en
Feedback
አብርሆት

አብርሆት

Open in Telegram

ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23

Show more
3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ዛሬ ከረፋዱ 5:30 ጀምሮ "ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ" በሚል የ2 ደቂቃ ፕሮግራም ይካሄዳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የኪነ ጥበብ ባለሞያዎችን ጥሪ የተቀበሉ ኢትዮጵያውያን በያሉበት ሆነው ለ
ዛሬ ከረፋዱ 5:30 ጀምሮ "ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ" በሚል የ2 ደቂቃ ፕሮግራም ይካሄዳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የኪነ ጥበብ ባለሞያዎችን ጥሪ የተቀበሉ ኢትዮጵያውያን በያሉበት ሆነው ለ1 ደቂቃ ቀኝ እጃቸውን በግራ ደረታቸው ላይ አድርገው በመቆም ለመከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ክብር ይገልጻሉ። ይህ ሲጠናቀቅ በቀጣዩ አንድ ደቂቃ ባሉበት ሆነው ባለማቋረጥ ለ አንድ ደቂቃ ያጨበጭባሉ። 5:33 ደቂቃ ሲሆን መገናኛ ብዙኃን የጥላሁን ገሠሠን ኢትዮጲያ የሚለውን ሙዚቃ ያጫውታሉ። Via Sheger

#Déjàvu_ምንድነው ??? (ቱካ ማቲዎስ) አንድ ሰው አሁን በዚ ቅጽበት የሚያከናውነውን ሊያከናውን ያለውን ድርጊት ወይም ክስተት ከዚህ በፊት በተመሳሳይ እንዳደረገው ሲሰማው ደጃቩ ይባላል። አንድ ነገር ስናደርግ ነገሩን ከዚህ በፊት ምንም ሳይለወጥ ያደረግነው ወይም በሕልም የተመለከትነው የሚመስለን ድርጊት ነው። በገዓዱ ዓለም የሚከሰተው አንዳች ያልተለመደ ድንገታዊና ቅጽበታዊ ግርታ ነው። ፈረንሳይኛ ትርጉሙም በቀጥታ "ዳግማዊ" ከዚህ ቀደም የታየ የተከሰተ ማለት ነው። ከትንቢትና አንድ ነገር ሳይከሰት በፊት ቀድሞ የማወቅ ጥበብና ኃይልም ጋር ሚያዛምዱትም አሉ። በአማካይ በዓመት ውስጥ አንድ ግዜ ሰዎች ይህ ሁኔታ ያጋጥማቸዋል። የኢንዱሂዝም እምነት "Deja Vu" ዳግም ሰለመፈጠር (ድጋሚ ስለመወለድ) የሚያመላክት ተጨባጭ ማስረጃ እንደሆነ ይናገራሉ። ብዙ ግዜ የሚከሰተውም ሰዎች በከፍተኛ ደስታ፣ድካም፣ጭንቀትና የተደላደለ የአእምሮ ሁኔታ ውስጥ ሲሆኑ ነው ይላሉ። በሴቶችም በወንዶችም በተመጣጣኝ መልኩ ቢከሰትም ዕድሜ በጨመረ ቁጥር ደጃቩ እየቀነሰ ይሄዳል።በተማሩና በኢኮኖሚ አቅማቸው ላቅ ባሉ ሰዎች የመከሰት ዕድሉም ላቅ ያለ ነው።እንዲሁም ብዙ ጉዞ የሚያበዙ ሰዎችም ደጃቩ አዘወትሮ ያጋጥማቸዋል። It can be produced by electrical Stimulation of the cortex & deeper brain structure. አንዳንድ ሰዎች እንደሚሉት ከዚህ ቀደም ያዩት ሕልም በገሃዱ አለም ቅልብጭ ብሎ እየተከናወነ ያዩታል። ደጃቩ ምናልባት ይሄን ፅሑፍ የሚያነበው ሰው ላይ ተከስቶ ይሆናል ከ3-5 ሰከንድ ድርጊቱ ይቆያል ይሄን በልምምድ ማስፋት ለቻልን ቀድመን መጪውን ማየት የመቻል ብቃቱ ይኖረናል ይላሉ። እኔም በዚህ እስማማለሁ የሰው ልጅ IQ በአግባቡ አልተጠቀመም እንጂ superhuman መሆን ይችል ነበር።ሌላውን ትተን በደጃቩ ብቻ ቀጥሎ ስለሚሆነው ማወቅ ይችላል ነገሮችን እያስተካከለ ይሄዳል ማለት ነው።ያቺን የደጃቩ ቅጽበት ማስፋት ከቻለ። ለምሳሌ:- መኪናችሁ ውስጥ ገብታችሁ በቁልፍ ሞተሩን ልታስነሱ ስትሉ ድንገት በዝንብ ትረበሻላችሁ።ወደ ቀልባችሁ ተመልሳችሁ በቁልፉ ሞተሩን ስታስነሱ ይህ ድርጊት አእምሯችሁ ውስጥ ቀድሞ እንደተደረገ ይነግራችኃል ይህ ሌላኛው አይነት ደጃቩ ነው። ሌላው ምሳሌ:- ኮንሰርት ታዳሚው ለመጀመርያ ግዜ ባንድ ሲጫወት ሲመለከት ከደስታው ብዛት ከዚህ ቀደም ይሄን ክስተት አይቼዋለሁ የሚል መልዕክት አእምሮው ላይ ይመላለሳል ይሄ ሊሆን ይችላል? #አይነቶቹ ፩.Deja Vecu ትርጉሙ "I have already experience this" ካለ አንድ ሰው በገሃዱ ዓለም ለሚከናውን ድርጊት ደጃ ቨኩ ይባላል። ፪.Deja Senti ከሰዎሽ ስሜት ጋር ተዛማጅ ሲሆን "I have already felt this" ወይም ይሄ አሁን የተሰማኝ ስሜት ከዚህ ቀደም ተሰምቶኝ ያውቃል ይሆናል።ከሁለቱ አይነቶች የሚለየው ክስተት ላይ ያልሆነና ሙሉ ተፈጥሯዊ ነው። ፫.Deja Visite ይሄ አይነት ደግሞ አይተውት ጎብኝተውት ስለማያውቁት ቦታ እንደምናውቀው ሲሰማን ነው። ለምሳሌ:- የሆነ ከዚህ በፊት የማናውቀው ከተማ ሄደን እንደምናውቀው አይነት መውጫ መግቢያውን ስናውቀው Deja Visite ይባላል። #የvu_አይነቶች የደጃቩ ተቃራኒ Jamais Vu ይሉታል። never seen ወይም ታይቶ የማይታወቅ ክስተት ሲሆን ከደጃቩ ያነሰ የመከሰት ዕድል አለው። Presque Vu ምላሴ ላይ አለ ብላችሁ አታውቁም? አንድን ነገር ታውቁታላችሁ ግን ሙስለ አልቻላችሁም። Jamais Vu የሆነ የምታውቁት ነገር እንደማታውቁት አይነት እንግዳ ሲሆንባችሁ ነው። #ጥያቄዬ :- Deja Vu አጋጥሟችሁ ያውቀል? የትኛው አይነት? ንገሩኝ እስኪ። (ነጽሩ ወዘሠናየ አጽንዑ) @JamesB23

