cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Show more
Advertising posts
30 385
Subscribers
+5024 hours
+3367 days
+60730 days
Posts Archive
መጋቢት ፳፯ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ መጋቢት ሃያ ሰባት በዚችም ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ። ፈጣሪዋ በዕንጨት መስቀል ላይ ተዘርግቶ ተሰቅሎ በአየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳትለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር። እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋራ አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደሲኦል ወረደች። መድኃኔዓለም ክርስቶስ ስለ ዓለም ሁሉ ድኅነት በሥጋ ተሰቅሏልና ሞቱን በአንክሮ እናዘክር ዘንድ የልቡናችን ዐይን ወደ ቀራንዮ እናንሳ! እነሆ ክፉዎች አይሁድ ሰይጣን ልባቸውን አስቶታልና እንደ ወረንጦና እንደ ወስፌ እንደመርፌም ያለ 300 እሾህ ያለው ስረወጽ አድርገው አክሊል ሠርተው ከፍላት አግብተው በጉጠት አንስተው ‹ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሥ ነህ ዘውድ ይገባሃል› ብለው በራሱ ላይ ደፉበት፡፡ ለአክሊለ ሦኩም 73 ስቁረት ነበረው፡፡ እራሳቸው እንደ መሮ፣ ወርዳቸው እንደ ሞረድ 4 ማዕዘን አሠርተው ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር፣ ስለታቸውን እንደ ወስፌ አድርገው 73 ችንካር ሠርተው በ73ቱ ስቁረት አግብተው በጌታችን በራሱ ላይ ቢመቱበት ሥጋ ለሥጋ ገብቶ መሐል ልቡን ወጋው፡፡ አክሊለ ሦኩን በራሱ ላይ አድርገው ሲያበቁ ከቤት ወደ አደባባይ እያመላለሱ ‹‹ንጉሥ ሆይ!...›› እያሉ ምራቃቸውን እየተፉበት ተዘባበቱበት፡፡ መስቀል አሸክመው ከሊቶስጥራ እስከ ቀራኒዮ ድረስ እያዳፉ ሲወስዱት 136 ጊዜ በምድር ላይ ጣሉት፡፡ ከኋላ ያሉት ‹‹ፍጠን›› እያሉ ገፍትረው ይጥሉታል፣ ከፊት ያሉት ደግሞ ‹‹ምን ያስቸኩልሃል?›› እያሉ መልሰው ገፍትረው ይጥሉታል፡፡ ከዚህ በኋላ ክፉዎች አይሁድ ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር ስለታቸው ደግሞ እንደ ወስፌ የሆኑ 5 ችንካሮችን ሠርተው ሳዶር በሚባለው ችንካር ቀኝ እጁን፣ በአላዶር ግራ እጁን፣ በዳናት ሁለት እግሮቹን፣ በአዴራ መሐል ልቡንና በሮዳስ ደረቱን ቸንክረው የአዳም ራስ ቅል ባለበት ቀራኒዮ አደባባይ ላይ ሰቅለውታል፡፡ ክፉዎች አይሁድ መድኃኔዓለም ክርስቶስን እንደያዙት የኋሊት አስረው አፍንጫውን 25 ጊዜ ቢመቱት ደሙ በመሬት ላይ እንደ ውኃ ፈሰሰ፡፡ ከጌቴሴማኒ እስከ ሐና ቤት ድረስ አስረው የፊተኞቹ ሲጎትቱት የኋለኞቹ እየለቀቁት የኋለኞቹም በተራቸው ሲጎትቱት የፊተኞቹ ይለቁታል፡፤ እንዲህ እያደረጉ 65 ጊዜ ከመሬት ጋር አጋጭተውታል፡፡ ሳውል በእግሩ ሲረግጠው ጌታችን ‹‹መመለስህ ላይቀር ለምን ትረግጠኛለህ?›› ቢለው ስለዚህ ንግግርህ ብሎ ሳውል 440 ጊዜ አስገረፈው፡፡ ክፉዎች አይሁድ መድኃኒታችንን በሁለት ግንዶች መካከል አድርገው 65 ጊዜ ከግንዱ ጋር አጋጩት፡፡ ቀያፋ በሚመረምረው ጊዜ ጌታችን ‹‹አምላነቴን አንተው ራስህ ተናገርኽ›› ቢለው አይሁድ በእጃቸው ሲመቱት እጃቸውን ቢያማቸው ድንጋይ ጨብጠው 120 ጊዜ ፊቱን ጸፉት፡፡ አይሁድ ወደ ጲላጦስ ዘንድ ሲወስዱት ‹‹ምናልባት ጲላጦስ ባይፈርድበት እንኳ እንዳይቆጨን›› ብለው 305 ጊዜ በሽመል ደብድበውታል፡፡ በአምላክነቱ ቻለው እንጂ የአንዱ ምት ብቻ በገደለው ነበር፡፡ በርባን የይሁዳ የሚስቱ ወንድም (አማቹ) ስለነበር እርሱ እንደፊታለትም ከዋጋው ከ30ው ብር ጋር አብሮ ተደራድሮበት ነበር፡፡ ሰይጣን ልባቸውን ለክፋት ያስጨከናቸው ክፉዎች አይሁድ በጲላጦስ አደባባይ የጌታችንን ፂሙን 80 ጊዜ ነጭተውታል፡፡ ጲላጦስ እንደ ሕጋቸው 41 ብቻ ገርፈው እንዲለቁት ቢያዝም ክፉዎች አይሁድ ግን ጌታችንን ሲገርፉት ‹‹አሠቃቂ ግርፋቱን አይተን ልባችን እንዳይራራ›› ብለው ሰንጠረዥ ገበጣ ሰርተው ሲጫወቱ አንዱ ተነስቶ እስከ 60 እና 70 ድረስ ይገርፍና ሲደክመው ‹‹ቆጠራችሁን?›› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ‹‹አልቆጠርንም›› ሲሉት ከድካሙ የተነሣ ‹‹እኔው ልግረፍ እንደገና እኔው ልቁጠር›› ብሎ ትቶት ሲቀመጥ ሌላኛው ይነሣና እንደዛኛው ሁሉ በተራው 60 እና 70 ይገርፈዋል፡፡ ሁሉም እንዲህ እያሳሳቱ የራሳቸውን ሕግ እየተላለፉ አይሁድ ጌታችንን ሥጋው አልቆ አጥንቱ እንደበረዶ ነጭ ሆኖ እስኪታይ ድረስ 6666 ጊዜ ጽኑ ግርፋትን ገረፉት፡፡ በእነዚህ ሁሉ ግርፋቱ ወቅት 366 ጊዜ ሥጋው ተቆርሶ መሬት ላይ ወድቋል፡፡ የመድኃኔዓለም ወገኖች ሆይ! የጌታችን ሞቱ በፈቃዱ መሆኑንና የትዕግሥቱን ብዛት አይተን እናደንቅ ዘንድ ከመጻሕፍት ጠቅሰን እንነግራችኋለን፡፡ አይሁድ ጌታችን አብርሃም ሳይወለድ በፊት እርሱ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን አምላክ መሆኑን ቢነግራቸው ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ፡፡ እሱ ግን ጊዜው ገና ነበርና ተሰውሮአቸው በመካከላቸው አልፎ ሲሄድ በፍጹም አላዩትም ነበር፡፡ በቅዱስ ወንጌል ላይ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡- ‹‹አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፥ አየም ደስም አለው። አይሁድም:- ገና አምሳ ዓመት ያልሆነህ አብርሃምን አይተሃልን? አሉት። ኢየሱስም:- እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ አላቸው። ስለዚህ ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ፤ ኢየሱስ ግን ተሰወራቸው ከመቅደስም ወጥቶ በመካከላቸው አልፎ ሄደ፡፡›› ዮሐ 8፡56-59፡፡ ዳግመኛም በዮሐንስ ወንጌል ላይ እንደተጻፈው አይሁድ መድኃኔዓለምን ሊይዙት የጦር መሣሪያቸውን ሰብስበው ወደ ጌቴሴማኒ በመጡ ጊዜ ‹‹ማንን ትፈለጋላችሁ?›› ቢላቸው ‹‹የናዝሬቱን ኢየሱስን እንፈልጋለን›› ሲሉት ‹‹እኔ ነኝ›› ቢላቸው ከአንደበቱ የወጣውን መለኮታዊ ቃል ብቻ መቋቋም አቅቷቸው መሬት ላይ ወድቀው ተዘርረዋል፡፡ ይህም ክስተት በተደጋጋሚ ተከስቷል፡፡ (ዮሐንስ ወንጌል ላይ ምዕራፍ 18 ከቁጥር አንድ ጀምሮ ይመለከቷል፡፡) እናም የጌታችን ሞቱ በፍጹም ፈቃዱ ባይሆን ኖሮ በጌቴሴማኒ ሊይዙት የመጡት ክፉዎች አይሁድን እንደመጀመሪያው ሁሉ በተሠወራቸው ነበር አሊያም ከአንደበቱ በሚወጣው አምላካዊ ቃሉ ብቻ ባጠፋቸው ነበር፡፡ በመጨረሻ ግን ጌታችን ወደዚህች ምድር የመጣበትን ዓላማ ይፈጽም ዘንድ እንዲገድሉት በፈቃዱ ራሱን አሳልፎ ቢሰጣቸው ያን ሁሉ እጅግ አሠቃቂ መከራ አደረሱበትና ለመስቀል ሞት አበቁት፡፡ ወዮ ለዚህ ለመድኃኒዓለም ፍጹም ትዕግስት አንክሮ ይገባል! ዓለምን በመዳፉ የያዘ አምላክ በአይሁድ እጅ እንደሌባ ተያዘ፡፡ ሠራዊተ መላእክት ለምሥጋና በፊቱ የሚቆሙለት መድኃኔዓለም እርሱ ሊፈረድበት በፍርድ አደባባይ ቆመ፡፡ በእስራት ያሉትን የሚፈታ እርሱ በብረት ችንካር ተቸነከረ፡፡ ሰማይን በከዋክብት ምድርም በአበባ ያስጌጠ እርሱ ግን የእሾህ አክሊል በራሱ ላይ ደፋ፡፡ ዓለሙን ሁሉ በቸርነቱ የሚመግብ እርሱ ተጠማሁ አለ፡፡ ወዮ የመድኃኔዓለም የማዳኑ ምሥጢር ምንኛ ድንቅ ነው!!! ለዚህ ባሕርይው አንክሮ ይገባል፡፡ በመድኃኔዓለም ክርስቶስ ሞት በአንድነት እናለቅስ ዘንድ ቅዱሳን ሁላችሁ ኑ! መድኃኒታችን ሙቷልና ፍጥረታት ሁሉ ያለቅሳሉ፤ መያዝንና መታሠርን የተቀበለ መድኃኒታችን ሙቷልና፡፡ ጥፊንና ግርፋትን የተቀበለ መድኃኒታችን ሞተ፡፡ መደብደብንና መመታትን የታገሰ መድኃኒታችን ሞተ፡፡ ሄኖክ እግዚአብሔር ‹‹በሴም ቤት ይደር›› ብሎ አብ ስለራሱ የተናገረለት የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ አብርሃም ቃልኪዳን የገባልህን
Show all...
