አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
ካታርሲስ(Catharsis)
፨፨፨
የአሪስቶትል የፍልስፍና ሃሳብ ካታርሲስ /ስሜትን ማጥለል / ይባላል ። የካታሪስ ቲዎሪ ባጭሩ ሲቀመጥ ይህንን ይመስላል...
" አንድ ሰው የቅርብ የሆነ ዘመዱ ወይም ወዳጁ ሲሞት የሚያለቅሰው ለሟቹ ሰው በማዘን ሳይሆን በማዘኑና በማልቀሱ ግን ራሱ የሚያገኘው እፎይታ(relief) ስላለ ነው። በለቅሶውም የራሱ ሃጢያትና ክፋት ካሳ እንደሚያገኝለት ያምናል። "
በሌላ አገላለጽ አሪስቶትል ይህንኑ ሲያስረዳን...
"አንድ ንፁህ ሰው በሞት ሲቀጣ ብትመለከትና ብታለቅስ፤ ንፁህ ሰው ያለጥፋቱ በመሞቱ ሳይሆን ያለቀስከው ራስህን በሰውዬው ቦታ በማስቀመጥ 'እኔ በዚህ ሰው ቦታ ብሆንስ?' በሚል ስሜት ስለምትንገላታ ነው። እንግዲህ በሰው ሞት ውስጥ የራስህን ሞት ማየት ካታርሲስ ይባላል" ይለናል ።
ምንጭ ፦ "ጥበብ ከጲላጦስ"
፨ የካታርሲስ ፍልስፍና ግን ምን ያህል ቅቡል ነው በእኛ ዘንድ...?
ከፍልስፍና ዓለም
@abrhott @abrhott @abrhott @abrhott
3 738
አጠር ያለ አስተማሪ መልዕክት
አንድ ሰው ነበር በባህር ብቻውን በመርከብ እየተጓዘ እያለ
በመዓበል ተመታና መርከቡ ተሰባብሮ በባህሩውሰጥ ሰመጠች ሰውዬው እንደምንም እራሱን አድኖ አንድ ደሴት ላይ ያርፍና ጎጆ ነገር
ሰርቶ ለቀናት ለብቻው እዛች ደሴት ላይ ይኖራል ,,,,,,,,ምግብ ዓሳ እያጠመደ እየተመገበ ብዙ ቆየ
አንድ ቀን ዓሳ ሊያጠምድ ወደ
ባህሩ እየሄደ በመሀል እዛች ባህር ላይ ጭስ ይሸተዋል ዞር ብሎ ሲመለከት ያቺ ጎጆው እየነደደች ነው ,,,,,,,እየሮጠ ቢመለስም ጎጆዋን ሊያድናት አልቻለም ለካ ዓሳ ለማብሰል ያቀጣጠለው እሳት ተያይዞ
ጎጆውን አንድዷታል አለቀሰ ፈጣሪውን ወቀሰ እንዴት እዚህ ባህር ላይ ለብቻዬ ጥለከኝ ከቤተሰቦቼ ነጥለኸኝ ስታበቃ በስንት ልፋት
የሰራዋትን ጎጆ ታቃጥልብኛለክ ብሎ አለቀሰ አማረ
,,,,,,,, ከደቂቃዎች በኋላ አንድ ድምፅ ሰማ ወደ ድምፁ ፊቱን ሲያዞር አንድ ትልቅ መርከብ አየ ተደሰተ ,,,,,, የመርከቡ ሰዎችም መጥተው ጭነው ወሰዱት ከዚያም ለመርከብ ሰዎች ጠየቃቸው !