#Rationalism / ምክኖአዊ #Rene_Descartes ********************* አንድ የማይጠረጠር ዕውነታ አሳዩኝ. አንድ ሊጠረጠር የማይችል ዕውነታ ንገሩኝ. አንድ ለቀልድ ተብሎ እንኳ
#Rationalism / ምክኖአዊ #Rene_Descartes ********************* አንድ የማይጠረጠር ዕውነታ አሳዩኝ. አንድ ሊጠረጠር የማይችል ዕውነታ ንገሩኝ. አንድ ለቀልድ ተብሎ እንኳን የማይጠረጠር ነገር ስጡኝ....ከዛ የዕውቀትን መሰረት አሳያችዋልሁ‼ ይላል ዴካርት። * የሬነ ዴካርት የስነ ዕውቀት ቀደምት ዘይቤው በ ‘Methodic doubting ‘ መሰረት የማይጠረጠር ነገር ላይ እስክንደርስ ድረስ፣ ሁሉንም ጠርጥር የሚል ነው። ይህን ዘዴ እራሱ ላይ ሞከረው፣ በሚከተለው ሂደት…… * - አለው? #Do_I_exist❓በህይወት ካለው ምን ዓይነት ፍጥረት ነኝ❓ - በህይወት መኖሬን እንዳምን፣ የትኛውን የእኔን ምንነት በፍፁም ልቤ ልመን❓ - ከሁሉም ነገሬ ማሳቤን ማመን አለብኝ‼ሆኖም ይህን ማሰቤንም ግን እጠራጠረዋልሁ። ግና ይህ ጥርጣሬዪ ደግሞ በህይወት መኖሬን ያረጋግጥልኛል። ምክንያቱም ለመጠርጠር ማሰብ ያስፈልገዋል። ስለዚህ ካሰብኩ አልሁ። ይቀጥላል

ሰበር ዜና ‼️ ከWegagen Bank of Ethiopia የተሰጠ መግለጫ❗️ _____ የወጋገን Bank President አሁን በሰጡት መግለጫ መሠረት በ ባንካችን ላይ ህገወጥ መሳሪያ ተገኝቷል ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ፍጹም ከእውነትነት የራቀ መሆኑን ገልጸው ይልቁንም በባንካችን የተገኘው መሳሪያ ህገ ወጥ ሳይሆን በውድ ደምበኞቻችን የተቆጠቡ መሆኑን አስተባብለዋል። ይህ አሰራር ቀድሞውንም በባንካችን ህገ-ደንብ ውስጥ የተካተተ እንደሆነ ገልጸዋል። አክለውም ይህን በባንካችን ላይ የተከፈተውን ስም የማጠልሸት ዘመቻ ወደ ጎን በመተው በባንካችን ለሚቆጥቡ ደምበኞች እድለኛ ለሆኑት የመትረነስ ፤ የታንክ ፤ የክላሽንኮቭ እጣዎች መኖራቸዉን ገልጸዋል !! ጉድ መጺሁ አለ ሰውዬው😂😂😂

💥Dear members According to the new policy, members who mute a channel are considered an "inactive members". Muting a channel reduces the views on the post, even though you are watching the posts, So Unmute it and let's go big.

የከተማዋ ነዋሪም የጦርነትን አስከፊነት በተደጋጋሚ ይናገራል። ነዋሪዎች ግጭቱ በቶሎ የሚፈታበትን ሁኔታና ዕድል እንዲፈጠር በጉጉት እየጠበቁ ይገኛሉ ይላል ባልደራባችን። አንዴት እዚህ ነገር ውስጥ ተገባ? በህወሓት እና በፌዴራል መንግሥቱ መካከል ልዩነቶች እየሰፉ የመጡት ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ያካሄዱትን የለውጥ እርምጃ ተከትሎ ነው። ኢሕአዴግ ከስሞ ወደ ብልጽግና ፓርቲ መቀየሩ እንዲሁም የፌደራል መንግሥት በኮሮናቫይረስ ስጋት ያሸጋገረው አገራዊ ምርጫን ወደ ጎን በመተው የትግራይ ክልል ክልላዊ ምርጫ ማካሄዱ በሁለቱ አካላት መካከል ከፍተኛ መቃቃር እንዲፈጠር ምክንያት እንደሆኑ ይነገራል። የፌደራል መንግሥት በትግራይ ክልል የተካሄደውን ምርጫ ሕገ-ወጥ ነው ሲለው ሕውሃት በበኩሉ የጠቅላይ ሚንስትሩ መንግሥት የሥራ ዘመን አብቅቶለታል ሲል ነበር። ነገሮች ተባብሰው ጥቅምት 24 ላይ የትግራይ ልዩ ኃይል፣ በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የአገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን በመጥቀስ ጠቅላይ ሚንስትሩ የአገር መከላከያ ሠራዊት ሕውሃት ላይ እርምጃ እንዲወስድ ማዝመታቸውን ተናግረዋል። via bbc

