en
Feedback
አብርሆት

አብርሆት

Open in Telegram

ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23

Show more
3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🌼2013ን🌼 #ምክንያታዊ ወይስ #ስሜታዊ ! ስሜታዊማለት ለአንድ ገጠመኝ ወይም ክስተት የሚሰጥ ድንገተኛ ምላሽ ነው፡፡ የዚህ አይነቱ ምላሽ ውጤት ምን እንደሆነ አይታወቅም፡፡ በተቃራኒው ምክንያታዊነት ማለት ለአንድ ገጠመኝ ወይም ክስተት በቂ ጊዜ ወስዶ፣ ውጤቱን አውጥቶና አውርዶ ውጤቱን ከጅማሬ አይቶ ምላሽ መስጠት ማለት ነው፡፡ አንድን ነገር ለማድረግ ስታስብ መነሻህ ስሜታዊነት ይሁን ወይስ አእምሮህ ያሰበበትና አጥጋቢ ምክንያት ያለው ተግባር ለይተህ የማወቅን ልምምድ አዳብር፡፡ ይህንን መለማመድ ዘወትር በስሜት እየተነዳህ ውሳኔና እርምጃ ውስጥ ከመግባትና ውጤቱ አፍራሽ ከሆነ ሁኔታ ይጠብቅሃል፡፡ ለምሳሌ፣ ከዚህ በፊት ለነበረህ ገጠመኝ የሰጠኸውን ምላሽ አስብና ያንን ምላሽ የሰጠህበትን መነሻ አሳብ አጢነው፡፡ “ያነሳሳኝ ስሜት ነው ወይስ አእምሮዬን ተጠቅሜ በቂ ምክንያት አግኝቼ ነው?” የሚል የማስታወሻ ጽሑፎችን በመጻፍ ልዩነቱን ማየት ትችላለህ፡፡ እንዲህ አይነት ልምምዶችን በመደጋገም በማድረግ ስሜታዊ ልማዶችህን ቀስ በቀስ ልትቀርፋቸው ትችላለህ፡፡ አንዲት ደቂቃ በመታገስ የእለቱን የጋለ ስሜት ማሳለፍ ሲችሉ የመጣላቸውን የስሜት ንዝረት በማስተናገድ የሌላውንና የራሳቸውን ታሪክ ያበላሹ ሰዎች ቁጥር እጅግ ብዙ ነው፡፡ በየእለት የሰው ለሰው ግንኙነት መካከል በሚነሱ ነገሮች ሁሉ የሚፈነዱና ቁጣ ቁጣ የሚላቸው ሰዎች፣ በትዳርና በቤተሰብ ሕይወት ውስጥ በስሜት በተናገሩት ንግግር ከተቆሳሰሉ በኋላ ለመወያየት የሚሞክሩ ሰዎች፣ በማሕበራዊውና በሃገር ደረጃ አንድን ነገር ገና ከመስማታቸው ስለሁኔታው በሚገባ ሳያጠኑና የምክንያታዊነት ሂደት ሳይከተሉ ለጥፋት የሚነሳሱ ሰዎች ምክንያታዊ ሳይሆኑ ስሜታዊ ሰዎች ናቸው፡፡ ምክንያታዊነት የበሳሎች መንገድ ነው፡፡ ምክንያታዊነት የአዋቂዎች ምርጫ ነው፡፡ ምክንያታዊነት ሚዛናዊ በራስ የመተማመን ደረጃ የደረሱና ከፍ ያሉ ሰዎች ምርጫ ነው፡፡ ስሜታዊነት ጠባብነት ነው፡፡ ስሜታዊነት አርቆ ማሰብ ያለመቻል ምልክት ነው፡፡ ስሜታዊነት የተስፋ መቁረጥ ምልክት ነው፡፡ ስሜታዊነት የመሸነፍና አቅም የማጣት ምልክት ነው፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ከስሜታዊነት ወደ ምክንያታዊነት የመሸጋገርን ጉዞ እንድትጀምርና የግልህን፣ የቤተሰብህንና የሕብረተሰቡን ሕይወት ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ የምትሰራ ብልህ ሰው እንድትሆን ላበረታታህ፡፡ @abrhott @abrhott @abrhott

