አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
የፀሐይ ግርዶሽ እና ጥንቃቄ!
የፀሐይ ግርዶሽን በዓይን በቀጥታ መመልከት ቋሚ ጉዳት በዓይን ላይ ያደርሳል። ግርዶሹን ለመመልከት ፦
1. ደረጃውን የጠበቀ የግርዶሽ መነፅር መጠቀም
2. ፒን ሆል ካሜራ ወይም በአነስተኛ ቀዳዳ ወደ ድፍን ካርቶን የሚገባውን ብርሃን የሚስለውን ስእል ጀርባ ለፀሐይ በማዞር መመልከት
3. ጨለማ ክፍል ውስጥ በቀዳዳ የሚገባውን የፀሐይ ብርሃን መሬት ወይም ግድግዳ ላይ የሚሰራውን ስእል መመልከት
4. በዛፎች ቅጠል አልፎ መሬት ላይ የሚያርፈውን የፀሐይ ስእል መመልከት
5. ለቴሌስኮፕም ሆነ ባይነኩላር የፀሐይ ብርሃን መጣኝ ደረጃውን የጠበቀ ፊልተር ግጥሞ መመልከት
6. ግርዶሹን የሚያሳዩ የቀጥታ ስርጭቶችን መመልከት
የፀሐይ መነፅር ፣ ፍሎፒ ዲስክ ፣ የፎቶ ፊልም ፣የራጅ ፊልም እና የመሳሰሉት ቁሶች መጠቀም በዓይን ላይ ጉዳት ያደርሳል - #ESSS
3 738
የጸሃይ ግርዶሽ ምንድነው ?
ፀሐይ ግርዶሽ ጨረቃ በፀሐይ እና መሬት መሃከል ስትገባና ፀሐይን እንዳናያት ስትጋርድብን የሚከሰት ክስተት ነው።
የጸሃይ ግርዶሽ አይነቶች ስንት ናቸው ?
'ሙሉ የፀሐይ ግርዶች' የምንለው ጨረቃ ጸሃይን ሙሉ ለሙሉ የምትጋርድ ከሆነ ሲሆን ጨረቃ ከፊሉን የፀሐይ ክፍል ብቻ የምትጋርድብን ከሆነ 'ከፊል የፀሐይ ግርዶሽ' (Partial Solar Eclipse) ይባላልም
ጨረቃ ፀሐይን ሙሉ ለሙሉ መሸፈን ሳትችል ስትቀርና በጨረቃ ጠርዝ ዙሪያ ቀለበት ሠርታ ፀሐይ የምትታየን ከሆነ 'ቀለበታዊ የፀሐይ ግርዶሽ (annular solar eclipse)' ይባላል።
ነገ በሀገራችን የምናየው ግርዶሽ ቀለበታዊ የፀሐይር ግርዶሽ የሚባለውን ነው - #ESSS
3 738
የዘንድሮ ነገር
(በእውቀቱ ስዩም)
ሟችን ባጀብ መቅበር
ተከልክሎ ባገር
የዘንድሮ ነገር
ተጎልቶ መድከም
ሐዘንን እንደ ዘውድ ለብቻ መሸከም!
በየሰው ጉንጭ ላይ ፤እንባ ቀልጦ እንደ ሰም
ደረት ሳይጎሰም
ፍታት ሳይፈታ
ያለ ምንም ሙሾ፤ ያለምን ዋይታ
ብቻየን ቀብር ዋልሁ
ከእድሜየ መካከል፤ አንድ አመቴ ሞታ ::
3 738
“የፖለቲካ ትልቁ ጥቅም ሽፋን መስጠቱ ነው”
በ አዳም ረታ
ታውቃላችሁ ፖለቲከኞቻችን ትልልቅ ነገር እየተናገሩ ይማርኩናል። ጋዜጣ፣ ሬዲዮና ቲቪ አስደግፈው ያማልሉናል።
አንድ ዛፍ ይተክሉና ስለዚህ ስለተከሉት ዛፍ አስር ሰአት ያወራሉ። ይሄን የሚሰሙ የዋሃን እና ቂሎች፣ ዛፍ ብቻ ሳይሆን በቃ ደን ያደገ ይመስላቸዋል። ድርጊቱ ደቃቃ ቢሆንም ከጥዝጠዛው ብዛት የእውነት ትልቅ ይመስላቸዋል። በደኑ ማደግም በጣም ከማመናቸው የተነሳ እቆሙበት ወይ እተቀመጡበት ስለዚህ ስለተወራለት ደን ስለሆነው ዛፍ (እንዴት አንድ ዛፍ ደን ሊሆን እንደሚችል የሚመረምር ጥቂት ነው) በሰፊው ሊወያዩ ይችላሉ። የሚወያዩት እንዲህ ነው፡
ለመሆኑ እንዲህ የተጠቀጠቀውን ደን እንዴት ልናልፈው ነው? (አንዱ ኮስታራ)
ለመሆኑ እዛ ውስጥ ያለው አውሬ ቢበላንስ? (ቦቅቧቃው)
