en
Feedback
አብርሆት

አብርሆት

Open in Telegram

ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23

Show more
3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
"ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ!" የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብር ማኅተም፤ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል ነው። ይህ ድል ያደረግንበት እንጂ ነፃ የወጣንበት
"ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ!" የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብር ማኅተም፤ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል ነው። ይህ ድል ያደረግንበት እንጂ ነፃ የወጣንበት ቀን አይደለም። እንኳን አደረሳችሁ! @abrhott

ጠላቴ ይቅርታ ጠላቴ ሆይ በርታ፣ ተበራታ በርታ፡፡ ፊቴም እንዲወዛ፣ እግሬ እንዲወረዛ፡፡ ጠላቴ ሲበዛ፣ ጦሬም እንዲበዛ፡፡ "ሰው አለሁ እንዲለኝ" በርታና በድለኝ፡፡ ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ እግር የሚወለድፍ፣ ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ የሚያስቀድመውን መድፍ፣ ህልሜን ልይዘው ስል፣ እጄን የሚመታ፡፡ ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ እግሬን የሚመታ፡፡ ጠላት የሌለው ሰው፣ ቢወጣ ቢወርድም፣ ወይ ህልም አላለመም፣ ወደ ህልሙ አይሄድም፡፡ ውሎዬ እንዲሰምር፣ ቀኔን የሚመቀኝ፣ አዳሬ እንዲሰምር፣ ሌሊት የሚመቀኝ፣ ጠላቴን አትንሳኝ፣ ጠላት አታሳጣኝ፡፡ ተባለ ምኑን ሰው ፣ ጠላት የሌለው ሰው! እባክህ ፈጣሪ፣ ጥሩ ጠላት ፍጠር፣ ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ የሚያስቀድም ጠጠር፡፡ (ይስማዕከ ወርቁ)

American kids:🚴🚴🚴🚴🚴 Habesha kids:🚴🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂ 😂😂😂

ማንም ነፃነትን አይሰጥህም። ማንም እኩልነትና ፍትህን አይሰጥህም። ወንድ ከሆንክ ራስህው ትወስደዋለህ። #MalcolmX _ @abrhott

#Tip It is not what we eat, but what we digest that makes us fat. It is not what we hear, but what we understand that makes us wise. It is not what we earn, but what we save that makes us rich. @IntegratedThoughtsQuotes

በቅርቡ ለትመት ከበቃው እና #ብስጦሽ_ቁዋጭ_ቁዋጣሽ_ቆር ከተሰኘው መጽሐፍ ላይ ሳነባት የሳበችኝን አንድ አንቀጽ ጀባ ልበላችሁ... የስብሰባዎች ብዛት እና የአጀንዳዎች እና የአቀራረቦች መደጋገም ሰውን ምን ያህል ለመሰላቸት እንደሚዳርግ የገለጸበትን መንገድ ወደድኩለት...መጽሐፉ ገጽ 18 ላይ ይህንን ይላል << ከዛሬው አይነት ስብሰባዎች የተማርኩት አንድ ነገር አለ። እሱም #ከአንድ_ቀን_አብራክ_ውስጥ_የሚወለድ_ዓመት መኖሩን ነው። ያ በአንድ ቀን የሚወለደው ዓመትም...አመቱን ሙሉ ተኑሮ የማያልቅ አንድ ቀን ይሆናል። >> ስብሰባ ሲበዛ፣ ሲደጋገም፣ ሲንዛዛ ምንያህል እንደሚያንገሸግሽ የገለጸበት መንገድ #እያዩ_ፈንገስን አስታውሶኝ ነበር... እያዩ ፈንገስም #ፌስታሌን የሚለው የትዕይንት አንድ ትወናው ላይ ይህንን ይላል... << እትዬ ገዝተውት የመጡት ዶሮ እንቅልፋም መሆኑን ባየሁ ሰዓት...ይሄ ዶሮ ፓርላማ ነው እንዴ ያደረው? >> ብያቸው ነበር...እያለ በቀልድ እያዋዛ ያጫውተናል ። ፨ ወደ መጽሐፉ ስመለስ... ስብሰባዎቻችን ላይ ያለው አስቀያሚነት ልክ እንዲያልፍ ያደረገው በተቸገርንባቸው ጉዳዮች ላይ ሳይሆን በተራ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አርገው...አስፈላጊውን ጉዳይ ትኩረትን መንፈጋቸው መሆኑን እያነሳ ይዘልቃል...ይነበብ ብዙ ጉዳዮችን የሚያነሳ መጽሐፍ ነው...። ምንጭ ፦ ብስጦሽ ቁዋጭ ቁዋጣሽ ቆር ደራሲ ፦ ታገል ሰይፉ 📚 ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል ✍ ንባብ ለሕይወት