👍 11😢 5 3😱 2
የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ይስሐቅ ከሰይፍ ቤዛ የሆነህን የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ያዕቆብ በበረሃ የታገለህ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ኢዮብ በደመና የታየህ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ሙሴ ስለ እርሱ ‹እንደእኔ ያለ ነቢይ ይነሣል› ብለህ የተናገርኽለት የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ዳዊት ‹‹እነሆ በኤፍራታ ሰማነው፣ በበረሃ ዛፍም አገኘነው›› ብለህ የተናገርኽለት የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ኤርሚያስ ‹‹የክቡሩን ዋጋ ሠላሳ ብር ተቀበሉ›› ብለህ የተናገርኽለት የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ኢሳይያስ ‹‹ወልድ ሰው ለመሆን ተገለጠልን፣ ሕፃን ተወለደልን፣ ድንቅ መካር ኃያል አምላክ›› ብለህ የተናገርኽለት የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ሕዝቅኤል ‹‹አምላክ ወደ ተዘጋች ደጃፍ ገባ፣ ከተዘጋች በርም ወጣ›› ብለህ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ዳንኤል ነጭ ሐር ለብሶ ያየኸውን የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ኤልያስ ከሞት በፊት የሰወረህ በእሳት ፈረሶች ያሳረገህ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ሕዝቅያስ የፀሐይ መግባቱን ያሳየህ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ምናሴ ችንካሮችህን ከእግር ብረት የፈታ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ኢዮስያስ ፋሲካውን ያደረግህ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤል ከእሳት ምድጃ ያዳናች የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ኑ፡፡ አብያና ሲላ ፌንቶስ ከመወለዱ አስቀድሞ ያመናችሁበት የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ኑ፡፡ የቀድሞ አባቶች ነቢያት ሁላችሁ ከፋራን ተራራና ከቴማን ይመጣል ያላችሁት የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ኑ፡፡ አሞፅ በአድማስ ቅጥር ያየኸው የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ዘካርያስ በተራራዎች መካከል ያየኸው የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ዕዝራ በአርፋድ በረሃ ያየኸው የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ስምዖን በክንድህ የታቀፍከውን ሕፃን የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ዮሴፍ እንደ አንተ የተሸጠ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ጠራቢ ዮሴፍ በትከሻህ ያዘልከው በክንድህ የተሸከምከው ሕፃን የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ከሕፃንነትህ ጀምሮ በበረሃ ያለ እናት ያለ አባት ያሳደገህ መንገዱንም እንድትጠርግለት ያዘጋጀህና መለኮትን እንድታጠምቅ የመረጠህ የመድኃኒታችንን ሞቱን ታይ ዘንድ ና፡፡ ኢያቄምና ሐና ሆይ የልጃችሁን ልቅሶዋን የልቧንም መዘንጋት ታዩ ዘንድ ኑ፡፡ ከሔዋን እስከ ፋኑኤል ልጅ እስከ ሐና ያላችሁ ሁላችሁ ቅዱሳት ሴቶች የድንግልን ልቅሶዋን ታዩ ዘንድ ኑ፣ አንድ ልጇ ሙቷልና፡፡ የለመለመ የሥጋ ሞት ሕንፃ የተጀመረበት የአቤል ተከታዩ፣ ከጎኑ የፈሰሰው ደም ሔዋንን ከጥፋት ያዳናት የተገደለ መድኃኒታችን ነው፡፡ የናቡቴ ጓደኛው የተገፋው መድኃኒታችን ነው፡፡ አቤል ስለሚስቱ ሞተ፡፡ ናቡቴም ስለ ወይኑ ቦታ ሞተ፡፡ መድኃኒታችን ግን በቀኙ ያነጻት ዘንድ ስለቤተክርስቲያን ሞተ፡፡ ነፍሳችሁን ይወስዷታልና መውረዱንም አላወቁምና ስለ ወገኖቹ ኃጢአት እስከ ሞት ደረሰ ብሎ ስለ እርሱ የተናገረ አባቱን እንስማው፡፡ ሙሴም እርሱን ያውቁት ዘንድ አላሰቡትም፣ በሚመጣበት ቀንም አላወቁትም አለ፡፡ ዕዝራ በባሕር ጥልቅ ያለውን ማወቅ እንዳይችሉ ወልድንም ማወቅ እንዲሁ ሆነባቸው አለ፡፡ ጳውሎስም ብታውቁትስ ኖሮ የክብርን ጌታ እግዚአብሔርን ባልሰቀላችሁት ነበር አለ፡፡ በመሰደድ፣ ያለምንም በደልም በፍርድ አደባባይ በመቆም መከራ መስቀልን በመሸከም አብነት የሆናችሁ ሰማዕታት ሁላችሁ ኑ የመድኃኔዓለምን የሞቱን ዕለት አስባችሁ በጋራ አልቅሱለት፡፡ ሁሉ የእርሱ ከእርሱ ለእርሱ ተፈጥሮ ሳለ በምድር ላይ ምንም ሳይኖረው ራሱን እንኳን የሚያስጠጋበት ቤት ሳይኖረው አብነት የሆናችሁ ባሕታውያንና መነኮሳት ሁላችሁ ኑ በዛሬዋ ዕለት ስለሞተው አምላካችሁ መሪር ዕንባን አልቅሱለት፡፡ ሕግ ጠብቆ፣ ሥርዓት አክብሮ፣ ነዳያንን በመመገብና ያዘኑትን በማጽናናት 33 ዓመት በምድር ላይ ኖሮ አብነት የሆናችሁ እናንት በዓለም ሆናችሁ ሕግ ጠብቃችሁ፣ አሥራት በኩራቱን አውጥታችሁ፣ ድሆችን በመርዳት የምትኖሩ ክርስቲያኖች ሁላችሁ የመድኃኔዓለምን የሞቱን ዕለት ታስቡ ኑ፡፡ ‹‹የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና›› ብሎ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደጻፈልን (1ኛ ጴጥ 2፡21) እርሱ ንጹሕ ባሕርይ ሲሆን ወደ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ ወደ ዮርዳኖስ በመሄድ ለተጠመቅን ለእኛ ለተነሣሕያን ለሁላችን አብነት የሆነን መድኃኒታችን ስለእኛ ሞቷልና ሞቱን እናስብ ዘንድ ኑ በቤቱ ተሰብስበን እናልቅስለት፡፡ መታሰያውንም እናድርግለት፡፡ ጌታችን ሞቶ ተቀብሮ ካረገ በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያትና ለቅዱሳን አባቶቻችን ለእነ አቡነ መባዓ ጽዮን፣ ለእነ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እንደነገራቸው የሞቱን መታሰቢያ የሚያደርግ ኃጠአተኛ እንኳ ቢሆን ሲኦልን አያያትም፡፡ የመድኃኔዓለምን የሞቱን መታሰቢያ የሚያድርግ ቢኖር ሲኦል ራሷ አፍ አውጥታ ‹‹ይህችን ነፍስ ወደኔ አታምጡብኝ›› ብላ ትጮሃለች እንጂ ችላ አትቀበለውም፡፡ የጌታችን ወዳጆቹ ዮሴፍ ኒቆዲሞስ በድርብ በፍታና በመቶ ወቄት ሽቱ ገንዘው በሐዲስ መቃብር ሊቀብሩት ቢሉ ጌታችን ያን ጊዜ ዐይኑን ክፍቶ ‹‹በሰውነቴ መዋቲ ብሆን በመለኮቴ ሕያው ነኝ እንጂ ምነው እንደ እሩቅ ብእሲ ዝም ብላችሁ ትገንዙኛላችሁን?›› አላቸው፡፡ ይህን ጊዜም ዮሴፍ ኒቆዲሞስ በታላቅ ድንዳጤ ሆነው ‹‹አቤቱ ጌታችን ሆይ! እንግዲያስ ምን እያልን እንገንዝህ?›› አሉት፡፡ መድኃኒታችንም እንዲህ እያላችሁ ገንዙኝ አላቸው፡- ‹‹ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት ዘተወልደ እማርያም እምቅድስት ድንግል ተሣሃለነ እግዚኦ፡፡ ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት ዘተጠምቀ በዮርዳኖስ ወተሰቅለ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሣሃለነ እግዚኦ፡፡ ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት ዘተንሥአ እሙታን አመ ሣልስት ዕለት ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ወነበረ በየማነ አቡሁ ዳግመ ይመጽእ በስብሐት ይኰንን ሕያዋነ ወሙታነ ተሣሃለነ እግዚኦ› እያላችሁ ገንዛችሁ ቅበሩኝ አላቸው፡፡›› ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን ለወዳጆቹ ለ12ቱ ሐዋርያት፣ ለ72ቱ አርድእት፣ ለ36ቱ ቅዱሳት አንስት ‹‹እስከ ሦስት ቀን እነሣላችኋለሁ እዘኑ አልቅሱ፣ እህል ውኃ አትቅመሱ በሏቸው›› ብሎ ለዮሴፍና ለኒቆዲሞስ አክፍሎት አስተማራቸው፡፡ ዳግመኛም መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከዕርገቱ በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት የሞቱን መታሰቢያ እንዲያደርጉ ነግሯቸዋልና፡፡ ሕማሙንና ሞቱንም እንዲዘክሩ አዟቸዋልና አሁንም ያንን ሁሉ የመድኃኔዓለምን ሞቱን ያላሰበና የሞቱን መታሰቢያ በዓል ያላከበረና እርሱንም የማይወደው ቢኖር ዕድል ፈንታው ጽዋ ተርታው ከአይሁድ ጋር ነው፡፡ የአምላካችንን የመድኃኔዓለምን ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ተባብረን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ከእርሱ ለመተባበር ያብቃን። @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 13 6😢 2
የ250 MB ዳታ ጥቅል ሽልማት Challenge 🎁 ቻናላችንን ወደ ወዳጅ፣ ዘመድ፣ ጓደኛ በብዛት Share ለሚያደርጉና ለሚያስተዋውቁ የተዘጋጀ የሁለት ቀናት ዳታ ጥቅል ሽልማት። https://t.me/Ethiopian_Orthodox https://t.me/Ethiopian_Orthodox 👆ይህን ሊንክ: 💎ለ50 እና ከዚያ በላይ ሰው Share ለሚያደርጉ 👉250MB 💎ለ35+ ሰው Share ለሚያደርጉ👉 200MB ይሸለማሉ። Share ያደረጉበትን ማስረጃ Screenshot በማድረግ በ @Ethiopian_Orthodox_bot ለሚልኩ ሽልማታችን ይደርሳቸዋል። ውጤቱን በDiscussion ግሩፓችን ይፋ የምናደርግ ይሆናል።
Show all...
14👍 5🤩 4😱 2😢 1