"አራት ዓይኖች አሉህ ፤ እነርሱም........ ግራ ዓይንህ ፣ ቀኝ ዓይንህ ፣ አዕምሮህና ልብህ ናቸው፡፡ አምስት እንዲሆኑልህ በህሊናህ ሥራበት፡፡ #ማኅትማ_ጋንዲ @abrhott

ከአህያና ከበቅሎ ፍጥነት ሳንወጣ ስንት ዘመናት አስቆጠርን ? @abrhott

If she gives you her phone No and ignores your call.... put her number on the streets and write “ የተበላሸ ፍሪጅ,ምጣድ ,ቲቪ እና ዲሽ እንሰራለን”😎

#ብር_የመለወጡ_ቀጥተኛ_ጥቅም ❗️ የአጭር ግዜ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች፡- በሀገራችን ከ113ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ከፋይናንስ ገበያው ቁጥጥር ውጪ አለ! ስለዚህ የገንዘብ ለውጡ ይህንን ገንዘብ ወደ ብሄራዊ ባንክ የመለወጥ እድል ይፈጥራል! #ለምሳሌ፡- ምንጩ ያልታወቀ በመሆኑ ወደ ባንክ ሳይመጣ ከሚበላሸው፤ ከሀገር ውጪ በጎረቤት ሀገር በመሸሹ ከማይመለሰው፤ የመቀየሪያ ወቅቱ ከሚያልፍበት፤ በጎርፍ፤ በቃጠሎ፤ ወዘተ ከወደመው ውጪ 100 ቢሊዮን ብር እንኳን ወደ ህጋዊ የባንክ ስርዓት ቢመጣ ከፍተኛ ገንዘብ ከገበያ የመሰብሰብ እድል ስለሚፈጠር የዋጋ ንረት በሚታይ መልኩ የመቀነስ አቅም ይኖረዋል! ምንጩ ያልታወቀ፤ በሙስና የተገኘ፤ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ ከፍተኛ ገንዘብ በገበያ በድርጅቶች እና በሰዎች እጅ እንደሚገኝ ይታወቃል! ስለዚህ የተቀመጠውን የጥሬ ገንዘብ ገደብ (1.5 ሚሊዮን ብር ለማለት ነው!) እና ከ5 ሺህ ብር በላይ በባለቤቶች እንዲቀመጥ የሚያዘውን መመሪያ ተከትሎ ህገወጦችን ለመለየት እድል ይፈጥራል፡፡ #ለምሳሌ፡- በህገወጥ መንገድ ሃብት ያከማቸ ሰው ወይም ድርጅት ህጋዊ ከሆኑት ሰዎች ተገቢ ያልሆነ Advantage እንደወሰደ ግልጽ ነው! ስለዚህ የብሩ መቀየር የተለየ እድል ያገኙ ሰዎችን በተወሰነ መልኩ ለመቆጣጠር ያሰችላል፡፡ የረጅም ግዜ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች፡- ኢትዮጲያ ውስጥ በባንክ ቤቶች ያለው የቁጠባ መጠን ማነስ እና ባንኮች ለባለሃብቶች የሚያቀርቡት የብድር መጠን ማነስ የታወቀ ጉዳይ ነው! ስለዚህ ለምሳሌ 100 ቢሊዮኑ ቢሰበሰብ እና የጥሬ ገንዘብ ዝውውር ገደቡን ተከትሎ 80 ቢሊዮኑ በባንኮች ቢቀመጥ ተጨማሪ ቁጠባ እና ተጨማሪ የብድር አቅርቦት እንዲገኝ ያደርጋል፡፡ #ለምሳሌ፡- መንግስት ባወጣዊ አዲስ መመሪያ መሰረት የግል ባንኮች የመንግስትን የግምጃ ቤት ሰነድ የመግዛት እድል ተፈጥሮላቸዋል! ስለዚህ መንግስት ወደ ፊት ለሚያስበው የበጀት ጉድለትን በሀገር ውስጥ የመሙላት ፍላጎት ተጨማሪ የገንዘብ ምንጭ ሆኖ ሊያገለግለው ይችላል፡፡ ገንዘቦች በመሰብሰባቸው እና በግል ባንኮች ውስጥ በመቀመጣቸው የሚቀርበው ብድር የግል ሴክተሩን በማነቃቃት ተጨማሪ ምርት እንዲመረት፤ ተጨማሪ ሰራተኛ እንዲቀጠር፤ ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶች አድገው የውጪ ምንዛሬ ግኝት እንዲያድግ፤ የሀገር ውስጥ አምራቾች ተበረታተው ከውጪ የሚገቡትን የመተካት አቅም የሚፈጥሩ ከሆነ የውጪ ምንዛሬ እንዲቆጠብ፤ ወዘተ የማድረግ አቅም ይኖረዋል፡፡ ነገር ግን ብር መለወጡ ብቻውን ስር ነቀል ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ያመጣል ማለት አይደለም! ምክንያቱም ዋጋ ንረት፤ ስራ አጥነት፤ የውጪ ምንዛሬ ክምችት ማነስ፤ የበጀት ጉድለት፤ ዝቅተኛ ምርት እና ምርታማነት መኖር፤ የንግድ ሚዛን መዛባት፤ ወዘተ በገንዘብ ምክንያት ብቻ የመጡም አይደሉም በገንዘብ ምክንያት ብቻም የሚፈቱ አይደሉም! ሌሎች ፖሊሲዎች እና ስራዎች በተጨማሪነት መሰራታቸው ግድ ነው። ©The Ethiopian Economist View