​እንኳንም ተሳሳትክ! (Samuel Geda) በአንድ ወቅት አንዲት የሒሳብ መምህርት የሚከተለውን በሰሌዳ ላይ ጻፈች፦ 9×1= 7 9×2= 18 9×3= 27 9×4= 36 9×5= 45 9×6= 54 9×7= 63 9×8= 72 9×9= 81 9×10= 90 ጽፋ እንደጨረሰችም ወደ ተማሪዎቿ ዞራ ስትመለከት ሁሉም እየሳቁባት ነው፣ የመጀመሪያውን እኩልታ (equation) ተሳስታለችና። ይህን ጊዜ መምህርቷ እንዲህ አለች፦ "የመጀመሪያውን ስህተት የጻፍኩት በዐላማ ነው፤ ከነገሩ ጠቃሚ ትምህርትን እንድትወስዱ ስለፈለኩኝ። ይኸውም፥ በውጪ ያለው ዓለም እንዴት እንደሚቀበላችሁ ታውቁ ዘንድ ነው። 9 ጊዜ ትክክለኛ ነገር እንደጻፍኩ ማየት ትችላላችሁ ይሁንና አንዳችሁም ስለዛ አላበረታታችሁኝም፤ ነገር ግን ሁላችሁም ስለ ሠራሁት አንድ ስህተት ሳቃችሁብኝ፣ ነቀፋችሁኝም። ትምህርቱም ይህ ነው፤ • ዓለሙ፥ ሚሊዮን መልካም ሥራን ብትሠሩ አያበረታታችሁም ግን አንድ የሠራችሁትን ስህተት ይዞ ይነቅፋችኋል። በዚህ ግን ተስፋ ልትቆርጡ አይገባም። ሁልጊዜም ቢሆን ከሳቅና ከነቀፋ በላይ ወጥታችሁ ቁሙ፣ ጽኑ፣ በርቱም!" ልብ በል፤ • መሳሳትን ከፈራህ መሞከር አትችልም፤ መሳሳት ያንተ መጨረሻ አይደለም የማወቅ መነሻ እንጂ። • ምናልባት የተማርከውን ትረሳ ይሆናል፣ የተሳሳትከውን ግን አትረሳም። • ከብዙዎች የስንፍና ፍፁምነት ይልቅ ያንተ የመሥራት ስህተት እንደሚሻል አስብ። • ከመሳሳትህ በላይ ሰው ምን ይለኛል? የሚለው ነገር ያስጨንቅህ ይሆናል፤ ሰው ግን እንዳንተው የሚሳሳት መሆኑን አትርሳ። ኖረህ ስላልጨረስክ እንኳንም ተሳሳትክ!፤ ስህተትህ ላይ ከዘገየህ ብዙ ነገሮች ያልፉሃል፣ በቶሎ ከተማርክ ግን አዲስ ነገር ታውቃለህ፣ ትሠራለህም!!