ሌሊት ያጠቃሃል፡፡    ሐ. ሌላው ከሕልመ ሌሊት ለመዳን ዋነኛው መፍትሔ ውኃ በብዛት አለመጠጣት ነው:: ይህን መንገድ መከተል ጥሩ መፍትሔ መሆኑን መጽሐፈ መነኮሳት ሲመሰክር «ወአልቦ ዘያየብስ ዓባለ ወይከልእ እምሕልም ወነቅዓ ፈሰስ ወያኅድዕ ሕሊናተ ደነስ በመዓልት ከመ ጽምእ» ይላል፡፡ ይህም «እንደ ውኃ ጥም አካልን የሚያደርቅ፣ ከሕልመ ሌሊትና ከዘር መፍሰስ የሚከለክል፣ በመዓልት ሐልዮ ኃጢአትን የሚያጠፋ የለም።› ማለት ነው:: (ፊልክ.ክፍ.3 ተስእ.38)    ስለዚህ አንድ ሰው ምንም ቢጾም አመጋገቡንም ቢቀንስ አብዝቶ ውኃ የሚጠጣ ከሆነ አይጠቀምም፡፡ ለምን ቢባል ሰውነቱ ስለሚለመልምና ሰይጣን እርሱን ለማሳት መንገድ ስለሚያገኝ ነው፡፡ ስለሆነም ከሕልመ ሌሊት ለመዳንና እፎይ ለማለት ከፈለግህ ጹም፣ አመጋገብህንም በልክ አድርግ። በተለይ ግን «ወአጽብብ ላዕሌከ እምሰትየ ማይ» ማለትም «ውኃን ከልክለህ ሰውነትህን አስጨንቀው» ተብለሃል፡፡ (ፊልክ.ክፍ.3 ተስእ.38)    ቅዱስ ወንጌልም ከላይ የተጠቀሰውን ሲያጠናክር እንዲህ ይለናል፡- «ርኩስ መንፈስ ግን ከሰው በወጣ ጊዜ ዕረፍት እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል፥ አያገኝምም:: በዚያን ጊዜም ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፥ ቢመጣም ባዶ ሆኖ ተጠርጎና አጊጦ ያገኘዋል፡፡» ማቴ12፥43-45 የዚህ ቅዱስ ወንጌል ቃል አንድምታ ብዙ ነው፡፡ ስለሆነም ከያዝነው ሐሳብ ጋር ተዛማጅ ያልሆኑትን ትተን የሚዛመደውን አንድምታ ብቻ መመልከት ይኖርብናል፡፡ «ርኩስ መንፈስ ግን ከሰው በወጣ ጊዜ ዕረፍት እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል>> ማለት ሰይጣን መግቢያ ካገኘው ብሎ ሰውነቱን በረኃብ በጥም ወደሚያስጨንቅ ሰው ይሄዳል ማለት ነው:: ይልቁኑም «ውኃ በሌለበት» ማለቱን መዘንጋት የለብንም:: «አያገኝምም» የሚለው ቃል ደግሞ ሰይጣን ሰውነቱን በውኃ ጥም በሚያስጨንቅ ሰው ላይ ለማደር አለመቻሉን ያሳያል፡፡ ስለዚህ ውኃን አብዝቶ አለመጠጣት ሰይጣን በሕልመ ሌሊት እንዳይፈትነን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ማለት ነው፡፡ የወንጌሉን ቃል በዚህ መልኩ የተረጎመው መጽሐፈ መነኮሳት ሰይጣን በሕልመ ሌሊት እንዳይፈትነን ውኃ አብዝቶ ከመጠጣት መቆጠብ እንደሚያስፈልግ ይናገራል፡፡    መ. በሕልመ ሌሊት በተደጋጋሚ እንዳትጠቃ ወደ ዝሙት ከሚያመራ ማናቸውም ነገር ሽሽ:: በመሽ ጊዜ የምታያቸውን ፊልሞች፣ ንባቦች፣ ሌሎችንም ነገሮች በጥንቃቄ መርምረህ ለፍትወት የሚያጋልጡትን ሽሻቸው፡፡ ከዚያ ይልቅ ደጋግ መንፈሳዊ መጻሕፍቶችን ለማንበብ ትጋ። ጠንክሮ መጸለይንም አትተው እንዲህ በማድረግህ ከእግዚአብሔር ዘንድ ረድኤትን ታገኛለህና፡፡   ከላይ የተጠቀሰውን የሕፃን መነኩሴ ሕይወትና የአባ ኢሳይያስን ምክር ተግባራዊ አድርግ:: ነገረ ዝሙትን በልቡናህ አታጣጥም፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን እንደ ተናገረው «ከሥራ ብዛት ሕልም ያታያልና» መክ5፥3 ብዙ የተመኘኸውም ነገር በሕልም ቢመጣ የሚያስደንቅ ነገር አይደለም፡፡ ስለዚህ ፍትወትን ጊዜ ሰጥተህ በልቡናህ አታጣጥመው፡፡ አፍህ «ይህን ነገር አርቅልኝ» እያለ ይጸልያል፤ ልቡናህ ግን ከዝሙት ጋር ተጣብቆ ይውላል፡፡ እግዚአብሔር ሥራ እንዲሠራልህ ከፈለግህ አንተ ራስህ አንድ ፈቃድ ይኑርህ፡፡    ሠ. ከመኝታህ በፊት ጠግቦ ላለመብላት ሞክር፡፡ ትኩስና የሞቁ ነገሮችን ላለመውሰድ ተጣጣር:: እንዲህ ያደረግህ እንደ ሆነ ቅዱስ ዳዊት «በሰላም እተኛለው አንቀላፋለሁ» እንዳለ አንተም የሰላም እንቅልፍ ትተኛለህ፡፡    ረ. ሌላው መፍትሔ ደግሞ ከመንፈሳዊ መምህራንና ከአበው ካህናት ጋር እየተማከሩ በሚያቀርቡት የመፍትሔ ሐሳብ መጓዝ ነው:: ነገር ግን በዚህ ጊዜ ሊጠነቀቁበት የሚገባ አንድ ነገር አለ፡፡ ይኸውም የምናማክረው ሰው ምሥጢራችንን ለመያዝ የታመነና በምንነግረውም ነገር ራሱ ወደ ፈተና ሊገባ የማይችል በሕይወቱ ብዙ ተሞክሮ ያለው መሆን ይኖርበታል::    ለዚህም መጽሐፈ መነኮሳት ሲመሰክር እንዲህ ይላል፡፡ «በከመ ኮነ በአሐዱ እምነ አኃው፡፡ በእንተ ዘኮነ ተቃትሎተ አሕላመ ኃጢአት ዘሰይጣናት ምስለ ፍቁሩ፡፡ እስመ ውእቱ ሖረ ምስሌሁ ኀበ በአቱ ከመ ይርድኦ:: ወኮነ ተቃትሎተ አርኩ ላዕሌሁ ዘይፈደፍድ እምኔሁ፡፡» ይላል:: ይህም «ከወንድሞች መካከል በአንዱ እንዲህ ሆነበት፡፡ ወዳጁን ሰይጣናት የሚያሳስቡት ሕልመ ኃጢአት በታሰበው ጊዜ እረዳዋለሁ ብሎ ከወዳጁ ጋር ወደ በአቱ ሄደ፡፡ የመንፈሳዊ ወንድሙ ፈተና ወደ እርሱ ከዚያኛው ይልቅ በዝቶ መጣበት::» ማለት ሲሆን ለምን እንዲህ እንደሆነ ምክንያቱን ሲያብራራ ደግሞ «ወሶበ ተኃሠሡ አዕሩግ በእንተ ዝንቱ ረከብዎ ዘኢፈጸመ ዓዲሁ በእንተ ተቃትሎተ ሥርዓቱ» በማለት ይደመድማል:: ይህም በአማርኛ «የዚህን ነገር ምሥጢር አበው በመረመሩ ጊዜ ያ ሰው ሕልመ ሌሊትን ለመቃወም የማይችልና ገና ከፍጹምነት ያልደረሰ ሆኖ አገኙት>> እንደ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ነገረ ጾታን በተመለከተ ካልበሰለ ሰው ጋር መማከር በሁለቱም በኩል ጉዳቱ ያመዝናል፡፡ (ፊልክ.ክፍ.7 ተስእ.98)    ሰ. ምንም እንኳን ሙሉ በሙሉ ከሕልመ ሌሊት መጽዳት ባይቻል ብዙ ፋታ ማግኘት ግን ይቻላል፡፡ ለዚህም ምስክር የሚሆን ቃል ከመጽሐፈ መነኮሳት እንዲህ ይነበባል፡፡ ‹‹ወሦበ አንጽሐ ልቦ በውስተ ጸብእ ሶቤሃ ይደልዎ ከመ ይትመጦ በመዓልትኒ ሕሊናተ ኀድአተ ወንጽሕተ ወበሌሊትኒ አሕላማተ ንጽሕተ ወጽሪተ» ይህም «አጋንንት በሚዋጉበት ጊዜ ልቡናውን ያነፃ ያን ጊዜ በቀን ንጹሕና የረጋ ሐሳብን በሌሊት ደግሞ ንጹሕና ጥረት ያለ ሕልምን ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል›› ማለት ሲሆን፤ ይህም ንጹሕ መኝታ ለማግኘት በቀንና በሌሊት ብርቱ ተጋድሎ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የሚያስረዳ ነው፡፡    ከባሕሪያችን ደካማነት የሚመነጨውን <<ጸዋግ ሕልም>> ሙሉ በሙሉ ማስወገድ ባይቻለን በራሳችን ከንቱ ሙከራና ጥረት ተስቦ የሚመጣውን ግን መከላከል እንችላለን፡፡ ሰይጣን ሳይተኛ እንደሚፈትነን ሁሉ እኛም ሳንሰንፍ አጸፋውን መመለስ እንደሚጠበቅብን ማስተዋል ይገባናል፡፡        ከእነዚህ የመፍተሔ ሐሳቦች ውጭ ለሕሊናችን የመጣልንን ሌላ የግላችንን ጎዳና መከተል ምናልባት የሚያስከትለው ችግር ስለሚኖር መጠንቀቅ ይበጃል:: የምንወስደው እርምጃ ከመንፈሳዊ ጽንሰ ሐሳቦች ጋር የሚጋጭ እንዳይሆን ከመንፈሳዊ መምህምራን ጋር መመካከር አስፈላጊ ነው፡፡     ሌላው ደግሞ አንዳንድ የቀበሮ ባሕታዊያንና መሪጌታ ተብዬዎች ሕልመ ሌሊት ለሚያስቸግረው ሰው <<ጥሩ መፍትሔ አለን>> እያሉ ሲያጭበረብሩ ይገኛሉ፡፡ ስለዚህ «ሥራይ» በማድረግና ‹‹ልፋፈ ጽድቅ» እንጽፋለን በማለት የብዙዎችን ቤት ከማራቆታቸውም በላይ የሰው ልጅን ነፍሱን ምትሐታዊ በሆነ ድጋማቸው ሥጋውን ደግሞ በማይታወቁ ሥራሥሮቻቸው ሲያስሩት፣ ሲያሳምሙትና አጋንንትን ሊያቆራኙት ማየት እጅግ ያሳዝናል:: ስለዚህ ወጣቶች ይህን ተረድተው እንዲህ ካሉ አጭበርባሪዎች መጠንቀቅ ይኖርባቸዋል::    ለዚህ ችግር ይሄኛው የጸሎት ዓይነት ለዚህ ደግሞ ይሄኛው ይበጃል ማለት የአጭበርባሪዎች ፈሊጥ እንጂ የመጽሐፍ ቅዱስ ዐዋጅ አይደለም:: የለመንነው ነገር እንዲሰማልን ከፈለግን ግድ ልዩ ልዩ የጸሎት ዓይነቶችን ማወቅና መድገም አይጠበቅብንም፡፡ ጸሎትን ተሰሚ የሚያደርገው በእምነትና ሳይሰለቹ ዘወትር መጸለይ ነው እንጂ አሳምሮ መጸለይ አይደለምና:: ሉቃ18፥1-11 በእርግጥ በጠራ መልኩ ቤተ ክርስቲያን የምታስተምራቸውን ብዙ የጸሎት ዓይነቶችን ማወቅ የሚነቀፍ ነገር አይደለም:: ለእያንዳንዱ ጉዳይ የራሱ የሆነ ጸሎት ስላለው «ያንን ካላወቅሁ ዋጋ
Show all...
👍 9 7🙏 2
የለኝም!» ማለት ግን ስሕተት ከመሆኑም ባሻገር በቀጣፊዎች እጅ ለመውደቅ ይዳርጋል:: በመሆኑም ለ<<ሕልመ ሌሊት>> የሚሆን ልዩ ተአምራታዊ ድጋም እንደ ሌለ ዐውቆ አቅም በሚፈቅደው ሁሉ ተግቶ መጸለይ ያስፈልጋል፡፡ በቀጣይ ምዕራፍ ፬፦ "<<ግብረ አውናን(Masturbation)>> ምንድር ነው?" በሚል ርዕስ ይቀጥላል... ለአስተያየትና ጥያቄዎቻችሁ @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ። @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
10👍 3🙏 1
Photo unavailableShow in Telegram
ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት) ምዕራፍ ፫/3 ክፍል ፪/2 .....................................................................          «ዝንየት»ና መንፈሳዊ ሥርዓቱ   1) ከላይ «ጸዋግ ሕልም>> ኃጢአት የሚሆንበትና የማይሆንበት ሁኔታ መኖሩን ተመልክተናል፡፡ ከሁለቱ ሁኔታዎች በየትኛውም መንገድ ቢሆን «ጸያፍ ሕልምን›› ያየ ወይም ዝንየት ያገኘው ሰው በዚያው ዕለት ሥጋ ወደሙ መቀበል (መቊረብ) አይችልም፡፡ አንድ ሰው ሌሎች ለቁርባን የሚደረጉ ዝግጅቶችን ያሟላ ቢሆንም ሕልመ ሌሊትን በማየቱ ብቻ ቅዱስ ቁርባንን ለመቀበል ብቁ አይሆንም፡፡    በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለ የሚከለከለው ከቅዱስ ቁርባን ብቻ አይደለም:: ወደ ቤተ ክርስቲያን ከመግባትም ይከለከላል:: ለመግባት የሚፈቀድለት ልብሱን ካጠበ ወይም ከቀየረና ገላውን ከታጠበ በኋላ በማግስቱ ነው፡፡ (ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ገጽ 24)    ስለ ወር አበባ በሚያትተው አንቀጽ እንደ ተገለጸው ሁሉ ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት አይቻልም ሲባል ወደ ቤተ መቅደስ መግባት አይቻልም ማለት እንደሆነ ግልጽ ነው::
ስለዚህ ወደ ቤተ መቅደስ አይግባ እንጂ የመጀመሪያውን ቅጽረ ቤተክርስቲያን ዘልቆ በመግባት ጸሎት፣ ትምህርትና የመሳሰሉትን መንፈሳዊ ተግባራት በዕለቱም ቢሆን ሊያከናውን ይችላል፡፡
Show all...
