አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
I seriously don't understand How pictures From 5 years ago suddenly look blurry now. I mean,They were clear back then. 😫🤔
3 738
ከ"መደመር" መጽሐፍ የተቆነጠረች ንባብ...
📖📖📖
" የሰው ልጆች የስምና የነፃነት ፍላጎታቸው ራሳቸውን ለሞት አሳልፎ እስከመስጠት የሚያደርሳቸው ጠንካራ ፍላጎት ነው። የስም ፍላጎታችን ካልተሟላና ለራሳችን የምንሰጠው ግምት ካሽቆለቆለ ለምግብ ቀርቶ ለሕይወት ፍላጎት አይኖረንም በርካታ ሰዎች ራሳቸውን የሚያጠፉትም ሆነ ከሌላው ጋር ጠብ ገጥመው የሚሞቱት ይህን የስም ፍላጎት ለማሟላት ነው ።
፧
የሰው ልጅ ፍላጎቶች ሁሉም እንደነባራዊ ሁኔታቸው እየታዩ በእኩልነት ሊስተናገዱ የሚገባቸው ወሳኝ ፍላጎቶች ናቸው። ሰዎች ሰው በመሆናቸው የሚኖራቸውን ፍላጎት ሟሟላት ይገባናል። ሰዎች ከእንስሳት የተለየ ፍላጎት ያላቸው ፍጥረታት በመሆናቸው የ ሰው ልጆችን ፍላጎት የምንመለከተው ከዚህ ውስብስብ ተፈጥሯቸው አንፃር ነው። "
/ መደመር...ገጽ 7 /
📖📖📖
🙏 ሰናይ ምሽት 🙏
📚 ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል
✍ ንባብ ለሕይወት
መደመር...ገጽ 7 ብዬ post ሳረግ...እስከ ገጽ 7 ብቻ ነው ያነበብከው😕ያልከኝ ልጅ ደና ነህ🧐እንዴት ነህ::😂
3 738
The sad truth is so many people are in love but not together, and so many people are together but not in love.
3 738
4. እርጅናን ይከላከላል
ጥናቶች እንደሚያመለክቱት አዘውትረው የሚመሰጡ ሰዎች ከማይመሰጡት ጋር ሲወዳደሩ ቀናቸውን በተመስጦ የሚያሳልፉ ሰዎች ከዕድሜቸው አንጻር ቶሎ የማያረጁና ረጅም ዕድሜ የሚኖሩ ሆነው ተገኝተው፡፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት መመሰጥና ተመስጦ እርጅና የሚያስከትሉ ቲሹዎችንና በሽታዎችን መግታት በመቻሉ ነው፡፡
5. ለውስጠ ስሜት መረጋጋትና አወንታዊ አስተሳሰብ
መመሰጥ ጭንቀት ውስጥ ለገቡ፤ በቶሎ ለሚናደዱ፤ ስሜታቸውን መቆጣጠር ለሚቸገሩና ድብርት ለሚያጠቃቸው ሰዎች እንደ ተፈጥሯዊ መከላከያ መድኃኒት ተደርጎ በባለሙያዎች ይታዘዝላቸዋል፡፡ በተጨማሪም መመሰጥ የአሉታዊ አስተሳሰቦችንና ስሜቶችን ከሰዎች አእምሮና አካላት ውስጥ አጥርቶ በማውጣት በአወንታዊ አስተሳሰብ እንዲገነቡ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ በአጠቃላይ ከጭንቀትና ተያያዥ ጉዳዮች ባሻገር ተመስጦን የሚያዘወትሩ ሰዎች ጥሩ ስሜት የሚሰማቸውና ደስተኞች ናቸው፡፡
ለተመስጦ የሚረዱ ጥቆማዎች
ዘውትርና በተመሳሳይ ሰዓት መመሰጥን ልምድ ማድረግ ይመከራል
ከመመሰጥ በፊት የማነቃቃት ባህሪይ ያላቸውን ትኩስ ነገሮች አለመውሰድ