WWIII USA vs Iran Here is the tips* USA win both halves #For Betting lovers😂

ሰላም ጤና ይስጥልኝ እንዴት ናቹ? እስቲ ይሄን ተጋበዙልኝ። የአንድ የታወቀ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆነ ፕሮፌሰር የሚከተለውን ድንቅ ጥናት እንዳገኘ በቅርቡ ይፋ አድርጓል!! ጥናቱም የእንግሊዘኛ ፊደሎችን ከመጀመሪያው አስከመጨረሻው በቅደም ተከተል አስቀመጠA b c d e f g h i j k l m n o p q r s t u v w x y z የነዚን ፊደላት አሃዳዊ ቅደም ተከተል ኣስቀመጠ 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 በጥናቱም ለያንዳንዱ ፊደላት በቁጥር ቅደም ተከተል ሚዛን ሰጠ ለ"A"=1 ፣ ለ"B"=2 ......... እያለ አስከ "Z" =26ን ሰጠ።በመጨረሻም የቃላት ደረጃን መመዘን ያዘ። ትጉ ስራ (H+a+r+d+w+o+r+k) (8+1+18+4++23+15++18+11)=98% እውቀት (K+n+o+w+l+e+d+g+e) (11+14+15+23+12+5+4+7+5)=96% ፍቅር (L+o+v+e) (12+15+22+5)=54% እድል (L+u+c+k)=47% በዚህ መሰረት ከላይ የጠቀስናቸው ቃላት አንዳቸውም ለውጥ መቶ ፐርሰንት(100%)ሊሰጡ አንደማይችሉ አስቀመጠ። ታዲያ (100%)ሊሰጠን ሚችለው ጉዳይ ምንድን ነው? ብር ይሁን እንዴ?? (M+o+n+e+y) (13+15+14+5+25)=72% አይደለም ምን አልባት አመራር ይሁን? (L+e+a+d+e+r+s+h+i+p) (12+5+1+4+5+18+19+8+9+16)=97% አሁንም አይደለም! ለሁሉም ነገራት መፍትሄ አለው። አስተሳሰብ፣አካሄድ አኳኋናችንን ስንቀይር ይቀየራል። ስለዚህ አስተሳሰብ ሁኔታን ሞከረ። (A+t+t+i+t+u+d+e) (1+20+20+9+20+21+4+5)=100% እናም ወዳጄ ውጤትና የ100% ለውጥ ሊያመጣልን የሚችለው የአስተሳሰብ ለውጥ መሆኑን አረጋገጠ ። እኔም ጤናማና ፖዘቲቨ አስተሳሰብ ከሌሉህ ስኬት እጅግ ሩቅ እንደሆነች እነግርሃለው። አስተሳሰብን ማስተካከል ከቻልክ ኑሮን ትኖራለህ አለበለዚያ ግን ህይወት ራሷ ትኖርብሃለች ይሄው ነው!። @abrhott @abrhott @abrhott

እግዚአብሔር ያፈቅራልም ይደፋልም …አሜን ! (አሌክስ አብርሃም) አንዳንድ ክርስቲያን ወገኖች ግን ወኒያቸው ግርም ይለኛል " እግዚአብሔር ፍቅር ነው " ሲባል ቀዝቀዝ ብለው " አሜን " ይሉና "ዳዊት ጎልያድን ግንባሩን ብሎ ደፋው" ሲባል " እልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልል ልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልል! እግዚአብሔር ሲደፋ እንጅ ሲያፈቀርና ይቅር ሲል የማይደንቀው ምእመን ግን እራሱ ይቅር ማለት የሚከብደው ይመስለኛል ! ለነገሩ ጥላችን ከስጋና ከደም አይደለም!! በጎልያድ ውስጥ ያንን ክፉ ሰይጣን እያያችሁ እንጅ የተጣላችሁትን ሰው እያሰባችሁ እንደማሆን ተስፋ አደርጋለሁ ጌታ ይባርካችሁ! @abrhott

"ማዘንበል ማለት መውደቅ አይደለም" "መውደቅ ማለት መሰበር አይደለም" በፈጣሪ ተስፋ አትቁረጥ፤ ምክንያቱም ቀና ሊያደርግህ ቀን አለውና፡፡

