አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
“የፖለቲካ ትልቁ ጥቅም ሽፋን መስጠቱ ነው”
በ አዳም ረታ
ታውቃላችሁ ፖለቲከኞቻችን ትልልቅ ነገር እየተናገሩ ይማርኩናል። ጋዜጣ፣ ሬዲዮና ቲቪ አስደግፈው ያማልሉናል።
አንድ ዛፍ ይተክሉና ስለዚህ ስለተከሉት ዛፍ አስር ሰአት ያወራሉ። ይሄን የሚሰሙ የዋሃን እና ቂሎች፣ ዛፍ ብቻ ሳይሆን በቃ ደን ያደገ ይመስላቸዋል። ድርጊቱ ደቃቃ ቢሆንም ከጥዝጠዛው ብዛት የእውነት ትልቅ ይመስላቸዋል። በደኑ ማደግም በጣም ከማመናቸው የተነሳ እቆሙበት ወይ እተቀመጡበት ስለዚህ ስለተወራለት ደን ስለሆነው ዛፍ (እንዴት አንድ ዛፍ ደን ሊሆን እንደሚችል የሚመረምር ጥቂት ነው) በሰፊው ሊወያዩ ይችላሉ። የሚወያዩት እንዲህ ነው፡
ለመሆኑ እንዲህ የተጠቀጠቀውን ደን እንዴት ልናልፈው ነው? (አንዱ ኮስታራ)
ለመሆኑ እዛ ውስጥ ያለው አውሬ ቢበላንስ? (ቦቅቧቃው)
ከመሄዳችን በፊት እንዲከላከለን የታጠቀ ሰው ካለ አብሮን እንዲሄድ ለምን እንለምንም? (ሌላ ብልጥ ነኝ ባይ ቦቅቧቃ)
ለመሆኑ ልጆቻችን ምን ሆነው ይሆን? እዚህ ቀረን እኮ። መላ ምቱ እስኪ! (ወላድ ወይዘሮ)
እንዴት እየመነጠርን መንገዱን ልንዘልቀው ነው (ቀጫጫ)
መንገድ መጀመራችን አይቀርም ብዬ ጠርጥሬ ገጀራ ልይዝ ነበር (ልበ ቢስ)
ያዝ ብዬህ ነበር ለምን ረሳህ? (ʻብዬ ነበርʼ ባይ)
ኧረ አላልክም! (ልበ ቢስ እንደገና)
ውሸታም አደረከኝ? (ነገር ነገር ሲለው ብዬ ነበር ባይ)።
ድርጅቶች ብናደርጋቸውም ይሰራል፤
የኮስታሮች ነጻ አውጪ ድርጅት (ኮነአድ)፣
ቦቅቧቆች ነጻ አውጪ ግንባር (ቦነግ)፣
የብልጥ ነኝ ባይ ቦቅቧቃ ግንባር (ብባቦግ)፣
የወይዘሮዎች ነጻ አውጪ ግንባር (ወነግ)፣
የቀጫጮች ካውንስል (ቀካ)፣
የልበ ቢሶች ኮሚቴ (ልበኮ)፣
የብዬ ነበር ግሩፕ (ብነግ)፣ ወዘተ……
እኔንና እኔን መሳዮች የሚሳነን የለም።
ቂሎች በሌለ ጉዳይ እንዲህ ያለ ቃል እየተመላለሱ ይቆዩና፣ ቁርሾ ተቀስቅሶ በበነጋታው የሁለት ወይም የሶስት ሰዎች ሬሳ እዛ ዛፍ ተተከለበት የተባለው ገጣባ ቦታ ላይ ይቀበራል።
ከቀብር መልስ ስለደረሰው ችግር የሚያጠና የሚመራመር አይኖርም። ʻእዚህ ጋ ዛፍ ነበር አልተባለም እንዴ?ʼ ብሎ የሚናገር፤ ʻሰው ሞቶ እንዲህ ስለ ዛፍ ታወራለህ ምነው ጨዋ አልነበርክም?ʼ ይባላል። ሰፋ አድርጌ ልመራመር ሲል፣ የሚቀናʻበት መዘናጊያ ይሰጠዋል። ከሰላሳ አመት በኋላ ʻምን አገኘህ?ʼ ቢባል የዚህ አገር ዶክተር የሚመልሰው የለውም። እንዲህ ዘመዶችዋ የተጋደሉባት አንዷ ቆንጆ፡ የሞተው ወንድሜ የገደለው ባሌ አዘኔ ቅጥ አጣ ከቤቴም አልወጣ ብትል ወዳ አይደለም። ቅጥ ማጣታቸው ከተጀመረ ቢከርምም ይረሱታል። ቅጥ ማጣት እንደ ቂጥኝ እንደሚወረስም ይረሳሉ። ቅጥ ማጣት መቼ እንደ ጀመሩ አያጠኑም። ቅጠ-ቢስ ሁሉ።