እንዴት አገኛችሁኝ እዚህ አካባቢ እዚህ ባህር ላይ ማንም አይመጣም እኮ እናንተ እንዴት መጣችሁ ? አላቸው ,,,,, መርከበኞቹም እኛም በዛኛው በኩል ዞረን እየሄድን ነበር ከዚያ በኩል ጭስ አየንና እዚህ ሰው ይኖራል ብለን መጣን አንተ አገኘን አሉት
አቤት ጌታዬ ለካ ከዚህ ከስቃይ ልታወጣኝ ፈልገህ ነው ትንሿ ጎጆዬን ያፈረስከው ወደ ትልቁ ቤቴ ልትወሰደኝ ነው አለአንዳንዴ የሆነ ነገር ስናጣ ሲበላሽብን ፈጣሪንም ሰውንም ስናማርር እንኖራለን ግን ካጣነው ነገር ከጎደለብን ነገር ጀርባ ብዙ ጥሩ ነገር ልናገኝ እንደምንችል እንዘነጋለን በችግራችን ጊዜ መጠጋት ያለብንን ፈጣሪን እንረሳለን ከዚያም አልፈን የሁሉ ነገር ፈጣሪውን እንኮንነዋለን
ያጣነውን የሰጠን ፈጣሪ አእምሯችን
ከሚያስበው በላይ ሊሰጠን እንደሚችል ማመን አለብን ።
3 738
የህይወት_ፍልስፍና ( Life_Philosophy )
📚📚📚
የሰው ልጅ ከተፈጠረበት ጀምሮ ኑሮን ለመምራት በሚያደርግበት ግዜ የተለያዩ መሰናክሎች ወይም አንቅፋቶች ያጋጥሙታል። ቁልፉ ግን የህይወትን አላማ ግብ መረዳት ነው። ባጋጠሙት እንቅፋቶች ምክንያት የህይወቱን አላማ ከዳር ሳያደርስ በመንገድ ላይ ሊገታ ይችላል። ስለዚህ ለስኬቱ መዳረስ የሚያራምደው የህይወት አመለካከት ወይም ፍልስፍና ቁልፍ ሚና ይጫወታል። አንዳንዴ ግን የህይወትን ፍልስፍና መያዙ ብቻ በቂ አይደለም። ፍልስፍናውን መከተልና መሆን(ዋነኛው የህይወቱ አካል አድርጎ መኖር) በጣም የተለያዩ ነገሮች ናቸው።
የህይወታችንን ግብ ከዳር አንዲደርስ ሁለት ግዙፍ የህይወት አመለካከት ግንባሮች አሉ (የሁለቱም ፍልስፍና አራማጆች በየግላቸው ትክክል ነው ብለው ያምናሉ ለምሳሌ ሁለት የእግር ኳስ ቡድኖች አሉ። ሁለቱም ለማሸነፍ ወደ ሜዳ ይገባሉ። ሁለቱም የአጨዋወት ስልት አላቸው። አንዱ የያዘው ስልት ለራሱ ትክክል ነው ለተጋጣሚው ግን ስህተት ነው ሌላውም በተመሳሳይ):-
🤔 1) ፕሮታጎኒስት (Protagonist):- የፕሮታጎኒስት አቀንቃኞች የሰው ልጅ እያንዳንዱን ቀን በታላቅ ትጋት መስራት አለባቸው ፣ በቻሉት መጠን ከራሳቸው አልፈው ለሌላው የሚፈይድ አንዳች መልካም ወይም ቀና የሆነ ተግባር መፈፀም አለባቸው። በህይወት ለሚያጋጥማቸው አያንዳንዱ መልካም ሆነ አሳዛኝ ገጠመኝ ሳይበገሩ ወደ ፊት መቀጠል አለባቸው ምክንያቱም ሁሉም የሰው ልጅ በምድር ላይ የተፈጠረበት ትልቁ ምክንያት በህይወት ዘመኑ መልካም ነገር ለመስራት አንጂ ኖሮ ኖሮ ለመሞት በቻ አይደለም ብለው ያምናሉ።