ከምግብ በኋላ አለመመሰጥና በቀን ውስጥ ሙሉ ኃይል የለኝም ብለው በሚያስቡበት ሰዓት መመሰጥ
መመሰጥ የሚፈልጉበትን ስፍራ ማዘጋጀትና በቂ ዓየር እንዲገባው መስኮት መክፈት
በጣም ደማቅ ብርሃን የሌለውን ስፋራ መምረጥና ሰፋ ያለ ልብስ መልበስ
ጸጥ ያለ አካባቢን መምረጥና በተመስጦ ጊዜ ሊረብሹ የሚችሉ ነገሮችን እንደ ስልክ ፤ ሬዲዮ ፤ ቴሌቪዥንና የመሳሰሉ ነገሮን ድምጽ ማጥፋት
በረጅሙ ዓየር ወደ ውስጥ ማስገባት
ያስገቡትን ዓየር ለጥቂት ሰከንዶች ሳይተነፍሱ ማቆየት
ከዚያም በረጅሙ መተንፈስ
በሚተነፍሱበት ወቅት ለሚሰማዎት ስሜት ትኩረት መስጠት፤ ዓየር በአፍንጫ ቀዳዳዎ ሲገባ ፤ ዓየሩን ለተወሰኑ ሰከንዶች ሲይዙት በመላ አካላቶ እየተሰራጨ እንደሆነና ሰውነቶን አዝናንቶ በአፍዎ እንደሚወጣ ማሰብ በቀላሉ የተረጋጋ ስሜትንና መዝናናትን አእምሮአችንና አካላችን እንዲሰማው ያደርጋል፡፡
3 738
ከላይ የቀጠለ
1. ውጥረትን ይቀንሳል
መመሰጥና ተመስጦ ከማንኛውም አካላዊ እንቅስቃሴ በላይ ውጥረትን የመቀነስ አቅሙ ከፍተኛ ነው፡፡
መመሰጥ ውጥረትን መቀነስ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በነርቭ ስርዓት ላይ ውጥረትን የሚያመጣውን ኮርቲሶል የሚባለውን ኬሚካል በመቀነስ በምትኩ ሰዎች ጥሩ ስሜት እንዲሰማቸው የሚያደርገውን ሴሮቶኒን የተባለውን ኬሚካል አንጎላችን እንዲያመነጭ ያነሳሳል፡፡
2. ጤናን ያሻሽላል
ተመስጦ የበሽታ መከላከል ኃይልን በማደርጀት፤ የደም ግፊትና የኮለስትሮል መጠንን በመቀነስ ጤናን ያሻሽላል፡፡ በተለይ በማይድን ጽኑ ህመም የሚሰቃዩ ሰዎች ህመማቸውን ለማስታገስና ለማገገም ከተመስጦ ብዙ ጥቅም ያገኛሉ፡፡ በእርግጥ ተመስጦን ለመጠቀም የግድ ጽኑ ህሙማን መሆን አይጠበቅብንም ከጉንፋንና እራስ ምታት ለመታቀብና ለመዳን ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡
3. ለእንቅልፍ
በስራ ጫና ብዛትና በውጥረት ምክንያት አንዳንድ ጊዜ ሰዎች እንቅልፍ ላይዛቸውና በቶሎ በመተኛት ከድካማቸው ፋታ ለማግኘት ይቸገራሉ፡፡
ይህ በሚሆንበት ወቅት መመሰጥት ችግራቸውን ተፈጥሮአዊ በሆነ መንገድ በቀላል እንዲፈቱ ይረዳቸዋል፡፡
ይቀጥላል
3 738
ተመስጦ/Meditation
የሰው ልጅ ዕለት ተዕለት በሚኖረው ኑሮ ውስጥ ሲደክመው ዕረፍት ማድረግን ፤ የሰውነት ክፍሎቹን ለማፍታታት መንጠራራትንና ማፍታታትን ፤ የድብርት ስሜት ሲሰማው ማፋሸግንና ሲጨንቀው ስሜቱን ለማረጋጋት ዓየር በደንብ ወደ ውስጥ አስገብቶና ወደ ውጭ በረጅሙ መተንፈስን በተፈጥሮ የታደላቸው ገጸ በረከቶች ናቸው፡፡
ከፍ ሲልም መንፈሱን ወደ ትልቁ ማማ ሰማየ ሰማይ በመውሰድና በመመሰጥ አእምሮውንና መንፈሱን ያድስበታል፡፡
ተመስጦ ሰዎች ከጥንት ጊዜ ጀምሮ አእምሯቸውንና ህይወታቸውን የሚቆጣጠሩበት እንዲሁም እራሳቸውን ፈልገው የሚያገኙበት የአእምሮ ፤የአካልና የመንፈስ እንቅስቃሴ ነው፡፡
