አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
‹‹በአዕምሮው ህልም የተያዘ ሰው በሕይወት ጉድጓድ መውደቁ አይቀርም››
---------------------------
፪ . . .
‹‹ማንም ሰው በጉዞ ላይ የሚገኝ አዕምሮውን እንዳሻው እንዲሄድ መፍቀድ የለበትም። ሥጋን እንደመለማመድና እንደመግዛት አዕምሮን መግዛት ቀላል አይደለምና። ለአዕምሮ የሚሰጥ ነፃነት እጅግ በጣም ጥቂትና ውሱን ሊሆን ይገባል። በተለይ ደግሞ አዕምሮን የሕይወት ዕድልና አጋጣሚ እንዳሻው እንዲያሽከረክራት መፍቀድ የማያቋርጥ ስቃይን በራስ ላይ እንደመጋበዝ ይቆጠራል።
እውነትና ፍፁም የሆነውን ነገር ሕይወት በአዕምሯችን ውስጥ ብታስቀምጥም አላዋቂነት ሁለቱንም እንደሌሉ አድርጎ እያሳየ ቅዠታችን ከፍቷል።›› በማለት ሳራስዋቲ ለእዚህ ተ ስማሚ የሆነ ወግ ያስከትላሉ።
‹‹ከሕንድ በአንዲት የገጠር ከተማ በልብስ አጣቢነቱ የታወቀ አንድ ሰው ነበር። ይህ ሰው የየሰዉን ልብስ ከየቤቱ እየሰበሰበ በአህዮቹ በመጫን ወደ ወንዝ ይወስድና ሲያጥብ ውሎ አመሻሽ ላይ በመመለስ ለየባለቤቱ ያጠበውን ልብስ ማስረከቡ የሚታወቅበት ሥራው ነበር።
ይሁንና አንድ ቀን ይኽ ሰው ይታመምና የተለመደ የአጠባ ሥራውን ማከናወን ይሳነዋል። በዚህ ጊዜ ወንድ ልጁን ጠርቶ በአህዮቹ ልብ ሱን ጭኖ ወደ ወንዝ በመውሰድ አጥቦ እንዲያመጣ ይነግረዋል።
ልጁም አባቱ እንዳዘዘው የሰበሰበውን ልብስ በአህዮቹ ላይ በመጫን ሊነዳቸው ቢሞክር አህዮቹ ከቆሙበት ቦታ አልንቀሳቀስ አሉ። አህዮቹ እግራቸው በገመድ ሳይታሰር ከቆሙበት አልንቀሳቀስ በማለታቸው ግራ የተጋባው ልጅ ወደ አባቱ በመሄድ፦
‹‹አባባ! አህዮቹን ለመንዳት ብሞክር ሊንቀሳቀሱልኝ ፈቃደኛ አልሆኑም›› ይለዋል።
በዚህ ጊዜ አባትየው ከተኛበት ቀና ብሎ፦ ‹‹ልጄ አንድ ምስጢር ሳልነግርህ ረስቼው ነው። አህዮቹን ማታ ወደ ማደሪያቸው ሳስገባቸው የሁሉንም እግር በእጆቼ እነካዋለሁ። አህዮቹም በገመድ ያሰርኳቸው ስለሚመስላቸው ከቦታቸው አይንቀሳቀሱም። በነጋታው መጥቼ የሁሉንም እግር በእጆቼ ስነካ ገመዱን የፈታሁላቸው ይመስላቸዋል።
በዚህ መንገድ ስላለማመድኳቸው ገመድ ሳልጠቀም በመሸና በነጋ ቁጥር ሳስርና ስፈታቸው ኖሬአለሁ። አሁንም ሂድና የሁሉንም እግሮች በእጆችህ ንካቸው። እንደፈታሀቸው አምነው መንቀሳቀስ ይጀምራሉ›› አለው።
ልጁም ወደ አህዮቹ ተመልሶ እንደታዘዘው ቢያደርግ አህዮቹ ከቆሙበት መንቀሳቀስ ጀመሩ።
~
‹‹እንግዲህ›› ይሉናል ሳራስዋቲ
‹‹የሰው ልጅ የሚገኝበት ሁኔታም ከዚህ ጋር በእጅጉ ተመሳሳይ ነው። ከፍጥረቱ ነ ፃ የሆነው ሰው በተለያዩ ህጎችና እምነቶች አዕምሮውን አስሮ ይሰቃያል። እነዚያ ሕጎችና እምነቶች ግን ቀድሞውኑ ለእሱው ነፃነትና ደስታ የተፈጠሩ መሆናቸውን አያውቅም፤ እናም በቅዠቱ በፈጠረው ገመድ ራሱን አስሮ የሚማቅቅ ፍጡር ሆኗል። ለዚህም ይመስላል እውነትና ቅድስና ለሰው ልጅ የሰማይ ያህል ርቀው ሲታዩ የኖሩት።›› በማለት ሳራስዋቲ የሕይወት ሥርዓት ራስን ለመግለጥና ለማወቅ ብሎም ወደ እውነታ ሁሉ ለመድረስ የተሻለው መንገድ መሆኑን የሚያስቀምጡት።
. . .
-----------------------------
📓 "ጥ በ በ"
🖌 ከ ጲ ላ ጦ ስ
(ኃይለጊዮርጊስ ማሞ)
📖 📖 📖 📖 📖 📖
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
‹‹በአዕምሮው ህልም የተያዘ ሰው በሕይወት ጉድጓድ መውደቁ አይቀርም››
---------------------------
፪ . . .
‹‹ማንም ሰው በጉዞ ላይ የሚገኝ አዕምሮውን እንዳሻው እንዲሄድ መፍቀድ የለበትም። ሥጋን እንደመለማመድና እንደመግዛት አዕምሮን መግዛት ቀላል አይደለምና። ለአዕምሮ የሚሰጥ ነፃነት እጅግ በጣም ጥቂትና ውሱን ሊሆን ይገባል። በተለይ ደግሞ አዕምሮን የሕይወት ዕድልና አጋጣሚ እንዳሻው እንዲያሽከረክራት መፍቀድ የማያቋርጥ ስቃይን በራስ ላይ እንደመጋበዝ ይቆጠራል።
እውነትና ፍፁም የሆነውን ነገር ሕይወት በአዕምሯችን ውስጥ ብታስቀምጥም አላዋቂነት ሁለቱንም እንደሌሉ አድርጎ እያሳየ ቅዠታችን ከፍቷል።›› በማለት ሳራስዋቲ ለእዚህ ተ ስማሚ የሆነ ወግ ያስከትላሉ።
‹‹ከሕንድ በአንዲት የገጠር ከተማ በልብስ አጣቢነቱ የታወቀ አንድ ሰው ነበር። ይህ ሰው የየሰዉን ልብስ ከየቤቱ እየሰበሰበ በአህዮቹ በመጫን ወደ ወንዝ ይወስድና ሲያጥብ ውሎ አመሻሽ ላይ በመመለስ ለየባለቤቱ ያጠበውን ልብስ ማስረከቡ የሚታወቅበት ሥራው ነበር።
ይሁንና አንድ ቀን ይኽ ሰው ይታመምና የተለመደ የአጠባ ሥራውን ማከናወን ይሳነዋል። በዚህ ጊዜ ወንድ ልጁን ጠርቶ በአህዮቹ ልብ ሱን ጭኖ ወደ ወንዝ በመውሰድ አጥቦ እንዲያመጣ ይነግረዋል።
ልጁም አባቱ እንዳዘዘው የሰበሰበውን ልብስ በአህዮቹ ላይ በመጫን ሊነዳቸው ቢሞክር አህዮቹ ከቆሙበት ቦታ አልንቀሳቀስ አሉ። አህዮቹ እግራቸው በገመድ ሳይታሰር ከቆሙበት አልንቀሳቀስ በማለታቸው ግራ የተጋባው ልጅ ወደ አባቱ በመሄድ፦
‹‹አባባ! አህዮቹን ለመንዳት ብሞክር ሊንቀሳቀሱልኝ ፈቃደኛ አልሆኑም›› ይለዋል።
በዚህ ጊዜ አባትየው ከተኛበት ቀና ብሎ፦ ‹‹ልጄ አንድ ምስጢር ሳልነግርህ ረስቼው ነው። አህዮቹን ማታ ወደ ማደሪያቸው ሳስገባቸው የሁሉንም እግር በእጆቼ እነካዋለሁ። አህዮቹም በገመድ ያሰርኳቸው ስለሚመስላቸው ከቦታቸው አይንቀሳቀሱም። በነጋታው መጥቼ የሁሉንም እግር በእጆቼ ስነካ ገመዱን የፈታሁላቸው ይመስላቸዋል።
በዚህ መንገድ ስላለማመድኳቸው ገመድ ሳልጠቀም በመሸና በነጋ ቁጥር ሳስርና ስፈታቸው ኖሬአለሁ። አሁንም ሂድና የሁሉንም እግሮች በእጆችህ ንካቸው። እንደፈታሀቸው አምነው መንቀሳቀስ ይጀምራሉ›› አለው።
ልጁም ወደ አህዮቹ ተመልሶ እንደታዘዘው ቢያደርግ አህዮቹ ከቆሙበት መንቀሳቀስ ጀመሩ።
~
‹‹እንግዲህ›› ይሉናል ሳራስዋቲ
‹‹የሰው ልጅ የሚገኝበት ሁኔታም ከዚህ ጋር በእጅጉ ተመሳሳይ ነው። ከፍጥረቱ ነ ፃ የሆነው ሰው በተለያዩ ህጎችና እምነቶች አዕምሮውን አስሮ ይሰቃያል። እነዚያ ሕጎችና እምነቶች ግን ቀድሞውኑ ለእሱው ነፃነትና ደስታ የተፈጠሩ መሆናቸውን አያውቅም፤ እናም በቅዠቱ በፈጠረው ገመድ ራሱን አስሮ የሚማቅቅ ፍጡር ሆኗል። ለዚህም ይመስላል እውነትና ቅድስና ለሰው ልጅ የሰማይ ያህል ርቀው ሲታዩ የኖሩት።›› በማለት ሳራስዋቲ የሕይወት ሥርዓት ራስን ለመግለጥና ለማወቅ ብሎም ወደ እውነታ ሁሉ ለመድረስ የተሻለው መንገድ መሆኑን የሚያስቀምጡት።
. . .
-----------------------------
📓 "ጥ በ በ"
🖌 ከ ጲ ላ ጦ ስ
(ኃይለጊዮርጊስ ማሞ)
📖 📖 📖 📖 📖 📖
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
" The School of Athens" ስዕል🇬🇷
*****************
#የቀጠለ...
የስዕሉ ፍልስፍናዊ ማብራሪያ📚📚
=========!==========
ፕሌቶም ሆነ አሪስቶትል ሁለቱም Realists ናቸው፡፡ ይሄም ማለት ‹‹ከእኛ ንቃተ ህሊና ውጭ የሚኖር እውነታ አለ Something beyond and above our consciousness exists out there›› በሚለው ሐሳብ ላይ ሁለቱም ይስማማሉ፡፡
ሁለቱ የተለያዩትና ጣታቸውን በተቃራኒ አቅጣጫ እንዲያመለክቱ ያደረጋቸው ‹‹ይሄ እውነታ የት ነው ያለው?›› በሚለው ጥያቄ ላይ ነው፡፡ የእውነታ መገኛ ቦታን ለማመላከት ፕሌቶ ጣቱን ወደ ሰማይ ሲጠቁም፤ አሪስቶትል ደግሞ ወደ ምድር ይጠቁማል፡፡
ፕሌቶ በፍልስፍናው ውስጥ ‹‹የማኛንኛውም ነገር የምንነት ባህሪ (Form/Essence - ለምሳሌ የሰው የምንነት ባህሪ ነፍስ (The Form of Man) ነው፤) የሚኖረው ከዚህ ዓለም ውጭ በሆነ ሌላ ዓለም ላይ ነው፤›› የሚል አመለካከት ሲኖረው፤ ይሄንን ፍልስፍናውንም በስዕሉ ላይ ጣቱን ወደ ሰማይ በማመላከት ይገልፃል፡፡
አሪስቶትል ግን ‹‹የነገሮች የምንነት ባህሪ ያለው በራሳቸው በነገሮች ውስጥ ሲሆን ሁለቱ ተነጣጥለው መኖር አይችሉም (ለምሳሌ - የሰው ነፍስ ከሰው አካል ተነጥላ ለብቻዋ መኖር አትችልም)›› የሚል አመለካከት ሲኖረው ይሄንን ፍልስፍናውንም ለማመላከት በስዕሉ ላይ እጁን ወደታች ወደ ምድር ዘርግቶ ይታያል፡፡
ሰናይ ቀን ተመኘሁ
ተቀላቀሉን
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
📓 ሰ በ ዝ
🖌 ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ
-----------------------
. . .
ልማት ልናፋጥን፣ ዲሞክራሲ ልናሰፋ፣ ፍትህ ልናሰፍን እንችል ዘንድ፤ ዕውቀት ልንጨምር ልንሰለጥን ተጠርተን 'ሰዓት አለማክበርን' 'በወቅቱ አለመጀመርን' በተግባር ሠለጠን።
ፍጥነትን በመዘግየት፣ መልስ መስጠትን በማጉላላት፣ ሥራ ለማቀላጠፍ ሥራን ዘግቶ በመጠበቅ ጀመርነው። ...
ድንቁርናችን ከመግዘፉ የተነሳ ነውራችን ክብራችን ሆነ። ...