👍 15 5
   ቅዱስ ዳዊት «ጽዮንን ክበቧት እቀፏትም» በማለት እንደተናገረው በበዓል ቀናት ቤተክርስቲያንን ከቦ ማደር የተለመደ ነው:: በአንድ ወቅት ለበዓል ወደ ቤተክርስቲያን ከመጡት ሰዎች መካከል ጥቂቶቹ በተክርስቲያን ውስጥ ተኝተው ሳለ «ሕልመ ሌሊት» ታይቷቸዋል:: በዚህ ጊዜ መልዐከ እግዚአብሔር ከእንቅልፋቸው ሳይነቁ ከቤተክርስቲያን አውጥቶ አርቆ ከውጭ አስተኝቷቸዋል:: ሰዎቹም በነቁ ጊዜ «ሕልመ ሌሊት» እንደ መታቸው ከቤተ ክርስቲያንም የእግዚአብሐር መልአክ እንዳወጣቸው አስተዋሉ፡፡ ይህ ታሪክ በእመቤታችን የተአምር መጽሐፍ ተጽፎ የሚገኝ ሲሆን «ሕልመ ሌሊት» ያገኘው ሰው ወደ ቤተ መቅደስ መግባት እንደሌለበት ተግባራዊ ትምህርት ያስተላልፋል፡፡ በተጨማሪ በመኝታ ወቅት ሕልመ ሌሊትን ጨምሮ ልዩ ልዩ ነገሮች ሊከሠቱ ስለሚችሉ በቤተ መቅደስ መኝታ ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡    መንፈሳዊ መጻሕፍትን የመረመረ ሰው ይህን የመሰለ ብዙ ታሪክ ያገኛል።
በቤተ ክርስቲያን የአፍንጫን ዛሕል እንፍ ማለት ነውር እንደሆነ ሁሉ በሕልመ ሌሊት ተይዞ ሳለ ወደ ቤተ መቅደስ መግባትም እንዲሁ ነው::
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ምራቃቸውን እየወረቁ ከዘበቱ አይሁዳዊያን ጋር እንዳትቆጠር በሕልመ ሌሊት ተነውረህ ሳለ ወደ ቤተ መቅደስ ተደፋፍረህ አትግባ፡፡ ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ የምታገኘውን ፀጋ ሥርዓቷን ለማክበር ብለህ ከቤተ መቅደስ በአፍአ (በውጭ) ብትቆምም አታጣውምና፡፡    2) የፍትሕ መንፈሳዊ አንድምታ መጽሐፍ ስለ ጸሎት በተናገረበት አንቀጽ ከመኝታ ተነሥተው ስለሚፈጸሙ ጸሎተ ነግህ እና ጸሎተ መንፈቀ ሌሊት እንዲህ ብሏል:: «ይጸልዩ እምድኅረ ተሐጽቡ እደዊሆሙ በማይ ወለእመ ኢረከቡ ማየ በውእቱ ጊዜ ይንፍሑ እንደዊሆሙ ወይሕጸቡ በምራቅ ዘይወጽእ እም አፋሆሙ::» ይህም «የነግሁንና (የንጋቱንና) የመንፈቀ ሌሊቱን ጸሎት እጃቸውን ከታጠቡ በኋላ ይጸልዩ በዚያ ሰዓት ውኃ ባያገኙ እፍ ብለው በአፋቸው በሚወጣው ምራቅ እጃቸውን አሸሽተው ያማትቡ» ማለት ነው፡፡    ይህ የፍትሕ መንፈሳዊ የጸሎት ሥርዓት ሐዋርያት በአጥሊስ ያስተማሩትና የደነገኑት ሲሆን መጽሐፈ ሰዓታትም መግቢያ አድርጐታል፡፡ መጽሐፈ ሰዓታት እንትፍ በማለት እጅን ማባበስ የሚሰጠውን ጥቅም ሲያትት «ወትከውን ንጹሐ እም ርዕስከ ወእስከ እገሪከ ዝ ውእቱ አምኃ መንፈስ ቅዱስ››፤ «ይህ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ነውና ከራስህ እስከ እግርህ ድረስ ንጹሕ ትሆናለህ» በማለት ይናገራል፡፡ በሌላም ስፍራ <<እስመ ማየ ዮርዳኖስ ይወጽእ እም አፉከ>> እንደተባለው ሁሉ ካልተጠራጠሩ የዮርዳኖስ ውኃ ከአፍ ሊገኝ ይችላልና፡፡    ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ ከመኝታ ተነሥተው ስለሚፈጸሙ ሁለቱ የጸሎት ጊዜያት መተጣጠብ ያም ባይሳካ ምራቅን እንተፍ ብሎ መተሻሸት አስፈላጊ የሆነበትን ምክንያት ሲያትት፦<<ሰው ከተኛ ዝንየት አይጠፋምና›› በማለት ይገልጻል:: ምናልባት ዝንየት ሊያገኘው ስለሚችል ተብሎ ሰው ሁሉ ከመኝታው በኋላ የሚያደርገውን ጸሎት ተጣጥቦ እንዲጸልይ ከታዘዘ ዝንየት እንዳገኘው እርግጠኛ የሆነ ሰው እንዴት የግድ መተጣጠብ ያስፈልገው ይሆን? አንዳንድ መምህራንና አባቶች በመኝታ ልብስ ጸሎት እንዳናደርግ የሚከላከሉትም በዚሁ ምክንያት ነው፡፡    3) ከዘር መንጠብ ጋራ ተያይዞ የተሠራው ይህ ሦስተኛ ሥርዓት ባልና ሚስትን ብቻ የሚመለከት ነው፡፡ ሩካቤ ያደረጉ ባልና ሚስት መተጣጠብን ምክንያት በማድረግ ከመጸለይ ወደ ኋላ ማለት የለባቸውም:: ሩካቤያቸው ንጹሕ ስለሆነ መላ አካላችንን ካልታጠብን አንጸልይም አይበሉ፡፡ ለባልና ለሚስት ዘር የወጣበትንና የነጠበበትን አካል ማለትም ኀፍረተ አካልን ብቻ መታጠብ ይበቃቸዋል፡፡ ይህ ሐሳብ በግዕዙ «ወኢይኅሥሡ ተሐፅቦ በቤተ ብለኔ ዘእንበለ ተሐፅቦ ዕድ ባሕቲቱ እስመ ሰብሳቦሙ ንጹሕ ውእቱ» ይላል::    «ተሐፅቦ ዕድ ባሕቲቱ» ማለት «እጅን መታጠብ ብቻ» ማለት ነው:: ባልና ሚስት «እጅን መታጠብ ብቻ» ይበቃቸዋል ማለት ወንድ አባለ ዘሩን ሴቲቱ ደግሞ አፈ ማኅፀንዋን መታጠባቸው ብቻ ይበቃቸዋል ማለት ነው። ኀፍረተ አካል በመንፈሳዊ መጻሕፍት «እጅ» ይባላልና:: ለምሳሌ:- ‹‹ሕፅውኒ ኢገብረ አበሳ በዕዴሁ» የሚል ኃይለ ቃል ይገኛል:: ይህም ‹‹ጃንደረባም በእጁ በደል የለበትም>> ማለት ሲሆን «እጅ» ተብሎ የተተረጐመው ኀፍረተ አካል ነው:: ጃንደረባ አባለ ዘርዕ የለውምና በሌላ ካልሆነ በቀር በአባለ ዘሩ በደል የለባትም እንደ ማለት ነወ:: ስለዚህ ባልና ሚስት ምቹ ሁኔታ ካለቸው ከጸሎት በፊት መላ አካላቸውን መታጠባቸው የሚመረጥ ቢሆንም የሚጠበቅባቸው ግን ዘር የወጣበትንና የነጠበበትን ኀፍረተ አካል መታጠብ ብቻ ነው::    ይህ ሥርዓት ለሚስቶች ቀላል ይመስላል፡፡ ምክንያቱም የግብር ውኃን መጠቀም በሴቶች ዘንድ የተለመደ በመሆኑ ነው:: ታዲያ ባሎች በሩካቤ ማግስት መላ ገላን መታጠብ ምቹ ባልሆነበት አጋጣሚና ቦታ ለጸሎት ከመቆማቸው በፊት ቢያንስ ንዑስ መሌሊታቸውን (ኀፍረተ አካላቸውን) መታጠብ እንዳለባቸው ያወቁ ኖሯል? ይህ አማራጭ ሥርዓት የተሠራው ሩካቤያቸው ንጹሕ በመሆኑ ለባልና ለሚስት ብቻ ነው እንጂ ሕልመ ሌሊት ላገኛቸው ላላገቡ ወጣቶች አይደለም፡፡ ያላገቡ ወጣቶች ሕልመ ሌሊት ሲያገኛቸው መላ ሰውነታቸውን መታጠብ አለባቸው፡፡        «ሕልመ ሌሊት» መፍትሔ አለው?    ብዙ ሰዎች ተግቶ ለመጸለያ፣ ለማስቀደስና፣ ለመቁረብ በወሰኑ ጊዜ ሕልመ ሌሊት እንቅፋት እየሆነ ይፈተኑበታል፡፡ በእርግጥ መብላትና መጠጣት ሳያቆሙ ሙሉ ለሙሉ ከሕልመ ሌሊት መለየት አስቸጋሪ ከመሆኑም በላይ የሚቻል ነገር አይደለም:: ለተአምራት ያህል ከሕልመ ሌሊት ፈጽሞ የተለዩ አንዳንዶች ነበሩ፡፡ ለምሳሌ፡- በተአምረ ማርያም ላይ በልጅነቱ የመነኮሰ አንድ ሕፃን ነበር፡፡ ወደ ወጣትነትም በሚሸጋገርበት ጊዜ ለመጀመሪያ ጊዜ ድቀት አገኘው፥ ድቀቱም በሕልሙ ነበር፡፡ ዝንየት መታው ማለት ነው፡፡ ከመኝታው በነቃ ጊዜ ግን ነፍሱን «የፍትወትን ጣዕም ዛሬ ቀምሰሻልና ወዮልሽ›› እያለ ይወቅሳት ጀመረ፡፡ ስለ መጪው ዘመኑ ወደ እመቤታችን በፍርሃት እየጸለየ ማለደ እንጂ በገጠመው ነገር ተደንቆ ደስ ስላልተሰኘ በእመቤታችን አማላጅነት ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሕልመ ሌሊትን ሳያይ ኖረ።    ሀ. አባ ኢሳይያስ የተባለ መነኩሴ በመጽሐፈ መነኮሳት ስለ ሕልመ ሌሊት እንዲህ ብሏል:: «ለእመ ወረደት ላዕሌክ በሌሊት ሕልመ ጽምረት ኢትዝክራ በመዓልት» ይህም «ሌሊት በሕልም ከሴት ጋር የተገናኘህ መስሎኽ ዘር ቢወርድህ በመዓልት አታስባት» ማለት ነው:: እንዲህ ማድረግህ ደግሞ በሕልም የተመለከትከውን በእውን እያሰብከው ደስታ ከማድረግ ይጠብቅሃል፡፡ ሕልምህን ደስ እየተሰኘህበት መላልሰህ ብታስበው ግን በነቢብና በገቢር ወደ መፈጸም ያደርስሃል፡፡ ስለዚህ ከሕልመ ሌሊት ፈተና ለመዳን አንዱ መፍትሔ ሕልምን በውን ደስ እየተሰኙ መላልሶ አለማሰብ ነው፡፡    ለ. ሕልመ ሌሊት በምታይበት ጊዜ ከነቃህ ቸል ብለህ ተመልሰህ አትተኛ «አላ ተንሥእ ፍጡነ» ፣ «ፈጥነህ ተነሥ እንጂ» እንደተባለው ፈጥነህ ተነሣና ተጣጥበህ ጸሎት አድርስ:: ከተቻለህ ስገድ ባይቻልህ ግን የባሕሪህን ድካም ፈጣሪህ ያውቀዋልና ይቅር በለኝ፣ እርዳኝ፣ አድነኝ፣ እያልክ ወደ እግዚአብሔር ለምን:: እንዲህ በማድረግህ የሰይጣንን መንገድ ትዘጋበታለህ፡፡ ቸል ብለህ ብትተኛ ግን አንድ ጊዜ መንገድ ሰብሮ የሄደ ውኃ ካልዘጉበት በቀር በመጣ ቁጥር በዚያው እንደሚመላለስ አንተንም ሰይጣን እንዲሁ መላልሶ በሕልመ
Show all...
👍 9 7🙏 1
"መጻጉዕ" ሰው የለኝም ያለ በሰው የተረሳ፣ የዳነው መጻጒዕ ያዳነውን ረሳ። በአምስቱ እርከኖች በአዕማደ ሚስጥራት፣ ቤተ ሳይዳ ላለች ከመቅደስ ላኖርካት፣ በበደል ለምናዝን ምሕረትን ፍለጋ፣ በንሰሐ ማረፍ ከዐራተ ዝንጋኤ ከኃጢአት አልጋ። አዝ= = = = = በጠበሉ ደጃፍ ለጸኑት የሚላክ፣ ለቀድሶተ ማይ የሚወርደው መልአክ፣ በመንገድ ጠብቆ ሞትን የሚያሳልፍ፣ ዛሬም ይድረስልን ቀድመው ከገቡት ጋር ነፍሳችን እንድታርፍ። አዝ= = = = = አልጋው ተሸክሞት ደክሞ ለሚጨነቅ፣ አልጋን አሸክመህ ሕመም የምታርቅ፣ ደዌያችንን ነስተህ ቆስለህ የምትፈውስ፣ የመጻጒዕ ረዳት የነፍሳት መጠጊያ መድኃኒት ክርስቶስ። አዝ= = = = = የባሰ እንዳያየው ቃሉን ያልጠበቀ፣ እጁን ሰዶ ጸፍቶ ከደዌው ታረቀ፣ 'ሰንበት የሻረ' ከሚሉት እንዳንውል፣ ለትንሣኤው ደስታ የሰንበትን ጌታ አርብን እንከተል። በዘማሪ ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 25 20🥰 16