ትግራይ፡ ሕይወት በጦርነት ቀጣና ውስጥ በምትገኘው መቀለ በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ኃይሉ መካከል ግጭት ከተከሰተ ዛሬ ሰባተኛ ቀኑን አስቆጥሯል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ የትግራይ ልዩ ኃይል በክልሉ በሚገኘው የአገር መከላከያ ሠራዊት የሠሜን እዝ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን በመጥቀስ ወታደራዊ ዕርምጃ እንዲወሰድ ማዘዛቸው ይታወሳል። የክልሉ መንግሥት በበኩሉ ጦርነቱን የከፈተብን የፌደራሉ መንግሥት ነው ይላል። ለመሆኑ ዕለታዊ ሕይወት በጦርነት ቀጠና ውስጥ ምን ይመስላል? ሪፖርተራችን ከስፍራው የሚከተለውን ዘገባ ልኮልናል። የስልክ እና ኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥ ማክሰኞ ጥቅምት 24 ምሽት ላይ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ በመቀለ ከተማ ተሰማ። ከዚያም ብዙም ሳይቆይ የስልክ እና ኢንተርኔት አገልግሎቶች ተቋረጡ። ነዋሪዎች በክልሉ እና ከክልሉ ውጪ ካሉ ዘመድ ወዳጆቻቸው ጋር የነበራቸው ግንኙነት ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ይናገራሉ። መምህሯ ንግሥቲ አበራ አራት ልጆች እንዳሏት ትናገራለች። አራቱም ልጆቿ ኑሯቸው በአዲስ አበባ ነው። ስለ ልጆቿ ትጨነቃለች። "ላለፉት ሦስት ቀናት መብላትም መተኛትም አቃተኝ። ልጆቼን ድምጽ ከሰማሁ ቆየሁ" ብላለች ለቢቢሲ። ኤሌክትሪክ ጦርነቱ እንደተጀመረ፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎቱ ተቋርጦ ነበር። ይሁን እንጂ ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ ከሁለት ቀናት በኋላ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲመለስ ተደርጓል። ይሁን እንጂ በመቀለ ከተማ በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ እያጋጠመ እንደሆነ ሪፖርተራችን አስተውሏል። ትግራይን የሚያስተዳድረው ህወሓት የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲቋረጥ ያደረገው የፌደራል መንግሥቱ ነው ይላል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በበኩላቸው የአሌክትሪክ አገልግሎቱ እንዲቋረጥ ያደረገው የህወሓት ኃይል መሆኑን ተናግረዋል። የውሃ ችግር ወትሮም የመጠጥ ውሃ ችግር የነበረባት የመቀለ ከተማ አሁን ችግሩ በርትቷል። ከዚህ ቀደም በተንቀሳቃሽ ቦቴ መኪናዎች እና በሌሎች ዘዴዎች ውሃ ያገኙ የነበሩ ነዋሪዎቸ አሁን ላይ የግንኙት መስመሮች በመቋረጣቸው ውሃ ለማግኘት መቸገራቸው ይናገራሉ። በመቀለ ከተማ በስልክ ትዕዛዝ ተሰጥቷቸው ውሃ ያቀርቡ የነበሩ ድርጅቶች አሉ። በአሁኑ ወቅት ግን የስልክ ግንኙነት ባለመኖሩ ውሃ በትዕዛዝ ማግኘት ከባድ ነው ሲል ሪፖርተራችን ይናገራል። በሳምንት አንድ ጊዜ ትመጣ የነበረው የቧንቧ ውሃ ሳትመጣ መቅረቷ ችግሩን አባብሶታል ይላል ሪፖርተራችን። በመቀለ ከተማ በተለያዩ ስፍራዎች ውሃ ማከፋፈያ ስፍራዎች አሉ። ከእነዚህ ማከፋፈያ ስፍራዎች በአሌክትሪክ ኃይል ተስበው በውሃ መጫኛ ቦቴዎች ነበር የሚጓጓዙት። በአሁኑ ወቅት የአሌክትሪክ አገልግሎት በመቋረጡ የውሃ እደላ የማካሄድ ሥራውን ከባድ ማድረጉን ባልደረባችን ይናገራል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በትግራይ ክልል ላይ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፀደቀ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም ወሰነ ስለ ፌደራል መንግሥትና የትግራይ ክልል ግጭት ማን ምን አለ? የባንኮች መዘጋት ከጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ጀምሮ የግል እና የመንግሥት ባንኮች በትግራይ ሙሉ በሙሉ ዝግ ናቸው። ከሁለት ቀናት በፊት ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በትግራይ የሚገኙ ሁሉም ባንኮች የደኅንነት ስጋት ስላለባቸው በክልሉ የሚገኙ ሁሉም የባንክ ቅርንጫፎች እንዲዘጉ ወስኗል። በክልሉ ነዋሪዎች ላይ አስቸጋሪው ኩነት የባንኮች አገልግሎት መቋረጥ መሆኑን ሪፖርተራችን ይናገራል። የሦስት ልጆች እናት የሆነችው ንግሥቲ መለስ በባንክ ያላትን ገንዘብ ወጪ ማድረግ ባለመቻሏ ችግር ላይ መሆኗን ትናገራለች። ወ/ት ዓለምነሽ ገብረሥላሴ በጉሊት ገበያ የችርቻሮ ንግድ ላይ ተሰማርታ ነው ህይወቷን የምትመራው። ወ/ት ዓለምነሽ ገዢ ጠፍቷል ትላለች። "ሰዎች እየገዙ አይደለም፤ እኔም ገቢ እያገኘሁ ስላልሆነ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነው የምገኘው" ብላለች። ባንኮች ከመዘጋታቸው አንድ ቀን በፊት፣ የጥሬ ገንዘብ እጥረት በገበያ ውስጥ መታየቱን ሪፖርተራችን ዘግቧል። የባንኮች መዘጋት እና የጥሬ ገንዘብ እጥረት ነዋሪዎች ወደ ገበያ ወጥተው መሠረታዊ ፍጆታዎችን እንዳይሸምቱ ጋሬጣ እንደሆነባቸው ይናገራሉ። መቀለ ከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት ጦርነቱ እንደተጀመረ ማክሰኞ ጥቅምት 24 የትግራይ ክልል መንግሥት ባወጣው የመጀመሪያው መግለጫ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቋረጥ መወሰኑን ይፋ አድርጎ ነበር። ይህ እግድ ለሁለት ቀናት ከዘለቀ በኋላ፤ ከመኖሪያ ቀያቸው ርቀው የነበሩ ሰዎች ከትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን ልዩ ፍቃድ እየተቀበሉ ወደ መኖሪያቸው መመለሳቸውን ሪፖርተራችን ተመልክቷል። ይህ ልዩ ፍቃድ የሌለው ወይም ማግኘት የማይችል የክልሉ ነዋሪ ግን ወደ የትኛው የክልሉ ስፍራ መንቀሳቀስ አይችልም። ክልሉ ከሌሎች አጎራባች ክልሎች ጋር በሚዋሰንባቸው ድንበሮች ዙርያ ወታደሮች ስለሰፈሩ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባና ወደሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች መጓዝ የማይታሰብ ሆኗል። የአየር ድብደባ ስጋት ሐሙስ ጥቅምት 26 ከሰዓት ላይ አንድ ተዋጊ ጄት በመቀለ ዙርያ በራ ነበር። ይህም ነዋሪዎችን በከፍተኛ ሁኔታ አስደንግጦ እንደነበረ ዘጋቢያችን ለመታዘብ ችሏል። ምሽቱን የክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ይህ የጦር ጄት ቦምብ እንደጣለና ሰዎች ላይ ግን ጉዳት እንዳልደረሰ ገለጧል። ይህ ግን በሪፖርተራችንም ይሁን በገለልተኛ አካል አልተረጋገጠም። ባሳለፍነው እሑድ ወደ ቤተ-ክርስቲያን ሲሄዱ የነበሩ ሰዎች የጦር ጄት ድምጽ ሲሰሙ በፍጥነት ተሯሩጠው ሲበተኑም ተመልክቷል። በዚያው ዕለት ምሽት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለትግራይ ሕዝብ በከተሞች አከባቢ እና በተለያዩ ወታደራዊ ጥቃት ሊያጋጥማቸው በሚችሉ ስፍራዎች በብዛት ሆነው ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡ ጥሪ አስተላለፉ። ይህም ተጨማሪ የአየር ድብደባ እንደሚኖር ያመላከተ ነበር። ጥቅምት 29 እሑድ ምሽት ላይ የፌደራል መንግሥቱን የጦር ጄት መትተን ጥለናል ሲሉ የሕውሃት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናገረው ነበር። የአገር መከላከያ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሜጀር ጀነራል መሐመድ ተሰማ ግን ይህ የሐሰት ዜና ነው ሲሉ ትናንት ጥቅምት 30 ለአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። የነዳጅ እጥረት በመቀለ የሚገኘው ሪፖርተራችን ግጭቱን ተከትሎ በትግራይ በተለይም በክልሉ መዲና የነበረው የንግድ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን ይናገራል። የንግድ ብቻ ሳይሆን የትራፊክ እንቅሴውም ቀንሷል ይላል። ለዚህ ደግሞ ከምክንያቶች አንዱ በክልሉ የነዳጅ እጥረት በመከተሱ ነው። አቶ ሐለፎም ተክላይ መኪናቸውን ሙሉ በሙሉ ለማቆም መገደዳቸውን ይናገራሉ። ለዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያታቸው የነዳጅ እጥረት እንደሆነ ይናገራሉ። የክልሉ መንግሥት ምን ይላል? ከፌዴራልም ሆነ ከክልሉ መንግሥት በትግራይ እየተከሰቱ ባሉ ሁኔታዎች ዙርያ በቂ የሚባል ማብራሪያ የክልሉ ሕዝብ ማግኘት እንዳልቻለ ሪፖርተራችን ይናገራል። የክልሉ ሕዝብ ግራ መጋባትና ስጋት ውስጥ ባለበት ሁኔታ ወሳኝ የሚባሉ መረጃዎች ከመንግሥት አካላት አያገኘ ነው ለማለት አያስደፍርም ይላል ዘጋቢያችን። የትግራይ ክልል የሕዝብ ግንኙት ቢሮ አሁን ያሉት ችግሮች 'በአጭር ጊዜ ውስጥ ይፈታሉ' ከሚል አጭር መልስ ውጪ ተጨማሪ ማብራሪያ ሊሰጥ አልቻለም። የነዋሪዎቹ ጥያቄዎቹ "ወደ የት እየተኬደ ነው? ይህ ሁሉ መጥፎ ሁኔታስ መቼ ነው የሚያበቃው?" የሚሉት ጥያቄዎችን እያነሱ መሆኑን ሪፖርተራችን ይናገራል።