በተጨማሪም ተመስጦ ሰዎች አእምሯቸውን እንደ ኤሌክትሪክ ማብሪያና ማጥፊያ ባሻቸው ሰዓት ማሰብ የሚፈልጉትን እንዲያስቡ ማሰብ የማይፈልጉትን ደግሞ ከአእምሮአቸው ውስጥ በቀላሉ የሚያጠፉበት ተፈጥሯዊ የአእምሮ ቁልፍ ነው፡፡
በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ በዓለም ላይ በሚገኙ ባህሎች ውስጥ ተመስጦና መመሰጥ አለ፡፡
ነገር ግን ተመስጦ በተደራጀና በተዋቀረ መልኩ የተጀመረው በሂንዱ ሸለቆ ውስጥ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ5000 እስከ 3500 ዓመተ ዓለም አካባቢ መሆንኑን የአርኪዮሎጂ ጥናቶችና ግኝቶች ያስረዳሉ፡፡
በሂንዱ ሸለቆች የተገኙ የግርግዳ ላይ ስዕሎች ከላይ ከተጠቀሰው ዓመተ ዓለም ጀምሮ ሰዎች ቁጭ ብለው እግራቸውን አመሳቀለው ተመስጦን ሲያከናውኑ እንደነበር ማስረጃዎች ያስረዳሉ፡፡
እንዲሁም በህንድ መጻሕፍት ውስጥ ከ3000 ዓመታት በፊት የተመስጦና መመሰጥ ዘዴዎች ተመዝግበው እንደሚገኙ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፡፡
ሁሉም ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች በውስጣቻው ተመስጦን ይዘው ይገኛሉ፡፡ በሃይማኖታዊ ስርዓት ምዕመናን ሲጸልዩ ፤ ሲያመሰግኑና ሲሰግዱ ወደ አምላካቸው ይመሰጣሉ፡፡
ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ ስለተመስጦና መመሰጥ ሲነሳ ሰዎች ወደ አእምሮአቸው የሚመጣው የቡድሃ ወይም የሂንዱ እምነት ነው፡፡
ምንም እንኳን እነኚህ ሃይማኖቶች በሃይማኖታዊ ክንዋኔአቸው ለተመስጦ ትልቅ ትኩረት ቢሰጡም በዘመናዊው እይታ ተመስጦና መመሰጥ ከየትኛውም ሃይማኖት ጋር አይያያዝም አልያም
ዘውትር መመሰጥንና ተመስጦን ማከናወን የቡድሃ ወይም የሂንዱ እምነት ተከታይ መሆን ማለት አይደለም፡፡ ለመነሻ ያህል ይህን ካልን የመመሰጥና የተመስጦን ጥቅም ከብዙ በጥቂቱ እንመለከታለን፡፡
ይቀጥላል..
ይቀጥል ✅
አይቀጥል ❌
3 738
የጥበበኛው ደራሲ #አዳም_ረታ የተዋቡ ቃላት
📖📖📖
፨ ወሬ ፨
...እንዳንተው አገሬን እጠብቃለሁ እኔ ግን ተረቷን ነው የምጠብቀው። ተረት ይከስማል። ችላ ካሉት ይሰደዳል። ይጠፋል"
"በምንህ ነው የምትጠብቀው?"
"እንዲህ እየዞርኩ በወሬ"
"በወሬ?"
"ምነው? በወሬ የፈለግሁትን መፍጠር እችላለሁ። በወሬ የትንሽ ልጅ እናት መግደል እችላለሁ። በወሬ ሰይጣን የእንጀራ እናትን ቅዱስ ማድረግ እችላለሁ። በወሬ ውሃ ማቃጠል እችላለሁ። በወሬ በሬ ማስወለድ እችላለሁ። ከድሮ ባሕልህ የቀረህ ምንድነው? ፍልስፍንም? አይደለም። ልዩ ሕንፃ ስራ? አይደለም። ለሁላችንም የቀረን የወሬ ቴክኖሎጂ። ይሄ ቴክኖሎጂ የሚቀመረው በቋንቋ ነው። ተረት የማበዛው ስለዚህ ነው። ግን ሁላችን እኩል እውቀት የለንም። ... ይሄ እውቀታችን ከአፍ ወደ መጽሐፍ አልገባም። ..."