ከመሄዳችን በፊት እንዲከላከለን የታጠቀ ሰው ካለ አብሮን እንዲሄድ ለምን እንለምንም? (ሌላ ብልጥ ነኝ ባይ ቦቅቧቃ)
ለመሆኑ ልጆቻችን ምን ሆነው ይሆን? እዚህ ቀረን እኮ። መላ ምቱ እስኪ! (ወላድ ወይዘሮ)
እንዴት እየመነጠርን መንገዱን ልንዘልቀው ነው (ቀጫጫ)
መንገድ መጀመራችን አይቀርም ብዬ ጠርጥሬ ገጀራ ልይዝ ነበር (ልበ ቢስ)
ያዝ ብዬህ ነበር ለምን ረሳህ? (ʻብዬ ነበርʼ ባይ)
ኧረ አላልክም! (ልበ ቢስ እንደገና)
ውሸታም አደረከኝ? (ነገር ነገር ሲለው ብዬ ነበር ባይ)።
ድርጅቶች ብናደርጋቸውም ይሰራል፤
የኮስታሮች ነጻ አውጪ ድርጅት (ኮነአድ)፣
ቦቅቧቆች ነጻ አውጪ ግንባር (ቦነግ)፣
የብልጥ ነኝ ባይ ቦቅቧቃ ግንባር (ብባቦግ)፣
የወይዘሮዎች ነጻ አውጪ ግንባር (ወነግ)፣
የቀጫጮች ካውንስል (ቀካ)፣
የልበ ቢሶች ኮሚቴ (ልበኮ)፣
የብዬ ነበር ግሩፕ (ብነግ)፣ ወዘተ……
እኔንና እኔን መሳዮች የሚሳነን የለም።
ቂሎች በሌለ ጉዳይ እንዲህ ያለ ቃል እየተመላለሱ ይቆዩና፣ ቁርሾ ተቀስቅሶ በበነጋታው የሁለት ወይም የሶስት ሰዎች ሬሳ እዛ ዛፍ ተተከለበት የተባለው ገጣባ ቦታ ላይ ይቀበራል።
ከቀብር መልስ ስለደረሰው ችግር የሚያጠና የሚመራመር አይኖርም። ʻእዚህ ጋ ዛፍ ነበር አልተባለም እንዴ?ʼ ብሎ የሚናገር፤ ʻሰው ሞቶ እንዲህ ስለ ዛፍ ታወራለህ ምነው ጨዋ አልነበርክም?ʼ ይባላል። ሰፋ አድርጌ ልመራመር ሲል፣ የሚቀናʻበት መዘናጊያ ይሰጠዋል። ከሰላሳ አመት በኋላ ʻምን አገኘህ?ʼ ቢባል የዚህ አገር ዶክተር የሚመልሰው የለውም። እንዲህ ዘመዶችዋ የተጋደሉባት አንዷ ቆንጆ፡ የሞተው ወንድሜ የገደለው ባሌ አዘኔ ቅጥ አጣ ከቤቴም አልወጣ ብትል ወዳ አይደለም። ቅጥ ማጣታቸው ከተጀመረ ቢከርምም ይረሱታል። ቅጥ ማጣት እንደ ቂጥኝ እንደሚወረስም ይረሳሉ። ቅጥ ማጣት መቼ እንደ ጀመሩ አያጠኑም። ቅጠ-ቢስ ሁሉ።
[…] አሁን የማወራው ስለ ሽፋን ነው።
ዘመን የሚያልፍ ልቡን የማይሰጥ ሽፋን አለ። ለአንድ ሐበሻ ከነጻነት የበለጠ ማታለያ አለ? ምን ይፈልጋሉ ከዚህ የበለጠ ውብ ነገር? ግን ይሄ ነጻነት የተባለውን ረቂቅ ነገር እስከዛሬ ምን እንደሆነ በትክክል ኖሮ ያየው አለ? (የ3000 ዘመን ታሪክ የጭቆና ታሪክ ነው እንል የለ) ካየ ነጻነት ነበርና ነጻነት ያስፈልገኛል አይልም። ከነበረበት ለምን ወደመረገጥ መርጦ ይመጣል? ካልነበረበት ደሞ ምን እንደሆነ አያውቅምና እንዴት ሊመኘው ይችላል? ግን በዚህ ቃል በነዚህ አራት ሆሄያት ብዙ ብዙ ሕይወት ያልፋል።
ብዙ ብዙ ሰው ይጠፋል።
ብዙ ብዙ ትሸወዳላችሁ።
***
የስንብት ቀለማት
3 738
"መርታት፤ መረታት፤ መገገም" በ በዕውቀቱ ስዩም
የሆነ ጊዜ ላይ ረከቦት ጎዳና፤ ባንዱ ካፌ ውስጥ፤ ቡና ስጠጣ፤አንድ ጎረምሳ ወደ ተቀመጥኩበት መጣ፤ልጁ ግድንግድ ነው፤ጎልያድ ዳዊትን አዝሎ ያክላል፤ እኔ ደሞ እንደምታውቁኝ ነኝ፤ከፊቴ ሲቀመጥ የሚጥሚጣ ብልቃጥ አከልኩ፤ ግብዳው ብዙ ሳይቆይ የምነት ክርክር ጀመረ፤በተቻለኝ መጠን ወደ ክርክሩ ላለመግባት ተግደረደርኩ፤ ሰውየው ግን አልከራከርም ብለው ንቀኸኝ ነው ብሎ ሊደበድበኝ ይችላል፤ከጥቂት ጊዜ በሁዋላ የነደደ ክርክር ውስጥ ራሴን አገኘሁት፤ሰውየው አረፋ እየደፈቀ ተተጋተገኝ።