በጎጃም ደጀን፣ አምቦ፣ ነቀምት፣ ጅማ፣ ቡሌሆራ (አገረ ማርያም) ሞያሌ ድረስ በዘለቀው አውድ ውጊያ ተሳትፈዋል፡፡ በሀረርም ጸረ ሰላም ሀይሎችን በመከላከልና በማጥቃት ዘመቻ ተሳትፈዋል፡፡ በሩዋንዳ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ በ1986ዓ.ም ግድጃቸውን በስኬት አጠናቀው ተመልሰዋል፡፡ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሲቋቋምም 20ኛ ክፍለ ጦር መድፈኛ ብርጌድ አንደኛ ሻለቃ አዛዥ ሆነው አገልግለዋል፡፡ በኢትዮ-ኢርትራ ጦርነትም ትምህርታቸውን አቋርጠው በመሄድ ብርጌድ አዛዥ በመሆን በጾረና፣ በባድመ፣ በሽራሮ አዲኋላ ግንባር ተሳትፈዋል፡፡ አሁንም በዳንሻ ከተማ በትግራይ ልዩ ሀይል የተካሄደውን ከበባና ሶስት ቀናት የዘለቀ ጥቃት ወስን ወታደሮችን መርተውና አዋግተው በተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት ዕገዛ መከላከሉን በድል አጠናቀው የማጥቃቱን ተልዕኮ በድል እየተወጡ ይገኛሉ። ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የተወሰደ