፧
፨ መለመን ፨
"...መብቴ ነው የሚመስልኝን መናገር። ወይስ መብቴን መለመን አለብኝ? ዳቦ ለምነን፣ መብት ለምነን፣ ሴት ለምነን፣ የሚጠጣ ለምነን። ዓለምን ስንዴ የምንለምነው ይሄ ለምዶብን ይሆናል። ምንም አትለምን። በሥነሥርዐት መብትህን ውሰድ። የአንተ ወዝ ያንተ ነው። "
፧
ምንጭ ፦ "ግራጫ ቃጭሎች"...ገጽ 329-330
ደራሲ ፦ አዳም ረታ
📖 ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል
3 738
"የዘመኑ ወጣት አእምሮ በር የለውም። ቢኖረውም የሚያስወጣ እንጂ የሚያስገባ አይደለም። ከራሱ ዓለም ሃሳብ አውጥቶ እኔ ያልኩት ካልሆነ ይላል እንጂ የሌላውን ሐሳብ አይመዝንም።
ሲወለድ ጀምሮ ሁሉን አውቆ የተፈጠረ ይመስለዋል። ያለብዙ ችግር ያገኘውን ዕውቀቱን ተፎካካሪ የሌለው ሀይል ያደርጋል።
በትንሽ ዕውቀት ብዙ ነገር ፈታቶ የሚገጣጥም ይመስለዋል።"
"ይወሰዳል መንገድ ያመጣል መንገድ"
#ደራሲ፦ #አዳም_ረታገፅ-233
3 738
"ከአሜን ባሻገር" መግቢያ ላይ
በዕውቀቱ ሥዩም እንዲህ ይለናል
📖📖📖
" ታሪካችን ይጫነናል……/ ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ /
#ታሪክ አሮጌ መጽሐፍት ውስጥ ተጠርዞ የቀረ ነገር አይደለም። ያለፈውን ነገር ትተን ወደፊት እንገስግስ የሚለው "ሾላ በድፍን" የሆነ አባባልም ፋይዳ የለውም። ያለፈውን ዘመን ቸል ብንለው ቸል አይለንም። የዛሬ ዘመን ምን ቢታገል ካለፈው ዘመን ተለይቶ ጎጆ መውጣት አይችልም። ያለፈው ዘመንና የዛሬው ዘመን እንዳይፋቱ ሆነው ተቆራኝተዋል። አንዳንዴ ሳስበው፣ "#ዘንድሮ" በሚለው ቃል ውስጥ "#ድሮ" የሚለው ቃል መገኘቱ አለምክንያት አይመስለኝም።
ያለፈውን ዘመን ተቀብለን ካለፈው ተምረን የተሻለ የጋራ ቤት መሥራት እንችላለን። "
/ ከአሜን ባሻገር...ገጽ 9 /
፧
፨ በዕውቄ እዚሁ መጽሐፉ ላይ እንዲህ ይለናል "ታሪክን መቀየር አንችልም ታሪክን የምናይበትን መነጽር ግን መቀየር እንችላለን።"
፨ ታሪካችን ሳይሆን ታሪካችንን የተረዳንበት እና የምናይበት መንገድ ይሆን እያጣላን ያለው? ወይስ ታሪክ ለፖለቲካ ፍጆታ መዋሉ...? ከታሪካችን መልካሙን እየወሰድን መቀጠሉ ላይ ሳይሆን መልካም ያልሆኑትን እያነሳን መቋሰሉ ላይ ያተኮርነው ለምን ይሆን...?
"የትናንት ዘረኝነት አለብን" ይለናል ቡርሐን አዲስም የዘር_ካርድ ላይ...!!
፨ ታሪክ እንደሸክም የተጫናቸው ሰዎች ሕዝቡን አላነቃንቅ ያሉት ይመስለኛል...!
3 738
በውጥረት ውስጥ የማለፍ ብቃት - የናርዲ የኑሮ ውጥረት
“ሁለቱ ክህሎቶች” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ አዲስ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰደ፡፡
በሞያ እየተሻሻልንና በኑሮ እያደግን በሄድን ቁጥር ከዚያው ጋር የሚመጡት ሃላፊነቶች እየበዙና እየጨመሩ መሄዳቸው ግልጽ ነው፡፡ እነዚህ ሃላፊነቶች ሲበዙ ደግሞ በተራቸው ውጥረትን ያስከትላሉ፡፡ ስለዚህም፣ በሁለት ተመሳሳይ የሞያ ብቃት፣ የኑሮ ደረጃና የሃላፊነት እርከን ባሉ ሰዎች መካከል ልዩነት የሚያመጣው ውጥረትን በተገቢው መንገድ የመያዝ ብቃት ነው፡፡