[…] አሁን የማወራው ስለ ሽፋን ነው።
ዘመን የሚያልፍ ልቡን የማይሰጥ ሽፋን አለ። ለአንድ ሐበሻ ከነጻነት የበለጠ ማታለያ አለ? ምን ይፈልጋሉ ከዚህ የበለጠ ውብ ነገር? ግን ይሄ ነጻነት የተባለውን ረቂቅ ነገር እስከዛሬ ምን እንደሆነ በትክክል ኖሮ ያየው አለ? (የ3000 ዘመን ታሪክ የጭቆና ታሪክ ነው እንል የለ) ካየ ነጻነት ነበርና ነጻነት ያስፈልገኛል አይልም። ከነበረበት ለምን ወደመረገጥ መርጦ ይመጣል? ካልነበረበት ደሞ ምን እንደሆነ አያውቅምና እንዴት ሊመኘው ይችላል? ግን በዚህ ቃል በነዚህ አራት ሆሄያት ብዙ ብዙ ሕይወት ያልፋል።
ብዙ ብዙ ሰው ይጠፋል።
ብዙ ብዙ ትሸወዳላችሁ።
***
የስንብት ቀለማት
3 738
ጉርሻ
በ አዳም ረታ
‘ጉርሻ የሚያቀራርብ ነው። በጉርሻ አይኖቻችን የፈጠሩት ርቀት ይጠፋል። በኋላ እንዳየሁት መጎራረስ ወደ ወሲብ የሚጠጋ ኢትዮጵያዊ ድርጊት ነው።
በማዕድ ዙርያ እንዲቀመጥ የተገደደው ተከፋፍሎ ግለሰብ የሆነው ቡድንና ማሕበረሰብ በሚዘረጋው የበላተኛ እጅ ድልድይነት ይቀራረባል። ‘አብረን በልተን’ ሲባል ውስጡ ከባድ የጉርሻ ይዘት አለ። ጉርሻ አገናኝ አቀራራቢ ድርጊት ነው።
ሌላም ዝርዝር ረድፍ አለው።
በርበሬና ሚጥሚጣ በመብላት ሂደት ውስጥ ዜጋ ያልበዋል። በዚህም በእያንዳንዱ እንጀራ ሰበከት ላይ የአብሮ በላተኛችን የወዝ አሻራ ይታተማል። ይሄ አስገራሚ የሆነ ግላዊ ማህተም ያለው (እያንዳንዱ ሰው የራሱ ከማንም ግለሰብ የሚለየው የጣት አሻራ ስላለው) የተቀናበረ ድራማ በሚጠጋ ‘ማጉረስ’ ተብሎ በተሰየመ ድርጊት ማሕበራዊ ቅንጅት ይከናወናል። በጉርሻ ሂደት የግልና የማሕበራዊ አላማዎች ሳይጋጩ ይቀርባሉ።
ይሄ ሁሉ አማካይ ወደ ሆነው ብልት ወደ አፍ ያመጣል።
ጉርሻ በአፍ መግባት አለበት። የጉርሻ አጉራሽና ጎራሽ የሚረካከቡት ታላቁ ቀዳዳ አፍ ነው። ለሕይወት የሚያስፈልገው ምግብ የሚገባበት፣ ቋንቋ የሚሰራበትና ሰዎች በራሳቸውና በሌላው መሃል ያለውን ልዩነት የሚያጠቡት ወይንም የሚያሰፉት በአፍ ነው። (ሃሃሃሃ) አፍን ሴቶችና ወንዶች የሚጋሩት ቀዳዳ ነው። ይሄ ግንዛቤአችንን ጠንካራ ሁለንተናዊነት ይሰጠዋል። ጎራሽ አፉን ሲከፍት አጉራሽ ሕይወት እንደሚሰጠው አምኖ ነው።
እኔና አንተ፣ አንተና አንቺ….. ወዘተ በስምረት ውስጥ የሚጠፉበትና ‘እኛ’ የሚሆኑበት ነው። የቦታ ርቀት የሚወድምበት ነው።
አብረው ተቀምጠው ሲበሉ የማይጎራረሱ ሃበሾች ቁጥራቸው ከበዛ ኢትዮጵያ የምትባል እንደሌለች ወይ በመለወጥ ላይ እንዳለች ምልክት ነው።’
፠፠፠
እቴሜቴ ሎሚ ሽታ
3 738
በመጠንቀቅ ያተረፈ እንጂ የተጎዳ የለም!
(በዶክተር ኃይለልዑል መኮንን)
የዛሬ ሁለት እና ሶስት ሳምንት አካባቢ የፋሲካው ግርግር ምን ሊያስከትል እንደሚችል በተለያዩ ሚድያዎች ስንሰማ ቆይተናል።
ነገር ግን 'ጆሮ ዳባ ልበስ' ብለን ፤ ሰምተን እንዳልሰማን ሆነን "ኮሮና እኛን አይነካም" በሚል የባለሙያዎችን ትእዛዝ ሳንተገብር ቆየን።
ይባስ ብሎ ደግሞ ቁጥሩ በጣት የሚቆጠር ሲሆን "አይ ፈጣሪ ይጠብቀናል፤ ችግር የለም" እያልን ከኛ የሚጠበቀውን ጥንቃቄ ረስተን ብዙ ተዘናጋን።
የዛሬ ሶስት ሳምንት ገደማ 'ለመጠንቀቅ የሞት ዜና አንጠብቅ' ብዬ ከፋሲካ ዋዜማ በስትያ የታዘብኩትን እና ሊመጣ ስላለው ከባድ ጊዜ አያይዤ ፅፌ ነበር።
ይኸው ጊዜ ደጉ አሁን ላይ አየነው፤ አሁንም አረፈደብንም ለመጠንቀቅ ጊዜው አለን። እባካችሁ በቁጥር ከፍ እና ዝቅ ማለት ጥንቃቄያችን እና ስሜታች ከፍ ዝቅ አይበል።
ከፍ ሲል"በቃ አለቀልን!!" ዝቅ ሲል ደግሞ" የት አባቱ ኮሮናን ድባቅ መታነው" እያልን ቁጥር ላይ መሰረት አናድርግ።
አሁን ከምን ግዜውም በላይ የምንጠነቀቅበት ሰዓት ላይ ነን ፤ የትላንቱን ስህተት አንድገመዉ።
እባካችሁን እንጠንቀቅ!!
የዛሬዋ የሴኮንድ ስህተት ዘመን ተሻግሮ ጠባሳ እንዳያሳርፍብን እንጠንቀቅ፤ ይሄን ከባድ ጊዜ አሳልፈን ነገን በደስታ እንየው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
3 738
ሞት ግን ምንድነው? የማይለመድ የማይዳሰስ ፡፡ሞትን
ለማቆም ካልሆነም ለማዘግየት የማይደረግ ነገር የለም ፡፡
.
ሞት መለያየት መሆኑ ከባድ እንደሚያደርገው ግልጽ ነው፡፡
.
★በተጨማሪም የምንሞትበትን ቀንና ሰዓት አለማወቃችን ነው
ሞትን ምስጢር የሚያደርገው፡፡
ተሂዶ የሚመጣበትን የደርሶ መልስ ቲኬት ያለው ቢሆን
ምንአልባት ያንን ያህል ግራ አያጋባንም ነበር፡፡ ወይስ ለመሞት
ስላልተፈጠርን ይሆን ሞትን እንደሸሸን የምንሞተው? ከሞትም
በኃላ ሰው ህይወት ቢኖር ብሎ ይናፍቃል፡፡
.
☞ስቃይንም ይኖር ይሆን ብሎ ይሰጋል ይህም የጽድቅንና የኩነኔን
ጉዳይ በቀላሉ የማይተው ጉዳይ ያደርገዋል፡፡
ሰው በምድር የሚኖረው ህይወቱ ከሞት በኃላ ላለው ህይወት
ዋጋ እንዳለው ያስባል፡፡
.
.
ሞት የህይወት መቋረጥና አደጋ ብቻ ሳይሆን ራሱ
የሰው ጠላትና የሰው ሌባ ተደርጎም ይወሰዳል፡፡
.
☞ሞት ባይኖርስ ህይወት ምን ይሆን ነበር?
በተለይ ይህ ሁሉ ስቃይና በሽታ ባለበት ዓለምና ሰው እንዲህ
ራስ ወዳድና ክፉ በሆነበት ዓለም ውስጥ ሰው አለመሞቱ ከሞት
አይከፋም ብላችሁ ነው?
.
.
# ጦርነትስ ይኖር ይሆንሞት ባይኖር ?
☞ማንስ ያሸንፍ ነበር ታድያ?
.
ሞት ባይኖር ፍቅርስ ምን ይመስል ነበር ?
ግን ሞት ባይኖር በእርግጥ ኑሮ ምን ይመስል ነበር የሚለውን
ለማሰብም አዳጋች ነው አሁን ሞት አለና፡፡
.
# የተቆለፈበት ቁልፍ
ገፅ 414-415
ዶ/ር ምህረት
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
ዝክረ _ሚያዝያ ፳፯
የድል በዓል
*ከክተት አዋጅ በኋላ
(የኢትዮጵያ የጦር ዝግጅት ምን ይመስል ነበር?) *
ኢትዮጵያ ለጦርነቱ አልተዘጋጀችም። ለዚህም ደግሞ አራት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ በማለት በጥላሁን ጣሰው የተሰናዳው "የኢትዮጵያ እና የጣሊያን ሁለተኛው ጦርነት ታሪክ" መፅሐፍ ያስነብበናል።
፩ኛው) ከአንደኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በኢትዮጵያ ላይ የተጣለው የመሣሪያ ማዕቀብ እና ማሻሻያ።
• ይህ ማዕቀብ ኢትዮጵያ ዘመናዊ መሣሪያ እንዳይኖራትና በኋላ ቀር መሣሪያ እንድትዋጋ አድርጓታል። (ጃ ራሳቸው በፃፉት ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ ቅፅ ፩ በተሰኘ መፅሀፍ ላይ ዝርዝሩ አለ ይመልከቱ)
፪ኛው) በዓለም መንግሥታት ደንብ ማመን
• ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የአለም መንግሥታት ማህበር እንደሌሎች ሀገራት ዋስትና ይሰጠናል ብለው መታለላቸው ቅድመ ጦርነት ዝግጅት እንደታደርግ አድርጓታል።
፫ኛው) የፈረንሣይ ከኢጣሊያ ጋር በድብቅ ማበር
• የተጣለው ማእቀብ ማሻሻያ ተደርጎ የጦር መሳሪያ ከተፈፀመ በኋላ ፈረንሣይ ከኢጣሊያ በማበር ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ተደርጓል፤ ለዚህ ሰበቡ ፈረንሣይ የምድር ባቡርን አስተዳደር ለኢጣሊያ ማስተላለፍ ነበር። ሀገራችን ያኔ የባህር በር አልነበራትም።
፬ኛው) የራሽያ ድጋፍ በራሽያ ኮሚኒስት መሆን ምክንያት መዳከም
• አፍሪካን ከቅኝ ግዛት መቀራመት ጨርሶ ለመቋቋም በዳግማዊ ምኒልክ የተነደፉ እቅዶች መካከል የነበረው ሀገራትን በጦር መሳሪያ ማስታጠቅ በዋነኝነት ይደገፍ በራሽያ ነበር። በአንደኛው የአለም ጦርነት ወቅት ራሺያ የተዳከመችና በ917 ዓም ደግሞ ኮሚኒስት የሆነችበት ግዜ ስለነበረ ኢትዮጵያ የራሽያን ድጋፍ አጥታለች።
እንግዲህ ከዚህ የምንረዳው ሀገራችን በወቅቱ ለጦርነቱ ለ40 ዘመን ያህል ራሱን በጦር ሲያደራጅ ከነበረው ወራሪ እኩል በጦር ዝግጁ አለመሆኗል ነው። ታዲያ በዚህ ሁኔታ ኢትዮጵያ የተከተለችው የጦር ስትራቴጂ ምን ይመስላል? እንቀጥላለን።
#ክብር_ይህቺን_ውድ_ሃገር_በደማቸው_ላቆዩልን_ጀግኖች_አባቶቻችን
3 738
ዝክረ ሚያዝያ ፳፯
የድል በዓል
* አርበኛ ኪዳኔ ወልደመድኅን *
ኪዳኔ ወልደመድኅን ሐምሌ ፪ ቀን ፲፱፻፯ ዓ.ም ቡልጋ በከሰም ወረዳ፤ ከናታቸው ከወይዘሮ አስካለ ደጀን እና ከአባታቸው ከቀኛዝማች ወልደመድኅን አዩደረስ ተወልዱ።
አካለ መጠን ሲደርሱ በ፲፰ ዓመታቸው በ፲፱፻፳፭ ዓ.ም. አዲስ አበባ በክብር ዘበኛ ደንብ ተቀጥረው ወዲያው በንጉሠ ነገሥቱ ትዕዛዝ ከስድሳ ዘጠኝ አዲስ ወታደሮች ጋር ባሌ ተመድበው እስከ ፲፱፻፳፯ ዓ.ም ድረስ በተራ ወታደርነት ከዚያም በሃምሳ ዓለቃና በባሻነት ማእረግ ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ሊወር ሲመጣ በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም በምስራቅ ደቡብ በደጃዝማች በየነ መርዕድ እና በጄነራል አስፋው ወልደ ጊዮርጊስ መሪነት ጥቅምት ፲፩ ቀን፲፱፻፳፰ ዓ.ም ከጎባ ወደ ኦጋዴን ዘመቱ።
በዚህ ጦር ግንባር ፱ ወራት ለበሽሊንዲ፤ ዋቢ ሸበሌ፤ እና የመሳሰሉ ሥፍራዎች ጠላትን ሲከላከሉ ከርመው ወደ ጎባ ተመለሱ። ከሰኔ ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሚያዚያ ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም ከአሩሲ፤ ከሲዳሞ፤ ከሐረርና ኦጋዴን ወደ ጎባ በሃይል የመጣውን የጠላት ጦር በራሳቸው መሪነት ሲዋጉ ከርመው፤ መጨረሻ ላይ ተማም ከሚባለው ሥፍራ ላይ በተካሄደው ጦርነት ላይ ማምለጥ በማይቻልበት ኹኔታ በጠላት እጅ ወደቀው ተማረኩ። ጠላትም ለአምስት ወራት በጽኑ እሥራት ከያዛቸው በኋላ፤ በጥር ወር ፲፱፻፴ ዓ.ም ጣሊያን መሳሪያ አስታጥቆ በሽፍን መኪና ከጎባ ወሊሶ አምጥቶ እስር ላይ አዋላቸው። ባሻ ኪዳኔም እዚሁ እስር ቤት እያሉ አብረዋቸው ከታሰሩት መሀል በምስጢር ቃለ መሃላ በመስጠት መቶ ሰዎች አሳብረው እዚያ ያለውን የጠላት ጦር ፈጅተው ለመሸፈት ከወሰኑ በኋላ ወደ ባላምባራስ (በኋላ ደጃዝማች) ገረሱ ዱኪ የሚላክ ሰው በማፈላለግ ላይ እያሉ ጠላት ሰምቶ ኖሮ አጥብቆ ይከታታላቸው ጀመር። ይኼን ሲገነዘቡ ነገሩን አብርደው ሲጠባበቁ ወደ ባላምባራስ ገረሱ የላኩት ብሩ የሚባለው መልክተኛ ጥር ፲፭ ቀን ፲፱፻፴ ዓ.ም በጠላት እጅ ተይዞ ቀኑን ሙሉ ሲመረመር ዋለ። ባሻ ኪዳኔም በዚያው እለት ከምሽቱ ፪ ሰዐት ሲሆን በቃለ መሃላ ያደራጇቸውን ሰዎች በያሉበት እየሄዱ ከነመሳሪያቸው እየሰበሰቡ ሲያከማቹ የጠላትም ዘቦች ነቅተው በተንቀቅ ተሰልፈው ይጠብቋቸው ጀመር። ባሻ ኪዳኔ ግን ወገኖቻቸውን ሸልሉ ብለው ሲያሸልሉ የጠላት ዘቦች ተደናግጠው እንዲያውም 'እነሱ ሳይተኩሱ አትተኩሱ' የሚል ትእዛዝ አስተላልፈው ይጠባበቃሉ። ባሻ ኪዳኔም በዚህ ጊዜ ቃለ መሓላ ከሰጧቸው ፻ ሰዎች ውስጥ ፶፭ ወታደር ከነመሳሪያው፤ አራት ድግን መትረየስ፤ አስር ሣጥን ጥይት፤ ስድስት ሽጉጥ ከጠላት እጅ ነጥቀው እየተታኮሱ ሲወጡ የጠላት ኃይል ሃያ ወታደርና አንድ መትረየስ ከ ሁለት ሣጥን ጥይት ጋር ብቻ ገንጥሎ ሲያስቀርባቸው የተረፈውን መሳሪያና ወታደሮች ጋር ድል አድርገው ሸፈቱ። ወዲያውም ኩሳ ኪዳነምሕረት ከሚባል ሥፍራ ላይ ከባላምባራስ ገረሱ ጋር ተገናኙ።
ከገረሱ ጋር ባለመስማማታቸው፤ በኅዳር ወር ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. አባሎቻቸውን አስከትለው ወደ ትውልድ አገራቸው ወደ ቡልጋ ገቡ። እዚህም ከፊታውራሪ ኃይለማርያም ማናህሌ እና ከፊታውራሪ ተረፈ ማናህሌ ጋር ተቀላቅለው እስከመጋቢት ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. ድረስ በውሽንግር፤ ጨፌ ዶንሳ ምሽግ፤ ነጭ ድንጋይ ምሽግ፤ ልዝብ ድንጋይ ከተባሉ ቦታዎች ላይ ከጠላት ኃይል ጋር ሲዋጉ ከረሙ።
ከዚህ በኋላ ክረምቱን ቡልጋ ውስጥ በነጭ ድንጋይ፤ ፍልፍል አፈር፤ ጦስኝ ምሽግ፤ በመስኖ ከነደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ፤ ከነፊታውራሪ በለጠ ሳሴና ፊታውራሪ አጎናፍር ሌሎችም ስመጥሩ አርበኞች ጋር ሆነው ጠላትን ሲያጠቁና ሲከላከሉ ቆይተው በመስከረም ፲፱፻፴፪ ዓ.ም በሰገሌ በኩል ተጉዘው ገሊላ ከሚባል ሥፍራ ላይ ከራስ አበበ አረጋይ ጋር ሲቀላቀሉ ባሻ ኪዳኔ የግራዝማችነት ማዕረግ ተሾሙ። ከብዙ ከተለያዩ ውጊያዎችና ጀብዱዎች በኋላ በየካቲት ፲፱፻፴፫ ዓ.ም መሶቢት ከሚባለው ቦታ ላይ በመሪነት የጠላትን ጦር ድል አድርገው ወደዋናው ሰራዊት ከተቀላቀሉ በኋላ ራስ አበበ የቀኛዝማች ማዕረግ ሾሟቸው።
#ክብር_ይህቺን_ውድ_ሃገር_በደማቸው_ላቆዩልን_ጀግኖች_አአባቶቻችን
Source 👉#kinchebchabi
3 738
፸፱ኛው ዓመት የድል በዓል ተከብሯል። ዘንድሮ ምናልባትም ዓለማችን ላይ ከተከሠተው ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ እንደቀደሙት አመታት አራት ኪሎ የድል ሃውልት ጋር በመሠባሠብ አላከበርነውም ። ሆኖም ግን እዚህ መንደር የአስር ቀን የታሪክ ዝክራችንን ዛሬ እንጀምራለን።
ተከተሉን ... ታሪኩን ለሌሎችም ያጋሩ
ይቅረብ 👍
አይቅረብ 👎
3 738
#የጥርሴ_ወላፈን
ፈገግ በል ይሉኛል ...
ምንድን ነው ፈገግታ
ጥርሴ አይሸፍነው ...
የልቤን ወለምታ
በግድ ልሳቅ ብዬ ...
ከንፈሬን ብገልጠው
ልቤ የነደደበት ...
ጥርሴ እሳት ወጣው ...
#አልሞት_ባይ
የምተኛበትን ፍራሽ ቢወስዱትም
እንቅልፌን ነው እንጂ ህልሜን
አይሰርቁትም
.
ይኸው ዛሬም ድረስ...
.
ሊጥሉኝ ቢጥሩ መች እኔ እረታለሁ
አስረውኝም ቢሆን ህልሜን እፈታለሁ
________________
🌀--- የሴት ጓደኛህን የት እንድታግብዛት እንደምትፈልግ አትጠይቃት። በምትኩ፣ የት ሆቴል ልትጋብዛት እንደሆነ እንድትገምት ጠይቃት እና እሷ መጀመርያ ላይ ወደ ገመተችው ሆቴል ይዘሃት ሂድ።
🌀--- ችግር ገጥሞህ የሆነ ሰው ምን እንደሆንን ሲጠይቀን "ያገባሃል?" ብሎ መመለስ ተቀባይነት የሌለው ምላሽ ነው። በንግግር የመለያየት ምንም መፍትሄ አያመጣም።
_____________________
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
Belay Bekele Weya
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
በልክሽ ተሰርቶ፤ ቀልዴ ቁምነገሬ
ከተውሽኝ በኋላ…..
አንቺን ለመርሳት ስል ፤
ከብዙ ሴቶች ጋር፤ ልላመድ ሞክሬ
ለማንም አልሆንኩም!
ላንዷ እጠባታለሁ፤
ላንዷ እሰፋታለሁ፤
ላንዷ እረዝማታለሁ፤ ላንደኛዋ አጥሬ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ይኸው በቀደም ለት…..
ሳቅሽን የሚመስል ፤
ሳቋን የምትስቅ ፤ አንዲት ሴት ወድጄ
ሳቋን ለማፅናት ስል..
አንቺን ባሳቅሁሽ ቀልድ፤ እንድትስቅ ቀልጄ
ቀልዴ አላስቅ ብሏት ...
ያንቺን የሚመስለው ፤ ያ ሳቋ ቢጠፋ
በቅፅበት ጠላኋት…
አንቺን ባሳቀሽ ቀልድ፤ ሳያት እሷ አኩርፋ፡፡
።።።።።።።፣፣፣፣፣፣፣።።።።።።።።።።።፣።።
ባለፈው ለት ደሞ…
ያንቺን የሚመስል፤
ኩርፊያ ካኮረፈች፤ ከአንዲት ሴት ጋራ
ላንች የነገርሁሽን...
አስኮራፊ ታሪክ ፣
ኩርፊያዋን ለማፅናት፤ አኩርፌ ሳወራ
ያንቺን የሚመስል ፣
ኩርፊያዋ እስኪጠፋ ፣ ሳቋን ብትለቀው
ድንገት አስጠላችኝ….
እሷ ማን ሆና ነው?
አንቺን ባስኮረፈሽ ፤ ታሪክ የምትስቀው!?
።፣፣፣፣፣።።።።፣።፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣።፣።።።፣፣፣፣
ሰሞኑን ደግሞ አንዷን…
የዋናውን መንገድ፤ ትንሽ ገባ ብላ
አራቴ ወደ ቀኝ...
ሶስቴ ወደ ግራ፤ ከታጠፈች ኋላ
ወደ ሌላ ሚወስድ
ሌላ ዋና መንገድ
ከማግኘቷ በፊት...
ያለው ድልድይ ጋር ፣ እንገናኝ ስላት
አንቺ ከምትወጂው...
አንቺ ከምትቀጥሪኝ፤ ቦታ ላይ ስቀጥራት
‹‹እንዲህ ያለ ቦታ...
በጭራሽ አላውቅም›› ፣ የሚል ነበር መልሷ፤
ዘልዓለም ጠላኀት!
አንቺ ምትወጂውን
ቦታ የማታውቀው ፤ ማን ሆና ነው እሷ?!
፣፣፣፣፣፣።።።።።፣፣፣፣፣፣።።።።፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣
ብቻ ምን ልበልሽ….
በልክሽ ተሰርቶ፤ ቀልዴ ቁምነገሬ
ከተውሽኝ በኋላ…..
አንቺን ለመርሳት ስል ፤
ከብዙ ሴቶች ጋር፤ ልላመድ ሞክሬ
ለማንም አልሆንኩም!
ላንዷ እጠባታለሁ፤
ላንዷ እሰፋታለሁ፤
ላንዷ እረዝማታለሁ፤ ላንደኛዋ አጥሬ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ይኸው ደሞ ዛሬ…
የሌላ እንዳልሆን ፤በልክሽ ሰርተሸኝ
ከተውሽኝ በኋላ…….
ምትወርጂውን መንገድ ፣
እኔ እወጣሁት፤ ድንገት አግኝተሸኝ
‹‹እንዴት ነህ? ››ስስትዪኝ ...
እንዴትም እስክሆን ፣ ግራ አጋባሽኝ
አንቺ ነሽ? እኔን ነው? እንዴት አናገርሽኝ?
እንዴት ነኝ ልበልሽ?
እንደዚያው ነኝ በቃ!
እንደዚህ አድርገሽ ፣ያኔው እንደተውሽኝ፡፡
አንቺ ግን እንዴት ነሽ?
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
3 738
ማዶ ለማዶ
(በእውቀቱ ስዩም)
ድንገት ዘወር ብየ ፤ ያለፈውን ስቃኝ
የመስክ ውሃ ነበርሁ፤ ሜዳ የማይበቃኝ
አሁን ግን ታሰርኩኝ፤ ባንድ ትልቅ ቀፎ
ያንችም ነፃ ገላ፤
በትንሽ ሰቀላ
ቀረ ተቆልፎ፤
ለሌሎች የመጣው፤ ለኔና'ቺ ተርፎ ::
ይሄ ግዙፍ መአት
ጠልፎ ሳያቀረን
ማታ፤ ሁለት ሰአት
ቀጠሮ ነበረን፤
ትመጫለሽ ማታ?
ቀፎየን ልበርግድ፤ ሰንሰለቴን ልፍታ?
ይነጠፍ ወይ አልጋው
ለኔ - ላንቺ- ለሞት
ሶስትዮሽ ምኝታ
ሶስትዮሽ ጨዋታ
ይሰረዝ ቀጠሮው ?
ወደ ፊት ይዛወር
ወደ ማናውቀው ቀን ፤ወደ ማናውቀው ወር፤
አሁን እዚህ ሆነን ፤ቅንጦት ነው መገመት
እናስተላልፈው ወይ፤
ከለታት ላንዱ ቀን፤ ካመቶች ላንዱ አመት፤
እንዳማረኝ ይቅር?
ያ ሙቀት! ያ ፍቅር !
ያ መስህብ ፤ ያለዛ
ያ ተረከዝ ! ያ ባት
ናፍቆትም ደዌ ነው፤ የሌለው ክትባት ፤
3 738
እንደገና እንካካድ!
(አሌክስ አብርሃም)
‹‹ከአምና በፊት ሃቻምና››
የዛሬን አያርገውና
ተቃቅፎ በመካካድ ጦስ
ባቧራ አቧራው ሲጨስ
ውጉዝ ከመ አርዮስ
ለአንዱ ክንፍ ለመትከል
ከሌላው ላባ መቀንጠስ
በተበደልኩ በደልኩ ሰበብ
ለውግዘት ስንሰበሰብ
ስንጠራራ ለጠብ
የፍቅር ሽቶን ድል አርጎ
የልህ ክርፋት ሲንጠባጠብ
አደግድጎ ሲያሸረግድ
ወዶ ገቢ ለጠብ ሲሰግድ
ያኛው ነገሩ ቀፎት
ታሪኩን በ,ልባት ሲያቆም
ምላሱን በምላስ ሲያግድ
እጅ ከፍንጅ ልንያያዝ
በየጢሻው ስናደባ
አንዱን ካንዷ ስናፋታ
አንዷን ካንዱ ስናጋባ
የቁጣ ችቦ ለኩሰን የፍቅር ምንቸት ውጣ
የበቀል ምንቸት ግባ
እንዲህ ሲያዩት በዚህ ዘመን
ቀሊል የውፍጮ መጁ የወፍጮ መጁም ላባ!
መዛኝ ተመዛኝ ገለባ !!
ይሄን ዘመን ማን ጠርጥሮ
ማንስ ነብይ ራይ አይቶ ማንስ ጠንቋይ ኮከብ ቆጥሮ
እንኳንስ በአፍላ ምኞት መተቃቀፍ ሊሆን ነበር
እንደገና እልፍ ልናቅፍ በልባችን ዝተን ነበር !
(አንተ ብትሄድ ሽ ወንድ አለ …ጥርግ በይ ሴት በገፍ ነው)
ይሄው ክፉ ቀን መጣ …
እንኳን ለጠብ መተቃቀፍ
ልብስን ታኮ መተላለፍ
ሊገለን ነው ሰቀቀኑ
አንች ! እንዴት ይፈጥናል ቀኑ?!
እንኳንስ ሙቅ እቅፋችን
ያይናችን ምኞት ራቀን
ኧረ ዳግም እንካካድ
የማትክድ ጌታ ታረቀን !
ጨነቀን …ከምር ጨነቀን !!
3 738
Belay Bekele Weya
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
ገላሽ ገላ አይመርጥም ፣ ከሁሉ ይጋደማል
ከንፈርሽ አየር ነው ፣ በሁሉም ይሳማል
ከሴት ክብርሽ ይልቅ ፣ ስሜትሽ ይቀድማል።
።።።
ነግሬሽ ነበረ፡፡
ጭን ከሰማይ ቢገዝፍ ፣ ከጭንቅላት ያንሳል
ምን ተራራ ቢመስል...
ጡትም አቅመ ቢስ ነው ፣ ሲነኩት ይፈርሳል፡፡
ነግሬሽ ነበረ....
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯ የአምላክ ነው ፣ እንደ እናት ስታስብ!!!
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ክብረቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ ፣ እናቶች አይደሉም
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ.
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
።።።።።
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።
ሴት ክብሯን ስታጣ ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
።።።።
ነግሬሽ ነበረ
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ስሜት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።
።።።
ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።
።።።
ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይተኛታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!