ደስታን መሻት ስንል? (ዓለማየሁ ገላጋይ) ክፍል ፪ ፨፨፨ ለደስተኝነት አስተዋፅኦ ያላቸው ግብአቶች ምን-ምን ናቸው? ግብአቶቹን ለሁለት በመክፈል መመልከት ይቻላል። ውጫዊና ውጫዊ በሚል። ለምሳሌ ሐብት፣ ጤናና ስጋዊ እርካታን መጥቀስ ይቻላል። ማህበራዊዎቹ ግብአቶች ደግሞ እንደ ክብር፣ ፍቅር(ጓደኝነት)፣ ሰላምና ፍትህ የመሳሰሉት ናቸው። ምሁራዊ ግብአቶች ደግሞ አሉ። ግንዛቤ፣ እውቀትና ጥበብ። እነዚህ ነገሮች ከሰው ልጆች ፍላጎት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው። እነርሱን ሐብት አድርጎ መያዝ ለሰው ልጅ ተፈጥሮ ፍፁማዊ መሳካት የራሱ አስተዋፅኦ አለው ማለት ይቻላል። እያንዳንዳቸው በራሳቸው የአንድ ሰው ፍላጎት ከመሆናቸውም በተጨማሪ የደስታ ምንጭም ናቸው። ፧ በሌላ በኩል ደስታ የመልካም ነገሮች ሁሉ ውጤት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ደስታን በተናጠል መመኘት ብቸኛው የሰው ልጅ የተጠመደበት ነገር ነው። <<ደስተኛ መሆን እፈልጋለሁ>> የተሰኘው ዘፈን ዝነኝነትን ያተረፈው፣ የአለም ህዝቦች በሙሉ ሁሉን አቀፍ ድምፅ በመሆኑ ነው። አንድ ሰው <<ደስተኛ መሆን እፈልጋለሁ፣ ምክንያቱም...>> ቢል፤ አረፍተ ነገሩን እንዲህ ብሎ ከማሟላት ውጭ አይሆንም። <<…ምክንያቱም ደስተኛ መሆን ስለምፈልግ።>> ፧ ...የአርስቶትል አገር ልጅ የሆነው ፕሌቶ ደስታን የሚተረጉመው በነፍስም በመንፈስም የሰመረ ትክክለኛ ስነ-ምግባራዊ ሰውነት ጥምረት አድርጎ ነው። እንደ አርስቶትል ለቁሳቁስ ወይም ለሐብት ግምት አይሰጥም። ፕሎቶ ምንም አይነት ውጫዊ ግብአቶች የስነ ምግባርን ሰው ሊያስደስቱት አይችሉም ይላል። ፧ ደስታ የህይወታችን ዋናኛ ግብ መሆኑን የከዳ ቢያንስ አንድ ፈላስፋ አለ። እሱም ጀርመናዊው ኢማኑኤል ካንት ነው። ካንት ደስታን መሻት እንደ ራስ ወዳድነት ድርጊት ይመለከተዋል። የግል እርካታን ከተጨባጩ ስነምግባራዊ ግዴታና መብት በላይ አድርጎ መመልከት ነው ይለዋል። <<የሥነ-ምግባር ህግ>> ይላል ካንት <<ደስታን ስለማግኘት ሳይሆን ሀላፊነትን ያለቅድመ ሁኔታ ስለመተግበር ብቻ ያዛል። ደስታ ኃላፊነትን ከመወጣት በኋላ የሚገኝ ውጤት እንጂ የሥነ-ምግባር ተተግባሪ አላማ መሆን አይደለም። ጥረት ማድረግ ያለብን ደስታን ለማግኘት መሆን የለበትም። ነገር ግን የሚገባንን ደስታ ለመቀበል መዘጋጀት እንጂ።>> ፨፨፨ ምንጭ ፦ "የፍልስፍና አፅናፍ...ገጽ 112-115" ደራሲ ፦ ዓለማየሁ ገላጋይ