፨ የፕሮታጎኒስቶችን ፍልስፍና ጠቅለል ስናደርገው:-
• የሰው ልጅ የተፈጠረው ለስራና ለስራ በቻ ነው ፣
• ሁሌም ቢሆን መልካም ነገር መስራት ይኖርብናል ፣
• ተስፋ መቁረጥ በምንም ተዓምር የለበትም ፣
• ዛሬን ሳይሆን ነገን ነው መኖር የሚገባን ፣
• ሁሌም ወደ ኋላ ሳይሆን ወደ ፊት ይሉናል።
🤔 2) አንታጎኒስት (Antagonist):- አንታጎኒስቶች ያላቸው የህይወት ፍልስፍና የሰው ልጅ ሞትን ማሸነፍ ካልቻለ አልያም የሰው ልጅ መጨረሻው ሞት ከሆነ ህይወት ነገ ሳትሆን ዛሬ በቻ ናት። ስለዚህ የሰው ልጅ መኖር ያለበተደ ዛሬን ብቻ ባሻው መንገድ መሆን አለበት። ስራ ፣ አላማ ፣ ፅናት ፣ ግብ ፣ ራዕይ ... ወዘተ የሚባል ኮተት ሁሉ ከንቱ ስንቅ ነው። አጅግ መናጢ የሆነው ግለሰብና የናጠጠው ሀብታምም መጨረሻው ሞት ነው። ጠ/ሚኒስትሩው ፣ ኩሊው ፣ የተማረው ፣ ያልተማረው ፣ ስኬታማው ፣ ስኬት አልባው ... ሁሉም ይሞታሉ። ታዲያ ሞት የማይቀርል ዕዳ ከሆነ ምን አስለፋን ፣ አስደከመን ...? ሞት የማይቀር ከሆነ የሰው ልጅ ነገን እያሰበ ሳይሆን ዛሬን ብቻ መኖር አለበት ምክንያቱም የሰው ልጅ ምንም ይሁን ምንም መጨረሻው ሞት ነውና የሚል አመለካከት ያራምዳሉ።
፨ የአንታጎኒስቶችን ፍልስፍና ጠቅለል ሲደረግ:-
• የሰው ልጅ ይሞታል ፣
• ዛሬን ብቻ ነው መኖር ያለብን ፣
• የተፈጠርነው ለደስታ በቻ ነው ፣
• ሁሉም ነገር የተፃፈልን ስለሆነ መለወጥ አይቻለንም።
፨ ስለ ህይወት ፍልስፍና አንዳንድ ጥሬ ሀቆች
# በምድራችን ላይ ካሉት በቢልዬን የሚቆጠር ህዝብ መካከል ሶስት አራተኛው ወይም 75% የአንታጎኒስት አመለካከትን አስበውበት ይሁን ሳያስቡበት ያራምዳሉ። አንድ አራተኛው ወይም 25% የፕሮታጎኒስት አመለካከት ተከታዮች ናቸው።
አኛስ ከየትኞቹ ወገን ነን ...? ሀሳብና ድርጊት በጣም የተለያዩ ጥሬ ሀቆች ናቸው። አንዳንዴ በሀሳብ ደረጃ ተቀብለን በድርጊት ካልገለፅነው ትርጉም የለሽ ይሆናል። ስለዚህ ስንቶቻችን ነን ሀሳብና ድርጊት ሆድና ጀርባ መሆናቸው ቀርቶ መርፌና ክር የሆኑልን?
ለበለጠ መፅሃፉን ያንብቡት!