የሶስቱ ቀናት ፈታኝ ተጋድሎ በብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አንደበት አዲስ አበባ ፣ ህዳር 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ዳንሻ ከተማ በሚገኘው የሰሜን ዕዝ አምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር ካምፕ ጊቢ ውስጥ የመከላከያ መኪናዎች በጥይት ተበሳስተው ይታያሉ፡፡ መስታወታቸው ረግፏል፤ዛፎቹም የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል፤ መጥረቢያ እንጂ የጥይት ውርጅብኝ የቆረጣቸው አይመስሉም።የግንብና ቆርቆሮ ቤቶች እንደ ወንፊት ተበሳስተዋል፡፡የጥይቶች ቀላሃ እንደ ጠጠር ተብትኗል፡፡ ዕለተ ማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ሰዓት አካባቢ በዳንሻ ከተማ ያልተጠበቀ፣ አሳዛኝ፣ አስደጋጭ ድርጊት ነው የተፈጸመው፡፡በከተማዋ የሚገኘው የሰሜን ዕዝ የአምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር የተደገሰለትን ጥቃት አያውቅም።በመካናይዝድ ክፍለ ጦሩ ስታፍ ውስጥ የሚሰሩት መደበኛ ስራቸውን ከውነው እንቅልፍ ላይ ናቸው፡፡ በዚህ ምሽት ግን የትግራይ ልዩ ሀይል አባላት ወደ ካምፑ ዘለቁ፤ ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አድማሱን እንደሚፈልጉትና እንዲጠራላችሁ የበር ጥበቃዎችን ይጠይቃሉ። ጀኔራሉም እንደማይመጡ ሲነገራቸው ተመልሰው ይሄዱና ተጨማሪ ሀይል ይዘው መጥተው በካምፑ ላይ የጥይት መአት ማውረድ ይጀምራሉ፡፡ውስጥ የነበሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላትም በጽናት የመመከት ስራ ውስጥ ገቡ፤ለሶስት ቀንና ሌሊት በጽናት ታገሉ፡፡ አንድ የመከላከያ ሰራዊት የመረጃ ሰራተኛ ወደ ጀነራሉ ጆሮ ተጠግቶ አካባቢውን የትግራይ ልዩ ሀይሎች ከቦታል፡፡ፍላጎት ካለህ ሽማግሌዎቹ ከአካባቢው እናስወጣው ብለው ነግረውኛል፤ ውሳኔህ ምንድነው ሲል ጠየቀኝ ያሉት ብርጋዴር ጀነራሉ፣ የእነሱ ፍላጎት እኔም ወኔዬን ተሰልቤ የሲቪል ልብስ ለብሼ ተደብቄ ወደ አማራ ክልል እንድወጣ አልያም እኔን አታለው እንድያዝ በማድረግ ካምፕ ውስጥና በአቅራቢያው ባለው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ለመሰንዘር ያቀዱትን ጥቃት የመከላከልና የመመከት ስራ ለማሰናከል ነው፡፡ በዚህም በቀላሉ ሰራዊቱንና መሳሪያውን በቁጥጥር ስር ለማዋል አስበው መሆኑን ገለጹልን፡፡ እኔም ምላሼ ሽምግልናውን አለመቀበል ብቻ ሳይሆን የመረጃ ሰራተኛው ከሽማግሌዎቹ ጋር ለጥሩም ይሁን ለመጥፎ መገናኘት እንደሌለበት አስጠንቅቄ ነገርኩት ።አሁን ይህን ያለኝ ልጅ ቆስሎ ለህክምና ወደ ጎንደር ሄዷል።ሲመጣ ጠይቄ ዓላማቸው ምን እንደነበር የምረዳው ይሆናል፡፡ተመትቶ ስለነበረ እኔም እንዳልሞት አስቦ ይሆናል የሚል ግምት አለኝ ብለውናል። የሶስት ቀን ከበባው በጣም አስቸጋሪ ነበር።24 ሰዓት ተኩስ ነው፡፡ያጠቃሉ እኛ እንከላከላለን፤ይሄዱና ምግብ በልተው ሀይል ጨምረው ያጠቃሉ፤ ሲታኩሱ የነበሩት ልዩ ሀይሎች ወደ ካምፓቸው ሄደው አርፈውና ጥይት ጭነው ይመጣሉ፡፡እኛ ካለንበት ቦታ ውጭ መፈናፈኛ ስፍራ የለንም፡፡ እንደ ቀለበት ዙሪያውን ከበውና ውሃ ፣ምግብ፣ጥይት የለም፡፡ያለችንን ነው በቁጠባ የምንጠቀመው ሲሉ ያብራሩት ጀነራሉ፣እኔም አልፎ አልፎ እንደ ምሽግ ከተጠቀምኩበት ግንብ ቤት እየወጣሁ ለወታደሮቼ ጥይት በቁጠባ ተጠቀሙ እያልኩ አሳስብ ነበር ሲሉ ይገልጻሉ፡፡እነሱም አላሳፈሩኝም በጽናት ተዋደቁ። የሰራዊታችን በጽናት የመከላከል ሞራል የሚገርም፣ የሚደነቅና ታምር የሚያስብል ነው ይላሉ፡፡ አርቢጂ፣ቦንብ፣መትረየስ ፤ክላሽ እንደ ዝናብ ቢያርከፈክፉብንም ለሶስት ቀናት ቀንና ሌሊት መክተናል፡፡በፍጹም እንተርፋለን ብለን አላሰብነም ፤ከቻልን እስከ መጨረሻው እንከላከላለን ፤ካልቻልን ደግሞ በመጨረሻ ላይ ራሳችንን እናጠፋለን የሚል አቋም ነበርን፡፡ ግን በእግዜአብሄር ቸርነት፤በመከላከያ ሰራዊት ፈጥኖ ደራሽነት ቀለበቱ ተሰብሮ ከመከላከል ወደ ማጥቃት ተሸጋግረናል ብለውናል፡፡ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም፡፡ ድርጊቱ የሚያሳዝን ነው፤ በህወሓት ከሀዲ ቡድን እንዲህ አይነት ጥቃት ይፈጸምብናል ብለን አስበን፤አልምንም አናውቅም የሚሉት በሰሜን ዕዝ የአምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ሙሉዓለም አድማሱ፤ ምክንያቱም ከኢትዮ-ኢርትራ ጦርነት ጀምሮ ትግራይ መሬት ነው እየኖርን ያለው።ህዝቡን መሪዎቹንም በደንብ እናውቃቸዋለን ብለዋል፡፡ “አብረህ እየበላህ እየጠጣህ፣ተዋልደህ ተጋምደህ፤ ትዳር መስርተህ ፣ልጆች ወልደህ፤ቤተሰብ ሆነህ በፍጹም ጥቃት ሊሰነዝርብኝ ይችላሉ ብለህ አታስብም፤ሆኖም ያልታሰበው ተፈጸመ፤ያልተጠበቀው ሆነ “ሲሉ በትግራይ ክልል ልዩ ሀይል የተሰነዘረባቸውን ጥቃት አሳዛኝ ሲሉ ይገልጹታል። ኩርፊያና የተለያዩ መገለጫዎች ይታያሉ ፡፡ይህን ተከትሎ ጥርጣሬዎች ቢኖሩም ደፍረው መከላከያ ሰራዊት ካምፕ ውስጥ ገብተው ያጠቃሉ ብለን አላሰብንም። ምክንያቱም ወንድምህ ሊያኮርፍ ይችላል እንጂ ያጠቃኛል፤ይገለኛል ብለህ ፈጸሞ አትገምትም የሚሉት ብርጋዴር ጀኔራሉ፤ግን የትግራይ ልዩ ሀይሎች ዕለተ ማክሰኞ 25ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ያለምንም ርህራሄ ዙሪያውን እንደ ቀለበት ከበውን አጠቁን ፣አጠቁን እኛም በጽናት ተከላከልን፤መከትን ብለዋል፡፡ የህወሓት ቡድን ዓላማ የመከላከያ ሰራዊትን መድፎች፣ ታንኮች፣ብረት ለበሶችን መንጠቅና መከላከያን ማፍረስ ነው፡፡ በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም ፤በራሳችን መሳሪያ ተመልሰው እኛን ለመውጋት ነበር ዕቅዳቸው፡፡ይህ አልተሳካላቸውም፡፡እኛም በያለንበት በጽናት ተዋግተን መክተናል፡፡ አሁን እነሱ ባሰቡት ሳይሆን እኛ ባሰብነው መንገድ እየሄደ ነው፡፡በአጭር ጊዜ ውስጥ ጦርነቱ ይቋጫል ብለን እናስባለን ሲሉ ገልጸውልናል። ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አንድ የሚገርማቸው የሚደንቃቸው ነገር አለ፡፡”እኔ አንድ ተራ ኢትዮጵያዊና ተራ ጄነራል ነኝ፣በአንድ ክላሽ ጥይት ግፋ ቢል ደግሞ በስናይፐር መግደል ይችላሉ፤ ግን የጭካኔያቸው ጭካኔ አርቢጂ ነው የተኮሱብን ። አርቢጂ የሚባለው መሳሪያ ደግሞ ለታንክ ወይም ለጠንካራ ምሽግ ነው የሚተኮሰው፤የእኔን ቤት ለማፍረስ ግን አርቢጂ ነው የተኮሱት ሲሉ የከሀዲው ቡድን የጭካኔ ጥግ ምን ያህል እንደሆነ ይናገራሉ ፡፡ እኔ ብሞትም ቤቱ የእነሱና የህዝቡ ንብረት ነው። ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ጸጥታ ለቆምኩ፣ለአገር ሉዋላዊነትና ለህዝብ ሰላም ውድ ህይወቴን ለመስጠት በተሰለፍኩ የክህደታቸው፣የክፋታቸው ጥልቀት እኔን በአርቢጂና በቦንብ ነው ያጠቁት ሲሉ የድርጊቱን ክፋት ገልጸውታል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከትግራይ ህዝብ ጋር አብሮ እየኖረ ያለ፣ለህዝቡ የልማት ስራዎች ወደ ኋላ የማይል፣ በማህበራዊ ድጋፎች የሚሳተፍ፣ ሁልጊዜ በየዓመቱ ለአቅመ ደካሞች የሚያርስ፣ የሚያርም፣ የሚያጭድና አንበጣ የሚከላከል ነው። በትምህርት ቤቶች፣በጤና ጣቢያዎች፣በመንገድ ግንባታዎች በሚሳተፍ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈጸም የህወሓት ቡድን እወክለዋለሁ ቆሜለታለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ እንደሌለው ያሳያል ይላሉ፡፡ የአገሩን ዳር ድንበር የሚጠብቀውን፤የኢትዮጵያ ብሄሮችና ብሄረሰቦች ስብስብ የሆነውን የመከላከያ ሰራዊት ለማውድምና ለማጥፋት ነው ጥቃቱን የሰነዘሩት ፡፡ እነዚህ ሰዎች ከዚህ በኋላ ስለኢትዮጵያዊነት፣ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቢሰብኩ፣ ቢለፈልፉ፣ ቢቀሰቅሱ ማን ጀሮ ይሰጣቸዋል ፡፡ ምክንያቱም ጥቃቱን በጽናት ለመመከት የተዋደቁት ከኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች የተወጣጡ ወታደሮች ናቸው ብለዋል፡፡ ጀኔራሉ በ1980ዓ.ም በወቅቱ ኢህዲን ተብሎ የሚጠራውን ትግል የተቀላቀሉ ናቸው፡፡ከዚሁ ዓመት ጀምሮ ደርግ እስኪደመሰስ ድረስ በተደረጉ ውጊያዎች ተሳትፈዋል።ቆቦ አካባቢ በተካሄደው ሰላም በትግል ኦፕሬሽን፤ሰሜን ሸዋ መራኛ፣ ጁሁርና መራቤቴ አውድ ውጊያዎች ተሳትፈዋል፡፡

እባኮ ይሄንን መረጃ ለሁሉም እንዲደር አጋሩት #ሼር #SHARE
እባኮ ይሄንን መረጃ ለሁሉም እንዲደር አጋሩት #ሼር #SHARE

#ጨረቃና_ጸሃይ_አይወዳደሩም! የራስህን ሕይወት በፍፁም ከማንም ጋር አታወዳድር። ምክንያቱም ብሎ የሚያስቀምጥል ነገር እራስህን ከሌሎች ጋር ስታወዳድር የምታገኘው ውጤት ከዛ ሰው የተሻልክ ከሆንክ #ኩራት ሲሆን ከዛ ሰው የምታንስ ከሆነ ደግሞ #ቅናት ነው የሚሆነው። ሁለቱም መጥፎ ውጤቶች ናቸው ። ጨረቃና ጸሃይ አይወዳደሩም ሁለቱም በጊዜያቸው ደምቀው ያበራሉ ። / ኦሾ /

መንግስት ተሸነፈ...መግደል መሸነፍ ነው... ........ እኔ እንደ ማንም አይደለሁም፣አምነት የጎደለኝ አይደለሁምና አምናለሁ መሪዎቼ ያሉኝን ። ያኔ መስቀል አደባባይ መግደል መሸነፍ ብዬ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥቼ ቦንቡ ስላልገደለኝ አለማሸነፌ አበሳጭቶኝ እሪ እያልኩ ነበር ቤቴ የገባሁት። በመጀመሪያ ኮሮና ቫይረስ ሰው ገደለ ሲባል እንደኔ የጨፈረ አልነበረም ። መግደል መሸነፍ ነዋ። ያው በሕይወት ህግ መሠረት ገዳይ ተሸናፊ ከሆነ ሟች አሸናፊ ነው። አምነት የጎደለው ሕዝብ የሞት ቁጥር ሲሰማ ሲበረግግ እኔ ግን ስጨፍር ነበር። ሰሞኑን ደሞ ኮሮናው ተረስቶ ሞት በአፈሙዝ ሆኗል። መንግስት ደሞ ህዝቡ እንዲያሸንፍ በርትቶ እየሰራ ነው መሠለኝ በርትቶ እያረገፈው ነው። ይባስ ብሎ ወንድም ከወንድሙ ጋር ጦርነት ገጥሟል። አሸናፊም ተሸናፊም የሌለው ከንቱ ነገር። በርግጥ ገዳይ ተሸናፊ፤ተጋዳይ አሸናፊ ነው according to ''LawOfAbiy'' በርግጥ በታሪክ ሞቶ ያሸነፈ አንድ ክርስቶስ ብቻ ነው። እሱም የሞተው መነሳቱን ስለሚያቅ ይመስለኛል።እናም እኔ ግን እላችኋለሁ መግደል እንዴት መሸነፍ እንደሆነ ያላችሁን ጠይቁ። መሞት ግን መሸነፍ ነው!!

ህሊና >ኤፍሬም ስዩም ከጫጫታው መሀል አልነበረም ስፍራው ራሱን ሸሽጎ አልታየም ከቦታው ለስጋ ዘመዱ ህሊና ባዳ ነው እንደ መስጊድ አዛን እንደ ቤተከርስቲያን ደውል ፤ ህሊናም የሚጮህ ሲነጋ ነው መሠል !!

ምኑ ሞኝ ነው ምን ጅሉ ነው ሲሰድቡት ዝም ያለ ሲገሉትም ያው ነው። በሽቄ የጻፍኩት !!

Life has taught me that you can’t control someone’s loyalty. No matter how good you are to them, doesn’t mean that they will treat you the same. No matter how much they mean to you, doesn’t mean that they’ll value you the same. Sometimes the people you love the most, turn out to be the people you can trust the least. @abrhott

#አንዳንድ_ሀሳቦች #ኦሾ ሁለት የካቶሊክ ቄሶች ሌላ ሰው ዝር ባላለበት ጫካ እየገሰገሱ ነው። ብዙም ሳይቆይ ከየት መጣች ሳትባል አንዲት ሴት በነሱ አቅጣጫ ስትጓዝ አዩ። ትንሽ እንደሄዱ እንደልብ የማያሻግር ለመሙላት የቀረበ ወንዝ ገጠማቸው። ይሄን ጊዜ ጣደፍ ብለው ለመሻገር ሲሰናዱ ብቻዋን መሻገር እንደማይሆንላት የተረዳችው ወይዘሮ " አባቶቼ፤ እባካችሁ አቅፋችሁ አሻግሩኝ " ብላ ተለማመጠቻቸው። በዚህ ጊዜ ከቄሶቹ አንደኛው ያለምንም ማንገራገር " የማይሆነውን! የለም። እኔ ሴት ነክቼ መሃላዬም አላፈርስም" ብሎ ጥሏት ሲሻገር፣ ሌላኛው ቄስ ግን ትንሽ አስቦ " እንዴት እዚህ ጥዬሽ ሄጄ እረፍት አገኛለሁ? ነይ በይ !" ብሎ አፈፍ አርጎ አቀፋት እና ወንዙን ካሻገራት በሁዋላ መንገዷ ሌላ ነበርና ተሰነባብተው ጉዞውን ከሌላኛው ቄስ ጋር ቀጠለ። መንገዳቸው ግን ሰላማዊ አልነበረም። ሴቲቱን አላሻግርም ያለው ቄስ አሻጋሪውን ቄስ በየ ደቂቃው ፤ "ሆ!" ..." "ተአምር እኮ ነው መሃላ በየወንዙ እንደ እድፍ ሲተው!" " አይ መጨረሻው ዘመን!" ፤ እያለ በነገር ሲሸረድደው፣ በምፀት ሲያቆስለው፣ በአግቦ ሲውርፈው ሰአታት አለፉ። ከሴቲቱ በተለያዩ ከሰአታት በሁዋላ ግን ንዝንዙ የመረረው ቄስ እንዲህ ብሎ ምላሽ ሰጠ። " ወንድሜ፤ እኔ እኮ ሴቲቱን ተሸክሜ ካወረድኳት አራት ሰአት ሆነኝ። አንተ ግን እስካሁን ተሸክመሃታል" #ሰናይ_ቀን_ተመኘሁ!

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1495ኛው የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል አደረሳችሁ!
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1495ኛው የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል አደረሳችሁ!

የቱጋ ነኝ? """""""""""" "ጭለማ ውስጥ ነበርክ አሁን ግን ነጋልህ" ብለው ያወጉኛል፤ የንጋ አይንጋ ሳላውቅ ባሉኝ ተደምሜ እኔም ደስስ ይለኛል! ግና ፈቀቅ የለም ካሰመርኳት ኑሮ ከቆምኩባት ዓለም ከኢምንቷ እርምጃ ከህይወቴ ቀለም አብበሀል ሲሉኝ ጭራሽ ወደ መክሰም ከከፍታ ሳይሆን ወደ ሽንቁር መክተም እሮጬ ፈርጥጬ ካንዱ ጋ መላተም የነፍሴ አውጪኝ አይነት ከውሀ እንደመስጠም! ግና ፈቀቅ የለም የእውር ድንብር ተፈተለኩ ብዬ የምሄደው ስንዝር የወግ እቴ ኑሮ ከማጡ መዳከር የእንቧይ ክምር መሆን አንዱ ላይ መሽከርከር ብል እንደበላው ጨርቅ ሲነኩኝ መተርተር በጎሳ ቦድኞ እንደሀገር መውተርተር ፆም ውዬ ፆም ማደር! ግና ፈቀቅ የለም ዘላለሙን እንባ መች ጢም ብሎ ይሞላል የሰፈሩት ተልባ እላይ ሲከምሩት ቁልቁል እየገባ አውቃለሁኝ ብዬ በሸኮፍኩት ደባ የእናት ጡት ነካሽ ዝተት የማ'ረባ ከስንዴው እንክርዳድ ከፍሬው ገለባ! ግና ፈቀቅ የለም ለብሶ መድመቅ ርቆኝ በአካላቴ ልክ ቁልቁል ወደኃላ ከእርምጃ ድክ ድክ እንደ አልቦካ እንጀራ ሲነኩኝ መፍረክረክ መቆም እያቃተኝ ሸብርኮኝ ብርክ ብርክ! ግና ፈቀቅ የለም እዪ እንግዲህ ምድሬ አሽመድምዶኝ ጠኔ ሰንፍጦኝ ጠረኔ አልጎድል አልሞላ ከዝብርቅርቅ ቀኔ ግን ነጋልህ ሲሉኝ ተትረፈረፍክ ሲሉኝ ደስ ይለኛል እኔ! ግና የቱጋ ነኝ? አብርሃም ፍቅሬ

የክብር ዶክተር ሎሬት አርቲስት ለማ ጉያ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ! ሰአሊ ሎሬት ሻምበል የክብር ዶክተር አርቲስት ለማ ጉያ ዛሬ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። የክብር ዶክተር
የክብር ዶክተር ሎሬት አርቲስት ለማ ጉያ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ! ሰአሊ ሎሬት ሻምበል የክብር ዶክተር አርቲስት ለማ ጉያ ዛሬ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። የክብር ዶክተር አርቲስት ለማ ጉያ በህክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ92 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡ #tikvahethiopiaBot #tikvahethiopia

#Just ፈታ Don't feel ashamed to fart when urinating. There is no rain without thunder 👀 😂 😂😂😂