አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
ጠቅላዩ እንዳሉት:- የዋጋ ግሽበትን በሚመለከት መንግስት እየወሰደው ባለው የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሸያ ቅናሽ በማሳየት ላይ መሆኑ ተመልክቷል። ከዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር የሳበኝ ይሄ ነው፡፡ እንዴት ነው ነገሩ ጎበዝ እኛና ጠቅላዩ ሁለት ሀገር ነው እንዴ የምንኖረው????
3 738
If she comes to a date with a friend, focus more on her friend she will never do that again 😂😂
3 738
በዓለም ላይ የሚከብዱ 3 ነገሮች
1፦ፀጉር መቁጠር አትችልም
2፦አይንህን በሳሙና መንካት አትችልም
3፦ምላስህን አውጥተህ መተንፈስ አትችልም
ኧረ አትጃጃል ምላስህን አስገባ😜😜
አሁን ፈገግ አልክ😃 ምክንያቱም ጅል ነህ 😂😁😂
መልካም ቀን!!
3 738
በአማራ ክልል ከ47ሺ በላይ አርሶ አደሮች ሰብላቸው በአንበጣ መንጋ መውደሙን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋሁን መንግስቴ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ከመስከረም ወር መጀመሪያ ሳምንት አንስቶ በሰሜንና በደቡብ ወሎ፣ በኦሮሞ ብሄረሰብና በሰሜን ሸዋ ዞኖች የተከሰተው የአንበጣ መንጋ ከ87ሺ 500 ሄክታር መሬት ላይ ባደረሰው ጉዳት ከ47ሺ በላይ አርሶ አደሮች ሰብላቸው በአንበጣ መንጋ ወድሟል።
በክልሉ የአንበጣ መንጋ ይከሰትባቸዋል ተብሎ ስጋት ከነበረባቸው አምስት ዞኖች ውስጥ በአራቱ መከሰቱን ምክትል ኃላፊው ጠቅሰው፤ የአንበጣ መንጋ በተከሰተባቸው በሰሜንና በደቡብ ወሎ፣ በኦሮሞ ብሔረሰብና በሰሜን ሸዋ ዞኖች 18 ወረዳዎችና 125 ቀበሌዎች ያሉ ሲሆን፤ ቅኝት ወይም አሰሳ ከተደረገበት ከ442ሺ 404 ሄክታር መሬት ውስጥ በ 218ሺ 406 ሄክታር መሬት ላይ የአንበጣ መንጋ መከሰቱን ተናግረዋል።
አቶ ተስፋሁን የአንበጣ መንጋ ከተከሰተበት 218ሺ 406 ሄክታር መሬት ውስጥ በ117ሺ 332 ሄክታሩ ላይ የመከላከል ስራ መሰራቱን ጠቁመው፤ 38ሺ 150 ሄክታሩ ላይ በአውሮፕላን የኬሚካል ርጭት የተካሄደ ሲሆን፤
225ሺ 415 አርሶ አደሮች፣ 3ሺ 278 ባለሙያዎችና 927 አመራሮች የመከላከል ስራው ላይ መሳተፋቸውን አስረድተዋል።
አቶ ተስፋሁን የአንበጣ መንጋው ወደ ሌሎች ዞኖችና ክልሎች እንዳይዛመት ህብረተሰቡን በማስተባበር በባህላዊ ዘዴ የመከላከል ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ፤ አንበጣው ከቦታ ቦታ በመብረር ላይ ያለ በመሆኑ የመከላከል ስራውን ውጤታማ የሚያደርገው በአውሮፕላን የኬሚካል ርጭት መሆኑን ጠቅሰው፤ በርጭት ሂደቱ አንዷ አውሮፕላን በመከስከሷና ሌላኛዋ ደግሞ ብልሽት ስለገጠማት አሁን ላይ በአንድ አውሮፕላን ብቻ የኬሚካል ርጭት ስራው እየተሰራ በመሆኑ መንጋውን በፍጥነት መቆጣጠር አለመቻሉን ተናግረዋል።
አቶ ተስፋሁን መንግስት ተጨማሪ አውሮፕላኖች ሰሞኑን ከውጭ ለማስገባት ስለተስማማ አውሮፕላኖቹ ሲገቡ የመከላከል ስራውን የተቀላጠፈ ስለሚያደርገው በአጭር ጊዜ የአንበጣ መንጋውን ለመቆጣጠር እንደሚቻል ፤ የአንበጣ መንጋው ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይዛመት ችግሩ ያልተከሰተበት አካባቢ ነዋሪዎች እነርሱ ዘንድ እስኪደርስና የጉዳቱ ሰለባ እስኪሆኑ እጃቸውን አጣጥፈው ሳይጠብቁ ተቀናጅተው የመከላከል ስራውን በመስራት ስርጭቱን መግታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
[አዲስ ዘመን ጥቅምት 4/2013]
3 738
ከ አብርሆት ቤተሰባችን የተላከ !!
//ስወድሽ ነው እንጂ//
እኔ አንቺን ባፈቅርሽ ምንድነዉ ጥፋቱ?
መዉደዴን ስነግርሽ ለምን ተባልኩ ከንቱ::
ባታውቂዉ ነዉ እንጂ ..
የኩራትሽ ምንጩን፡ የከፍታሽ ፍንጩን ፣
እኔ እንዲህ ስወድሽ ፡ አንቺ ምታለግጪዉ፡፡
ባይገባሽ ነው እንጂ...
ያንቺን ኩራት ሚስጥር፡ የከፍታሽ ስሩ፣
እኔ ስወድሽ ነው...
