en
Feedback
አብርሆት

አብርሆት

Open in Telegram

ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23

Show more
3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ከናፍቆትና_ከእንቅልፍ …ትናንት ናፍቀሽኛል “ተኝታለች” አሉኝ ስልክሽን ያነሱት እናትሽ መሰሉኝ፤ “መሰሉኝ” አለ አይደል እንዲህ ነው እንግዲህ እርግጥ መሆን ሲፋቅ የሚያውቁት ሲነደል። ዛሬ አንቺ ደወልሽ “ናፍቀኸኛል” አልሺኝ ልጠይቅ ከልቤ ልጠርጥር ከሆዴ መናፈቅን የሚያውቅ እንቅልፍ ይሉት መንገድ ይወስደዋል እንዴ? ልጠርጥርሽ ደግሞ ልጠይቅሽ ደግሞ ሙሽራዬ ውዴ። ---------------------//---------------------- ✍©በላይ በቀለ ወያ ---------------------//--------------- @abrhott

" አለመግባባት መፍትሄ የሚያገኘው በውይይት ወይም በኃይል ከሁለቱ መንገዶች በአንዱ ነው። የመጀመሪያው የሰው ባህሪ ሲሆን ሁለተኛው ግን የአራዊት ነው። " @abrhott

「❝ ኢትዮጵያዊነትን፡አታዉሩት ኑሩት፡እንጂ። ❞」

መልካም ቀን @abrhott
መልካም ቀን @abrhott

ሽሙጥ😁 ╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮ 「❝ የሀገራችን፡ገበሬዎች እርሻን፡ለወይፈን፡ለማስተማር የሚጠምዱት፡ልምድ፡ካለው በሬ፡ጋር፡ነው። ❞」

" ጥላቻ ማለት በድን አስክሬን ነው ። አላዋቂዎችም የጥላቻ ዋሻዎች ስለሚሆኑ የጥላቻ መቃብሮች ይሆናሉ ። ማናችን ነን ታድያ የጥላቻ መቃብሮች...? " / ካህሊል ጂብራን / @abrhott @abrhott @abrhott

አንቀጽ 39 እያለ እውነት ግን ግድቡ የኔ ነው ???? እንደ ቤንሻንጉል ጉምዞች ፍቃድ …… ይሁልን

#የቴዲ አፍሮ አዲስ ሙዚቃ ❗️ ደሞ በአባይ Mp3 🎵 @abrhott

"Animal Farm" ተረት መሰል መጻሕፍ ነው። በአንድ ገበሬ እርሻ ውስጥ የሚኖሩ እንሰሳት "አራት እግር መልካም፤ ሁለት እግር መጥፎ" በሚል መርህ ተደራጅተው ባለቤታቸው ላይ በማመጽ የራሳቸውን አ
"Animal Farm" ተረት መሰል መጻሕፍ ነው። በአንድ ገበሬ እርሻ ውስጥ የሚኖሩ እንሰሳት "አራት እግር መልካም፤ ሁለት እግር መጥፎ" በሚል መርህ ተደራጅተው ባለቤታቸው ላይ በማመጽ የራሳቸውን አገዛዝ የመሠረቱትን ታሪክ ነው የሚያስነብበን። ዓመፁን ያስተባበሩት እና የመሩት ናፖሊዮን እና ስኖውቦል የተባሉ ሁለት አሳማዎች ናቸው። ነገር ግን በስኬታቸው ማግስት ናፖሊዮን የአብዮቱን ዓላማ በመጠምጠዝ ወደ አምባገነንነት ተቀየረ። ለዚህ ጉዞው ደንቃራ ሆኖ የታየውን ስኖውቦልን ከእርሻው አባረረ። ሕግጋቱን ቀያየረ። የአሳማዎችን የበላይነት አወጀ። ትዕዛዛቱን የማያከብሩትን ልክ የሚያስገቡ ጠብደል ውሾች አዘጋጀ። የእርሻው የህልውና መርህም "እንሰሳት ሁሉ እኩል ናቸው" ከሚለው ተለውጦ "እንሰሳት ሁሉ እኩል ናቸው፤ ግን አንዳንድ እንሰሳት ይበልጥ እኩል ናቸው (All animal are equal. But some are more equal than the other)" የሚል ሆነ። • #ምንጭ:- "ፖለቲካዊ ፍልስፍና" በቃልኪዳን ይበልጣል ገጽ-174

ኢትዮጵያዊ መልኩን .. / እንደ አቤል ቃየን ብንመስልም ለሚያየን ያለን ተኮራርፈን ያለን ተራርቀን ምድር ይጠበናል አንቺን የነኩሽ ቀን :: ( ኢዛና መስፍን )
ኢትዮጵያዊ መልኩን .. / እንደ አቤል ቃየን ብንመስልም ለሚያየን ያለን ተኮራርፈን ያለን ተራርቀን ምድር ይጠበናል አንቺን የነኩሽ ቀን :: ( ኢዛና መስፍን )

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውነታዎች! ➡️የግንባታው የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠበት እለት - መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም፤ ➡️የግንባታው ስፍራ፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ጉባ ወረዳ
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውነታዎች! ➡️የግንባታው የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠበት እለት - መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም፤ ➡️የግንባታው ስፍራ፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ጉባ ወረዳ፤ ➡️የዋናው ግድብ ከፍታ -145 ሜትር፤ ➡️የዋናው ግድብ ርዝመት -1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር፤ ➡️የዋናው ግድብ ውፍረት - የግድቡ ግርጌ 130 ሜትር ሲሆን የግድቡ ጫፍ ወይም የላይኛው ክፍል 11 ሜትር፤ ➡️ግድቡ የሚይዘው የውሃ መጠን -74 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር፤ ➡️ግድቡ የሚሸፍነው የቦታ ስፋት -1 ሺህ 680 ስኩዌር ኪሎ ሜትር፤ ➡️ሲጠናቀቅ ውሃ የሚተኛበት መሬት ርዝመት 246 ኪሎ ሜትር፤ ➡️የኮርቻ ግድብ /Saddle Dam/ ከፍታ- 50 ሜትር፤ ➡️የኮርቻ ግድብ /Saddle Dam/ ርዝመት 5.2 ኪ.ሜ ➡️ግድቡ16 የኃይል ማመንጫ ዩኒቶች አሉት፤ ➡️እያንዳንዱ ዩኒት የሚያመነጨው የኃይል መጠን ከ375 እስከ 400 ሜጋ ዋት፤ ➡️ጠቅላላ ግድቡ ሲጠናቀቅ የሚያመነጨው ኃይል መጠን፡ 6 ሽህ 450 ሜጋ ዋት ➡️ከ500 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ማልማት ያስችላል፤ ➡️ከ10 ቶን በላይ ዓሳን ማምረት ያስችላል፤ ➡️ከ40 በላይ ደሴቶች ይኖሩታል። ➡️ከግድቡ የውሃ ላይ የትራንስፖርት፣ የአሳ ልማትና ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ አገልግሎት ይውላል። ➡️ታዳሽ ኃይል በመሆን የከባቢ ብክለትን ይከላከላል። ➡️የከተሞችን ተሞክሮ በመቀመር በአዲሱ የህዳሴ ሐይቅ ዙሪያ ዘመናዊ ከተማ ለመመስረት ያስችላል። ➡️አጠቃላይ ግንባታው የደረሰበት ደረጃ- 74.26%፤ ➡️ግድቡ በትልቅነቱ በአፍሪካ አንደኛ ደረጃን ይዟል። ምንጭ፡- የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት/Prosperity Party Official FB page @abrhott

photo content

'One Voice for Our Dam' ለግድባችን ያለንን ድጋፍ ነገ እሁድ ሐምሌ 26/2012 ከቀኑ 10:00 ሰዓት ሁላችንም በአንድ ላይ ባማረና በደመቀ ሁኔታ በያለንበት ሆነን በዓለም አቀፍ ደረጃ ድምፃችንን እናሰማለን! @abrhott

ያልጣዱት አይበስልም (በእውቀቱ ስዩም) ፍቅር እንደ ዝናብ ከሰማይ አይወርድም ያበባ መደብ ነው በሰው የሚታነፅ : በሰው የሚወድም ተዘርቶብን እንጂ :ተሰብከን አንወድም:: "ወዳጄ ወዳጄ " የሚያቀነቅኑ አገር ያቀኑ ለት መች ልብን አቀኑ ሳይወጡ ሳይወርዱ ውብ ስራን ከውብ ቃል :ሳያስተባብሩ ከድሜ እና ከምቾት ቆርሰው ሳይገብሩ ፍቅር መች ይፈልቃል? በስብከት በምልጃ በየዋህ ሰዎች ህልም ያልጣዱት አይበስልም ያልዘሩት አይበቅልም::

እንደምን አደራችሁ !!

#Be a nice human @abrhott

ለመላው ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በተለይም የህዳሴ ግድብ እንዲሳካ ሽንጣችሁን ገትራችሁ በአረብኛ ቋንቋ የተከራከራችሁ ጀግና ያገሬ ልጆች ለኢድ-አል አድሐ አረፋ በዓል እንኳን በሠላም አደረሳችሁ። ኢድ-ሙ
ለመላው ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በተለይም የህዳሴ ግድብ እንዲሳካ ሽንጣችሁን ገትራችሁ በአረብኛ ቋንቋ የተከራከራችሁ ጀግና ያገሬ ልጆች ለኢድ-አል አድሐ አረፋ በዓል እንኳን በሠላም አደረሳችሁ። ኢድ-ሙባረክ @abrhott @abrhott @abrhott

ኒህሊዝም(Nihilism) ምንድን ነው? ፨፨፨ #ኒሂሊዝም (Nihilism) በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ በምድረ አውሮፓ የተነሳ ርዕዮት ሲሆን ቃሉን ለመጀመሪያ ጊዜ የተገለገለው ጀርመናዊው ፈላስፋ ፍሬድሪክ ሄኔሪክ ጃኮቢ (1743-1819) ነው፡፡ ኒሂሊዝም እንደ የሚገባበት አውድ እና ዲሲፕሊን የተለያዩ መልኮች ቢኖሩትም አስኳሉ “ክህደት” ነው፡፡ ሃይማኖት ቢሉ እምነት፣ ባህል ቢሉ እውቀት፣ ህግ ቢሉ መተዳደሪያ ደንብ፣ ስነ ምግባር ቢሉ ስሜት… ከነጓዛቸው በኒሂሊዝም ይገፋሉ፤ ይካዳሉም፡፡ ፧ እውቁ አሜሪካዊው ፈላስፋና ደራሲ ኮርኔል ዌስት ኒሂሊዝምን አስመልክቶ እንዲህ ይላል:- የሰው ልጅ በማህበር ሲኖር ህልውናውን የሚያስጠብቅባቸው ፣ ባህሉን የሚያስከብርባቸውና ለትውልድ የሚያስተላልፍባቸው፣ እውቀቱን የሚሰፍርባቸው፣ ስሜቱን የሚገልጽባቸውና ስነ ምግባሩን የሚተረጉምባቸው እሴቶች አሉት፡፡ እነዚህ እሴቶች የሰው ልጅ ራሱ ፈጥሮአቸው በብዙም ሆነ በጥቂቱ ተገዝቶ የሚኖርባቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡ አንድ ማህበረሰብ እንደ ማህበር ራሱን የሚገልጥበትና ህላዌውን የሚያዘልቅበት ባህል አለው፡፡ ባህል ለተፈጥሮአዊ ጉዳዮች የሚሰጥ “ምላሽ” (expression) ነው፡፡ እምነት፣ ሃይማኖት፣ እውቀት፣ ሞራል፣ ልማድ፣ ህግ/መተዳደሪያ ደንብ፣ ኪነ-ጥበብ፣ ምርትና ማምረቻ መሳሪያ፣ አልባሳት፣ ወዘተ. . . የባህል ዘርፎች ናቸው፡፡ ፧ ተፈጥሮአዊ ባለመሆኑ አይነቱ ይለያይ እንጂ በየትኛውም ማህበረሰብ ውስጥ ባህል አለ። ማህበረሰቡ ለዘርፎቹ ያለው አመለካከት ቢለያይም ለእሴቶቹ እውቅናን ይሰጣል፡፡ አስፈላጊነታቸውንም ያምናል፡፡ ኒሂሊዝም እነዚህን ሰዋዊ እሴቶች ይክዳል፤ አላስፈላጊነታቸውንም ይሰብካል፡፡ መሰረት የሌላቸውና አንዳችም ጥቅም የማይሰጡ መሆናቸውን በመግለጽ በሰው ልጅ ህላዌ ውስጥ ያላቸውን ህልውና ይገዳደራል። ፧ በሀገረችን ካሉ ደራስያን መሃከል ጋሽ ስብሃት ገብረእግዚአብሔር #ኮተት በሚለው ስራው ኒህሊዝምን ጭብጥ አድርጎ መቅረቡን እና ያንንም ማሳየቱን የሚናገሩ ጽሑፎች አሉ ። እውቅ ከምንላቸው ፈላስፋዎች ውስጥ ደግሞ #ፍሬድሪክ_ኒቼ የዚህ አስተሳሰብ ተከታይ እና በዚህም ዙርያ ሰፊ ትንታኔዎችን ያቀረበ መሆኑን ጥበብ ከጲላጦስ ቅጽ ፩ ላይ ሰፍሮ እናገኛለን። ፧ Credit to ፦ Ermi Osho ፨ አስባችሁታል አሁን በኛ አገር #ኒህሊዝም...ህምምም!!? @abrhott @abrhott @abrhott

ሰላም ለእናንተ ይሁን

" ታላቅ ስልጣኔ የሚመጣው በሰው አእምሮ ውስጥ በሚገኝ ነፃነት ነው። " / ፍሬድሪክ ኒቼ / ይህ ነፃነት ደግሞ ከሰው ልጅ ፍላጎት ውጪ የሚሆንበት አንዳች ምክንያት የለም...ከዚህ በተጨማሪ ሕይወትን ያለአንዳች #የሞራልና #የወግ ገደብ የሚኖራት ሰው ደስታውም እንዲሁ ሙሉ እንደሚሆንና እንዲህ ዓይነቱ ደስታ ደግሞ ለጊዜው አስደስቶ የሚሰወር ሳይሆን በምድራዊ ሕይወት እስካለ ድረስ የሚከተል ነው ። እያለ ያወጋናል #ኒቼ ፧ ሞራልን እና ወግን እንደ ነፃነት ገዳቢ ማነቆ አድርጎ ይወስዳቸዋል ኒቼ ትክክል ነው ማለት ይቻል ይሆን ግን...? ከራስ ጋር መነጋገር ነው እንግዲህ...!! @abrhott @abrhott @abrhott