የእውነት ጠቢብ ወደ ራሱ ጥበብ ቤት እንድትዘልቁ አይጠራችሁም ። ወደ ገዛ አዕምሮ አችሁ ደጃፍ ይመራችኋል እንጂ። በመቀጠልም አንድ መምህር ተናገረ ፦<<ስለማስተማር ንገረን? አለውም እሱም አለ፦ ማንም ሰው ቢሆን ገና ድሮ በእወቀታችሁ መክፈቻ ንጋት ላይ፥በከፊል እያንቀላፋ ተጋድሞ ካለው በስተቀር፥ ሌላ ምንምነገር ሊገልጥላችሁ አይቻለውም......<< በቤተመቅደሱ ጥላ ስር ከተከታዮቹ ጋር የሚንሸራሸረው መምህርም ከእምነቱ፣ ጋር ከፍቅር ውጪ ጥበቡን ሊሰጣቹ አይችልም። በእውነት ጠቢብ ከሆነም፤ ወደ ራሱ ጥበብ ቤት እንድትዘልቁ አይጠራችሁም። ወደ ገዛ አእምሯችሁ ደጃፍ ይመራችሁዋል እኝጂ.... << የከዋክብት ተመራማሪውም ያለውን ግንዛቤ ይነግራችሁ ይሆናል። ግን ግንዛቤውን ሊሰጣቹሁ አይችልም....<< ዘማሪውም በህዋ ላይ ያሉትን ዜማዎች ሁሉ ይዘምርላችሁ ይሆናል ። ዜማውን የሚያዳምጥ ጆሮንም፤ ሆነ የተደመጠውን የሚያስተጋባ ድምፅ ሊሰጣችሁ ግን አይቻለውም ። <<በሂሳብ ሳይንስ የተካነውም ሰው ቢሆን ስለክብደትና የልኬት ወሰኖች ሊነግራችሁ፥ ይችላል እንጂ ወደ እነዚያ ወሰኖች ሊያስኬዳችሁ አይችልም። የአንድ ሰው ዓይንስ ብርሃኖቹን ለሌላ ሰው ያውሳልን?..... << እናም በእግዚአብሔር እውቀት ውስጥ እያንዳንችሁ ለየብቻ እንደምትቆሙት ሁሉ፤ ስለ እግዚአብሔር ባላችሁ እውቀትና ስለዓለም ባላችሁ ግንዛቤም ለየብቻቹሁ መቆም ይገባችኋል ። ፧ ፧ 📚📚📚 ምንጭ፦👉 የጥበብ መንገድ ደራሲ ካህሊል ጅብራን ገፅ 78_79