መጻጉዕ የዐብይ ጾም አራተኛ እሑድ(ሳምንት) መጻጉዕ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ላይ ታሪኩ የተጻፈው ለ፴፰ ዓመት አልጋ ላይ ተኝቶ የኖረ በቤተ ሳይዳ/በቤተ ዛታ ስፍራ ይዞ የመልአኩ መምጣት ፤የውሃው መባረክ፤ የውሃው መናወጥ እና ድኅነቱን በተስፋ የሚጠብቅ ግን ድኅነቱ በሳምንት አንዴ እርሱም አንድ ሰው ብቻ ስለሆነ የሚያገኘው ይህን እድል ማግኘት ያቃተው ተሸክሞ ወደ ውሃው የሚያደርሰው በተባረከ ጊዜ እንዲድን የሚያግዘው ሰው አልባ ህመምተኛ ነው። ጌታችንም ወደ ቤተ ሳይዳ መጥቶ የልቡን ሃሳብ ያውቃልና "ልትድን ትወዳለህን?" አለው ጌታችን መጻጉ የሚፈልገው ጠፍቶት ሳይሆን 'ሙሉ ሰው ነህና መስክር ፍላጎትህ ከአንደበትህ ይውጣ' በሚል ነው። ይህም ታማሚ እዛጋ ለብዙ ዘመን ያየው የነበረው በሰዎች ተረድተው ወደ ተቀደሰው ውሃ ገብተው ድነው ሲወጡ ነበርና ብቸኛ መሆኑን መዳን እየቻለ ግን ወደ ውሃው የሚያደርሰው ጎረምሳ ስለፈለገ "ሰው የለኝም" አለ። አንድም ጌታችን ገና የ፴ ዓመት ወጣት ነበርና 'ተሸክሞ ያደርሰኛል' ወይም ከርሱ ጋር ብዙ ሰዎች ነበሩና 'ሰው ቢያዝዝልኝ' በሚል ሰው የለኝም አለ። ጌታችንም "ለ፴፰ ዓመት አልጋህ አንተን ተሸክማለችና አሁን ተነስ አልጋህን ይዘህ ሂድ" አለው። ያላሰበው ደስታ አደናግሮት ማን እንደ አዳነው እንኳን ሳያውቅ ነበረ የተነዳው በዚህም ገጠመኝ በሰንበት ስራ አይሰራም የሚሉ አይሁዶች ያዙትና "እንዴት በሰንበት አልጋ ትሸከማለህ?" ብለው ያዙት ፴፰ አመት ሲተኛ ግን ማንም አልጠየቀውም። "ያዳነኝ እርሱ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለኝ" ብሎ መለሰላቸው። "ማን ነው ያዳነህ?" ይህ ምላሽ እርሱ ባይመልስም ለእነርሱ ግልጽ ነው በዛ ሰአት ከእርሱ ከመድኃኔዓለም ውጪ እንዲህ አይነት ተግባር የሚሰራ አነበረምና። መጻጉ በውስጡ ዘወትር ማን ነው ያዳነኝ የሚለውን ጥያቄ አንግቦ ጌታም በመቅደስ አግኝቶት "ኃጢአትህ ተሰርዮልኻል ግን ዳግመኛ ከዚ በላይ እንዳያገኝህ ደግመህ አትበድል" ሲለው ምስክር አይሉት ፈጥኖ ሄደና ለአይሁድ "ያዳነኝ እርሱ ነው" ብሎ ተናገረ። ሕማማተ መስቀል ላይ አባቶቻችን የጌታ ፊት በጥፊ ጸፍቶታል ይላሉ። ከ፴፰ አመት በላይ አልጋ ላይ የነበረውን "ከዚህ በላይ እንዳያገኝህ" ሲል 'ሲኦል እንዳትገባ ከዚ የከፋ ስቃይ እሳት እንዳያገኝህ ደግመህ አትበድል' ሲል ነው። እኛ ስንቶቻችን ዳግማዊ መጻጉዕን ሆነናል!?: በቤቷ ኖረን፣ የስጋችን ፈውስ ከፀበል ከእምነቱ ተደባብሰን ድነን፣ ለነፍሳችን ንስኃ ከአባቶች አግኝተን፣ ስጋውንም በልተን ደሙንም ቆርሰን ዛሬ ግን ከእርሷ ርቀን፣ በውሸት መስክረን ሁለተኛው ንጉስ ገንዘብን ያነገስን ዳግማዊ መጻጉ ሆነን የተገኘን! ዛሬ ካለው መከራ የባሰ የወደፊቱ የቆየው መከራ ሳያገኘን ሮጥ ብለን እንድናመልጥ አምላካችን ይርዳን። በዚህ ሳምንት መጻጉዕ ብቻ ሳይሆን ጌታችን በመዋለ ስጋዌ ዘመን ያዳናቸው ድውያን ሁሉ ይታወሳሉ። እኛም የስጋ የነፍስ በሽታ አለብንና እርሱ በቸርነቱ ይታደገን ይፈውሰን አሜን። በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ ጥቅሶች፦ -ገላ ፭፥፩ እስከ ፍጻሜ -ያዕ ፭፥፲፬ እስከ ፍጻሜ -የሐዋ ሥራ ፫፥፩-፲፪ ምስባኩም፦ መዝ ፵፥፫-፬ "እግዚአብሔር ይረድኦ ውስተ ዐራተ ሕማሙ ወይመይጥሎቱ ኩሎ ምስካቤሁ እምደዌሁ አንሰ እቤ እግዚኦ ተሣህለኒ" "እግዚአብሔር በደዌው አልጋ ሳለ ይረዳዋል መኝታውን ሁሉ ለበሽታው ጊዜ ያነጥፍለታል እኔስ አቤቱ ማረኝ" ወንጌሉም፦ ዮሐ ፭፥፩-፳፭ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
26👍 9🥰 2🙏 2😢 1
በዐፍላ ጉርምስና ወቅት ፈጣን ዕድገት ከሚያሳዩና ከሚለጠጡ የሰውነት ክፍሎች መካከል የድምፅ ጅማቶች ስለሚገኙበት አንዳንድ ጊዜ ሳይታሰብ «ቀጭን» ድምፅ ማውጣትና የድምፅ መጎርነን እንደ ጉርምስና ምልክት ይታያሉ፡፡ የአዳም ፍሬ በመባል የሚታወቀው ‹‹ማንቁርትም» ማደግና መታየት የሚጀምረውም በዚሁ ጊዜ ነው፡፡ ከዚህም ሌላ ብዙ ወንዶች ብጉር የሚያበጉሩ ሲሆን፣ በብብት፣ በደረትና በብሽሽት (በአባለ ዘርዕ) አካባቢ ፀጉር ማብቀል ይጀምራሉ፡፡ እንደዚሁም ከራስ እስከ ጽሕም በግራና በቀኝ የሚወርድ ለጊዜው ለስለስ ያለና ስስ ጠጉር ወይም ሪዝ ማቆጥቆጥ ይጀምራል፡፡ ይህንን ጽሕም (ሪዝ) መከርከምና መቀነስ እንጂ ሴት እስኪመስሉ ድረስ ሙሉ በሙሉ ልጭት አድርጐ ማንሣት የሚገባ አይደለም፡፡ ይህን በተመለከተ ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊና ዲድስቅልያ የተሰኙ መጻሕፍት እንዲህ ብለዋል፡፡ «ወባሕቱ ኢመፍትው ለነ ንላጺ ጽሕመነ ወኢንወልጥ ፍጥረተ ብእሲ ውስተ ካልዕ ግዕዝ - ነገር ግን ጽሕማችንን ልንላጭ የወንድነት መልካችንን ወደ ሌላ ማለትም ሴት ወደ መምሰል እንለውጥ ዘንድ አይገባንም::›› ማለት ነው:: ዲድ.አን.1፤ ፍት.መን.አን .11 የጉልምስና ምልክት የሆነው የዚህ ጠጉር ብዛት ከሰው ሰው ይለያያል:: ሆኖም ምን ያህል <<ወንድ>> መሆንን አመልካች አይደለም:: ሌለቹ የዐፍላ ጉርምስና ምልክቶች ደግሞ የሰውነት ጠረን መለወጥ፣ የዘር ፍሰት ወይም ሕልመ ሌሊት ማየት መጀመር ናቸው፡፡ «ሕልመ ሌሊት» ምንድር ነው? በዐፍላ የጉልምስና ወቅት አባለ ዘርዕ ወደ ሙሉ የዕድገት ደረጃ መድረስ ብቻ ሳይሆን መሥራትም ይጀምራል:: በዚህ ጊዜ ከንዑስ መሌሊት (ኀፍረተ አካል) ዘርዓ ብእሲ የሚባል የአፍንጫ ዛሕል (ንፍጥ) የሚመስል ፈሳሽ ነገር ይወጣል፡፡ ወንድና ሴት ግንኙነት በሚያደርጉበት ጊዜ ወደ ሴቲቱ ማኅፀን በመግባት ፅንስ እንዲፈጠር የሚያደርገው ይህ ፈሳሽ ንጥረ ነገር ነው፡፡ የወንድ ወጣቶች ሰውነት ይነስም ይብዛ በየጊዜው ከላይ ‹‹ዘርዓ ብእሲ›› ወይም «የወንድ ዘር» ተብሎ የተጠቀሰውን ፈሳሽ ንጥረ ነገር ያስወጣል፡፡ ለዘር የበቁ ወጣቶች ዘር የሚከፍሉት ወይም የሚወጣቸው በልዩ ልዩ መንገድ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ግን ተኝተው ሳለ በጠለቀ እንቅልፍ ሆነው ሕልም በሚያልሙበት ወቅት ነው፡፡ ይህ ሲሆን እንደ ጤናማ የተፈጥሮ ሂደት ይቆጠራል። የዚህ ዓይነቱን ሕልም መጽሐፈ መነኮሳት በአንድ ስፍራ «ሕልመ ጽምረት» በሌላ ቦታ ደግሞ «መስቆርርት ሕልም» ሲለው ይገኛል:: ሕልሙን ያየው ሰው ደግሞ «ዝንየት መታኝ» ወይም «ሕልመ ሌሊት» አገኘኝ ይላል፡፡ ይህ በቤተ ክርስቲያን ልጆች ዘንድ የተለመደና በቀላሉ የሚያግባባ የቃል አጠቃቀም ነው:: ወደ አቅመ አዳም እየደረሱ ባሉ ልጆች ላይ ይህ «የዘር ፍሰት» ባልጠበቁት ጊዜ ሲከስት በጣም ሊረብሻቸው ይችላል፡፡ ይልቁኑም ልጆቹ ከዚህ አስቀድሞ ስለ ጉዳዩ በተለያየ መንገድ በቂ ግንዛቤ ያላገኙ ከሆኑ መረበሻቸው በእጅጉ ይጨምራል፡፡ እነዚህ ታዳጊዎች እንዳይረበሹና ስለ ጉዳዮ የተሳሳተ ሐሳብ ይዘው እንዳያድጉ ለነገሩ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ ከማድረግ ጋራ እንደ አስደሳች ተግባር በመውሰድ እያወቁ ዘራቸውን በራሳቸው እጅ ማፍሰስ እንዳይጀምሩ የነአውናንን በዚህ ተግባራቸው መቀሠፍ እየጠቀሱ ኃጢአትነቱን ኣጥብቆ ማስረዳት ያስፈልጋል:: መጽሐፍ ቅዱስ ስለ <<ዘር መውጣት>> እና በአጠቃላይ <<ፈሳሽ ነገር>> ስላለበት ሰው በዝርዝር ይናገራል፡፡ ዘሌ.15፥16፡ 15፥1-33  ይህንን ጨምሮ የወንድ ዘርን የሚመለከት ሐሳብ የያዙ መንፈሳዊ መጻሕፍቶችን ማንበብ ለወጣቶች የተሻለ ግንዛቤ ይሰጣቸዋል፡፡ ይህን በመሳሰሉ ፆታዊ ጉዳዮች ላይ ወጣቶች ጥያቄ ሲኖራቸው ከማን ጋር መወያየት የተሻለ እንደሚሆን ሊለዩ ይገባል፡፡ ልጆች የሚጓዙበት ተፈጥሮአዊ የሕይወት ጐዳና በሙሉ ጤናማ ወላጆች የተጓዙበት ስለሆነና ሌሎችም ብዙ ተሞክሮዎች ስላሏቸው ለልጆች ፆታዊ ችግር ጉዳት የሌለበት የመፍትሔ ሐሳብ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ ካህናትና መምህራነ ቤተ ክርስቲያንንም ማማከር ለወጣቶች መንፈሳዊውን ሥርዓት እንዲያውቁ ይረዳቸዋል፡፡ እኩዮችንና ሌሎች ወጣቶችን ወይም የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቃል መሠረት ያላደረጉ ጽሑፎችን መስማትና ማንበብ ጥቂት እውነትና ብዙ የፈጠራ ወሬ ያለበትን የተሳሳተ መረጃ በመስጠት ወጣቶችን ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ ሊመሯቸው ይችላሉና ሊጠነቀቁባቸው ይገባል፡፡ «ሕልመ ሌሊት» ኃጢአት ነውን? በጠለቀ እንቅልፍ ላይ ሳሉ የሚከሠት ሕልመ ሌሊትን እንደ ኀጢአት እንዲቆጠርና እንዳይቆጠር የሚያደርጉ የተለያዩጨሁኔታዎች አሉ:: ስለዚህ ሕልመ ሌሊትን በጥቅሉ ኀጢአት ነው ወይም አይደለም ማለት አይቻልም፡፡ ነገር ግን እንደ ኀጢአት እንዲቆጠር የሚያደርጉ ሁኔታዎችን በመጠኑ መዘርዘር ይቻላል፡፡ ሀ. አጋንንት የሰው ልጆችን በልዩ ልዩ መንገድ ክፉኛ ይዋጓቸዋል፡፡ የሰው ልጆች ሲያንቀላፉ አጋንንት ግን ለቅጽበት እንኳን እያሸልቡም፡፡ ያንቀላፋውን ሰው እስኪነቃ ድረስ እንኳን አይጠብቁትም: አጋንንት የሰውን ልጅ በተኛበት ክፉ ክፉ ሕልም በማሳየት ይፈትኑታል፡፡ አንድ ጊዜ የተራቆተ የሴት ገላ፣ በሌላ ጊዜ ደግሞ እንደ ወንድና ሴት አለሌና ባዝራ እየሆኑ ሲጨዋወቱና ሲደራረጉ በምትሐት ያሳዩታል፡፡ በዚህ ጊዜ እርሱም በዝሙት ሐሳብ ይሳብና በሕልሙ ዝሙት ሲፈጽም ያድራል፡፡ በዚህ መልኩ የተከሠተ ሕልመ ሌሊት «ጸዋግ» ወይም «ኅሡም» ሕልም ይባላል፡፡ ክፉ ወይም ጥፉ ሕልም ማለት ነው:: በዚህ መልኩ አጋንንት ሰውን እንደሚዋጉት በመጽሐፈ መነኮሳት እንዲህ ተጽፏል፡፡ «ይትቃተልዎ ሰይጣናት በመዓልት በሕሊናት እኩያት ወበሌሊት በአሕላማት ኅሡማት» በአማርኛ «ሰይጣናት የሰውን ልጅ ቀን ቀን ክፉ ሐሳብ በማሳሰብና በማሠራት በሌሊት ደግሞ ዝሙት የሞላበት አስጸያፊ ሕልም በማሳየት ይዋጉታል» ማለት ነው፡፡ በዚህ መልኩ ሰይጣናት ያቀረቡለትን ረቂቅ ፈተና ከመቃወም ይልቅ ደስ እያለው የሚያጣጥም ማለትም ከመጸጸትና ከመቆጨት ይልቅ በደስታ ስለ ዝሙት የሚያሰላስል፣ የሚዳራ፣ የሚዛለል፣ ወደ ዝሙት ከሚያመሩ ማናቸውም ነገሮች የማይሸሽ ሰው እነዚህ ነቅቶ ሳለ ያልተቃወማቸውን ተግባራት በሕልሙ በሚፈጽማቸው ጊዜ በተግባር እንደፈጸማቸው ያህል ኃጢአት ሆነው ይቆጠሩበታል:: ይህን የሚያስረዳ እንዲህ የሚል የመጻሕፍት ቃል ይገኛል:: «ዘይትቄበል በመዓልት ስሕተታተ ፍትወት ውስተ ልቡ ወኢይከሥታ ወለዝንቱ ሕሊናቲሁ ወአሕላማቲሁ ወፍትወታቲሁ ርኩሰት ትትሐሰብ ሎቱ ኃጢአተ» ይህም ‹‹በቀን ነቅቶ ሳለ ኃጢአትን ወዶ የሚቀበልና ገልጾ የማይናዘባት ለዚያ ሰው የረከሰች ሐሳቡ፣ ሕልሙ ኃጢአት ሆና ትቆጠርበታለች፡፡» ማለት ነው፡፡ በተጨማሪም <<ወኢይጻሙ ውስተ ንስሐ ወኢየኀሥሥ እም እግዚአብሔር ሥርየተ አበሳቲሁ በቀዳሚ ወለዝንቱ አሕላማቲሁ መስቆርርት ትትሐሰብ ሎቱ ኃጢአተ::›› ወደ አማርኛ ሲመለስ <<በንሥሐ ሥራ የማይደክም (ንስሐ የማይገባ)፣ በቀደመው ኃጢአቱ እግዚአብሐርን ይቅር በለኝ የማይለው ለዚያ ሰው የሚያጸይፉ ሕልሞቹ ዕዳ በደል ሆነው ይቆጠሩበታል::» ማለት ሲሆን ይህ የሆነበት ምክንያት ሰውዬው የነዚህ ሥራዎች ተቃዋሚ ባለመሆኑ ነው፡፡ ይህም ንስሐ ባለመግባቱ ይታወቃል:: እነዚህን ኃጢአቶች የማይቃወም ሰው ደጋፊ ስለሆነ በነዚህ ኃጢአቶች ለምን እጠየቃው ለማለት አይችልም፡፡
Show all...