ጎረርህ በሉኝ ብትፈልጉ ! አስር ቀቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ልጁን መፈናፈኛ አሳጣሁት፤ መግብዳው ክርክክራችንን ያሳረገው እንዲግ በሚል ቃል ነው፤
“‘ ልታሳምነኝ አትድከም ! እገግምብሃለሁ”
አሁን ሳስበው፤ አስተምረዋለሁ ያልሁት ያ ግብዳ ሰውየ ትልቅ ቁምነገር አስተምሮኛል ፤ ባፍለኝነቴ ፤የሰው ልጆች ለሀቅ እና ለምክንያታዊነት የሚኖሩና የሚሞቱ ይመስለኝ ነበር፤ሰዎች በውይይት የሚያምኑ ይመስለኝ ነበር፤ አዋቂ ባላዋቂ ላይ የሚበረታ፤፤ እውነት የያዘ ሰው ሀሰተኛውን የሚረታ ይመስለኝ ነበር፤ እየኖርኩ ስሄድ ይሄ እምነቴ ጥሎኝ ሲመንን ታዘብኩት፤ አብዛኛው ሰው ለውነት ደንታ የለውም፤ አብዛኛው ሰው፤ ስለ እውቀት ስለተጨባጭ መረጃ ግድ አይሰጠውም፤ በተፈጥሮ ይሁን በልማድ እንጃ፤ አብዛኛው ሰው ችኮ መንቻኮ ነው፤ ልብ አድርቅ ነው፤ የውይይት አላማ ከላይ ከላይ የእውቀት ልውውጥ ቢመስልም ውስጥ ውስጡን መሸናነፍ ነው ፤ሽንፈት መራራ ፍሬ በሚያስለቅምበት አገር ውስጥ ደሞ፤ ማንም መሸነፍ አይፈቅድም፤ ብታሸንፈው ተሸነፍኩ አይልህም፤ ተዘርሮም ይፎክርብሃል! ይገግምብሃል!
ቀኛማች በላይነህ የተባሉ ባላባት በዳግማይ ምኒልክ ጊዜ ነበሩ፤በዘመናቸው፤ ከስራቸው ጋራ የማይመጣጠን አንጀባ ስለሚያበዙ ” ቁንን በላይነህ” የሚል ቅፅል ስም ተሰጥቱዋቸው ነበር፤የሆነ ጊዜ ላይ ከሸገር ወደ ጎንደር ይሄዱና ባንድ ደብር ውስጥ ይስተናገዳሉ፤ቁንን በላይነህ ፊደል ያልቆጠሩ ጨዋ ቢሆኑም በሊቃውንቱ ፊት የተማሩ ለምምሰል ተጋጋጡ፤ ዳዊት እየደገምኩ ነው ለማለት ዳዊት ገለጡ፤ ግን የማያውቁትን ዳዊት ገልብጠውት ነበር የያዙት፤
ይህንን የሾፈ አንድ ደብተራ ሳቁን በጋቢው ለመጨቆን እየሞከረ፤
“ጌቶች ዳዊቱን ዘቅዝቀው ነው የያዙት” ቢላቸው፤
))“ጠላቴን እንዲዘቀዝቅልኝ ብየ ነው! ጠፍቶኝ እንዳይመስልህ ” አሉት ይባላል፤
ቁንን በላይነህ አላዋቂ ናቸው፤ግን አላዋቂነታቸውን አምነው ማረም አይፈልጉም፤ ማንን ደሰ ይበለው ብለው!?ተሸንፈው፤አሸናፊ መስለው ቆመዋል! ገግመዋል!
ታዋቂው የታሪክ ፀሀፊ ተክለፃድቅ መኩርያ በግለታሪካቸው ላይ አንዲት ገጠመኝ ጠቅሰዋል፤ ገጠመኚቱን በኔ አማርኛ ሸክሽኬ ሳቀርባት ይቺን ትመስላለች፤ የሃይለስላሴ ባለስልጣኖች በደርግ ወጣት መኮንኖች እየተለቀሙ በሚታጎሩበት ቀውጢ ወቅት ፤ ሁለት ወጣት ታጣቂዎች ተክለፃድቅ ቤት ድረስ ይመጡና በቁጥጥር ስር ያውሉዋቸዋል፤ በገዛ መኪናቸው፤ይዘዋቸው በሚሄዱበት ጊዜ አንዱ ታጣቂ ለጉዋደኛው_-_
“ከተማ ይፍሩ በቁጥጥር ስር በዋለበት ወቅት አስር ሚሊዮን ብር በኪሱ ተገኘ” ይላል፤(ከተማ ይፍሩ የዘመኑ ባለስልጣን ነው)
“ይሄን የሚያክል ገንዘብ በኪስ ሊያዝ አይችልም” አሉ ተማራኪው ተክለፃድቅ፤
“ባይኔ በብረቱ ያየሁትን” አለ ወታደሩ፤
“ይህን ጊዜ” ይላሉ ተክለፃድቅ መኩርያ “ ይህን ጊዜ ዝም አልኩ፤”
ዝም ባይሉ ኖሮስ?