ትንሽ ስለማለት... የአብይ አሕመድ አስተዳደር ትልቁ ሐጥያት ጅምላ ግድያን ለመላው ኢትዮጵያውያን ማለማመዱ ነው። ገና ከጅምሩ አስተማሪ እርምጃ እንደመውሰድ "በለውጥ ወቅት የሚያጋጥመን እንቅፋት ነው፤ ችግሮች አያስቆሙንም እንሻገራቸዋለን" እየተባሉ ታለፉ። የሕዝብ ፍጅት "እንቅፋት" የሰዎች በማንነታቸው መጨፍጨፍ "ግጭት" እያስባለ ሕዝቡን ከግድያ ጋር አለማምዶታል። ከዚህ በኋላ ሐገር ተገልብጦ መላው ሕዝብ ቢጨራረስ እያንዳንዱ ዜጋ እራሱ ላይ እስኪደርስ ድረስ የሌላው ሰው ሕመም አይሰማውም። እንደ Pavlov ውሻ ሕዝቡ Mass conditioned ተደርጓል ጅምላ ግድያን ተለማምዶታል። ይሄኛው በጣም አስፈሪ ነው ለማሰብም ይዘገንናል።

Don't Give up on your Dreams, Keep Sleeping!

A strong friendship doesn’t need daily conversation. @abrhott

"ምሥጢሩን ማወቅ" ለንባብ በቃ። ሁሉም ነገር አዎንታዊና አሉታዊ ጎን አለው፤ በማንኛውም ክስተት ውስጥ ሁለቱንም ማግኘት ትችላለህ፡፡ ስኬታማ የሚሆነው አስቀድሞ አዎንታዊ ጎኑን መመልከት የሚችለው ነው
"ምሥጢሩን ማወቅ" ለንባብ በቃ። ሁሉም ነገር አዎንታዊና አሉታዊ ጎን አለው፤ በማንኛውም ክስተት ውስጥ ሁለቱንም ማግኘት ትችላለህ፡፡ ስኬታማ የሚሆነው አስቀድሞ አዎንታዊ ጎኑን መመልከት የሚችለው ነው፡፡ ፒተር በርዋሽ ቀናም ሆነ ክፉ አሳቢ ለመሆን ሙሉ ነፃነት አለህ፡፡ በውስጥህ ተደርቶ የኖረውን አሮጌ አመለካከት አውልቀህ በአዲስ ለመተካት እያንዳንዱ ቀን ያንተው ነው፡፡ ያን ያህል ቀላል ነገር ነው፡፡ ሁሉን ነገር በአሉታዊ ጎኑ የምትመለከት ከሆነ ሕልምህን ይገድለዋል፡፡ - አናስታዢያ ሶሬ ነገሮች ሲጨልሙብን እንደሰው የመናደድ የማማረር ዝንባሌ አለን፡፡ ንዴት፣ ማማረርና ማላከክ ዘመዳሞች ይመስሉኛል፡፡ ያደግኩት ከሰዎች ምንም ነገር መጠበቅ እንደሌለብኝ አምኜ ነው፡፡ ስላለህ ነገር ማመስገንን ልመድ፤ ምክንያቱም በሰከንዶች ውስጥ ሊጠፋ ይችላልና! ይህ አመለካከት ነው ሊኖርህ የሚገባው፡፡ - ሊዝ ሙሬይ ፍርሃትን ምንጊዜም ልታስወግደው አትችልም፡፡ ምክንያቱም ፍርሃት ተፈጥሮአዊ ነው፡፡ - ሊዝ ሙሬይ በሕይወትህ አደጋን መጋፈጥ የማትፈልግ ከሆነ ሲጀምር ጠንካራ እንደሆንክ ልታውቅ አትችልም፡፡ ሲቀጥል ደግሞ መቼም ላታድግ ትችላለህ፡፡ - አናስታዢያ ሶሬ ሁሉንም ደረጃዎች አስቀድመህ ለማየት የምትፈልግ ከሆነ ተሳስተሃል፡፡ ስህተት የም•ሰራው ሁሉንም ነገሮች መቆጣጠር እንደምንችል ማሰብ ስንጀምር ነው፡፡ - ሊዝ ሙሬይ ሕይወት ፈተና ነች፡፡ ሕይወት ቀላልና እንከን አልባ ከመሰለችህ ተሳስተሃል፤ አልያም ቅዥት ላይ ነህ፡፡ -ሊዝ ሙሬይ