👍 23 9😢 2
በገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም ላይ ተጽፎ የሚገኝ አንድ መንፈሳዊ ታሪክ አለ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን የእመቤታችን የድንግል ማርያም በዓል በሚከበርበት ዕለት ቅዳሴ ለመቀደስ የተዘጋጁ አንድ ካህን ነበሩ፡፡ እኚኽ አባት ማታ ተኝተው ሳለ አንድ ጋኔን በሴት አምሳል አብሯቸው በማደር ሕልመ ሌሊት እንዲያገኛቸው አደረገ፡፡ ከመኝታ ሲነቁም ቅዳሴ መግባት የማያስችል እንቅፋት እንደገጠማቸው ስላወቁ በእርሳቸው ቦታ ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም ተተክተው ቅዳሴውን አከናውነዋል፡፡ የገድላቸው መጽሐፍም የእመቤታችን ፈቃድ ቅዳሴውን አቡነ ሀብተ ማርያም እንዲቀድሱት ነበረ በማለት በግልጽ ይተርካል፡፡ ይህ ሁኔታ የተፈጸመው ስለ አቡነ ሀብተ ማርያምም ክብር ሲባል ነው። አቡነ ሀብተማርያም በእመቤታችን በድንግል ማርያም ዘንድ ምን ያህል ተወዳጅ እንደሆኑ ያሳያል:: ከዚህ አልፎ ግን “ያኚኽ ካህን ምን በደል ቢገኝባቸው ነው» ማለት አይቻልም፡፡ እንዲህ ማለት በሰው መፍረድ ነውና፡፡ መጽሐፈ ገድሉም ካህኑ እንደዚህ ያለ በደል ነበረባቸው ብሎ የሚጠቅሰው ምንም ነገር የለም፡፡ ያልተጻፈውንና የማናውቀውን መናገር በእግዚአብሔር ሥራ ገብቶ እንደ መተቸት ይቆጠራል፡፡ ይህ ታሪክ በሕልመ ሌሊት በሚፈተኑ ሰዎች ላይ እንዳንፈርድ ይልቁኑም በሌላ አቅጣጫ ማየት የሚገባን ነገር እንዳለ ያስረዳል፡፡ በቀጣይ «ዝንየት»ና መንፈሳዊ ሥርዓቱ ይቀጥላል.... @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
31👍 23🥰 4
ከሥራ ብዛት ሕልም እንደሚታይ ጠቢቡ ሰሎሞን «ሕልም በሥራ ብዛት ይታያል» በማለት የተናገረው ቃል ያስረዳል፡፡ መክ5፥3 እንደዚሁም ሁሉ ከምኞት ብዛትም ሕልም ሊከሠት ይችላል:: ክፉ ምኞት በሕልምም ቢሆን ማርከሱ አይቀርም፡፡ ሐዋርያው ይሁዳ «እያለሙ ሥጋቸውን ያረክሳሉ» በማለት የጻፈው መልእክት እዚህ ቦታ ላይ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ይሁዳ 1፥ (ቁ8) እንደሚታወቀው ነፍስ እንደ ሥጋ አትተኛም እንቅልፍም በእርሷ ዘንድ የለም:: ስለዚህ ነፍስ በእንቅልፍ ልቤ ነው በማለት ማመካኘት አትችልም፡፡ ነፍስ በረከሠ ሕልም ምክንያት ከተጠያቂነት ነፃ መሆን የምትችለው ሥጋ ከእንቅልፍ ውጭ በሚሆንበት ጊዜ ተግባረ ዝሙትን በመቃወምና በመጥላት ከእግዚአብሔር ጋር መሆኗን ስታስመሰክር ብቻ ነው፡፡ ሌላው ሕልመ ሌሊትን እንደ ኃጢአት የሚያስቆጥረው ሁኔታ አብዝቶ መመገብ ነው:: ጾም ለጽድቅ ሥራ ሁሉ መሠረት እንደሆነ እንደዚሁ አብዝቶ መመገብም የኃጢአት ሁሉ መሠረት ነው:: <<እኅልም ጉልበትን ያጠነክራል>> ተብሏልና፡፡ ሰው ሁሉ ለቁመተ ሥጋ ያህል መመገብ ያሻዋል፡፡ መዝ103፥15 ሆኖም ለልዩ ልዩ የምግብ ዓይነቶች መጐምጀትና ከዚያም አልፎ አብዝቶ መመገብ ነፍስን ለሥጋ ማስገዛት ነው:: ይህ ደግሞ ገዥዋን ተገዥ ማድረግ በመሆኑ ግፍ ነው፡፡ ሊቀ ጳጳስ ለዐቃቢት እንደመገዛት ያህል ነውና፡፡    ለሥጋ መገዛት የሚያሻውንም ሁሉ ጥሮ ግሮ ማቅረብ የገዛ ሰውነትን ማምለክ ነው፡፡ ሐዋርያው «ሆዳቸው አምላካቸው ነው፡፡» በማለት የተናገረው «እንብላ እንጠጣ ነገ እንሞታለን» በማለት ከሞት በኋላ ተከትሎ የሚመጣባቸውን ወቀሳና ፍርድ ችላ ላሉ ሰዎች ነው፡፡ በአዳምና በሔዋን ሊነገር የማይችል ውርደትና ጉስቁልና ያመጣባቸው ለሆዳቸው መገዛታቸው ወይም ለመብል መሳሳታቸው መሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ፊልጽ3፥19፣ 1ቆሮ 15፥32፡ ዘፍ3፥ 1-24 ወጣቶች ይልቁኑም በዝሙት ሥራና ሐሳብ በእጅጉ የሚፈተኑ ስዎች በሚገባ መጾም አለባቸው:: በሰውነት ላይ የዝሙት ፆር ጸንቶ ሳለ አብዝቶ መመገብ የሚቃጠል ክርን ሰም እንደ መመገብ (መቀባት) ነው:: ሰም ክሩን የበለጠ እንደሚያቀጣጥለው አብዝቶ መመገብም የዝሙት ፍላጐትን የበለጠ እንዲበረታ ያደርገዋል፡፡ መጽሐፈ መነኮሳትም ይህን ሲገልጽ <<መብዝኀ መባልዕትኒ ምስለ ኃይለ ውርዝውና ያስተዳልው ምጽአተ ሕማማት በኃይል፣ አብዝቶ መመገብ ከወጣትነት ጋር የኃጢአት ሐሳብን በግድ እንዲመጣ ያደርጋሉ» ይላል፡፡ (ማር ይስ አን.20 ምዕ.1) አብዝቶ መመገብና ለመብል መሳሳት የኃጢአት ምንጭ ከመሆናቸው ባሻገር በራሳቸው ኃጢአት ሆነው ይቆጠራሉ፡፡ የሰዶም ኃጢአት አብዝቶ መመገብና ጠግቦ መብላት እንደ ነበር መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር፦ «እነሆ የእኅትሽ የሰዶም ኃጢአት ይህ ነበረ፡ ትዕቢት፣ እንጀራን መጥገብ፣ መዝለልና ሥራ መፍታት በእርስዋና በሴቶች ልጆቿ ነበረ>> ይላል:: «እንጀራን መጥገብ›› ኃጢአት መባሉን ተመለከትክን? ሕዝ16:49 ስለዚህ በልክ ተመገብ እንጂ ለስስት አትሽነፍ፡፡     ሳይጠነቀቅ ቀርቶ አብዝቶ ከመመገቡ የተነሣ ሕልመ ሌሊት ያገኘው ሰው እንደ ኃጢአት ይታሰብበታል፡፡ ምክንያቱም አብዝቶ መመገብ ኃጢአትን እንደሚወልድ እያወቀ ችላ ብለሎ በመመገቡ ነው፡፡ መጽሐፈ መነኮሳት አብዝቶ ከመመገብ የተነሣ ሕልመ ሌሊት ስለሚከሠትበት ሰው እንዲህ በማለት ይተርካል፡፡ «ወመንጸፈ ኅርትምናሁስ ወልብሱ ወትፍግዕተ ሥጋሁ ኩለንታሁ ርሱሕ፡፡ በእንተ ብዝኀ ውኂዝ ርኵስ ዘይውኅዝ እም ሥጋሁ ከመ ዐይነ ማይ አኮ በሌሊት ባሕቲቱ ዘይመጽእ ዝንቱ እስመ ሥጋ ያውኀዝ ወትረ ወያረኩሶ ለሕሊና›› ወደ አማርኛ ሲመለስ «ከሰውነቱ እንደ ምንጭ የሚነቃ ርኩስ ዘር በዝቶ ስለ ፈሰሰ ጎስቋላ ምንጣፉ፣ልብሱ፣በዝሙት ደስ የተሰኘ ሥጋው ሁለንተናው የረክሰ ነው:: ሥጋ ሁልጊዜ ያነቃዋልና ዘሩ የሚፈሰው በሌሊት ብቻ አይደለም፡፡ ሕሊናውንም ያረክሰዋል›› ማለት ነው፡፡ ይህም ለምግብ ከመሳሳትና አብዝቶ ከመመገብ የተነሣ የሚመጣ ሕልመ ሌሊት እንዴት ሰውን እንደሚያረክስና ኃጢአት ሆኖ እንደሚቆጠርበት ያስረዳል:: ማር.ይስ. አን.20 ምዕ.2 አንድ ሰው በንቁ ልቡና ሳለ ወደ ኃጢአት የሚየመሩትን ነገሮች ተግቶ እየተቃወመ ነገር ግን በተኛና ባንቀላፋ ጊዜ ዝንየት ቢያገኘው በተራክቦ፣ ዘር በማፍሰስ ያያት ሕልሙ ዕዳ ሆና አትቆጠርበትም፡፡ መሐሪ የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውዬው ተቃወማት እንጂ ወዶ ወደ እርሷ እንዳልተሳበ ያውቃልና፡፡ አንቀላፍቶ ላለ ዘሩ ቢወርድ ፈልጎ አለመጣውምና ዕዳ አይሆንበትም፡፡ ነገር ግን ተቃውሞ ለማራቅ አልተቻለውም:: ይህ ከዚህ በላይ የሰፈረው ሐሳብ በግዕዙ እንዲህ ይነበባል። <<ወዘሰ ይትጋደል ሕሊናተ እንተ የሀውክዋ ሰይጣናት ውስተ ልቡ በመዓልት ወዝኒ አሕላማቲሁ መስቆርርት ዘበሐሊመ ስዕበት ኢትትሐሰብ ሎቱ ኃጢያተ፡፡ እስመ እግዚአብሔር ጻድቅ ወመሐሪ የአምር እስመ ውእቱ በጊዜ ፈቂዶቱ ኢተሰፍጠ በፍትወት አላ ተቃተላ ወሰደዳ፡፡ ወለእመኒ ወረደት ላዕሌሁ በጊዜ ንዋሙ ኢየሐስባ ላዕሌሁ ኃጢያተ እስመ ውእቱ ኢተቀበላ በፈቃዱ ወኢኮነ ክሀሌ ለተጋድለሎታ ወሰዲዶታ ወአርኅቆታ::>> ኃጢአትን ከልቡ በሚቃወምና በሚጠላ ሰው ላይ ሕልመ ሌሊት እንደ ኃጢአት እትቆጠርበትም፡፡ ይህን ለማስረዳት አረጋዊ በፊልክስዮስ መጽሐፍ እንዲህ የሚል ሐተታ አስፍሯል፡፡ ሰይጣን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን:- የኔን ወገኖች አጋንንትን ባንተ ወገኖች ላይ አሰለጥናቸዋለው፣ ነገር ግን ወገኖቼ የአንተን ወገኖች አይችሏቸውምና ድል ይሆናሉ:: እነርሱ ምንም ባይችሏቸው እኔ ግን «በሕልመ ሌሊት አስሕቶሙ» «በሕልመ ሌሊት አስታቸዋለሁ።» አለው:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ለሰይጣን እንዲህ ሲል መለሰለት <<ለእመስ ድቀት ይወርስ አባሁ ዛቲኒ ትትሐሰብ ኀጢአተ ላዕለ እሊአየ።» ትርጓሜውም <<ጭንጋፍ አባቱን ለመውረስ ከቻለ ሕልመ ሌሊትም በወገኖቼ ላይ ዕዳ ሆና ትቆጠርባቸዋለች» ይህም ማለት ተስዕለተ መልክዕ ያልተፈጸመለት ጭንጋፍ አባቱን መስሎና አህሎ ባለመገኘቱ የአባቱ የሆነውን ነገር መውረስ እንደማይቻለው እንደዚሁም በተግባር ያልተፈጸመች ሕልመ ሌሊትም እንደ ተግባር ኃጢአት ተቆጥራ አታስኮንንም ማለት ነው፡፡ : አረጋዊ እንዲህ ማለቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስና ሰይጣን ከሕልመ ሌሊት አንጻር ያላቸውን ፈቃድ ለማስረዳት ፈልጐ ነው እንጂ ሰይጣን ደፍሮ ኢየሱስ ክርስቶስን ተናግሮት ኢየሱስ ክርስቶስም እንዲህ ተዋርዶ ለዲያብሎስ መልስ ሰጥቶት አይደለም:: ይህ ቃለ ምልልስ በመጽሐፈ ኢዮብ ምዕራፍ አንድ ላይ እና በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አራት ላይ ከሰፈረው የሰይጣንና የእግዚአብሔር ንግግር ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ በሕልመ ሌሊት በተደጋጋሚ የሚፈተን ሰው በቅርብ እናውቅ ይሆናል:: እንዲህ ባሉ ሰዎች ላይ መፍረድ ተገቢ አይደለም፡፡ ለምን ቢባል ጥፋት ሳይገኝባቸው በዚህ መልኩ የሚፈተኑ ብዙ ሰዎች ስለሚገኙ ነው:: እኛም ብንሆን በዚህ ፈተና እንዳንወድቅ መጠንቀቅና መጸለይ ይገባናል፡፡ በሰው መፍረድ ራስን ወደ ወጥመድ ማስገባት ነውና፤ በሰው ከመፍረድ ለሚፈተን ለዚያ ሰው መጸለይ በእጅጉ ይበልጣል፡፡ ሰው ራሱ በራሱ ላይ ይህን የመሰለ ፈተና ማምጣቱን እየመረመረ ኃጢያተኛ ነኝ ቢል ተገቢ ነገር ነው:: ሌሎች ግን በእርሱ ላይ ቢፈርዱበት ኃጢአት ሠሩ ማለት ነው:: ፈጣሪ በሌላው እንድንፈርድ አይፈልግምና፡፡
Show all...