ታጣቂው ይገግማል!
ጠመንጃውም ያስገመግማል፤
አስከሬን ይለቀማል
እና ይሄ ማን ይጠቀማል?
አንዳንዴ በፌስቡክ ማለቂያ አልባ ክርክር ውስጥ ዘልየ ለመግባት ሲቃጣኝ እኒህን ነገሮች አስታውሳለሁ፤አንዳንዴ ዝም አልክ ማለት እውነቱን ከመናገር ተቆጠብክ ማለት አይደለም፤ሃይልህን ቆጠብክ፤ሰላምህን ቆጠብክ፤ ህይወትህን ቆጠብክ ማለት ነው።
3 738
እሷ. . . .
በ አዳም ረታ
. . . እየተስለመለምኩ ፊትዋን በእጆቼ ያዝኩ። አሟልጮኝ እንደሚወድቅ ሁሉ። እንደሚፈስ ሁሉ።
ፊቴ ገነት ላይ ወደቀ – አፌ ውስጥ ከንፈሮቿን እንደ ቢራቢሮ ክንፎች (እንዲህ የሚቀስሙት አበባ ላይ አርፈው ምናልባትም በወለላ ሰክረው ልባቸውን ነስቷቸው እያሉ ክንፎቻቸውንም እንደመፅሐፍ ገጾች ገጥመው – በቀስታ ከበስተሁዋላቸው ተጠግቼ በአውራ ጣቴና በአመልካች ጣቴ አጣብቄ እንደማጠምዳቸው) ይዤአቸዋለሁ።
በገላዬ ውስጥ አየር እንደሚያልፍ ሁሉ ነበር።
እንኮይ እንኮይ ከሚል . . . . . . . ውሃ እናቶች ከሚከናበሉበት የአምቦ ምንጭ ውስጥ እንደተኛሁ ነበር።
አይኖቿ ወተት መሃል እንደወደቁ አጋሞች ነበሩ።
ልቤ እንዳይፈነዳ እጸልያለሁ፤ ልቤ እንዳይፈርስ እንቀጠቀጣለሁም።
ጣቶቼ በጀርባ ቆዳዋ ላይ ተማስለው እንደተኙ ነበሩ።
ደማችን ተደባልቆ ሲፈስ – ፈረሰኛው ከተራሮች በላይ ነበር።
መዝፈን አማረኝ።
እንደ ጥላሁን መጮህ አማረኝ።
እንደ አስቴር መተከዝ አማረኝ።
እንደ ሙሉቀን መጨፈር አማረኝ።
ከእግሮቻችን ስር የዚህች ከተማ የልብ ምት ከተቀበረበት ይሰማኛል።
የዚህች ከተማ የልብ ምት ከተቀበረበት ይሰማኛል።
የዚህች ከተማ የልብ ምት ከተቀበረበት ተሰማኝ መሰል።
በከንፈሮቼ ተሰማኝ መሰል።
በጉበቴ፣ በጣፊያዬ ተሰማኝ መሰል፣
በብልቶቼ ሁሉ ተሰማኝ መሰል።
ገና ከሩቅ እንደሚሸት
ትኩስ
ሕብስት
ነበረች።
ይቺ ልጅ ተጣጥፋ አፌ ውስጥ እንደ ናና ከረሜላ ነበረች።
ናናዬን አገኘሁ
በፍቅር ልምጠጣት፣
መይሳው ዕድል ነው
ወደ እኔ ያመጣት።
ከዚህች አስደሳች የሚገድበኝ ማን(ምን) ነበር?
ከዚህች ከገነት የሚያቆመኝ ማን(ምን) ነበር?
እግዚአብሔር ተመልሶ እስኪመጣ እስከ ፍካሬ ኢየሱስ አቅፌአት ልጠብቀው ተመኘሁ። ልቦቻችን እጆች ቢኖሯቸው ደረቶቻችንን ሰብረው ወጥተው ያጨበጭባሉ።
…….. እንዴት ይቀላል ፍቅር! ደ’ሞ እንዴትስ ይከብዳል!
እንዴትስ ትንሽ . . . ደ’ሞ እንዴትስ ትልቅ ነው።
አንጀቴ እስዋን ምን ላድርግሽ? አላት. . . .አንጀቴ በእርዝመቱ ተንሰፈሰፈ. . . .
ምናለበት ትንሽ በሆንሽ?. . . .ምናለ እጆቼ መሐል ሀባ ዘቢብ ብትሆን ኖሮ. . . .
ውጬአት ብተነፍስ ተመኘሁ . . .
ቢሉኝ –
ውጠሀት እንደሆን ትፋት እንያት
ምድር ላይ ያለችው እሷው አንዲት ሴት
ቆዳዬ ስር በደም ሥሬ ግድግዳዎች ላይ እንደረቂቅ ነገር ተሸክሜአት እንደምዞር ገባኝ. . . .