እኔ ሳፈቅርሽ ነው...
በፍቅርሽ ስርድ ነዉ ፡ንግስናሽ ምስጢሩ፡፡
በህዝብ ብዛት እንደሆነ የንጉስ ወንበሩ፣
አንቺም እንደዛዉ ነሽ ፡ እኔዉ ነኝ ዙፋኑ፡፡
ባትረጂው እንጂ...
የቆረጥኩት ለታ፡ የጠላዉሽ ዕለት ፣
በዛን ቀን ይሆናል : ያንቺ ምንምነት፡፡
ተፃፈ እሁድ
ሰኔ 2012
ደሲ Op
3 738
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ከሃገራችን ታላቅ ሰዎች የተወሰዱ አባናሎች
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
• “ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያጣላን ታሪክ ሳይሆን ተረክ ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህን ተረኮች ማጽዳት ያስፈልጋል፡፡ አንድ ግለሰብ በምግብ ቢመረዝ ቢበዛ እራሱን ነው የሚገለው፤ ሃሳቡ ቢመረዝ ግን እራሱን ብቻ ሳይሆን አካባቢን ያጠፋል፡፡”
~ ጠ/ሚር ዶ/ር አብይ አህመድ
• “ጽዳት ከውጭ አይመጣም፤ጽዳት የሚመጣው ከውስጥ ነው፡፡ የውስጥ ማንነት ከጸዳ ውጪ የምናየው ነገርም ንጹህ ይሆናል፡፡”
~ ቤተልሄም ለገሰ/የፍልስፍና ባለሙያ
• “ልቦና የሚቆሽሸው እውቀት ላይ ያልተመሰረተ ተግባር ሲኖር ነው፡፡ የግለሰብ ልቦና የማህበረሰብ ልቦናን ይገነባል፡፡ የማህበረሰብ ልቦና ደግሞ በዕድር፤በእቁብ በመሳሰሉት ይገነባል፡፡”
~ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ/ገጣሚ እና ደራሲ
• “አዕምሮ ሶስት ትልልቅ ነገሮች አሉት፡- እሳቤ፤ትውስታ እና እይታ፡፡ የእነዚህ ነገሮች መመረዝ አዕምሮን ለተለያዩ የጤና ችግሮች ተጋላጭ ያደርጋል፡፡”
~ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ/የስነልቦና ባለሙያ እና መምህር
• “ሞራልን ወደ ቁስ ለማውረድ ሃሳብ ያስፈልጋል፤ቁሱ አለም በሃሳብ አለም ይገዛል፡፡ የሃሳቡ አለም በሞራል አለም ይገዛል፡፡ሃሳብ በሞራል ካልተገዛ አደገኛ እና አጥፊ ሊሆን ይችላል፡፡ ቁስም በሃሳብ ካልተገዛ ትክክል አይሆንም፡፡”
~ ዶ/ር ምህረት ደበበ/የአዕምሮ ሃኪም
@abrhott
3 738
What we human beings should be learnin from dogs: loyalty
What we actually learnt: position😂🤦🏾♂
3 738
መጥፎ ብሔር ወይም ጥሩ ብሔር የሚባል ነገር የለም። መጥፎ ባህሪና አተሳሰብ ያላቸው ሰዎች ግን በየቦታው አሉ። እንኳንስ አንድ ብሔር መንታ እህትና ወንድማማቾች እንኳን አንድ አይነት ፀባይ የላቸውም።
# ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ
3 738
#አብርሆት
ነፃ አውጪ
ቁስል ላያደርቁ ወድቀን ለደማብን
ሰልፍ ያዙ ይባላል መርጠው ሊሻሙብን
ግባ ከዚህ በሚል ጎሬ ይቆፈራል
ነፃ ላወጣህ ነው ተብሎ ይፎከራል
ማነው ነፃ አውጪ?
.
• ቄሱም ነፃ አውጪ!
• ሼኩም ነፃ አውጪ!
• ፓስተር ነፃ አውጪ!
• አዝማሪ ነፃ አውጪ!
• ተማሪው ነፃ አውጪ!
• መምህር ነፃ አውጪ!
• ጎሰኛው ነፃ አውጪ!
• ሹመኛው ነፃ አውጪ!
.
ሁሉም ነፃ አውጪ በሆነበት አገር
ነፃ አውጡን ብለን ለማን እንናገር !!!
✍@JamesB23
3 738
"...ምግብ ቀረበ ተብሎ ያለ አሳብ አይበላም፣ አልጋ ተመቸ ተብሎ ያለ አሳብ አይተኛም፡፡ ጨዋታ ደራ ተብሎ ያለ ልክ አይወራም፤ ገንዘብ አለ ተብሎ ያለ መጠን አይወጣም፤ እግር አለ ተብሎ ያለ ምዕራፍ አይኬድም፡፡ ይህ ኅሊናን ማቦዘን ነው፡፡
🕸🕸🕸🕸
ዝግ ኅሊና እንጂ ዝግ መንገድ የለም፡፡ መንገድ የሚከፈተው ኅሊናህ ውስጥ ነው፡፡ አስቀድመው በኅሊና መንገድ ወደ ጨረቃ የሄዱ ሰዎች በኋላ በመንኮራኩር መንገድ ለመሄድ አልቸገራቸውም፡፡ የኅሊናቸው መንገድ ዝግ የሆነባቸው ግን ይኼው አሁንም «ጨረቃ ድንቡል ቦቃ ዐጤ ቤት ገባች ዐውቃ» እያሉ በመዝፈን ላይ ናቸው፡፡...
@abrhott