👍 16 11🙏 2
Photo unavailableShow in Telegram
.                      ምዕራፍ ሦስት              የዐፍላ ጉልምስና ምልክቶች     ዐፍላ የጉርምስና ወቅት የጉልምስናን የመጀመሪያ ወቅት ይሸፍናል፡፡ ጉልምስናና ጉርምስና የሚሉት ቃላት አንድ ናቸው። የዘይቤ እንጂ የምስጢር ልዩነት የላቸውም፡፡ ይህ ወቅት በፆታ የመብሰል ምልክቶች የሚታዩበት ዕድሜ ነው፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው ጉልምስና የሚጀምርበት ዕድሜ እንደየሰዉ ሁኔታ ከፍና ዝቅ ሊል ስለሚችል የኔ ፈጥኗል የኔ ደግሞ ዘግይቷል በማለት ሊጨነቁበት የሚገባ አይደለም፡፡ የሆነው ሆኖ አንድ ሰው በጉልምስና ወቅት ሊከሠቱ ከሚችሉ የአካል ለውጦች ጋር ተያይዘው የሚከሠቱ ሌሎች ለውጦችንበሚገባ ሊያውቃቸውና ሊጠብቃቸው ይገባዋል:: እነዚህም ለውጦች በአጭሩ ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል፡፡   በጉልምስና ወቅት ከሚከሠቱ የአጥንቶች ዕድገትና የጡንቻዎች መለጠጥ የተነሣ በወጣቶች ላይ የመፍዘዝና የቅንብር ጉድለቶች ይስተዋላሉ:: በዚህ ምክንያት ለአደጋ መጋለጥ እንዳይኖር ተጨማሪ ጥንቃቄ ቢያስፈልግም ይህ ዓይነቱ የመቅዘዝና ቅስስ የማለት ሁኔታ ጊዜውን ጠብቆ ያልፋልና የሚያሳስብ ጉዳይ አይደለም:: ወጣቶች በብዙኀኑ ዘንድ የሚታወቁበት ገጽታ ንቁነትና ቀልጣፋነት ቢሆንም በአፍላ የጉልምስና ወቅጥ መፍዘዝና ቅስስ የማለት ሁኔታ መከሠቱን ማወቅ ለሚያሳዩት ባሕርይና ያልተለመደ እንቅስቃሴ ሌላ ትርጓሜ ከመስጠት እንድንቆጠብ ይረዳል፡፡
Show all...
👍 12 6😢 1
Do you enjoy reading this channel? Perhaps you have thought about placing ads on it? To do this, follow three simple steps: 1) Sign up: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox 2) Top up the balance in a convenient way 3) Create an advertising post If the topic of your post fits our channel, we will publish it with pleasure.
Show all...
2👍 1🔥 1👏 1🤩 1
ምኩራብ የዐብይ ጾም ሦስተኛ እሑድ(ሳምንት) ሦስተኛው ሰንበት ምኩራብ ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት «ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ» «ምኩራብ» ማለትም ቀጥተኛ ፍችው ኮረብታ፣ ተራራ የሚያኸል ታላቅ ሕንጻ ማለት ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ወይም ቤተመቅደስ ማለት ይሆናል፡፡ ዐቢይ ፍሬ ቃሉ ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያነ ሥጋን በትምህርቱ፣ ድውያነ ነፍስን በታምራቱ ሲፈውስ በምኩራብ እየተገኘ የፈጸመውን የማዳን ሥራ በኀሊና እያሳሰበ የሚያስተምር ሦስተኛ ሳምንት ነው፡፡ ዮሐ. 2:12 «ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ» እያለ ኢየሱስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እየጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ሳምንት ነው። የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ) ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ ምኩራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡ ትርጉም:- ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል (እያለ የሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው፡)፡ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ። ምስባኩም፦ መዝ ፷፰፥፱ "እስመ ቅንዐት ቤትከ በልዐኒ ትዕይርቶሙ ለእለይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ" "የቤትህ ቅናት በልቶኛል የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆብኛልና ነፍሴን በጾም አስመረርኳት" በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ ጥቅሶች፦ -ቆላ ፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ -ያዕ ፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ -የሐዋ ሥራ ፲፥፩-፱ ወንጌሉም፦ ዮሐ ፪፥፲፪ እስከ ፍጻሜ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 31 18😱 1
"ምኩራብ" በዲያቆን ዘማሪ ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 15 12🥰 7
"በእጸ መስቀሉ የተከፈለልኝ" ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
48👍 30🥰 3
መጋቢት ፲ በዓለ ቅዱስ መስቀል መጋቢት አስር በዚህች እለት የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት ነው። የዚህም የከበረ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት ጊዜ ሆኗል። መጀመሪያ የፃድቁ ንጉስ የቆስጠንጢኖስ እናት በሆነች በንግስት እሌኒ እጅ ነው። እርሷ ለእግዚአብሄር ተስላ ነበርና ልጇ ቆስጠንጢኖስ ወደ ክርስቲያን ሀይማኖት ቢገባ ወደ ኢየሩሳሌም ሄዳ መስቀሉን እስከ አገኘችው ድረስ ልትፈልግው በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ልታንፃቸው ነው። ከዚህ በኋላ ልጇ አምኖ የክርስትና ጥምቀትን በተጠመቀ ጊዜ እሌኒ ቅድስት ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች ከእርሷ ጋርም ብዙ ሰራዊት ነበር ደርሳም ስለ ከበረ መስቀል መረመረች የሚያስረዳት አላገኘችም የአይሁድ ወገን የሆነ አንድ ሽማግሌ ሰው አስራ በርሀብና በጥማት አስጨነቀችው። በተጨነቀም ጊዜ ለንግስት እሌኒ "የጉልጎታን ኮረብታ አስጠርጊ" ብሎ ነገራት እርሷም ይጠርጉ ዘንድ አይሁድን አዘዘቻቸው። ቤቱን የሚጠርግ ሰው ሁሉ ጥራጊውን በውስጡ የከበረ መስቀል በአለበት በጌታችን መቃብር ላይ እንዲጥል አይሁድ አስቀድመው አዝዘው ነበርና ንግስት እሌኒ እስከደረሰችበት ጊዜ ከሁለት መቶ አመት በላይ ጥራጊያቸውን ሲጥሉበት ኖሩ ኮረብታም ሆነ። አይሁድም በጠረጉ ጊዜ ሶስት መስቀሎች ተገለጡ የክብር ባለቤት ክርስቶስ የተሰቀለበት የትኛው እንደሆነ አላወቁም። የሞተ ሰውም አግኝተው አመጡ። አንዱንም መስቀል አምጥተው በሞተው ሰው ላይ አኖሩት አልተነሳም ደግሞ ሌላውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አኖሩ አሁንም አልተነሳም ከዚህም በኋላ ሶስተኛውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አደረጉት ያንጊዜ የሞተው ሰው ተነሳ እሌኒም የክርስቶስ መስቀል እንደሆነ አውቃ ሰገደችለት የክርስቲያንም ወገኖች ሁሉ ሰገዱለት። ለልጇ የላከችው ይህ መስቀል ነው የሚል በሌላ መፅሀፍ ይገኛል የቀረው ግን ግንዱ በውስጡ ተተክሎበት የነበረው ከእርሱም እኩሌታውን ከቅንዋቱ ጋራ ወደ ልጅዋ የላከችው ነው። ከዚህም በኋላ ስርዓታቸውና የህንፃቸው ነገር በመስከረም ወር በአስራ ሰባት ተፅፎ የሚገኝ አብያተ ክርስቲያናትንና የከበሩ ቦታዎችን አነፀች። ሁለተኛው በሮሙ ንጉስ በህርቃል ዘመን የሆነው ሲሆን የፋርስ ሰዎች በግብፅ አገር ሳሉ ወደ አገራቸው ሊመለሱ ወደዱ። ከሹማምንቶቻቸው አንዱ የጦር መኰንን ተነጥሎ ወደ ኢየሩሳሌም አልፎ ደረሰ ወደ ከበረ መስቀል ቤተ ክርስቲያንም ገባ። መስቀሉም በላዩ በተተከለበት ግንድ ፊት ታላቅ ብርሀን ሲበራ አይቶ ሊያነሳው እጁን ዘረጋ። እሳትም ወጥታ እጁን አቃጠለችው። ከክርስቲያን በቀር ማንም ሊነካው እንደማይችል የመስቀልን የክብሩን ነገር ሰዎች ነገሩት። ሁለት ዲያቆናትንም ይዞ የከበረ መስቀልን እንዲሸከሙ አዘዛቸው ከኢየሩሳሌምም ብዙ ሰዎችን ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ። የፋርስ ሰዎች ኢየሩሳሌምን እንዳጠፏት ብዙዎች ሰዎችንም እንደማረኩና የከበረ የክርስቶስንም መስቀሉን እንደወሰዱ የሮም ንጉስ ህርቃል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ስለርሱም እንዲፆሙ ምእመናንን አዝዞ ወደፋርስ ዘምቶ ወጋቸው ብዙዎችንም ገደላቸው የከበረ እፀ መስቀልንም እየፈለገ በሀገራቸው ሁሉ ዞረ ግን አላገኘውም። ያ ዲያቆናቱና መስቀሉን የወሰደ መኰንን ከቦታዎች በቤቱ አንፃር ባለ በአንድ ቦታ ላይ ወስዷቸው ጥልቅ ጉድጓድ እንዲቆፍሩ አዝዞ በዚያ የከበረ መስቀልን አስቀበረ እነዚያንም ዲያቆናት ገደላቸው። ነገር ግን ያ መኰንን የማረካት የካህናት ወገን የሆነች በእርሱ ቤት የምትኖር አንዲት ብላቴና ነበረች። እርሷም የከበረ መስቀልን ሲያስቀብርና ሁለቱን ዲያቆናት ሲገድላቸው በቤቱ ውስጥ ሁና በመስኮት ትመለከት ነበር ወደ ንጉስ ህርቃልም ሂዳ መኰንኑ ያደረገውን ሁሉ ነገረችው። ይህም ንጉስ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያቺ ብላቴናም መራችው ከእርሱም ጋራ ብዙ ሰራዊት ሆኖ ኤጲስቆጶሳትና ካህናትም ነበሩ ።ወደ ቦታውም እስከምታደርሳቸው ያቺን ልጅ ተከተሏት ቆፍረውም የከበረ እፀ መስቀልን አገኙት ከአዘቅቱም አወጡት ንጉሱና ሰራዊቱም ሰገዱለት። በልብሰ መንግስቱም አጎናፀፈው ታላቅ ክብርንም አከበረው ከሰራዊቱም ጋር እጅግ ደስ አለው። የዚህም መስቀል ሁለተኛ የተገለጠበትና የተገኘበት በዚች ቀን በመጋቢት አስር ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ንጉሱ የከበረ እፀ መስቀልን ተሸክሞ ወደ ቁስጥንጥንያ ከተማ ወሰደው፡፡ የመድኃኒታችን የመስቀሉ በረከት ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ©ስንክሳር @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 20 8👏 2