የትግራይ ምርጫ ውጤት: ✅ህወሓት - 98.2 % ✅ባይቶና - 0.8% ✅ውናት - 0.71% ✅ሳወት - 0.27% ✅ዓሲምባ - 0.01% ከአጠቃላይ ድምፁ አግኝተዋል፡፡ የጨረቃም ይበሉት የጨረባ ምርጫውን
የትግራይ ምርጫ ውጤት: ✅ህወሓት - 98.2 % ✅ባይቶና - 0.8% ✅ውናት - 0.71% ✅ሳወት - 0.27% ✅ዓሲምባ - 0.01% ከአጠቃላይ ድምፁ አግኝተዋል፡፡ የጨረቃም ይበሉት የጨረባ ምርጫውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀውታል፡፡ ጠቅላዩን ጨምሮ ለብልጽግና ኢዜማ ያለን መልክት ቢኖር የቦፖለቲካችሁን እዛው ተብኳኩበት፡፡ የእድር የእቁብ ምርጫ ነው እያላችሁ የተከበረውን የዕድር እሴቶታችንን ተውሉን፡፡

🌼🌼🌼🌼🌼🌻🌻🌻🌻🌻 ዛሬ የ 2012 የመጨረሻ ቀን ነው 😜 እናንተስ ይህ ነገር ዛሬ የመጨረሻዬ መሆን አለበት የምትሉት ነገር የላችሁም ? ይህ ነገር እማ ወደ 2013 አብሮኝ መሻገር የለበትም ብላችሁ ያሰባችሁትስ ነገር የለም? ብዙ ዘመን አብሯችሁ ከእናንተ ጋር የቆየ በቃ ከዚህ በኋላማ ብላችሁ ነገር ግን አሁንም ድረስ ተጣብቆባችሁ ያለ ነገር የለም? አያችሁ ከዚህ በፊት የወሰናችሁ መስሏችሁ ነው እንጂ አልወሰናችሁም ውሳኔ ማለት ስሜት ና ፍላጎት ሳይሆን ቁርጠኝነት ና ተግባር ነው የሰው ልጅ ማለት እኮ ከሁሉም በላይ ነው ከእግዚአብሔር ብቻ በታች ስለዚህ ከምንም ነገር በላይ ከፍ ማለት እንችላለን ካልፈቀድንለት በቀር ምንም ነገር ሊያሸንፈን አይችልም ዛሬ በስሜት ሳይሆን በእርግጠኝነት ወስኑ አሮጌውን ና ያስቸገራችሁን ማንኛውንም ነገር ከላያችሁ ላይ እርግፍ አርጉት ጳውሎስ ሲናገር ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ እንዳለ እኛም በእኛ አቅም እና ኃይል ሳይሆን በክርስቶስ ኃይል ሁሉን እንችላለን ሁሉን እናሸንፋለን የእናንተን ኃይል አቁሙ እና የክርስቶስን ኃይል ወደ ውስጣችሁ ጋብዙት እሱ ሁሉን ያስችላችኋል አዲሱ ዓመት እማ የኛ ነው 🌻በአዲሱ ዓመት🌻 አዲስ ማንነት አዲስ ህይወት አዲስ ምዕራፍ አዲስ መንፈስ አዲስ ክብር ይሆንልናል ካመናችሁ ደሞ አሁን ሁኗል 🌞እንኳን ለአዲሱ ዓመት ና ለአዲሱ ሰው በሰላም አደረሳችሁ🌞 🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻😍😍😍😊

የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቀመር! መጋቢ ሃዲስ ስቡህ አዳምጤ ይባላሉ። በሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የአንድምታ ትርጓሜ መምህር ናቸው። እንደ እሳቸው ኢትዮጵያ ከብሉይ ዘመን በፊት
የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቀመር! መጋቢ ሃዲስ ስቡህ አዳምጤ ይባላሉ። በሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የአንድምታ ትርጓሜ መምህር ናቸው። እንደ እሳቸው ኢትዮጵያ ከብሉይ ዘመን በፊት አመታትን ትቆጥር ነበር። የዘመን አቆጣጠር (ባህረ ሃሳብ) ቁጥር ያለው ዘመን በሚል ትርጉም ይታወቃል ይላሉ። ‘ባህረ ሃሳብ’ እንደ ስያሜው ትንታኔው ጥልቅና ምስጢሩም የረቀቀ እንደሆነ በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ሊቃውንት ይናገራሉ በማለትም ያብራራሉ። በዚህ ውስጥ ደግሞ የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር ቀመር /ስሌት እንደሚገኝ አመልክተዋል። እንደ መጋቤ ሃዲስ የኢትዮጵያ የዘመን ቀመር ከጁሊያንም ሆነ ከጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በጣም የተለየ ነው። በዓመቱ ውስጥ ጊዜያቸውን ጠብቀው የሚከሰቱ ወራትም የየራሳቸውን የሁኔታ ትርጓሜ በመያዝም አገሪቱ ከሌሎች የተለየች ሆና እንድትታይ አድርገዋታል። Via ENA

ይህ ጽሁፍ በኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገመንግስት አንቀጽ 29 መሰረት ተጻፈ የአብሮነት ፓርክ ለማስመረቅ ወታደራዊ ሰልፍ አስፈላጊነቱ ላይ በኋላ የምንመልሰው ጉዳይ ይሁንንና ስለ ልዩ ሀይል ጥቂት እንበል፡፡ አሁን የምላችሁ ልዩ ሀይል እንደኛ አገሮቹ በየክልሎቹ ተኮልኩለው እና ከተማ ሲቃጠል ቁጭ ብለው የሚሞቁትን አልያም ቤንዚል የሚያቀብሉትን ሳይሆን በሳይንስ ደረጃ ያለውን ወይም የሌሎች ሐገራትን ተሞኩሮ ነው፡፡ ልዩ ሃይል በከተማ እና በመስክ ስኬታማ ግዳጅ እንዲፈጽም በልዩ ሁኔታ እጅግ ውድ ወጪ ወጥቶበት በውሃ ውስጥ፣አየር፣በከተማ፣በገጠር፣ በተለያዩ መልከ አምድሮች እና የአየር ጸባዮች ላይ ስልጠና የሚወስድ አካል ነው፡፡ ከትጥቅ ወጪ አንጻር አንድ ወታደር ቀረጥን ሳይጨምር የአንድ ፒክአፕ ሀይሉክስ ዋጋ ይዞ ይዞራል፡፡ ጥያቄ በምሰሉ ላይ የምናያቸው መታደሮች እና ትጥቅ መልክቱ ምንድነው ነው፡፡ በእርግጠኝነት ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር እነዚህ ወታደሮች ከትጥቃቸው አንጻር ዋና አላማቸው ለከተማ እንጂ ለመስክ ግዳጅ አልተዘጋጁም፡፡ አሁንም ሌላ ጥያቄ እንወርውር ኢሄ ልዩ ሀይል በቀጥታ በፌደራል መንግስት የሚታዘዙ ሆነው ሳለ እንዴት ሁለት ከተማዎች ሙሉ በሙሉ በአንድ ቀን ውስጥ ሊወድሙ ቻሉ? ከ300 መቶ በላይ ሰዎች በቆርቆሮ ታርደው እንዲሞቱ አስክሬናቸው እንዳይቀበር የሚያስገድድ ሀይል ተፈጠረ? ቤንሻንጉል ጉምዝስ በየቀኑ የሚረግፉት ዜጎች እንዴት መፍትሄ አጣ? ትግራይስ እያየናት በአንድ ቡድን ፍላጎት ወደ ዲፋክቶ ስቴትነት አመራች?ሌላም ጥያቄ እናንሳ ጠ/ሚሩ የመንግስቱ ሐይለማርያም እጣ ቢገጥማቸው እንደምንግስቱ ሐይለማርያም ህዝብ አላስጠርስም ብለው ሐገር ለቀው ይወጣሉ ወይስ አዲስ አበባን ከ አራት አቅጣጫ ዘግተው አንድ ጥይት እና አንድ ሰው እስኪቀር ብለው የከተማውን ሕዝብ ያስፈጃሉ? ትግራይን ያልታደገ፣ሻሸመኔን ያልታደገ፣ዝዋይን ያልታደገ፣ የቤኒሻንጉልን ሕዝብን እና ባለስልጣናትን ያልታደገ፣የአማራ ሕዝብን እና ባለስልጣናትን ያልታደገ ጦር ስራው ምንድነው፡፡ ይህ ጦር የኢትዮጵያዊያ ጦር ወይስ የጠቅላዩ እና ቡድናቸው የግል ጠባቂ? ሌላም ጥያቄ እንሰንዝር ይህ ጦር የአዲስ አበባን ሕዝብ ይክዳል ወይስ ይታመናል? አብረን እናየዋለን፡፡