ደስታን መሻት ስንል? (ዓለማየሁ ገላጋይ) ክፍል ፩ ፨፨፨ ከእለት ተዕለት ንግግሮቻችን አንፃር ከታየ <<ደስታ>> የሚሰኘው ቃል ባለብዙ ፈርጅ ፍቺ ይዞ እናገኘዋለን። ነገር ግን ታላላቆቹ አሳቢያን(Thinkers) ቃሉን ለተወሰኑ ትክክለኛ ፍቺዎች ይጠቀሙበታል። በታላላቆቹ የስነ-ምግባር መፃህፍት ውስጥ ደስታ ለሚመተልጉን ፍላጎቶቻችን ሁሉ የመጨረሻ የእርካታ ነጥብ ወይም ግብ ነው ይሉታል። ከዚህ በመነሳት የአሜሪካው የነፃነት አዋጅ ደስታ መሻትን እንደሰው ልጆች መሰረታዊና ተፈጥሯዊ መብት አድርጎ ተቀብሎታል። ፧ ደስታን የተመለከተው ፍልስፍናዊ ፅንሰ-ሐሳብ ከተለምዷዊው ግንዛቤያችን መሰረታዊ ልዩነት አለው። ሰዎች የእርካታና የፈንጠዝያ ሁኔታ ውስጥ ሲሆኑ ደስታን እንዳገኙ ሲናገሩ እናደምጣለን። ወይም ጥሩ ጊዜ በማሳለፋቸው ብቻ ደስተኛ እንደሆኑ ይናገራሉ። ነገር ግን ከአርስቶትልና ከሌሎች ፈላስፎች አንፃር ደስታ በተወሰነ ጊዜ ውስጥ በህይወት የምንመላለስበት ልምድ ወይም በስሜት የምናጣጥመው ነገር አይደለም። ደስታ መላው ህይወታችን ተገምግሞ የምናገኘው ጥራት ነው ይላሉ። ደስተኛ ህይወት ደግሞ ጥሩ የሚባለው ህይወት ነው። ፧ አብዛኛዎቹ ሰዎች ከፍልስፍና ፅንሰ ሀሳብ ጋር ባለመተዋወቃቸው የተነሳ ህፃናት ደስተኞች ናቸው ብለው ደምድመዋል። ነገር ግን አርስቶትል እንዲያ ሊሆን እንደማይችል ይሞግታል። ልጆች ሊቦርቁና ሊፈነጥዙ ቻሉ ማለት ደስተኛ ናቸው ብለን እንድንደመድም አያደርገንም። ምክንያቱም ህፃናት ሙሉ ህይወታቸውን ኖረው ያላጠናቀቁ ገና በጅማሬ ላይ ያሉ በመሆናቸው ነው ይላል። በእርግጥ አርስቶትል የማምሰልሰልን ጥበብ ተጠቅሞ እርቆ በመሄድ አንድ ሰው ኑሮውን አጣጥሞ ሳይጨርስ ደስተኛ ህይወት መርቶ ነበር ብሎ በእርግጠኝነት ለመፍረድ አይቻልም ብሏል። ፧ በሌላ ግንዛቤ ደግሞ በጥሩ ነገር ተማልቶ መገኘት ደስተኛ ህይወት ስለመኖሩ ማረጋገጫ ነው የሚል አስተሳሰብ አለ። ሮማዊው ፈላስፋ አንሺየስ ማንሊየስ ቦይቲየስ(Anicius Manlius Boethius) እንደተናገረው <<መልካም የተባሉትን ነገሮች በሙሉ አጠቃሎ ሀብቱ በማድረግ አንድ ሰው ደስተኛነት ላይ ይደርሳል። ያ ሰው ደስተኛ ስለመሆኑ ማረጋገጫ ምልክቱ ደግሞ ምንም ነገር አለመፈለጉ ነው። የእርሱ ምኞት ርካታን በማግኘት ብቻ ይጠቃለላል። ሰዋዊ የመኖር ትግሉ ሁሉ፣ በእዚሁ ድምዳሜ ላይ ይደርሳል።>> ፧ በግልፅ እንደሚስተዋለው ይሄ ሁሉ ነገር በአንድ ቀን ወይም በአንድ ዓመት ኑሮ ተፈፃሚ አይሆንም። የግድ ህይወት ተገባዳ መሟጠጫዋ ላይ መድረስ ይኖርባታል። ያኔ ወደኋላ መለስ ብሎ ጥሩ ጥሩ ነገሮችን በተጨባጭ መቃኘት ይችላል። ደስተኝነት በሌላ ሳይሆን በራሱ በግለሰቡ ተመዝኖ እንዲህ በማለት ይጠቃለላል። <<በእርግጥም ጥሩ ህይወት መርቻለሁ፤ በግሩም ሁኔታ ኖሬአለሁ>> ፧ ለደስተኝነት አስተዋፅኦ ያላቸው ግብአቶች ምን-ምን ናቸው? ...ይቀጥላል... ፨፨፨ ምንጭ ፦ የፍልስፍና አፅናፍ ደራሲ ፦ ዓለማየሁ ገላጋይ

