፋ፦ “ በከተማችን ላይ የፋኖ ታጣቂ የለም። ከእነርሱም ጋር ግጭት አልፈጠረም። ምናልባት የፋኖ ታጣቂ የሚባለው ችግሩ ከመንግሥት ጋር ነው። መንግሥትን ካልሆነ በስተቀር የኦሮሚያን ብሔር በዚህ ቦታ ሂዶ ተጋጨ የሚል እንደ ከተማችን የለም። ችግሩ የተፈጠረው በእኛ በከተማው ታጣቂዎችና በእነርሱ መካከል ነው። ዞሮ ዞሮ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች በአንድ ገበያ የሚገበያዩ፣ ተስማምተው የሚኖሩ፣ በማኀበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎ የሚያደርጉ ስለሆኑ፣ አማርኛ ተናጋሪው ኦሮሞው ላይ፣ ኦሮምኛ ተናጋሪውም እንደ ህዝብ ጥቃት ያደርሳል፣ ፈልጎ ይዋጋል ብለን አናስብም። ልዩ የሆነ ቡድን፣ ፀቡ እንዲነሳ የሚፈልግ (ምናልባት ደግሞ ከዚያ ተጠቃሚ ሊሆን የሚችል) ቡድን አለ። እሱም ደግሞ ኦረምኛ ተናጋሪ ይሆናል ተብሎ የሚታሰበው ‘ሸኔ’ ነው። ስለዚህ የእኛ ፍረጃ አሁን የኦሮሞ ሕዝብ የአማራን ሕዝብ ወጋው ሳይሆን፣ የኦሮሞ ‘ሸኔ’ አማርኛ ተናጋሪውን በከተማው ላይ መጥቶ ወግቷል የሚል ግምገማ ነው ያለን። Q. ዘላቂ ሰላም ለማምጣት እንዲቻል መንስኤውን ማወቅ ያስፈልጋልና የሰሞኑ ተኩስ መነሻው ምን ነበር ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርቧል። አቶ ተመስገን ተስፋ፦ “ እንደ አጠዬ ከተማ ነዋሪ፣ እንደ ከተማ አመራር መነሻው ይሄ ነው የሚል ነገር የለም። ግጭቶቹ የተካሄዱት በወሰን ብቻ ሳይሆን በከተማው መሀል ላይ ነው። ድንገት ገቡ ተወረረ ከተማው። ከንጹሐን ሞት በተጨማሪ ሆቴሎች፣ ሱቆች ተዘርፈዋል። አረጋዊያን፣ ሴቶች፣ ህፃናት ከከተማ ወጥተው ወደ ገጠራማው ክፍል ተፈናቅውለዋል። አጣዬ ከተማ ያሉት ወንዶችና የጸጥታ አካላት ብቻ ናቸው። አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ አካባቢውን መከላከያ ተቆጣጥሯል። አንጻራዊ የሆነ ሰላም አለ። ” ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በኩል ስለጉዳዩ ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው አልተሳካም። ፈቃደኛ ሆነው የሚሰጡት ማብራሪያ ካለ በቀጣይ ይቀርባል። @tikvahethiopia
Show all...
😭 442 159😡 88🕊 25😱 20😢 18🙏 10🥰 8🤔 8
#AddisAbaba የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፥ በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ በሚገኘው የኮሪደር ፕሮጀክት እና ተያያዥ የልማት ሥራዎች ምክንያት በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ መስመር የማዛወር ሥራዎች እየተሰራ መሆኑን ገልጿል። በዚህም ሥራው ሲከናወን ተገቢውን ጥንቃቄ ለማድረግ እንዲሁም አደጋ እንዳይከስት ሲባል ሥራው በሚከናወንባቸው አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ሙሉ ለሙሉ ወይም አልፎ አልፎ ለተወሰኑ ሰዓታት #እየተቋረጠ እንደሚገኝ አመልክቷል። " የመስመር ማዛወር ሥራዎቹ በጥንቃቄና በፍጥነት ለማከናወንና አገልግሎቱን ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት እያደረግን ነው " ያለ ሲሆን ነዋሪዎች ይህን ተረድተው በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጥሪ አቅርቧል። በዚህ ምክንያት ለሚፈጠሩ ለአገልግሎት መስተጓጎሎችም #ይቅርታ ጠይቋል። በሌላ በኩል፥ ከመጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከ4 ኪሎ እስከ ፒያሳ ባለው መስመር የራስ መኮንን ድልድይ እየተሰራ በመሆኑ የመንገድ ግንባታው እስከሚጠናቀቅ በተለይ በስራ መግቢያ እና መውጪያ ሰዓት አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል። በዚህም፦ ➡ ከ4 ኪሎ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ ➡ ከደጎል አደባባይ ትራፊክ መብራት ወደ 4 ኪሎ ➡ ከቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ ➡ ከደጃች ውቤ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ ➡ ከአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ ➡ ከባሻ ወልዴ ችሎት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ እና ከቀበና ወደ ፒያሳ የሚመጡ አሽከርካሪዎች መንገዱ ግንባታ ላይ መሆኑን ተገንዝበው ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ተብሏል። @tikvahethiopia
Show all...
😡 565 312👏 84🙏 70😭 42🕊 22🥰 19😢 19😱 18🤔 8