en
Feedback
አብርሆት

አብርሆት

Open in Telegram

ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23

Show more
3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
" የሰው ልጅ ታላቅነት የሚገለጸው በሚያገኘው ነገር ሳይሆን ለማግኘት በሚያሳየው ጽናት ነው ። " / ካህሊል ጂብራን / @abrhott @abrhott @abrhott

የማልቀስ አስገራሚ የጤና ጥቅሞች ለቤተሰባችን ********************** ብዙዎቻችን ማልቀስ የጤና ጥቅም እንዳለው አናውቅም ይሁን እንጂ ማልቀስ ጤናችን ላይ ስላለው ጥቅም ልናካፍላችሁ ወደድን እነሆ፡- • መርዛማ ንጥረ ነገሮችን ከሰውነታችን ማስወገድ ( እንደ ኦክሲቶሲን እና ኢንዶርፊን የመሰሉ ኬሚካሎች) • ባክቴሪያዎችን ይገላል • እይታን ያሻሽላል • ሙድን (ስሜትን) ያስተካክላል • ጭንቀትን ያስታግሳል • ከሰዎች ጋር ያለንን ግንኙነት ያስተካክላል • እንቅልፍን ይረዳል ወይም እንድናገኝ ያደርጋል • ህመምን ያስታግሳል ************************* መልካም ቀን 😊

☀️ እስኪ ነጋ ጠብቃ … እኔ ነኝ ፀሐይ ትላለች 😂

#ሜሎስ የሚለው የይስማዕከ ወርቁ መጽሐፍ ላይ የተሳሉ ሰዎች(ገጸ ባህሪያት) እንዲህ ሲሉ ያወጋሉ... 📚📚📚 " ...ይህች አገር የምትለወጠው በግለሰቦች የግል ጥረት ነው። ግለሰቦች ካልተለወጡ አገሪቷ አትለወጥም።" " ሀገሪቷ የምትከተለው ሥርዓት ቡድንን እንጂ ግለሰብን የማያበረታታ መሆኑን ረሳሽው እንዴ?" " አውቃለሁ ግን አንድ ነገር ማወቅ ነበረባቸው። በመንጋ ማሰብ አይቻልም። መንጋ መንጋጋት እንጂ ማንጋት አይችልም። ይህች ዓለም የተለወጠችው አንዳንድ ግለሰቦች ባመነጩት የሀሳብ ወገግታ ነው። ሰው በመንጋ ማሰብ ሲጀምር ጭንቅላቱ በስብሷል ማለት ነው። በጋራ ታስቦ የተፈታ ችግር ሰምተህ ታውቃለህ? " " እንዲያውም....የዝህች አገር ችግር ኮታና ኮሚቴ ነው። ችሎታ ሳይሆን የኮታ ኮተት ነው እስከዛሬ ድረስ በንኩቲት ሲያስኬዳት የኖረው " 📚📚📚 ምንጭ 📖 ሜሎስ...ገጽ 76 ደራሲ ✍ ይስማዕከ ወርቁ ፨ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ እኔ ዛሬ ያለንበትን ሁኔታም አየዋለሁ የናንተን ባላውቅም...!! 📚 ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል ✍ ንባብ ለሕይወት @abrhott @abrhott @abrhott

"መኖር ማለት አለመሞት ከሆነ እስትንፋስ ያለው ሁሉ እየኖረ ነው። ግን መኖር ማለት እራስን መሆን፣ ለዓላማ መቆም፣ ህሊናን አለመዘንጋት፣ ፍርድን አለማጓደል፣ ለራስ ብቻ ሳይሆን ለሌላው እራስን መስዋዕት ማድረግ ብሎም አርአያ የሚሆን ነገር ጥሎ ማለፍ ከሆነ ስንቶቻችን ነን በህይወት ያለነው???" ዶክተር ምህረት ደበበ @abrhott @abrhott @abrhott

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኖርዌይ፣ ኦስሎ የኖቤል የሰላም ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፡- • የኖርዌይ የኖቤል ኮሚቴ ለሰጠኝ እውቅና አመሰግናለሁ፡፡
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኖርዌይ፣ ኦስሎ የኖቤል የሰላም ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፡- • የኖርዌይ የኖቤል ኮሚቴ ለሰጠኝ እውቅና አመሰግናለሁ፡፡ • ለኢትዮ-ኤርትራ የሰላም ስምምነት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሰላም ቁርጠኝነት ወሳኝ ነበር፡፡ • ይህንን ሽልማት የአፍሪካ ህዝቦችና የዓለም ህዝቦችን ወክዬ ነው የምቀበለው፡፡ • ከ20 ዓመታት በፊት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የሬድዮ ኦፕሬተር ነበርኩ፡፡ • ጦርነቱ በርካታ ቀውሶችን አስከትሎ ነበር፡፡ • በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ለሁለት አስርት ዓመታት ሰላም አልነበረም፤ ሰዎች ተለያይተዋል፤ በርካታ ሰራዊት በሁለቱ አገራት ድንበር ላይ መሽጎ ነበር፡፡ • ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆንኩ በኋላ የሁለቱ አገራት ህዝቦች ልዩነት መቆም እንዳለበት ወሰንኩ፡፡ • ሁለቱ አገራት ጠላቶች እንዳልሆኑ ይልቁንስ ድህነት የጋራ ጠላታችን እንደሆነ አውቀን ለአገራቱ እና ለቀጠናው ብልፅግና መስራት ጀመርን፡፡ • መደመር አገር በቀል ሀሳብና የጋራ ብልጽግና ላይ ያተኮረ ፍልስፍና ነው፡፡ • የመደመር ጽንሰ ሀሳብ እንደ ዘር ውስጤ የበቀለው በኦሮሚያ ክልል በምትገኝ የትውልድ መንደሬ በሻሻ ውስጥ ነው፡፡ • በመደመር ጽንሰ ሀሳብ ውስጥ እኛና እነሱ የሚባል ነገር የለም፡፡ • ኢትዮጵያውያን በአንድነት በመቆማችን ለዓመታት ነፃ አገር ሆነን ቆይተናል፡፡ • የአፍሪካ ቀንድ የአሸባሪዎች ቀጠና እንዲሆን አንፈልግም፣ የሰላም ቀጠና እንጂ፡፡ • ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሰላም ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ • ለዴሞክራሲ ግንባታ መንገድ ዘርግተናል፤ በቅርቡ ነፃና ፍትሓዊ ምርጫ እናካሂደለን፡፡ • ለሁሉም ዜጎቿ እኩልነት መረጋገጥ አብረውኝ እንዲሰሩ ለኢትዮጵያውያን ጥሪ አቀርባለሁ፡፡ (ኢቢሲ)

"የስልጣኔ ትልቁ መለኪያው ገንዘብ ሳይሆን ለሰው ልጅ ያለን ክብርና እውነተኛ ሰባዊነት ነው።" በቅንነት ሼር ያድርጉልኝ 👇 @abrhott

ሰዎች ከአንገት በላይ ከአላደጉ ከአንገት በታች ነው የሚኖሩት ከአንገት በታች ደግሞ ምንም ማሰብ የሚችል ነገር የለንም ።ስሜትን መግዛት የሚችል ነገር የለንም''

“ያገኘውን ሁሉ የሚበላ ሰው ጤናማ እንደማይሆን ሁሉ የሰማውን ሁሉ የሚወስድ ሰው አእምሮው የተበላሸ ይሆናል፣ አንድ ግለሰብ በምግብ ቢመረዝ ቢበዛ ራሱን ነው የሚገድለው፣ በሀሳቡ ቢመረዝ ግን ራሱን ብቻ ሳይሆን አከባቢን ያጠፋል፤ አከባቢን ከማጥፋት ራሱን ለመታደግ አእምሮውንና ውስጡን ማጽዳት ይኖርበታል” ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

When they say, Behind Every Successful Man there is a Woman. They mean His Mother Not you....sit down

መሠላል ስትወጣ የጫማህን ንጽህና አረጋግጥ ምክንያቱም ስትወጣ የረገጥከውን ስትወርድ ትጨብጠዋለህና!

Adam Reta @abrhott

#አብርሆት Time is not money. Time is far more valuable than money. You can always make more money when you run out of money. You can’t get more time when you run out of time. If you want to succeed, value your time!

አባ አለም ለምኔ አባ አለም ለምኔ ጀምበር ወጣ አትገባም ሳልሰራ ኩነኔ ×2 ሠው ወደድኩኝ እያልኩ ደሞ እጠላለሁ ደሞ ይከፋኛል እደሰታለሁ ዛሬ ቀጭን ኩታ ነገ እራቁቴን አገኘው ስል ወዳጅ ደሞ ማጣትን ደሞ ማጣትን አባ አለም ለምኔ አባ አለም ለምኔ ጀምበር ወጣ አትገባም ሳልሰራ ኩነኔ ×2 አባ አለም ለምኔ ለምን ለምን ለምን አባ አለም ለምኔ ደሞ ለምን ይክፍኝ×2 ብስጭት ጭንቀት ጤንነት አይሆነኝ×2 ሰው በአፉ እያነሳ በእጁ ይጥለኛል የልቡን አላውቅም ግራ ይገባኛል የልብን ጥያቄ ማነው የሚፈታ ካንተ በቀር አባት ካንተ በቀር ጌታ ዛሬ ጥያቄ አለኝ ለምን ለምን ለምን ደሞ ለምን ይክፉኝ ብስጭት ጭንቀት ጤንነት አይሆነኝ×2 ደስታን ስጠኝ ለህይወቴ አይሳንህም እና አባቴ አርቅልኝ ክፉውን እንዳልማር ክፋትን በቀኝ አውለህ አሳድረኝ ክፉ ነገር ሳይወጣኝ ሳይወጣኝ ክፉ ነገር ሳይወጣኝ ምን ሊሠራልኝ ጥላቻ ሀሜት ሀብት አይሆነኝም ቤት አልሰራበት ልብ ያጨልማል ክፉ ነገር ልቤን አብሩልኝ ስጡኝ ፍቅር አባ አለም ለምኔ ጀምበር ወጥታ አትገባም ሳልሰራ ኩነኔ

      የሌሎችን ስህተት መዳኘቱ ቀላል ሲሆን የራሳችንን ድካም ማስተዋሉ ደግሞ ከባድ ነው፡፡ ቀላሉ ሳያገናዝቡ ማውራት ሲሆን ከባዱ ደግሞ ምላስን መግታት ነው፡፡ የሚወደንን ሰው መጉዳት ቀላል ሲሆን የሚከብደው ደግሞ ያንን ቁስል ማዳኑ ነው፡፡ ሌሎችን ይቅር ማለት ቀላል ሲሆን ይቅርታን መጠየቅ ግን ከባድ ነገር ነው፡፡ ሕጎችን ማውጣት ቀላል ሲሆን እነርሱን መከተሉ ደግሞ ከባድ ነገር ነው፡፡ ቀላሉ በእያንዳንዱ ምሽት ማለሙ ሲሆን ከባዱ ደግሞ ለስኬታማነቱ መዋጋት ነው፡፡ 🙂ሰናይ ምሽት🙂 @abrhott

ፈረንጅ 10ኛው ፎቅ ላይ ወቶ ወደታች ያይና አቤት ደስ የሚል ቦታ ነው ይላል ። **** #Habesha ደግሞ ወደታች ያይና አሁን ከዚ ሰው ቢወድቅ ይተርፋል ?!😂

Alex Abreham በነገራችን - ላይ ተው አንተ ደመና ! (አሌክስ አብርሃም) ተው አንተ ደመና ….. ካናቴ ላይ ነግሰህ ፀሃይን አትጋርደኝ ተው አንተ ጥቁር ጉም ነጎድጓድ ያጀበው ግርማህ አያርደኝ የሰማይ ዙፋንህ ነገ ይቀዘቅዛል …. አትከርምም ካናቴ በክብር ስታንዣብብ ነገ ትዘንብና ካፈር ተደባልቀህ ታየኛለህ ሽቅብ ! @abrhott

እ ን ጀ ራ ለ እ ን ጀ ራ ----------------------------- ✍ ከዓለማየሁ ገላጋይ ብንን ስል እናቴ እጆቿን አጣጥፋ ተቀምጣለች። እራት አልነበረም ቁርስም አይኖርም እያለች መሠለኝ "ህልም አየሁ" አልኳት "አንተ ብሎ ባለ ህልም፣ ፈሳም" አለች "እትዬ ደጅ ይጥኑ እንጀራ በሰፌድ አድርገው ሲሰጡኝ ብንን አልኩኝ" "ትንሽ ብትቆይ ወጥ አድርገውልህ ልትበላ አልነበር? ምን አስቸኮለህ?" የቁርስ አለመኖር ችግሯን በእኔ ህልም ልታሳብብ እየከጀላት መሰለኝ። "በል ሂድና ይሄንኑ ህልም ለእሳቸው ንገራቸው። ነገር ግን ህልሙን እንዳየኸው ሳይሆን ልጅዎት ልኮኝ እንጀራ በስፌድ አምጥቼ ሰጠሁዎት በላቸው።" ህልም ይስተካከላል? ወይስ እንደታየ ይነገራል? እትዬ ደጅ ይጥኑ ደጃፍ ደረስኩ። እንጀራ እየጋገሩ ነበር። ቅመም ያለው ሻይ አፍንጫዬ ላይ ወረራ አካሄደ። ህልም እንዳየሁ ስነግራቸው ልክ እንደ እናቴ ፦ "አንተ ብሎ ባለ ህልም፣ ፈሳም" አሉኝ። እናቴ እንዳስተካከለችው አድርጌ ህልሜን ነገርኳቸው። "ትልልቆቹ ቢሆኑ ደስ አይበላት ብለው አይነግሩኝም ነበር። አቤት ሲሳይ፣ አቤት ሲሳይ፣ የትኛው ልጄ? የቱጋ ቆሞ? እንዳለ አምጥተህ ሰጠኸኝ?" እያሉ ህልሙን አስደጋገሙኝ፤ ትኩስ እንጀራ ከትኩስ ሻይ ጋር ሰጡኝ። የተጣበቀውን ትኩስ እንጀራ ስቆርስ የእርቦው ስፌት በጥፍሬ እየተቃኘ እርካታዬን አጀበልኝ። ወደ ቤት ስመለስ እናቴ ድምጿን ከፍ አድርጋ እየተሳደበች ገረፈችኝ። "እዚህ የሰራሁልህን ቁርስ ዘርግተህ ቅልውጥና ሄድክ? አ ፈ ር ብላና..." ---------------------------- 📔 "ው ል ብ ታ"

ነገ መቼ ነው...? 📖📖📖 "....እንግሊዝ ውስጥ ነው። ድሮ አንድ እባብ ነበር። ሕዝቡን በጣም አስቸገረ። ማን ጀግና ይድፈረው። አንዱ ብልጥ "እኔ እይዘዋለሁ" አለ። ንግሥቲቱ "እሾምሃለሁ" አለችው። የወርቅ ሳጥን ገዛና ሳጥኑ ውስጥ የሐር ምንጣፍ አነጠፈበት። ወደ ጫካ ሄዶ እባቡን "ይህ ለክብርህ የተዘጋጀ ዙፋን ነው" አለው። እባቡ ጠርጥሯል። ነገር ግን የወርቅ ሳጥኑንና የሐር ምንጣፉን ወደደው። "ግባና ለካው" አለው ሰውየው። ከአንገቱ በታች ያለውን አካሉን አስገብቶ ለካው። ይመቻል። "ሙሉ ሰውነትህን አስገባው" አለው። "ብትዘጋብኝስ?" አለ እባቡ። ሰውየው ማለለት። "ሙሉ አካልህን ካላስገባህ ይስፋህ ይጥበብህ ማወቅ አይቻልም" አለው። እየጠረጠረ ገባ። ዘጋና ቆለፈበት። እባቡ "ክፈት" እያለ ጮኸ። ሰውየውም "ነገ እከፍትልሃለሁ" አለው። ከዚያም ወስዶ በፈረንሳይና በእንግሊዝ መካከል ባለው የእንግሊዝ ባሕር ውስጥ ጣለው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ዓሣ አጥማጆች ዓሣ ሲያጠምዱ "ነገ መቼ ነው?" እያለ ይጠይቃል። ነገ መቼ ነው? ትክክለኛ ጥያቄ ነው። ነገ፣ ነገ የማይሆንላቸው አሉና።... " 📖📖📖 ምንጭ 📖 "የአዲስ አበባ ውሾች"...ገጽ 27-28 ደራሲ ✍ ዳንኤል ክብረት ኅትመት ፦ ሐምሌ 2010 ዓ.ም. Credit to ፦ ይሁን ዓለም 📖 ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል @abrhott

ሰው ሰራሽ ሰውን አጥፊ የሆነ ነገር " ዘረኝነት " እንጠየፈዉ በአስተሳሰብ መስፋት እያለ ለምን እንጠባለን?። የሰዉ ልጅ በመሆንህ ብቻ ወንድሜ ነህ። ሁለታችንም ከአንዲት ምድር የተሰራን ፍጡራን።