#__ ባሕርን መሆን ___ ባንድ ወቅት በሕይወቱ ደስታን ያጣው ታዳጊ ወጣት አንድ የዕድሜ ባለጸጋን ሽማግሌ ሕይወት እንዳማረረችው ገልጾ መፍትሄ እንዲጠቁሙት ጠየቃቸው፡፡ #ሽማግሌው የወጣቱን ሀሳብ በጥሞና ካደመጡ በኋላ በእፍኙ ሙሉ ጥሬ ጨው በብርጭቆ ውሃ ጨምሮ በጥብጦ እንዲጠጣው አዘዙትና “ጣምናው እንዴት ነው?” በማለት ጠየቁት፡፡ ፊቱን አኮሳትሮ “በጣም አስቀያሚ ነው!” #ሲል መለሰላቸው፡፡ ሽማግሌው ፈገግታ እያሳዩት ወጣቱን ወደ ባሕር ዳርቻ ወስደው ሌላ ጭብጥ ሙሉ ጨው ባሕሩ ውስጥ እንዲጨምርበት አመላከቱት፡፡ በመቀጠልም ከባሕሩ ጨልፎ እንዲጠጣ ካደረጉ በኋላ “ጣዕሙ እንዴት ነው?” ሲሉ በድጋሜ ጥያቄ አቀረቡለት፡፡ “ጥሩ ነው” በማለት መለሰ ታዳጊው፡፡ አስከትለውም “የጨው ኮምጣጣነትና ያ አስቀያሚው ስሜት ተለይቶሃል?” በማለት ጠየቁት፡፡ “በፍጹም” ሲል መለሰ ወጣቱ፡፡ #ከዚህ ሁሉ የተግብር ትምህርት ቀጥሎ ሽማግሌው የወጣቱን እጅ ይዘው ከጎኑ ተቀመጡና ይሄንን መከሩት፡፡ በሕይወት ጎዳና የምታደርጋቸው ትግሎች እንደ ንጹህ ጥሬ ጨው ናቸው፡፡ #ነገር ግን የስቃዩ መጠን ተመሳሳይ ቢሆንም የምንሸከመው ስቃይ የሚወሰነው በምንይዝበት ዕቃ መጠን ይወሰናል፤ ችግሩን የምናስተናግድበት አግባብም የሚፈጥረውን ጫና በዛው ልክ ይለያየዋል፡፡ #ችግሩ ሲጠናብህ ልታደርገው የሚገባው ዋናው ነገር ምልከታህን ማስፋት ብርጭቆውን ሳይሆን ባሕሩን መሆን ነው ትልቁ የአኗኗር መላው፡፡# እናም ብርጭቆ መሆንህን አቁመህ ባሕሩን ሁን በማለት አሰናበቱት፡፡ ምንጭ፡-Stop being a glass, Become a lake. መልካም አዳር የነገ ሰው ይበለን #አሜን

ሰው ማለት እኮ የትዝታውና የትውስታው ድምር ነው። ሕይወት የመርሳትና የማስታወስ ሚዛን ናት። መርሳት ያለብንን መርሳት ሲያቅተን ሕይወታችን ይመሳቀላል... ደግሞ ማስታወስ ያለብንን የሕይወት ልምዶች ጠቃሚ ሰዎችና ነገሮች ከረሳን ...የእኛነታችን መለያና የስብእናችን ድንበር ይጠፋና ሌላ ሰው እንሆናለን።" ከሌላ ሰው መፅሃፍ ገፅ 285 የተወሰደ። ሰው ማለት እኮ የትዝታውና የትውስታው ድምር ነው። ሕይወት የመርሳትና የማስታወስ ሚዛን ናት። መርሳት ያለብንን መርሳት ሲያቅተን ሕይወታችን ይመሳቀላል... ደግሞ ማስታወስ ያለብንን የሕይወት ልምዶች ጠቃሚ ሰዎችና ነገሮች ከረሳን ...የእኛነታችን መለያና የስብእናችን ድንበር ይጠፋና ሌላ ሰው እንሆናለን።" ከሌላ ሰው መፅሃፍ ገፅ 285 የተወሰደ። @abrhott

ራስ መኮንን ወልደሚካኤል ልዑል ራስ መኮንን የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። ልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። ከአልቃሾቹም አንዱ ደግነታቸውን ለማስታወስ እንዲህ ብሎ አሟሸ፤- «ስልከኛው ሲያረዳ ነገር ተሳሳተው፤ መኮንን አይደለም ድኃ ነው የሞተው»

Your attitude, not your aptitude, will determine your altitude. - Zig Ziglar @abrhott @abrhott @abrhott

ያልወደደ አበደ (በላይ በቀለ ወያ) . . በሰው የደረሰ... በኔ ላይ እንዳይደርስ ፣ ስፈራና ስቸር ወድጄሽ እንዳላብድ ፣ ስጠነቀቅ ነበር፡፡ ታድያ ምን ያደርጋል በከንቱ ፍርሃት ፣ ባክኖ መጠንቀቄ ዋናው እብደት ነበር ፣ ከመውደድ መራቄ፡፡ @abrhott @abrhott

ይማርህ """""""""" በአፍንጫ ቀዳዳ በሰርኔ ጎድጓዳ ትንሽ ብናኝ ገብታ፤ አሀ..ን..ጥ..ሼ ብዬ አይኖቼን ጨፍኜ ለጥቂት ሰኮንዶች ትንፋሼ ቢገታ። ግድም የማይሰጠው ባጠገቤ እያለ ተመልካቼ በዝቶ ወገን እንደሌለው በንጥሻ ሞትኩኝ ይማርህ ባይ ጠፍቶ..! #አብርሃም

"ዘረኝነትን ወደ መጣበት መልሱት ከጫካም ከሆነ ወደ ጫካ ከባህርም ከሆነ ወደ ባህር ጨምሩት …… " ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር