አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
ከጸሎቱ ራሴን አግልያለሁ.....
....
ከሶስት ቀን በፊት የጸሎት አዋጅ ታውጇል። እስከ ዛሬ አሰብኩበት ግን ምንም ፈጣሪን የምጠይቀው ነገር አጣሁ።ምን አድርግ ልበለው?ምንስ አጠፋ? ማረን እንኳን ብዬ ብጸልይ እውነት መማር የሚገባን ሰዎች ነን?የሚለውን ጥያቄ አሳማኝ መልስ አጣሁለት። የህዝቡን ልብ ሳየው ጸሎቴን መጠንዛት ሆነብኝ። ማረን ብዬ ከማረን በኋላ የሚመጣውንም ሳስብ ተቃራኒውን አስመኘኝ። ፈጣሪን አንሸውደው።አይ ግድ የለም ይሕ ነገር ይለፈኝ ብጸልይም ጸሎቴ የምህረት አልመስልህ ብሎኛል።
ከሀሳቡ የሚስማማ 🤙
የማይስማማ ✋
ድምጸ ተአቅቦ 😖
3 738
ከጸሎቱ ራሴን አግልያለሁ.....
....
ከሶስት ቀን በፊት የጸሎት አዋጅ ታውጇል። እስከ ዛሬ አሰብኩበት ግን ምንም ፈጣሪን የምጠይቀው ነገር አጣሁ።ምን አድርግ ልበለው?ምንስ አጠፋ? ማረን እንኳን ብዬ ብጸልይ እውነት መማር የሚገባን ሰዎች ነን?የሚለውን ጥያቄ አሳማኝ መልስ አጣሁለት። የህዝቡን ልብ ሳየው ጸሎቴን መጠንዛት ሆነብኝ። ማረን ብዬ ከማረን በኋላ የሚመጣውንም ሳስብ ተቃራኒውን አስመኘኝ። ፈጣሪን አንሸውደው።አይ ግድ የለም ይሕ ነገር ይለፈኝ ብጸልይም ጸሎቴ የምህረት አልመስልህ ብሎኛል።
ከሀሳቡ የሚስማማ 🤙
የማይስማማ ✋
ድምጸ ተአቅቦ 😖
3 738
🛑 #ETHIOPIA | የኮቪድ19 በሽታ የየቀኑ ምልክቶች
📌 ከ1-3 ቀን
• በነዚህ የመጀመሪያ ቀናት ቀላል ጉንፋን መሰል ሆኖ ቀለል ያለ ትኩሳት እና ጉሮሮ ህመም ብቻ ሲኖር የምግብ እና መጠጥ ፍላጎት ጥሩ ነው ።
• የሰውነት መከላከያ ደከም ያለባቸው ስዎች ቀለል ያለ ተቅማጥ እና ማቅለሽለሽ
ሊኖራቸው ይችላል ።
📌 በ 4 ኛው ቀን
• የጉሮው ህመም ይጨምራል እንደዚሁም የድምፅ መወፈር ይኖራል ።
• ብዙ ጊዜ ትኩሳት አይኖርም 36.5 degree ብቻ ይሆናል
• ቀለል ያለ እራስ ምታት እና የምግብ እና መጠጥ ፍላጎት ሊስተገዋጎል ይችላል ።
📌 በ 5 ኛው ቀን
• ስሜቶች የበለጠ ይጨምራሉ ፦ የጉሮሮ ህመም ይጨምራል ፣ ድምፅ የበለጠ ይጎረንናል ።
• በእንቅስቃሴ ወቅት የስውነት ህመምና ቁርጥማት ይኖራል ፤ የሰውነት ድካም ይኖራል ።
📌 በ 6 ኛው ቀን
• ትኩሳት ይጀምራል
• ደረቅ ሳል ከጉሮሮ ህመም ጋር ይበረታል
• ምግብ በመመገብ ፣ የሚጠጣ ነገር ሲወስድ እንደዚሁም በንግግር ጊዜ የጉሮሮ ህመም ይኖራል ።
• ተቅማጥና ማቅለሽለሽ የበለጠ ይጨምራል ።
📌 በ 7 ኛው ቀን
• ትኩሳት ከ 38 ድግሪ በላይ ይሆናል
• ደረቅ ሳል ይኖራል ፣ ይጨምራል
• የስውነት ቁርጥማት ፣ ራስ ምታት ፣ ተቅማጥና ማቅለሽለሽ ይጨምራል ።
📌 በ 8 ኛው ቀን
• መተንፈስ መቸገር
• የደረት መክበድና ህመም
• ደረቅ ሳል ይኖራልም ይጨምራልም
• የስውነት ቁርጥማት ፣ ራስ ምታት ይቀጥላልም በጣም ይጨምራል ።
• ትኩሳት ይቀጥላል ፣ ይጨምራል
📌 በ 9 ኛው ቀን እና በሚቀጥሉት ቀናት
• ሁልም ከላይ የተጠቀሱት ምልክቶች በጣም ይጨምራሉ ።
ይሄንን መረጃ ለሁሉም በፍጥነት አጋሩ
@abrhott
3 738
#COVID19 😷 #Ethiopia‼️
በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ ሁኔታ፦
• አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ - 2,496
• በ24 ሰዓት የተከናወነ ላብራቶሪ ምርመራ - 225
• ዛሬ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ - 3
• በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ህክምና ያሉ - 47
• በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ - 2
• ያገገሙ - 4
• በበሽታው ህይወታቸው ያለፈ - 2
• ወደሀገራቸው የተመለሱ - 2
• እስካሁን በበሽታው የተያዙ - 55
#DrLiaTadesse
3 738
በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ ሁኔታ፦
• አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ - 2271
• በ24 ሰዓት የተከናወነ ላብራቶሪ ምርመራ - 264
• ዛሬ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ - 8
• በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ህክምና ያሉ - 44
• በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ - 1
• ያገገሙ - 4
• በበሽታው ህይወታቸው ያለፈ - 2
• ወደሀገራቸው የተመለሱ - 2
• እስካሁን በበሽታው የተያዙ - 52
3 738
ኮሮና ቫይረስ የሚስፋፋበትን ፍጥነት ተመልከቱ ፦
• ጥር 27/2012 ዓ/ም አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 28,000
• የካቲት 27/2012 ዓ/ም አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 98,500
• ዛሬስ ? ዛሬ አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 1,245,207
ቁጥራዊ መረጃው ዓለም አቀፍ ሁኔታን የሚመለከት ነው!
3 738
#BREAKING
አንዲት የ60 ዓመት ታማሚ መጋቢት 19 ፣ 2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክት ታይቶባቸው በለይቶ ማከሚያ ገብተው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው የነበረ ሲሆን በመጋቢት 22፣ 2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው መረጋገጡ ይታወሳል፡፡
ይሁንና ከመጋቢት 22 አንስቶ ላለፉት ስድስት ቀናት በፅኑ ህክምና ላይ የነበሩ ሲሆን በዛሬው እለት ህይወታቸው አልፏል፡፡
የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በህልፈተ ህይወታቸው የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል፡፡
ምንጭ፦ ኢቢሲ
3 738
#FightCOVID19
በአሁን ሰዓት በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ1.2 ሚሊዮን የበለጠ ሲሆን 64,787 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ከቫይረሱ ያገገሙት 247,301 ደርሰዋል።
በኮቪድ-19 ከፍተኛ የሟቾች ቁጥር የተመዘገበባቸው ሀገራት ዝርዝር ፦☝️
3 738
በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ ሁኔታ ፦
• አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ - 1843
• ባለፉት 24 ሰዓት የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 59
• ዛሬ በበሽታው የተያዙ ታማሚዎች - 5
• በአሁን ጊዜ በለይቶ ማቆያ ያሉ ታማሚዎች - 37
• ፅኑ ህሙማን - 1
• ህይወታቸው ያለፈ - 0
• ከበሽታው ሙሉ በሙሉ ያገገሙ - 4
• በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ድምር - 43
ማስታወሻ፦ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጡ 2 ታማሚዎች ወደሀገራቸው ተመልሰዋል።
3 738
#FightCOVID19
በአሁን ሰዓት በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ1.2 ሚሊዮን የበለጠ ሲሆን 64,787 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ከቫይረሱ ያገገሙት 247,301 ደርሰዋል።
በኮቪድ-19 ከፍተኛ የሟቾች ቁጥር የተመዘገበባቸው ሀገራት ዝርዝር ፦
• ጣልያን - 15,362
• ስፔን - 11,947
• ዩናይትድ ስቴትስ - 8,454
• ፈረንሳይ - 7,560
• ዩናይትድ ኪንግደም 4,313
• ኢራን - 3,452
• ቻይና - 3,326
• ኔዘርላንድ - 1,651
• ጀርመን - 1,395
• ቤልጂየም - 1,283
• ስዊዘርላንድ - 666
• ቱርክ - 501
• ብራዚል - 431
• ስውዲን - 391
• ፖርቹጋል - 266
• ካናዳ - 231
• ኢንዶኔዥያ - 191
3 738
"የጥሩ ጊዜ መጥፎነቱ ያልፋል፤
የመጥፎ ጊዜ ጥሩነቱ እሱም ያልፋል፡፡"
እና ምን ልልክ ፈልጌ ነው ወዳጄ ዛሬ ክንድህ አዝሎ፣ የአይምሮክን ጡንቻዎች አዝለፍልፎ መኖር እንዲያስጠላክ የሚያደርግ ሁኔታ ላይ ትሆን ይሆናል። ነገር ግን እመነኝ ይህ ሁሉ ፈተናና መከራ ያልፋል፡፡ ፈጣሪክን ለምን ይህ ሁሉ ችግር ገጠመኝ ብለክ ከማማረር ይልቅ ችግረሮቼን የምቋቋምበት ፅናትና ብርታት ስጠኝ በለው፡፡ የዛኔ ድልድይ ሆኖ ያሻግርህና ፈፅሞ ከማትጠብቀው መልካም ቦታ ያስቀምጥሀል፡፡
ወዳንተኛው ደሞ ልምጣ፤ አዎ አንተኛው ዛሬ ከሰማይ በታች ሁሉ ነገር የሞላልክ፤ አለምን በመዳፍክ የጨበጥክ መስሎ የሚሰማክ፤ ድሆችን እንዳንተ አንዱ እግዚአብሔር ሳይሆን አንተ እራስክ የፈጠርካቸው መስሎ የሚሰማክ፤ ይህ ሁሉ የምትመካበት እና የምትኮራበት ሀብትና ዝና በአንድ ጀምበር እንዳልነበር ሊሆን ይችላል፡፡ ሁሉም አልፎ ዳግም ከዜሮ ትጀምር ይሆናል፡፡ እናም ባለህ ነገር አትዘባበት፤ ፈፅሞ አትኩራራ፡፡
መልካም የCOVID19 ፍልምያ ጊዜ ።
ድል ለሠፊዉ ህዝብ✌️🏾
3 738
ይህን ፅሁፍ እንዳተነብበው!!...(መቼም የተከለከልነው ነው ሚያምረን አይደል?!...)
ለሚያልፍ ዝናብ ባንበሰብስ😌
¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤ ውጣ ውረድ አይታ ላሳደገችህ ውድ እናትህ ወደቤት ስትሄድ ላደረገችው ውለታ ይዘህላት የምትሄደው 'የሞት ፅዋ' ነው ወይ?...መከታ ሆኖ አሁን ላለህበት ያደረሠህ ለምትወደው አባትህስ በእጅህ እና በትንፋሽህ ይዘህለት የምትገባው ውዱ ስጦታህ 'የሞት ጥቅል' ነው?!...እሺ ይህቺን ዓለም እያለቀስክ ከመጣህባት በእልልታ ለተቀበሉህ አሳዳጊዎችህ ወይም ዘመድ ወዳጆችህ? ያንተ ስጦታ በቸልተኝነትህ የምትሸከመው 'መግደያ መሣሪያ' ነው?....ለወንድሞችህስ?...ለእህቶችህስ?..እሺ ለልጆችህስ አያሳዝኑህም?!..እሺ አይኑሩህ ...ለወንድምህ ወይም ለእህትህ ልጆች..ወይም ለሚወዱህ ለምታጫውታቸው ህፃናትስ መጫወቻ አመጣሁላችሁ ብለህ በእጆችህ ወይም በትንፋሽህ አንከርፍፈህ የምትሰጣቸው 'ሞት'ን ነው ወይ?!...ደጅ እያደሩ በብርድና በርሃብ እየተገረፉ ለሚኖሩ 'ጎዳና ተዳዳሪዎችስ' ከምትሰጣቸው ሳንቲም ወይም ሌላ ነገር ጋር በገዛ ቸልተኝነትህ 'ሞት'ን ቀላቅለህ እንደምትሰጣቸው አስተውለሃል?!..ፍርድህ ይሄ ነው?!...ስለምን ለሚወዱህና ለምትወዳቸው ስትል አትኖርም?....ወጣት ነህ!..ይህ መዓት ደግሞ ብዙ ጊዜ ወጣቶችን አያስከነዳም?!...ኧረ ባክህ?!..አትለኝም!...እሺ ባንተ ምክንያት የሚጎዱትና የሚሰቃዩት ቤተሠቦችህስ?..የአካባቢህ ሠዎችስ?...ስለምን ተጠንቀቅ እየተባልክ ችላ ትላለህ?!...ቢያንስ ለራስህ ስትልም ባይሆን ካንተ ባሻገር ስላሉ ወዳጅ ቤተሠቦችህ ስትል ተጠንቀቅ!!...ቢያንስ ከፀፀት ትድናለህ!...ሳትጠነቀቅ ከምትሞት ተጠንቅቀህ ብትሞት ይሻላል!..ምክንያቱም ፀፀት ዳግመኛ ሞት ነውና!!..ብትተርፍም ከሙት የማይሻል ስጋ ተሸክመህ መንከርፈፍ ዋጋ አይኖረውም!..ማስክ አድርግ ከተባልክ አድርግ!(በዛውም ከአላስፈላጊ ጠረን ትድናለህ!)..ታጠብ ከተባልክ ታጠብ!(ከልጅነትህ ጀምሮ የዘመርከውን "ሳይንስ ሳይንስ መዳኒቴ!..."እያልክ መዘመር ትችላለህ!..ብቻ ታጠብ!
መንገድ ላይ ቆመህ ትሸና የለ...እስኪ ቆመህ ታጠብ)..ጓንት አድርግ ከተባልክ አድርግ!(ለእጅህም ጥሩ ነው!..በልጅነትህ የነበረውን ሐኪም የመሆን ምኞትህን ለአፍታ ታጣጥመዋለህ!..)..ርቀትህን ጠብቅ ከተባልክ ጠብቅ!(እግረ መንገድህን ከኪስ አውላቂ ሰለባነት ትድናለህ!)....ወደ ፈጣሪ ቅረብና ለምነው!..ሃገርህን ዓለምህን ከዚህ መዓት እንዲያሻግራት...ይህን በማድረግህ የምትጎዳውም የሚጎድልብህም አንዳች ነገር የለም!...እንደውም ካስተዋልከው በጫንቃህ የብዙ ሠዎችህ ነፍስ ታተርፋለህ!!... ከዛ ፈጣሪም ታዛዥነትህንና ትህትናህን ዓይቶ መዓቱን ያነሳልሃል!...ያኔ ሠው ትሆናለህ!...ከእንተ ባሻገር ላሉ ሠዎችህ ስትል ተጠንቀቅ!!..
(መጠንቀቅ መፍራት አይደለም!...እኔም ከዚህች ቀን ጀምሮ ለምወዳቸው ሠዎች ስል እጠነቀቃለሁ!!)
3 738
ደመና ሲያይ መስሎት የጨለመ
አለ ቂል ሰው 'ሁሉም አከተመ'
ደቂቅ ተስፋን ካየናት አርቀን
ነገ ሌላ ይሆናል ጥሩ ቀን!
ጨለማው በብርሀን ይለወጣል!
ሕይወት በብርሀን ጊዜ ብቻ የምንደሰትባትና የምንፈነጥዝባት አይደለችም። ይልቁኑም በጨለማውና ግራ በገባን ጊዜ ጭምር ከጨለማውና ከውጥንቅጡ ለመውጣት በምናደርገው ጥረት ይበልጥ ህይወታችንን ወደ በለጠ ደስታ ውስጥ እንጨምረዋለን።
በጨለማው ጊዜ በውጥንቅጡ ጊዜ በችግሩ ጊዜ ተስፋ የቆረጡ፣ህይወታችን አበቃላት ብለው ጉዟቸውን ያቆሙና ህመሙ በዛብኝ ብለው ህልማቸውን ያቋረጡት ሁሉ አስደናቂዋን የብርሀን ፍንጣቂ ለማየት አይታደሉም።
የብርሀኗን ፍንጣቂ ለማየት በህመሙ ጊዜ መጠንከር፣ በስቃዩ ጊዜ መበርታት በጨለማው ጊዜ መታገስ ያስፈልጋል፤ ያኔ ህመሙ ወደ መዳን፣ ማጣቱ ወደ ማግኘት፣ ጨለማውም ወደ ብርሀን ይለወጣል!
በጨለማው ጊዜ ጥርስህን ንከስና ጉዞህን ቀጥል ወደ ስኬትህ መጨረሻ የሚያደርስህን ትግል በፍጹም አታቁም። አዎ ፈተናው ምን ያህል ቢበዛና ሊጥልህ ቢያንገዳግድህም አንተ ግን በፍጹም አትውደቅ። ብትወድቅም እንኳ እየተንፏቀቅ መሄድህን ቀጥል። ያኔ ብርሀን ከፊትህ ይመጣል!
ይፈትናል እንጂ ድሉ ያንተ ነው!
አስተውል! አበቃ የሚባል ነገር የለም ሕይወት ይቀጥላል...
3 738
የቻናል ግብዣ ነው ከስር የምትመለከቱት ሊንክ በመጫን ይግቡና JOIN ያድርጉ ፣ ጠቃሚ መልዕክቶች አስተማሪ ፅሁፎች about COVID19 የሚያገኙበት ቻናል ነው ።
@zegabiephrem
3 738
"እነሱ፤ እነሱ የምትሉት እነማን ናቸው? እኛስ እነማን ነን? እነሱ እነሱ ከማለት ራሳችንን ዞር ብለን እንመልከት። ወደኛ ዞር ብንል የምናየው ምንድን ነው? ወኔ ቢስ፤ የምቾት አታሞዎች ሆነን እንገኛለን። ከካስቴሊ ወይም ከኢትዮጵያ ሆቴል ስንወጣ ፤ ለማኞች ላይ እያገሳን የምናልፈው እኛው ነን። ወገኖቻችን መሬት ቆፍረው፤ ከመሬት ላይ ያገኙትን በልተው፤ እጦት ካፍንጫቸው ስር ላንድ ቀን ሳትርቅ እዚያው መሬት ላይ ሞተው እንደሚቀበሩ እያወቅን፤ በስምንትና በዘጠኝ መቶ ብር (በአሁኑ 8 እና 9 ሺ ማለት ነው) ላይ ደመወዝ ይጨመርልን በማለት ጧት ማታ ማመልከቻ የምናንጋጋው እኛው ነን…
"ለሀገር ልማት ይህን ያህል ከደሞዛችሁ ስጡ ብንባል መጀመሪያ የምናለቅሰው እኛው ነን። መንግስት ጀርባ ላይ እንደቱሀን ተጣብቀን የምንኖረው እኛው ነን። ከሞግዚት ጉያ ወጥተን፤ በሁለት እግራችን መቆም ያስፈራናል። በራሳችን ላይ እምነት የለንም። ማንነታችንን አናውቅም…
"እንደኛ ያሉት ሰዎች በየትኛውም መንግስት ስር ያው ናቸው፤ ከማማረር አያልፉም። ታዲያ ይህ ሁሉ የጓዳ ወሬ፣ ይህ ሁሉ አሉባልታ፣ ይህ ሁሉ የትችት መአት የራሳችንን ጉድለት ለመደበቅ፤ ወኔ ቢስነታችንን ለመሸፈንና ያደፈውን ህሊናችንን ለመደለል ነው እንጂ ለሌላ አይደለም። ግን እስከመቼ ድረስ? እስከመቼ ድረስ?"
፧
፧
📚📚📚
ምንጭ:- 👉"ከአድማስ ባሻገር" ከበዓሉ ግርማ
ገጽ 71-72
ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል
✍ ንባብ ለሕይወት
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
ተሸካሚ በሌለበት ሸክም የለም...!!
፨፨፨
<< አንድ ነገር የሚታየው በሌላ አካል ለመታየት ስለሚችል ሳይሆን ነገር ግን ሌላ አካል ስላየው ነገሩ ሊታይ ቻለ፤ ወይም አንድ ነገር ተመሪ የሚሆነው መሪ ስላለው እንጂ ነገሩ ተመሪ ስለሆነ አይደለም። አንድ ነገር ሸክም የሆነው ተሸካሚ ስላለው እንጂ ነገሩ በራሱ ሸክም ሆኖ አይደለም። ይኽ ማለት አንድ ውጤት በራሱ ልቆ የወጣበት አካል ውጤቱ የራሱ ሳይሆን ምክንያት ስላለው ነው። ውጤት የሆነ ነገር በራሱ ውጤት አያመጣምና። ቅድስናም እንዲሁ ቅዱስ የሚሆነው አማልክት ስለሚወዱት እንጂ በራሱ ቅዱስ ስለሆነ አይደለም። >>
/ ሶቅራጥስ /