. . .
ጊዜና የጊዜ ግንዛቤ የሰው ልጆችን ከሌሎች እንስሳት የሚለዩት ጉዳዮች ናቸው። አምና፣ ዘንድሮ፣ ከርሞ፤ ትናንት፣ ዛሬና ነገ እንዲሁም ቅድም፣ አሁንና ኋላ በእንስሳት ዓለም ውስጥ የሉም። የሰው ልጅ ግን ቅድምንና አሁንን ለይቶ የማወቅ የሞራል ግዴታ አለበት።
እድሜ ጊዜ ነው ፡፡ ሰው ሞተ የሚባለው እኮ ጊዜው ሲያልቅ ነው፡፡ ጊዜ ሲረዝም እድሜ ሲያልቅ ደግሞ ሞት ነው፡፡ ሞት መራራ ከሆነ ምነው ጊዜ መባከን ቢያንስ ህመም አይሆንብንም?
ሰው ቀጥሮህ ሲቀር ከእድሜህ እቀነሰብህ ነው፡፡ የሆነ ሰው ያለአግባብ የወሰደብህን ገንዘብ አንድ ቀን ሊመልስልህ ይችላል፤ የወሰደብህን ጊዜ ግን መቼም አይመልስልህም፡፡ አንድ ሊቅ እንዳለው ለሰው የምትሰጠው ትልቁ ስጦታህ ጊዜ ነው፡፡ እንዴት? የሰጠኸው ጊዜ ከእድሜህ ላይ የቀነስከው ነውና!
. . .
-------------------------
📖 155 - 156
📙 📙 📙 📙 📙
3 738
#የንባብ_ቅምሻ...
እንቅልፍ ይሞታል ?
አዎን እንቅልፍ ይሞታል ። ገዳዩም የእንቅልፍ ባለቤት ነው ። ዕረፍትን የሚገድል ረፍት የሌለው ነው ። ሲሰራ ፣ ሲተጋ ዕረፍት (እንቅልፍ) የሌለው አለ ። ይሄ ግን እንቅልፉን ገደለ አይባልም ። እንቅልፉን ሰዋ እንጂ ።
ሲያሴር ፣ ሲያደባ ፣ ተንኮል ሲጎነጉን ለሰው ልጆች የመውደቂያ ጉድጓድ ሲምስ ከራሱና ከሕዝብ የተጣላ እንቅልፍ የሌለው አለ ። " ከተማው ዕረፍት የለውም " እንቅልፍን ገድሏልና ። ሕይወትን በመመርመር ፣ ውበትን በመፈለግ ፣ ጥበብን በመጠበብ እንቅልፍ የሌላቸው አሉ ። ከእረፍታቸው ላይ ለትጋታቸው የሚቀንሱ ። በመልካም ስራቸው ስማቸውን ለመፃፍ ከአጭሩ የጊዜ ጅረት ላይ በእጥፍ የሚቀዱ " እነሆ ይሄ ሰው አንቀላፍቶ አያውቅም " ተብለው ለመጠራት ካላንቀላፉት ተርታ ለመሰለፍ መተኛት እየቻሉ ፣ የማያርፉ አሉ ።
እንቅልፋቸውን የሚገድሉ አሉ ። ደግመኛ ላያሸልቡ በቁማቸው በፈፀሙት ቅዠት ሁለተኛ ማለም የማይችሉ ። በተንኮላቸው ፣ በሴራቸው ፣ በፍርደ - ገምድልነታቸው ፣ ሰነድ በመሸጣቸው ፣ ሀገር በማጥፋታቸው ፣ ፍርድ በማጉደላቸው ፣ አልጋቸው ላይ በመትፋታቸው ፣ ሕ ዝብን በመበደላቸው እንቅልፍን የገደሉ ። መተኛት የማይችሉ ። በመዓልት ጥፋታቸው ሌሊት የሌላቸው በሌሊቱ ሴራቸው ቀናቸውን ያጨለሙ ፣ ከዕረፍት የተለዩ እንቅልፍን የገደሉ አሉ ።...
ምንጭ 📖 የይሁዳ ድልድይ እና ሌሎች ሃሳቦች ገጽ 149
ደራሲ ✍ ኤፍሬም ሥዩም
ኅትመት 📝 ኅዳር 2007
3 738
Hello everyone👋...Support us to make our architectural thesis by filling this questionnaire.