ቆዳዬ ስር ደም ሥሬ ግድግዳ ላይ ከውስጥ ተለጥፋ. . . . አይፍቁኝ፣ እሷን አይበጡኝ ነገር።
. . . .እየተስለመለምኩ ፊቷን በሁለት እጆቼ ያዝኩ። ሾልካ እንደምታመልጠኝ ሁሉ፣
ኮለል ብላ እንደምታመልጠኝ ሁሉ. . . .
ፊቴ ፊቷ ላይ አረፈ. . . . .
***
ግራጫ ቃጭሎች
3 738
በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በሆስፒታሎች (በለይቶ ማከሚያ ) ውስጥ ላሉ ህሙማን እየተሰጡ ያሉ መድሀኒቶች
1.ቪታሚን c 1000
2.ቪታሚን E
3.ለ 10...11 ሰአታት ለ,15ደቂቃዎች የፀሃይ ብርሃን ላይ መቀመጥ
4 እንቁላል መመገብ
5. እረፍት መውሰድ (ከ7..8 ሰአታት መተኛት )
6.1.5 ሊትር ውሃ በየቀኑ መጠጣት
7.ሁሉም ምግቦች ሞቃት መሆን አለባቸው (ቀዝቃዛ አደለም )
በሆስፒታል ውስጥ የሰውነትን የመከላከል አቅም ለማሳደግ እየተደረገ ያለው ይሄ ነው።
# የኮሮና ቫይረስ ph
ከ 5.5....8.5 ድረስ ተለዋዋጭ ነው
ስለዚህም ቫይረሱን ለመግደል ከቫይረሱ አሲድነት በላይ የሆኑ የበለጠ የ አልካላይን ይዘት ያላቸውን ምግቦች መመገብ ነው
ለምሳሌ
አረንጓዴ ሎሚ....9.9 ph
ቢጫ ሎሚ......8.2 ph
አቮካዶ...15.6 ph
ጋሪክ...13.2ph
ማንጎ...8.7ph
ታንግራይን...8.5ph
ፓይን አፕል ....12.7 ph
ወተር ክረስ...22.7ph
ብርትኳን ....9.2ph
የቫይረሱ ምልክቶች
1.የጉሮሮ ማሳከክ(መቁሰል)
2.የጉሮሮ መድረቅ
3.ደረቅ ሳል
4.ከፍተኛ የሆነ ሙቀት
5.ለመተንፈስ መቸገር
6.ለማሽተት መቸገር
እና ሎሚ በሞቀ ውሀ መጠጣት ቫይረሱ ገና ሲጀምር ሳንባ ጋር ሳይደርስ እንዲገለው ይረዳል ።
ይሄንን መረጃ ለራሳችሁ አታስቀሩት
ለቤተሰቦቻችሁ እና ጓደኞቻችሁ አጋሩት።
ጥሩ ጤና እና ረጅም እድሜ እመኝላችኋለሁ።
Join
@abrhott
3 738
Police: You are under arrest!
Me: Why?
Police: Because you transport 6 people at once on a single motorcycle.
Me: Did you say six?
Police: that is correct, six!
Me: Damn it, we have lost Marta.
3 738
የኒቼ እና የኦሾ ቅራኔ ምን ነበር...?
፨፨፨
በፍልስፍናው ዓለም በሃይማኖት እይታ ላይ ጥሩ ነገር ያላበረከቱ ወይም ክፉኛ ሃይማኖትን እና አምላክን ተዳፍረው አልፈዋል ከሚባሉት ፈላስፋዎች መሃል
ፍሬድሪክ ኒቼ እና ራጅናሽ ኦሾ ግንባር ቀደሞቹ ናቸው ።
ፍሬድሪክ ኒቼ ምን ነበር ያለው...?
" አምላክ ሞቷል(God is dead) ዛሬ እናንተ አምላክ የምትሉት በሰዎች አስተሳሰብ ውስጥ ተፈጥሮ አድጎና ጎልምሶ እንዲሁም አርጅቶ ያለፈ አስተሳሰብ ነው። "
፧
በነገራችን ላይ ፍሬድሪክ ኒቼ የሱ ቀዳሚ የነበረው ፈላስፋ #አርተር ሾፐንሀወር አድናቂ ነበር እንዲሁም በፍልስፍና እይታዎቹ ላይም የሱ ተጽእኖ አለበት ይባላል...አርተር ሾፐን ሀወርም በፈጣሪ ህልውና የማያምን እንዲሁም ለስነ መለኮት መምህራን ከፍተኛ ጥላቻና ንቀት የነበረው ፈላስፋ ነበር ።
ኒቼ ይህንን ሃሳብ ማለትም "God is Dead" የሚለውን እይታውን "Joyful wisdom" በሚለው መጽሐፉ ላይ ለሕትመት ባበቃ ሰአት ከብዙ የሃይማኖት ተከታዮች ተቃውሞ ደርሶበት ነበር...ይህንን ንግግሩንም አንስቶ ራጅናሽ ኦሾ እኔም በጊዜው ብኖር እቃወመው ነበር ይለናል።
፧
ይህንን እይታም ያስቀምጣል...
<< ፍሬድሪክ ኒቼ አምላክ ሞቷል ሲል ብዙ እምነቶች ተቃውሞ አንስተውበት ነበር። እኔም እቃወመዋለሁ ምክንያቱም እኔ ደግሞ የምለው እንኳን ሊሞት መጀመርያም #አልነበረም ነውና >> ይለናል ይህንን ንግግሩን ብርሃነ ኅሊና የሚለው መጽሐፍ ላይ እናገኘዋለን ።
ባብዛኛው ሰዎች ራጅናሽ ኦሾን የሳይኮሎጂስቱን ሲግመን ፍሩድ እና ፍሬድሪክ ኒቼን ፍልስፍናዎች ያስተጋባ ብለው የሃሰት ካባ ሊያለብሱት ቢሞክሩም እሱ ግን ከነሱም የተለየ አስተሳሰብ እንደነበረ ካሳየባቸው ንግግሮቹ አንዱ ይህ ነበር ።
፧
#አሁን ታድያ ማን ይፍረድ እንደ ኒቼ የፈጣሪን ህልውና የተገዳደረ ፈላስፋ የለም የሚባለው ሚዛን ይደፋ ይሆን የኦሾን አይን ያወጣ #ክህደት በሉት #እውነት አፍጥጠን ስናይ...?
መልሱን ለህሊናችሁ...!!
፨ የዚህ ጽሑፍ አላማ የፈጣሪን መኖር መካድ ሳይሆን በሁለቱ ፈላስፎች መሃከል በሀለዎተ ፈጣሪ ዙርያ ያለውን እይታ ማሳወቅ ነው። በሌላ እንዳይተረጎም...
ግብዓት ምንጮች ፦ ጥበብ ከጲላጦስ እንዲሁም ብርኀነ ኅሊና መጽሐፍት
3 738
የፈላስፋው ፍርድ
"የሰው ልጅ #ለተፈጥሯዊው_ሕግ የሚገዛበትን አዕምሮ #በዓለማዊው_ሕግ በከለው"
/ ላኦ-ዙ /
.....ላዎ-ዙ በመላዋ ቻይና ጠቢብ ለመሆኑ በተመሰከረለት ዘመን ላይ ቆሞ ነበር ። ይኸን የሰማው የቻይና ንጉስ ላኦ-ዙን አስጠርቶ በታላቅ ትህትና ከተቀበለው በኋላ ..."እባክህ!የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዋና ዳኛ እንድትሆን እለምንሀለሁ?"ሲል የሹመት ጥያቄ አቀረበለት ።
፨ ላኦ-ዙ ግን "ንጉስ ሆይ! ተሳስተሀል!ለዚህ ቦታ የሚሆን ትክክለኛው ሰው እኔ አይደለሁም ፤ ልቅርብህ...ሌላ ሰው ፈልግ!" አለው ።
ንጉሱ ግን የላዎ-ዙን እምቢታ መቀበል ቀርቶ መስማት እንደማይፈልግ ነገረው፦"ከአንተ በቀር ማንንም ሰው በዚህ ወንበር ላይ ማስቀመጥ አይቻልምና የሰጠሁህን ሥልጣን ግድ መቀበል አለብህ"ሲል ወተወተው ።
፧
፨ ላዎ-ዙም፦ "እንግዲ አልሰማህም የምትል ከሆነ በመጀመሪያው ቀን ችሎት የምፈፅመውን ስትመለከት መሳሳትህ ይገባሀል ። ከትህትና በመነጨ ወይም ለአንተ ካለኝ አክብሮት ለቦታው የምገባ አለመሆኔን ነገርኩህ እንጂ ፣ እውነቱ ግን መንግስትህ የዘረጋው ሥርዓት የተሳሳተ መሆኑን ማወቄ ነው!እናም በቦታው ላይ ወይ እኔ እኖራለው ፤ ወይም ደግሞ የአንተ ህግና ሥርዓት። ፣ እንዲሁም እሱን የሚከተለው ሕዝብህ ይኖራል"በማለት ሥልጣኑን ለመቀበል ተስማማ ።
፨ ላዎ-ዙ ጊዜ ሳያባክን በነጋታው ችሎት ተቀመጠ ። ተከሻሱ ሰው በቻይና ዝነኛ ከነበረ ሀብታም ብዙ ገንዘብ ዘርፏል ተብሎ ከፊቱ ቀረበ። ላዎ-ዙ የተከሳሹን ወንጀል አድምጦ ሲያበቃ ፍርድ ሰጠ ። "ከሳሽም ተከሳሽም እያንዳንዳቸው በስድስት ወር እስራት እንዲቀጡ ፈርጃለሁ"።
፧
ከሳሽ የሰማውን ማመን አልቻለም ። ምናልባት ላኦ-ዙ ክሱ አልገባው ይሆናል ፤ አልያም እርጅና እየተጫጫነው ስለሆነ መርሳት ጀምሮት ይሆናል ፥ ወይም ደግሞ ለስራው አዲስ ስለሆነ ...ብቻ አስቦ ሲጨርስ ፈገግ ብሎ፦"ክቡር ዳኛ!ምን እያሉ ነው? ገንዘቤን የተዘረፍኩት እኮ እኔ ነኝ ፤ ይሄ ምን አይነት ፍርድ ነው? ሀብቴን ተዘርፌ እንዴት እንደገና ከዘረፈህ ሰው ጋር አብረህ ወህኒ ውረድ እባላለው ? ግዴለም የሆነ ቦታ አልገባዎትምና ያልተገባ ፍርድዎን ያስተካክሉልኝ!"