ውጥረትን መቻል ማለት በሚወጥሩና በሚያጨናንቁ ሁኔታዎች ውስጥ ሲያልፉ ከዋና ዓላማ ሳይወጡና ከተግባር ሳይገቱ ብቻ ሳይሆን ምንም አይነት አካላዊም ሆነ ስሜታዊ ቁስልን ሳያተርፉ በተገቢ ሁኔታ ተቋቁሞ ማለፍ ማለት ነው፡፡ አንዳንድ የሕይወት ገጠመኞች ልክ የተመካከሩ ይመስል በአንድ ላይ የሚጎርፉበት ጊዜ አለ፡፡ ለምሳሌ፣ የፍቅር ሕይወት መናጋት፣ ድንገተኛ የሆነ የገንዘብ እጥረት፣ የሰዎች ባህሪይ መቀየር፣ ስጋት ውስጥ የሚጨምር የግል ገጠመኝና የመሳሰሉት ሁኔታዎች በአንድ ላይ ሲመጡ መፍትሄን የምናገኘው በእጃችን ባለው ሞያ (ጠጣር ክህሎት) ሳይሆን ባሉን የለስላሳ ክህሎቶች ብቃት ነው፡፡
ናርዲ ከዘጠነኛ ክፍል ጀምሮ ከምትተዋወቀው መልከ-መልካም ወጣት ተቀራርበው በማደጋቸው ምክንያት ገና በዩኒቨርሲቲ የአራተኛ አመት ተማሪ ሆነው ነው የተጋቡት፡፡ ሰርጋቸውን አነስተኛ ለማድረግ ቢወስኑም፣ “ለካ የሰርግ ትንሽ የለውም” እስከሚሉ ድረስ የገንዘብ እዳን ጫና አምጥቶባቸዋል፡፡ ከተጋቡ በኋላ ገንዘብ ከዚህም ከዚያም ብለው ባመጡት ገንዘብ በተከራዩት ኮንዲሚኒየም ውስጥ እየኖሩ ሁለቱም በአንድ ላይ በመጀመሪያ ዲግሪያቸው ተመረቁ፡፡
ናርዲና የትዳር አጋሯ በተመረቁ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ስራ ወደመፈለግ ሩጫ ውስጥ ነው የገቡት፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት በአንድ ጎኑ ለሰርጋቸውና ቤታቸውን ለማደራጀት የተበደሩት ገንዘብ መከፈል ስለነበረበት ሲሆን፣ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ገና እንደተጋቡ በመጸነሷ በቅርቡ ለሚጠብቁት ወንድ ልጅ ለመዘጋጀት ነው፡፡ የእዳ ክፍያ፣ ለወሊድ የሚወጣ ወጪና አዲስ ልጅ ሲመጣ ልጁ የሚጠይቃቸው ፍላጎቶች በአንድ ላይ አፍጥጠው መጥተዋል፡፡ ናርዶስና ባለቤቷ ግን ከመቼውም የበለጠ ጠንክሮ የመስራትን ቁርጠኝነት ይዘዋል፡፡
የናርዶስ ባለቤት ከእርሷ ቀድሞ ስራ እንዳገኘ ብዙ ሳትቆይ እሷም ስራ አገኘች፡፡ ሁለቱም በተማሩበት የሞያ ዘርፍ ስራን በማግኘታቸው ደስተኞች ናቸው፡፡ ሆኖም፣ ናርዶስ ስራ ባገኘች በአንድ ወር ውስጥ ልጅ በመውለዷ ምክንያት የሶስት ወር ፈቃድ ወስዳ ካረፈች በኋላ ወደ ስራ መስኳ ተመለሰች፡፡ ስራዋ እረፍት አይሰጥም፣ ባለቤቷ ካለው ስራ ጫና የተነሳ ከእርሷ ቀድሞ ወጥቶ ከእርሷ በኋላ ነው እቤት የሚገባው፡፡ ልጅ እንዲጠብቁላት የምትቀጥራቸው “ሞግዚቶች” በየሁለት ሳምንቱ ጥለው ይወጣሉ፡፡ አልፎ አልፎ የልጇ ጤንነት እየታወከ ከስራ ገበታዋ ላይ ይወስዳታል፡፡ በነጋታው ወደ ስራ ስትመለስ አቅም የሚያሳጣ ስራ ተከምሮ ይጠብቃታል፡፡ ከዚህ የተነሳ አለቃዋ ባህሪው ተቀይሮባታል፡፡ አንዳንድ የስራ ባልደረቦቿ ለእርሷ የተለየ አድሎ እየተደረገ እንደሆነም እንደሚያስወሩ ሰምታለች፡፡ ከዚህ የተነሳ ናርዲ ብዙ ስሜታዊ ውሳኔ ውስጥ የሚጨምሩ ሃሳቦች እየመጡባት ነው፡፡
ከላይ ያነበብከውን የናርዲን ሁኔታ ስታስበው፣ ያለባትን ውጥረት ለማስተንፈስ የሚያስችላትን ምክር ለግሳት ብትባል ምን ትመክራታለህ? ምናልባት አንተ ወይም አንቺ ልክ ናርዲ በምታልፍበት የውጥረት ሁኔታ አሁን በማለፍ ላይ ብትሆኚ/ን ምን ታደርጊያለሽ/ታደርጋለህ?
✍@JamesB23
✍@bellalsina