# ቸር_ጊዜ !
•
ምንጭ :- "ኦያያ ፣ 2000 ከፓሪስ መልስ"
✍ በአዘርግ
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
<<<<ሞራል>>>>
ብዙዎች ፈላስፎች የሰው ልጅ ስለሞራል ሲያወራ ቅድሚያ ሊያነሳ የሚገባው የጥሩና የመጥፎ ነገርን መመዘኛ ነው ይላሉ። በአንድ ማህበረሰብ ውስጥ ጥሩ የሚባለው ነገር በሌላው መጥፎና ጎጂ ይባላል። ለምሳሌ አንድ ሰው ከሚስቱ ውጪ ከሌላ ሴት ጋር ቢዳራ ማህበረሰቡ ሀጢያት የሚያደርገው ምናልባትም የዛ ሰው መጨረሻ ገሀነም ለመሆኑ አረጋግጦ በማስተማር ነው። በሌላው ማህበረሰብ ዘንድ ደግሞ ይኸንኑ ድርጊት አለማድረግ የደካማነትና የልፍስፍስነት ባህሪይ ተደርጎ ይወሰዳል እንጂ ከገሀነምና ከገነት ጋር ጉዳዩን የሚያገናኘው የለም።
እንዳውም የዚህ ማህበረሰብ ፈላስፎች "ሀጢያት የእውቀት ማጣት ውጤት እንጂ የሞራል ጉዳይ አይደለም" ይላሉ።
ይሄ ሲብራራ "አዋቂነትህ እያደገ ሲመጣ ከሀጢያት ትርቃለህ" ነው። እዚህ ላይ የሚነሳው ጥያቄ ታዲያ "በአዋቂነት ከሀጢያት መራቅ ከተቻለ "ሀጢያት" የሚባል ጉዳይ በራሱ አለማለት ነው?" ይሆናል።
ለዚህም ደግሞ በተለይ የዘመናችን ፈላስፎች ከጥንታዊያኑ የተለየ መልስ አላቸው። ለዚህ እሳቤ የፍራሲስ ቤከን ሀሳብን ጣልቃ አስገብተን እንመልከት። በቤከን አስተሳሰብ <ሁሉም ነገር ሁለት መልካም ነገሮችን ይዟል፤ የመጀመሪያው ግላዊ ሞራል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ማህበረሰባዊ ሞራል ነው። ከሁለቱ ደግሞ ማህበረሰባዊ ሞራል እጅግ አስፈላጊና ጠንካራም ነገር ነው። ምክንያቱም በግላዊ ሞራል ውስጥ ሰፊውን ቦታ የሚይዘው "እኔነት" ነውና። እኔነት ደግሞ ከሰብዓዊ ሞራል ይልቅ ተቃራኒውን ለመፈፀም ሰፊ እድል አለው። ዞሮ ዞሮ ሰው ባሪያ መሆኑ አይቀሬ ነው። ምነው ቢሉ (አታድርግ) የሚል እስር ቤት ማህበረሰቡ ፈጥሮበታልና> ይላል። አልደስ ሀክስሌይ ይህን ሀሳብ ይቃወማል።
እንደ ሀክስሌይ አስተሳሰብ ሞራል ማለት ጠንካራ ሆኖ ደካማውን መርዳት ነው። ሞራል በአጭሩ <<በሰብዓዊነትና በክብር የታጠረ ነገር ነው። ከዚያ የወጣ ነገር ሞራል አልባ ድርጊት ይሆናል… ስለሆነም የሞራል ግብ ሰላም ሲሆን ከሞራል የራቀው ነገር መጨረሻ ደግሞ ጦርነት ይሆናል>> ይላል። በሀክስሌይ ሀሳብ አንዳንድ ፈላስፎች ሲሳለቁ <<ሞራል ማለት እንደብዙሀኑ ማሰብ ከሆነ የብዙሀኑ ሀሳብ ትክክለኛነት መጀመሪያ ሊጤን ይገባዋል>> ይላሉ።