፨ላዎ-ዙ ፈገግ ብሎ ምክንያቱን አስረዳው፦"ይልቁንስ ያልገባህ አንተ ነህ!ያልተገባ ፍርድ የሰጠሁ መስሎህ ከታየህ ምናልባት ያልተገባ ፍርድ የሰጠሁትም ገንዘብህን ዘርፏል በተባለው ሰው ላይ ነው ። የአንተ ወህኒ መውረድ ግን ከሌባው በላይ የተገባ ሆኖ አግኝቼዋለው ። ምክንያቱም አንተ የበዛ ሀብት ለራስህ ያከማቸኽው ፥ ሌላው ሰው ማግኘት የሚገባውን እያሳጣህ ነው...ብዙዎች በችግር የሚማቅቁባት በዚህች ሀገር አንተ ገንዘብ በገንዘብ ላይ ታከማቻለህ ። ለምን ይሆን? አየህ! የአንተ ከልክ ያለፈ ስግብግብ ባህሪህ እነዚህን ሌቦች ፈጠረ! ስለሆነም ሌባው በድርጊቱ ፤ አንተ ደግሞ ሌባ በመፍጠርህ እኩል ፍርድ ይገባችኋል ! የመጀመሪያው ወንጀል ፈጣሪ ግን አንተ ነህ ።
፧
ላዎ-ዙ፦"የሰውን ልጅ ዓለማዊው እውቀትና ሕግ ሳይሆን የተፈጥሮ ሕግ ሊገዛው ይገባዋል" የሚለው ለዚህ ይመስላል ። ይህ ከላይ የተሰጠው ፍርድ መለስ ብለን ብንቃኝ የሰው ልጅ ተፈጥሮ በውስጡ ያስቀመጠችውን የእኩልነት ፣ የመፋቀር ፣ የመተሳሰብ ፡ባህሪይ እንዲጥል ያደረገው ራስ ወዳድነት በመስፈኑ ነው ። የራስ ወዳድነት ምንጩ ደግሞ ይህንን ስሜቱን የሚጠብቅለት ሰው ሰራሽ ሕግ መፈጠሩ ነው ። ሀብትን ለማንም ሳታካፍል ማከማቸት እንደምትችል እርግጠኛ ያደረገህ ማንም እንደማይወስድብህ የሚጠብቅልህ ሰው ሰራሽ ሕግ መኖሩ ነው ። ለዚያም ነው "የሰው ልጅ ለተፈጥሯዊው ሕግ የሚገዛበትን አዕምሮ በዓለማዊው ሕግ በከለው/corrupt አደረገው" የሚለን ላዎ-ዙ ።
📚📚📚
ምንጭ ፦ ኃይለጊዮርጊስ ማሞ-ፍትህ መፅሔት ቁ.57(የተወሰደ)
3 738
~ፍቅር ፈራን~
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን።
©ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
Join us @abrhott
3 738
እንደምን አደራችሁ!
በሀገራችን በኮሮና ቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1,486 ደርሷል ።
ከሰሞኑ ከጤና ሚኒስቴር የሚወጣው እለታዊ መግለጫ እንደሚያሳየው ቫይረሱ የተገኘባቸውን አዲስ ታማሚዎችን ከማስታወቅ በዘለለ አንድ፣ ሁለትና ሶስት እያለ በቫይረሱ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎችን እያረዳን ይገኛል።
የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክና ከህመምተኛው ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸ ነገር ግን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም እንዲሁ መበራከቱን እየተመለከትን ነው።
ይህ ማለት በየትኛውም ቦታና በማንኛውም ጊዜ ከማንኛውም ሰው የኮሮና ቫይረስ ሊይዘን ይችላል ማለት ነው።
ስለሆነም እርሶ ሁል ጊዜም ማድረግ የሚገባዎትን ጥንቃቄ እያደረጉ እራሶን፣ ቤተሰቦንና ፣ሌሎችን ከኮሮና ቫይረስ ይጠብቁ።
በያላችሁበት በሰላም ዋሉ!
3 738
Him : Hi baby,
you are look so beautiful
Her: Hi, You look so handsome.
Him:Anyway, I LOVE YOU .
Her: Thanks.
Him: I want you to be my
girlfriend?
Her:Accepted, but no sex.
Him:Why, babe?
Her:because, i want to keep it
for my future husband.
Him:OK Agree, but no money
Her:Why?
Him:because, i want to keep it for my future wife
3 738
አስተማሪ አጭር ታሪክ .!