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

የወራት ስያሜ/ስያሜ አውራኅ ከመስከረም እስከ ጳጉሜ የተሰየሙት ወሮቻችን ስያሜያቸውን ከየት እንዳገኙ ያውቃሉ? እስኪ የሚከተለውን ይመልከቱ፡፡ 1 የወሩ ስም - መስከረም የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መሴ እና ከረም ትርጉም - መሴ-አለፈ ፣ መሸ ፤ ከረም-ክረምት፤ ክረምት አለፈ ፣ ክረምቱ መሸ 2 የወሩ ስም - ጥቅምት የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ጠቀመ ትርጉም - ሠራ፤ ጠቃሚ ጊዜ 3 የወሩ ስም - ኅዳር የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ኀደረ ትርጉም - አደረ-ሰው በወርኃ አዝመራ ማሳ ውስጥ ለጥበቃ ማደሩን ይገልፃል 4 የወሩ ስም - ታኅሳስ የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ኀሠሠ ትርጉም - መረመረ- በመኸር ወቅት የሰብል ምርመራን ያመለክታል ፤ ሰብዐ ሰገል በታኅሳስ ወር የተወለደውን ጌታችንን ማሰሳቸውን ፣ መፈለጋቸውንም ያመለክታል 5 የወሩ ስም - ጥር የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ነጠረ ፣ አጥረየ ትርጉም - ነጠረ - ጠረረ- ብልጭ አለ፤ ነጻ፤ የፀሐይን ግለት ወቅት ያሳያል ፤ አጥረየ - ገዛ (ከብቱም ምርቱም የሚሸጥበት የሚገዛበት ወቅት) 6 የወሩ ስም - የካቲት የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ከተተ ፣ ከቲት ትርጉም - መክተቻ (እኅልን ወደ ጎተራ) 7 የወሩ ስም - መጋቢት የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መገበ ትርጉም - በቁሙ የሚመግብ (በጎተራ የተከተተው የሚበላበት) 8 የወሩ ስም - ሚያዝያ የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መሐዘ ትርጉም - ጎለመሰ ጎበዘ ሚስት ፈለገ (ወርኀ ሰርግ መሆኑን ሲያጠይቅ) 9 የወሩ ስም - ግንቦት የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ገነበ ትርጉም - ገነባ፤ ሠራ፤ ቆፈረ፤ ሰረሰረ (ለእርሻ የመሬቱን መዘጋጀት ያሳያል) 10 የወሩ ስም - ሰኔ የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ሰነየ ትርጉም - አማረ (አዝርዕቱ) 11 የወሩ ስም - ሐምሌ የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ሐመለ ትርጉም - ለመለመ ፣ ሐመልማል ሆነ ፣ ለቀመ (ለጎመን) 12 የወሩ ስም - ነሐሴ የግእዝ ሥርወ ቃሉ - አናሕስየ ትርጉም - አቀለለ፤ ተወ (የክረምቱን እያደር መቅለል ያሳያል) 13 የወሩ ስም - ጳጉሜ ሥርወ ቃሉ - ኤጳጉሚኖስ (ግሪክ) ትርጉም - ተጨማሪ ማለት ነው (1.ኅብረ አትዮጵያ፤ ከቴዎድሮስ በየነ፤ አዲስ አበባ፤ 1999ዓ.ም.፤ ገጽ 16-17 2. ከሊቃውንት አስተምህሮ) #ምንጭ ግዕዝ ሚዲያ