ለምሳሌ መንገድ ላይ ተቀምጦ ለሚለምነው ደሀ ሳንቲም መስጠትህ በራሱ ነገሩን ሞራላዊ አያደርገውም፤ ነገር ግን የሰጠህበት እሳቤ ነገሩን ከሞራል ጋር ሊያገናኘው ይችል ይሆናል። ደሀውን የምትረዳው ከሞት በኋላ ህይወት ወይም ገነት እንደሚጠብቅህ አስበህ ከሆነ ይህ ከጥቅም እንጂ ከሞራል ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም እንደማለት ይሆናል።
ለነገሩ የእግዚኣብሄርን የሞራል እሳቤም ብንመለከተው "ሰው የዘራውን ያጭዳል" የሚል ከሆነ ጉዳዩ ከሞራል ወይም ከህሊና ጋር የተገናኘ ሳይሆን ለምታደርገው ነገር ዋጋ እንደሚከፈልህ እንድታውቅ ነው። ፈላስፎቹ ከላይ ያነሳነውን ምሳሌ በማንሳት ሲናገሩ፦ <<ከሚስትህ ውጪ ከሌላ ሴት ጋር የምታደርገውን መዳራት ገሀነም እንደምትገባ አስበህ ከተውከው ያለመዳራትህ ምክንያት ሞራላዊ ሳይሆን ጥቅማዊ ነው>> ይላሉ። ገሀነምን መፍራት ወይም ገነትን መመኘት ከሞራል ጋር የሚያገናኘው አንዳች ጉዳይ የለምና።
ስለዚህም ሞራል የእውቀት ጉዳይ እንጂ ሌላ አይደለም የሚሉት ፈላስፎች ለእነ አናቶሌ ፍራንስ ጥያቄ ግን አንዳንድ ምላሽ ሲያጥራቸው ይስተዋላል።
ለአናቶሌ ፍራንስ ብቸኛውና ትልቁ የሰው ልጅ ሞራል (ንፅህና) ነው። ይህንንም ሲገልፀው "አንድ በሀብት የናጠጠ ከበርቴ ተመልክተህ ስታደንቀው ትኖርና ከእለታት አንድ ቀን የሀብቱ ምንጭ ሀሺሽ በመሸትጥ የተገኘ እንደሆነ ትደርስበታለህ፤ በግለሰቡ ላይ ያለህ አመለካከትም መለወጥ ይጀምራል። ለምን ቢሉ የሀብቱ ምንጭ የሌላው ሰው ጥፋት እንደሆነ ስለምትቀበል ነው። በሞራልም ተቀባይነት የሌለው ሀብት እትዲህ አይነቱ ነው" ይላል።
አሁንም በዚህ የአናቶሌ ፍራንስ አስተሳሰብ የሚሳለቁ የዘመናችን ፈላስፎች ደግሞ አልጠፉም። <<ንፅህና>> የሚለው ነገር የህሊና ንፅህና ከሆነ የንፅህናስ መለያው ምን ይሆን?>> ይሉናል።
<<አንስታይን የፈጠረው ቦምብ ለአለማችን እልቂት ሲውል ተመልከተናል። ነገር ግን አንስታይንን ከማድነቅ ውጪ የእሱን 'ሞራል አልባ' ድርጊት በማለት የኮነነው አልተገኘም>> ይላሉ።
በዚህ መንገድ ሞራል አንድም የእውቀት ሌላም ጊዜ የእምነት ጉዳይ ሁኖ እስከዘመናችን ቢዘልቅም ቢዛን ደፍቶ ያጋደለው ግን ወደ እምነቱ ሆኗል። በተለይም የፍልስፍና አባቶች ከሚባሉት ከሶቅራጥስና የእሱም ደቀመዝሙር ከነበረው ከፕሌቶ ጊዜ አንስቶ ሞራላዊ እሳቤዎች ከአምላክ ጋር የተቆራኙ በመሆናቸው ሁለቱን ለመነጠል መሞከር የሰውን ተፈጥሯዊ ዋጋ ዝቅ እንደማድረግ ነው የሚሉ በብዛት ይገኛሉ። ከዚህ በተቃራኒው የቆሙት ደግሞ እንኳን ለራሱ ቀርቶ ለአምላክም ሞራልን የፈጠረ እራሱ ሰው ነው፤ ስለዚህ ሞራል የእውቀት እንጂ የእምነት ነገር ሊሆን አይገባውም ባዮች ናቸው።
ምንጭ፦ ጥበብ
ከቁ.፪
ሀይለጊዮርጊስ ማሞ
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
የባከነ ሌሊት!
Aug 26, 2018 / በ በዕውቀቱ
ስዩም /
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ።
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
“በኡራኤል ርዱኝ ” ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ
አላፈራሁ።
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
” እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ”
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው።
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ
ሳለጥፍ
” እናትዋን ጨረቃ” የሚል ግጥም
ሳልጥፍ።
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ
ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
” እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?” ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ።
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ
ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ።
3 738
#ኢትዮጵያ ||| #ኮሮናቫይረስ ||| #የአስር_ቀን
#የሐምሌ_ወር በሀገራችን በ10 ቀን ውስጥ ብቻ ቫይረሱ በምን ያክል ፍጥነት #እያሻቀበ እንዳለ ልብ ይበሉ!
ይህንን አሀዝ ለወዳጅ ዘመዶ #ሼር በማረግ እንዲጠነቀቁ ያስገንዝቡ
1. ሐምሌ - 7
የተያዙ፦ 212
ህይወታቸው ያለፈ፦ 7
2. ሐምሌ - 8
የተያዙ፦ 294
ህይወታቸው ያለፈ፦ 2
3. ሐምሌ - 9
የተያዙ፦ 328
ህይወታቸው ያለፈ፦ 2
4. ሐምሌ - 10
የተያዙ፦ 344
ህይወታቸው ያለፈ፦ 13
5. ሐምሌ - 11
የተያዙ፦ 356
ህይወታቸው ያለፈ፦ 4
6. ሐምሌ - 12
የተያዙ፦ 704
ህይወታቸው ያለፈ፦ 3
7. ሐምሌ - 13
የተያዙ፦ 304
ህይወታቸው ያለፈ፦ 3
8. ሐምሌ - 14
የተያዙ፦ 561
ህይወታቸው ያለፈ፦ 7
9. ሐምሌ - 15
የተያዙ፦ 452
ህይወታቸው ያለፈ፦ 8
10. ሐምሌ - 16
የተያዙ፦ 409
ህይወታቸው ያለፈ፦ 9
#በአጠቃላይ #በ10 ቀን ውስጥ ብቻ፦
#በቫይረሱ #የተያዙ፦ 3,964
#ህይወታቸው #ያለፈ፦ 58
እንጠንቀቅ እንጠንቀቅ እንጠንቀቅ‼️
3 738
ራስን ማጠብ ይመረጣል
*
"ደስታንም እንደቆሎ ቅሜአለሁ።
ፍስሃ ደጋግማ የተባረከውን የቤቴን በር አንኳኩታለች። ችግርም በፈንታው የተለያየ ክብደት ባለው ኮቴው ወጥቶብኛል፣ ወርዶብኛል። በአዲስ አበባም ራስ ወዳድ ጎዳናዎች ላይ እስኪሳቅብኝ ቼ ቼ ብሎኛል። አንዳንዴም የአለም ችሎታዋ መቆንጠጥ ብቻ እስኪመስለኝ ተቆንጥጫለሁ። እንዲህ ሲሆን እንደ ጌታዬ 'ተፈፀመ' አላልኩም።
የተሳሳትኩትን አረምኩ።
ከአሳሳቾችም ራቅኩ።
ጥንካሬዬንም አየሁ።
ስህተት የማይፈፅም የሰው ልጅ የለም።
ዛሬ የለበስነው ንፁህ ነገር ከትላንት ወዲያ ቆሽሾ ትላንት የታጠበ ቢሆን እኮ ነው።
"ወእምሐበ ወረደ አንብዑ ነቅዓ ማይ ፀዓዳ--- ዕንባው ከፈሰሰበት ቦታ ፅሩ ውሐ ወጣ" ይላል ገድለ ተክለሃይማኖት።
ታዲያ ቆሻሻው ወጥቶልን ነፍሳችን የምትፀዳው ሒስ ወይ ግለ ሒስ ስናደርግ ነው።
ከሁሉ ከሁሉ ግን እልሃለሁ
ራስን ማጠብ ይመረጣል።"
*
መረቅ
3 738
ዲዮጋን
፨፨፨
📖 የታላቁ ፈላስፋ የዲዩጋን ምርጥ ምላሾች!!
❇️ በቆሻሻ ቦታ ሲዘዋወር የተመለከተው የአቴና ነዋሪ ወዳጁ
ቢገስጸው፡-
‹‹አትሳሳት! ጸሀይ የማትወጣበት ቦታ የለም እስከዛሬ ግን አልቆሸሸችም ብሎታል››፡፡
❇️ በሌላ ግዜም በገበያ ቦታ ላይ ሲበላ የተመለከቱት የአቴና ነዋሪዎች በዙሬያው ተሰብስበው
‹‹ውሻ ውሻ ! ›› በማለት ሲጮሁበት፡-
‹‹እኔ የማውቀው ሰው ምግብ ሲበላ በዙሪያው ከቦ የሚመለከትና የሚጮህ ብቻ ነው››በማለት
መልሳል፡፡
❇️ ሰዎች ለለማኝ እንጂ ለምን ለፈላስፋ ገንዘብ እንደማይሰጡ ሲጠይቁት
‹‹ምክንያቱም አንድ ቀን ለማኝ እንጂ ፈላስፋ እንደማይሆኑ ስለሚያውቁ ነው›› ብላቸዋል፡፡
❇️ ምግብ ለመመገብ የተመቸ ሰአት የቱ እንደሆነ ተጠይቆ፡-
‹‹ሀብታም ከሆንክ ስትፈልግ'ድሀ ከሆንክ ደሞ ስትችል ምግብ ለመመገብ ጥሩ ሰአት ነው››ብላል፡፡
❇️ ለዲዩጋን ምጽዋት የሚሰጡት ሰዎች ለምን
እንደማያመሰግናቸው ሲጠይቁት
‹‹እናንተ በመስጠታችሁ ብቻ ሳይሆን እኔም የናንተን ምጽዋት በመቀበሌ ምስጋን ይገባኛል››ብላቸዋል፡፡
❇️ ስለጸሎተኛ ሰው ሲጠይቁት
‹‹ጸሎተኛ ሰው የሚፈልገውን እንጂ መጠየቅ የሚገባው የማይጠይቅ ሰው ነው››ብላል፡፡
❇️ ሲሞት እንዴት እንዲቀብሩት እንደሚፈልግ ሲጠየቅም
‹‹ፊቴን ወደታች ዘቅዝቃችሁ ቅበሩኝ
ምክንያቱም ዝቅ ያለ ነገር ጥቂት ቆይቶ ከፍ ማለቱ እንደማይቀር ስለማውቅ ነው›› ብላቸዋል፡፡
❇️ እንድ የአቴና አስተማሪ ስለህይወት ክፉነት ደጋግሞ ሲያስተምር ሰምቶ
‹‹ህይወት ክፉ ያደረጋት የሚኖራት እንጂ ህይወት በራሷ ክፉ አይደለችም››ብሎታል፡፡
❇️ በባርነት የገዛው ዜነዲየስ ‹‹እኔን ልትታዘዝ የግድ ነው››አለው፡፡
‹‹ምንም እንኮን ባሪያህ ብሆንም አዋቂና የነቃ ሰው በባርነትም ሆኖም ሊታዘዙት ያስፈልጋል››፡፡
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
መሳጭ ከሆኑ የፈላስፋው #ኮንፊሽየስ ንግግሮች በጥቂቱ...