አንድ ቤተሰብ ውስጥ አባት ከሞተ በኋላ የሚመገቡት እስኪያሳስባቸው ድረስ ይቸገራሉ ። አንድ ጌጣጌጥ መሸጫ ሱቅ ያለው ዘመድ አላቸው እና እናትየው ለልጇ ያላትን ለረጅም ጊዜ የተቀመጠ የአንገት እና የጣት ዳይመንድ ጌጥ ሰጥታው እዛ ሱቅ ሄዶ እንዲሸጠው ትሰጠዋለች፡፡
ልጁ የተባለው የዘመድ ጌጣ ጌጥ ሱቅ ሄዶ እናቱ እንደላከችው አስረድቶ እንዲገዛው ይጠይቃል፡፡ ሰውየውም ከመረመረው በኋላ "አሁን ገበያው ወድቋል ትንሽ ግዜ ጠብቀን በጥሩ ዋጋ
እንሸጠዋለን፡፡" ብሎ ይመልስለትና የተወሰነ ገንዘብ ከሰጠው በኋላ ለልጁም እስከዛው በየጊዜው እየመጣ እዛው ሱቅ ስራ እንዲሰራ ያደርጋል ።
ልጁ በየግዜው እየሄደ የጌጣጌጥአሰራር ጥበብ ተካነ ፡፡ የገበያም እውቀት አካበተ በስራውም ታዋቂም ለመሆን ቻለ ፡፡
ይሄኔ ባለሱቁ "የሆነ ግዜ ልትሸጠው አምጠተኸው የነበረውን ጌጥ አሁን አምጣው አሁን ገበያው ጣራ ነክቷል እና ታተርፋላችሁ ፡፡ ብሎ ይልከዋል ፡፡ ልጁ እንደተባለው እቤት ሄዶ ጌጣጌጡን በአይኑ በማየት ብቻ አርቴፊሻል ሆኖ ያገኘዋል፡፡
ወደ ሱቅ ይመለሳል ፡፡ባለቤቱ ይጠይቃል "ዳይመንዱስ ?" ልጁም "አርቴፊሻል ነው ግን እያወክ ያን ጊዜ ለምን አልገርከኝም ?አሁንስ ለምን ላከኝ?ሲል ጠየቀው፡፡ ዘመዱም "ያን ጊዜ ለረጅም ዘመን ዳይመንድ ነው ብላችሁ ያመናችሁትን ነበር ይዘህ የመጣኸው ፡፡ያለምንም እውቀት፤ ባዶህን እና በሙሉ እምነት ብቻ ! በሰዓቱ ባለህበት ሁኔታ ልክ ያልሆነ ነገር ለማስረዳት ይከብዳል፡፡ ምናልባት ላታምኑኝ ትችሉ ነበር ፡፡ምናልባትም ባለመግባባት የሚፈጠሩ የቃላት ልውውጥ አሁን ላይ መጥፎ ስሜት ሊያሳድርብን በቻለ ነበር ።" ብሎ በትህትና መለሰለት፡፡
እንዲህ ያለ የላቀ ስብዕና ባለቤትና ነገሮችን
በብዙ አቅጣጫ የምናይበት ህሊና ይስጠን፡፡
በቅንነት ሼር ያድርጉልኝ 👇
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
ይድረስ ለጥቁሩ ሰው!
..ይኸውልህ ወንድሜ - ጠላትህን ሳታውቅ - አንተ ካንቀላፋክ፥
ገዳይ ዘራፊህን - ለማየት ተስኖህ - ዐይንህን ካልገለጥክ፥
እንደ ዶሮ አንገት - ጉሮሮኽ ላይ ቆሞ - ቢገድልህ አይክፋክ!
፤፤፤
አንተ ሚያስጨንቅህ - የጎሣ ጸብ ሆኖ - አንድነት ስላጣክ፥
የአፍሪካ ልጅ ሲናቅ - ተረግጦ ሲገደል፥
በአደባባይ መሐል - በነጭ ሲጨፈለቅ - እውነታው ካልገባክ!!!
ኣንድ ባንድ እያሉ - ሲፈጁህ እንዳይክፋክ፤
(ምስሉ ከሰሞኑ ኣንድ የአሜሪካ ነጭ ፖሊስ ጥቁር አፍሪካ አሜሪካዊን በጠራራ ጸሐይ፣ በአደባባይ ጉሮሮውን አፍኖ ሲገለው የሚያሳይ ምስል ነው። ያገሬ ህዝብ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን ጥቁርነታቸውን ለመቀበል እንደሚቸገሩ አውቃለሁኝ። ነገር ግን ወደድንም ጠላንም ድብን ያልን ጥቁሮች ነን። ዓለም የሚያውቀን በፈረንጅ ወይ በአረብ ወይ በላቲንነታችን ሳይሆን በጥቁርነታችን ነው። አፍሪካውያን ነን። በታሪክ መሰረት ያፍሪካ ኃያልነት ምንጩ ደግሞ ኢትዮጵያ ነበረች። አሁን ግን እንኳን ለሌላው ልንተርፍ ለራሳችንም በጎሣ ተከፋፍለን፣ ከእውቀትና ከሥራ ሰንፈን ቁጭ ብለናል። ፈረንጆቹ በበኩላቸው ከጥንት እስካሁን ለኛ ተኝተውልን አያውቁም። ጥቁርነት እንደ እኩል ሰውነት አይቆጥሩም። አንጡራ ሐብታችንን ከስር ለመበዝበዝ ከላይ ቢስቁልንና በእጅ መንሻ ቢደልሉን እውነት እንዳይመስላችሁ። ያገሬ ህዝብ እባክህን እውነተኛ ጠላትህን እወቅ! ከወንድምህ ጋር መባላትህን አቁምና አገርና አህጉርኽን አጠንክር!!!
(ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አዕምሮ)
@EliasGebru