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSejvsJYWyqIJ93UVUNJAaUX_rtazjdxtpih8b8IIjSagrawHQ/viewform?usp=sf_link
3 738
" The School of Athens" ስዕል🇬🇷
***************
የዚህ ስዕል መጠሪያ ‹‹The School of Athens›› ሲባል ሰአሊውም ራፋኤል (Raphael) ይባላል፤ የህዳሴው ዘመን (Renaissance) ካፈራቸው ምርጥ ሰአሊዎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ራፋኤልና በእሱ ሥር የሚመራው የሰአሊዎች ቡድን ይሄንን ስዕል ለመጨረስ ሦስት ዓመታት (ከ1509―በ1511) ወስዶባቸዋል፡፡
የሚገርመው ነገር ስዕሉ የሚገኘው በቫቲካን የጳጳሳት መኖሪያ አፓርትመንት (The Apostolic Palace) ውስጥ መሆኑ ነው፡፡ ልክ የፈላስፎችን ስዕል በቤተ መቅደስ ውስጥ እንደማለት ነው!!
ስዕሉን ስፖንሰር ያደረጉት Pope Julius II ናቸው፡፡ የጳጳሳቱ መኖሪያ አፓርትመንት ክፍሎች በተለያዩ ቅዱሳን ስዕሎች ያሸበረቀ ሲሆን፣ 3ኛ ፎቅ ላይ የሚገኙት ‹‹የሩፋኤል ክፍሎች (Raphael Rooms)›› ደግሞ የወቅቱን የህዳሴ መንፈስ የያዘ የጥንታዊ ግሪክ ፈላስፎችን በአንድነት ያካተተ ስዕል እንዲሳልበት ተደርጓል፡፡
‹‹The School of Athens›› ከሚለው ስዕል ውስጥ ማዕከላዊውን ሥፍራ የሚይዙት ፕሌቶና አሪስቶትል ናቸው፡፡ በስዕሉ ላይ በግራ በኩል የሚታየው አዛውንት ፕሌቶ ሲሆን፣ እሱም Timaeus - የተባለውን መፅሐፉን በግራ እጁ ይዟል፡፡
በቀኝ በኩል ያለው ጎልማሳ ደግሞ አሪስቶትል ሲሆን እሱም እንዲሁ Nichomachian Ethics የተባለውን መፅሐፉን በግራ እጁ ይዟል፡፡ ስዕሉ ፕሌቶና አሪስቶትል ከፕሌቶ ከአካዳሚያ የፍልስፍና ት/ቤት እየተከራከሩ ሲወጡ የሚያሳይ ነው፡፡
**
ይቀጥላል
የስዕሉ ፍልስፍናዊ ማብራሪያ📚📚
Via እንደ_ራስ_ፍልስፍና
ተቀላቀሉን
@abrhott
3 738
#አንዳንድ_ስእሎች
#ሶቅራጥስ
አልጋው መሀል ላይ ሶቅራጥስ ተቀምጧል። ደማቅ ብርሀን አርፎበታል። በራስ መተማመን ተሞልቶ ፣ እጆቹን ከፍ አድርጎ ይናገራል። በዙሪያው ያሉት ሰዎች ግን ተጨንቀዋል ፤ ተጠበዋል ፤ ተከፍተዋል። ከሰዎቹ አንደኛው ለሶቅራጥስ አንዳች ፈሳሽ እየሰጠው ነው። መስጠት የፈለገ ግን አይመስልም። ሶቅራጥስ በበኩሉ ፈሳሹን ለመቀበል በሙሉ እርግጠኝነት እጁን ዘርግቷል። ፈሳሹ መርዝ ነው። “የሶቅራጥስ ሞት” ይሰኛል ስእሉ። በሶቅራጥስ ሞት አካባቢ የነበረውን መንፈስ በአንድ ጠቅሎ የያዘ ነው። የሶቅራጥስ ሞት ሁሉን አሳዝኗል—ከሶቅራጥስ በቀር!ምን ተአምር ነው ሟች በሙሉ ልብነት ጽዋውን ለመጠጣት ሲዘጋጅ ኗሪዎች የተፍረከረኩት?!
ተቀላቀሉን
@abrhott
3 738
ቤይሩት ፡ ኢትዮጵያዊነት በሰው አገር
በሌባኖሷ መዲና ቤይሩት በተከሰተው ከባድ ፍንዳታ ቢያንስ 100 ሰዎች ሞተዋል።
ከ4ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ይህቺ ብላቴና ...
ኢትዮጵያዊነት በሰው አገር -
በዚህ እሳት ውስጥ ... የነፍስ አድን ሰርታለች።
ዓለም በአድናቆት እና በክብር እጅ እየነሷት ነው።
ኢትዮጵያዊነት በሰው አገር …
እንዲህ ነው ኢትዮጵያዊነት!