<< የታላቅ ሰው ታላቅነት የሚገለጸው #በተግባሩ እንጂ #በንግግሩ አይደለም። የተግባር መሰረቱ ደግሞ #ጽኑ_ፍላጎት ነው።....የአንድን ተራ ሰው ጽኑ ፍላ ፍላጎት ከውስጡ ከመውሰድ፣ የአንድን ታላቅ ሃገርን የጦር አዛዥ መማረክ ይቀላል። >>
፧
<< ሰዎች እያወሳሰቧት እንጂ ሕይወት ቀላል ናት...ሰዎች በጨለማው ላይ ከሚያፈጡና ከሚያለቅሱ ይልቅ አንዲት ሻማ ቢለኩሱ ለጨለማው ችግራቸው በቀላሉ መፍትሄ ያገኛሉ። >>
፧
<< ታላቅ ሰው ችሎታውን ለማሳየት አይሽቀዳደምም...የአላዋቂን ሰው ስንፍና ልኩን የሚያውቅ አዋቂ ሰው ብቻ ነው። እናም በሌሎች ዘንድ ለመታወቅ ከመድከም ይልቅ ልታወቅ የሚገባኝ ነኝ በሚለው እምነት ውስጥ ሞልተህ ተቀመጥ። የእውቀቱ አንዱ ጥቅሙ በራስ መተማመንን ማምጣቱ ነውና።...ታላቅ ሆኖ ሳለ ነገር ግን ታላቅነቱ ባለመታወቁ የማይናደድ ሰው እሱ በእርግጥ ታላቅ ነው። >>
፧
<< አንድን ነገር መቼም ላውቀው አልችልም በሚል ስሜት ተማረው፤ ስታውቀው ደግሞ ላጣው እችላለሁ በሚል ስሜት አጥብቀህ ያዘው። >>
ምንጭ ፦ ጥበብ ከጲላጦስ...ቅጽ ፩
@abthott @abrhott
3 738
✍ Bewketu Seyoum
ስሙኝማ! ባለፈው የስድሳ አምስት አመት ሴት ወለደች ሲባል ሰማን አሁን ደግሞ የመቶ አስራ አራት አመት ሰው ከኮረና አገገመ ተባለ ! አልገባኝም! ሚድያዎች ላይ የእድሜ ቆጠራ የሚያደርገው የድሮው ምርጫ ቦርድ ነው እንዴ? አንድ ሴት በስድሳ አመቱዋ አይደለም የወር አበባ ለማየት፤ የሱፍ አበባ ለማየት እንኩዋ የመነፅር እገዛ ያስፈልጋታል ! የሆነ ክፍለ ከተማ ሴትዮዋን እንደ ተአምረኛ ቆጥሮ ሽልማት ለቆባታል ! እድሜዋን ጨምራ የተናገረች የመጀመርያዋ ሴት ስለሆነች እንደ ተአምረኛ ብትቆጠርም አይገርመኝም!
በቀደም ደግሞ የመቶ አስራ አራት አመት እድሜ ባለፀጋ አገገመ ተባለ! እስቲ ጠይቁልኝ! ይሄ ስውየ እስከዛሬ የት ነበረ? ፤ በነገራችን ላይ አንተ እምለው ወድጄ አይደለም፤አንድ ሰው መቶ አመት ከሞላው በሁዋላ ሁለተኛ ዙር መኖር ስለጀመረ አንተ እንጂ አንቱ ሊባል አይገባም!
ይሄ ሰውየኮ ከስድስት ያላነሰ መንግስት አይቱዋል ! ካሞሌ ጨው እስከ atm ድረስ ተገበያይቱዋል ! ሎተሪ ከሚደርሰኝ፤ ይሄ ሰውየ ደም ይለግሰኝ !
ይህ በእንዲህ እያለ የአዲሳባ ከተማ የሚያደርገውን የልማት ስራ እየተከታተልሁ ነው ! ይበል እሚያሰኝ ነው! በተለይ ምችት ያለችኝ “ ብልፅግና “ ስትባል ውሃ እምትለቀው ቡዋንቡዋ ናት! ይቺን ማሽን የፈለሰፋት ሰውየ እንደነገረኝ “ ብልፅግና ስትል ውሃ ታፈሳለች መረራ ጉዲና ስትላት ታቁዋርጣለች “
በተረፈ it is my Dam
ሰብስክራይብ ማድረግ ማንንም አይጎDam
Join
@abrhott