ጐርፍና ነፋስ ምን ዓይነት ትርጓሜ እንዳላቸው ከላይ ተብራርቷል። <<ዓለት>> የተባለ ግን የእግዚአብሔር ቃል ነው። ስለዚህ ወጣቶች በቤት የተመሰለ ሕይወታቸው እንዳይናጋና እንዳይፈርስ ኑሮአቸውን መመሥርት ያለባቸው በምክረ ካህን በፈቃድ ካህን ላይ ነው:: ካህናት ወጣቶችን የሚመክሩበት የእግዚአብሔር ቃል እውነተኛ የ<<መሠረት ድንጋይ>> ነውና፡፡   ወጣቶች ከፈቀዱ በእግዚአብሔር ቃል ላይ መመሥረት ብቻ ሳይሆን ቃሉ ከውስጣቸው እንዳይጠፋ ማድረግ ይችላሉ፡፡ ምክንያቱም ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ <<የእግዚአብሔር ቃል በእናንተ ስለሚኖር>> በማለት የተናገረው ከአረጋውያንና ከባልቴቶች ይልቅ የእግዚአብሔርን ቃል በልቡና መያዝ ለወጣቶች የሚቻል ነገር ስለሆነ ነው፡፡ 1ዮሐ2፥14         ወጣቶችና ፆሮቻቸው(ፈተናዎቻቸው)   በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አስተምህሮ መሠረት ምዕመናን በአምስት መደብ ይመደባሉ። ይህም መደብ <<ፆታ ምእመናን>> ይባላል፡፡ አምስቱ ፆታ ምእመናን የሚባሉት ካህናት፤ መነኮሳት፣ አዕሩግ(አረጋውያን)፣ ወራዙት(ወንድ ወጣቶች)፣ እና አንስት(ሴት ወጣቶች) ናቸው።   አምስቱም ፆታ ምእመናን በየራሳቸው የሚቸገሩበት ዓቢይ ፈተና አለ፡፡ <<ፆር>> በመባል የሚታወቀው ይህ ዓቢይ ፈተና ነው:: የካህናት ፆራቸው ትዝኅርት (ትዕቢት) ነው:: የመነኮሳት ፆር ስስት ሲሆን የአረጋውያን ደግሞ ፆራቸው ፍቅረ ንዋይ ነው። ቀሪዎቹ ወጣት ወንዶች ሲሆኑ ዐቢይ ፆራቸውም ዝሙት ነው:: የወጣት ሴቶች ዓቢይ ፆር ደግሞ ትውዝፍት(የምንዝር ጌጥን መውደድ) ነው።(ዮሐ 5፥4 ትርጓሜ)   ይህ ማለት ግን ዋና ዋና ፈተናቸውን አንጓሎ ለመናገር ነው እንጂ እያንዳንዱ ፆታ ምእመን የሚፈተነው በአንድ ነገር ብቻ ነው ማለት አይደለም። <<ሰውነቱ በደዌ የተጠቃን ሰው ጉንፋን እንኳን እንደሚያልበት>> እንዲሁ በዋና ፈተናው ድል የተደረገ ምእመን ሌሎች ጥቃትን ፈተናዎች ይረባረቡበታል። ነገር ግን ዋናውን ፆሩን ድል ካደረገ የሚመጡበትን ሌሎች ፈተናዎች በቀላሉ ድል ለማድረግ ይቻለዋል።   ወጣቶች ልዩ ልዩ ፆር(ፈተና) እንዳለባቸው ነገር ግን ዕድሜያቸው እየገፋ በመጣ ቁጥር ወጣትነታቸው ሲያልፍ የወጣትነት ፈተናቸውም አብሮ እንደሚያልፍ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ሲህ ተናግሯል:: <<ወከመ ሥጋ ሶበ ይረክቦ ሕማመ ፈጸንት ወካልዕ ደዌያት ይደክም። ወለእመኒ ጥቀ ጽኑዕ ውእቱ ወእመሰ ድኅነ እምደዌሁ ይገብእ ኅቤሁ ኃይሉ ወከማሁ ነፍስኒ ትደዊ በዘመነ ውርዛዌ እስመ ባቲ ፍቅረ ትዕቢት ወተድላ ወተዋስቦ። ወዘይመስሎ ለዝንቱ ጣዕመ ፍትወታት ወእመሰ መጽኣ ጊዜ ርስአን ይሴስል ሕማም እምኩለንታሁ።>> ይህ ንባብ ወደ አማርኛ ሲመለስ <<ሥጋን ንዳድ ሌላም ልዩ ልዩ ደዌ በያዘው ጊዜ ምንም ብርቱ ቢሆን እንደሚደክምና ከበሽታው በዳነ ጊዜ ግን ኃይሉ እንደሚመለስለት እንደዚሁ ነፍስም በወጣትነት ወራት በደዌ ኃጢአት ትያዛለች። ትዕቢተኛነት፣ ሥጋዬ ይድላው ማለት፣ በጾታ መፈላለግና ይህን የመሳሰሉ ብዙ የምኞት ጣዕም ያድርበታል። የእርጅና ወራት በደረሰ ጊዜ ግን ፈቃደ ሥጋ ፈጽሞ ከሰውነቱይርቃል።>> ማለት ነው:: ዮሐ.አፈ.ተግ.7 ምዕራፍ ሦስት ይቀጥላል... @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 26 11😱 3
             የወጣቶች ምኞት   የሰው ልጆች ከልጅነት ወደ ወጣትነት በሚሸጋገሩባቸው ወራትና ዓመታት አካላቸው እንደሚደረጅና አእምሮቸው እንደሚዳብር ሁሉ ምኞታቸውም በዓይነትና በመጠን እየሰፋና እየጨመረ ይሄዳል፡፡ ይህ የወጣቶች ምኞት በአመዛኙ ከመንፈሳዊነት ጋር የሚቃረንና ሥጋዊ በመሆኑ «እኩይ ፍትወት» ይባላል፡፡   ከዚህም በተጨማሪ በጎልማሶችና በኮረዶች ላይ የሚከሠተውን ምኞት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ <<አንተ ግን ከክፉ የጎልማስነት ምኞት ሽሽ>> በማለት የክርስትና ልጁን ጢሞቴዎስን በመከረበት ጊዜ ይህንን የወጣትነት ምኞት «ክፉ የወጣትነት ምኞት>> ብሎ ሲጠራው እናነባለን፡፡   በእርግጥ በወጣትነት ዘመን የሚገኝ ምኞት እጅግ ክፉ ነው:: ወጣትነት የሚሠራበት ዘመን እንጂ የሚመኙበት ዘመን አይደለምና። በተጨማሪም በዚህ ዘመን የሚከሠት ምኞት በወጣቶች አእምሮ ክፉነቱ ሊደረሰበት የማይችልና አታላይ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ «ሰው ራሱ በገዛ ምኞቱ ሲሳብና ሲታለል ይፈታናል::>> በማለት እንደተናገረው በወጣትነት ዘመን የሚገኝ ምኞት ከመጠን በላይ ወደ ጥፋት የሚስብ፥ የሚጐትትና <<የሚያታልል>> ነው፡፡   በተለይም <<በገዛ ምኞቱ ሲሳብ>> የሚለው ቃል ምኞት ከፍተኛ ጉልበት እንዳለው ይጠቁማል፡፡ በወጣትነት ዘመን ምንም አእምሮ የበሰለ ቢሆን ከዚያ የሚበረታው ግን ምኞት ነው፡፡በወጣቶች ላይ ከዕውቀታቸው ይልቅ ምኞታቸው መበርታቱን ለማስረዳት ወጣትነት <<በዘመነ ኦሪት>> ይመሰላል፡፡   ኦሪት ከመሠራቷ በፊት ያለው ዘመን የሕገ ልቡና ዘመን ይባላል:: በዘመኑ ምንም ሕግና ሥርዓት ባለመኖሩ ሰው በልቡናው እንደ መሰለው ይኖር ነበር። እንዲሁም ሁለ ሕፃናት በልቡናቸው እንዳሰቡት ስለሚኖሩ በሕገ ልቡና የሚኖሩ ሰዎችን ይመስላሉ:: በዘመነ ኦሪት ደግሞ በመስፍኑ ሙሴ አማካኝነት ለእስራኤላዊያን ሕግ ተሰጠ:: ዘመኑም ዘመነ ኦሪት ተባለ፡፡ ሕገ ኦሪት በዘመኗ ክፉና ደግን ለመለየት አስችላለች:: እንደዚሁም ሁሉ ወጣትነት ከሕፃንነት ዘመን ይልቅ ክፉና ደግን ለመለየት የሚቻልበት ዕድሜ በመሆኑ በዘመነ ኦሪት ይመሰላል፡፡ ሆኖም ምንም ዕውቀት ቢገኝ በዘመነ ኦሪት የሰው ባሕርይ በኃጢአት የጐሰቆለ ስለ ነበር ሕጉን ፈጽሞ ለመጽደቅ አልተቻለም ነበር። በተመሳሳይ መልኩ ወጣቶች ዕውቀታቸው እየጨመረ ቢመጣም ምኞታቸውም የዛኑ ያህል ስለሚበረታና ስለሚስባቸው ዕውቀታቸውን ተጠቅመው የሚያጸድቃቸውን ጐዳና ለመከተል ይቸግራሉ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ <<በብልቶቼ ውስጥ ያለው ይህ የኀጢአት ሕግ (ምኞት) ወደ እርሱ ማረከኝ ተበረታታብኝ።>> ሮሜ7፥23 በማለት የተናገረው በወጣቶች ዘንድ ምኞት ምን ያህል ወጥመድ እንደሆነ ሲገልጽ ነው፡፡   ቅዱስ አባ ሕርያቆስም ስለ እመቤታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም አስተዳደግ በተናገረበት የቅዳሴ መጽሐፍ እንዲህ ብሏል “አኮ ድንግል ወራዙት ስፉጣን ዘናዘዙኪ አላ መላእክተ ሰማይ ሓወጹኪ፤ ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጕልማሶች ያረጋጉሽ አይደለሽም:: የሰማይ መላእክት ጎበኙሽ እንጂ>> ይህ አገላለጽ ወጣቶች በወጣትነት ምኞት እንደሚታለሉ ከመግለጹም ባሻገር እነርሱ በምኞታቸው ተሸንግለው ሌላውን ለማታለል እንደሚያባብሉ ይናገራል፡፡ እመቤታችን ግን በሰማይ መላእክት ተጎበኘች እንጂ በሚያታልሉ ጐልማሶች አልተጽናናችም፡፡    <<ምኞት>> በውስጣችን እንዲኖርና እንዲያድግልን የምንንከባከበው ነገር መሆን የለበትም:: ምኞት ተስፋ አይደለምና፡፡ ኃጢአተኛ ሰው ምኞት ያበዛል። <<ኃጥእ ቀኑን ሙሉ ይመኛል።>>በማለት ጠቢቡ ሰሎሞን የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ ምኞት ተጭኖን እንዳንሞት ምኞታችንን መወሰን ጥረትን ግን ማብዛት መልካም ነው።    «ምኞት። አስደሳችና ጣፋጭ ነገር ትመስል ይሆናል እውነቱ ግን እንዲህ አይደለም፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ምኞት እንዲህ ይላል፡- <<እስመ ፍትወት አኮ ጣዕም ይእቲ አላ ስሕተት ወዳኅፅ>> ይህም <<ምኞት ስሕተትና ውድቀት ናት እንጂ ጣፋጭ አይደለችም::>> ማለት ነው፡፡ ምኞትን ማብዛት ልፋትን ወይም ተስፋ መቁረጥን ማብዛት ነው። ምክንያቱም ምኞትን ለማሳካት ብዙ መድከም ከማስፈለጉም በላይ ብዙ ምኞት ካልተሳካ የሚያስከትለው ተስፋ መቁረጥም እንደዚሁ ብዙ ይሆናል።   ብዙ ወጣቶች የሚመኙት ጉዳት የሚያስከትልባቸውንና ከጥቂት ጊዜ በኋላም በብርቱ የሚያስቀጣቸውን ነገር ነው፡፡ ከሁሉ የሚደንቀው ደግሞ ጓጉተው ይፈልጉት እንጂ ሲያገኙት ወዲያው የሚሰለቹት ወይም የሚጸጸቱበት መሆኑ ነው:: አሁን ሀብታም ከመሆን በላይ ምንም የምፈልገው ነገር የለም ትላለህ:: ሀብታም ስትሆን ግን ይህ ከንቱ እንደሆነና ሌላ የሚቀርህ ብዙ ነገር እንዳለ ይሰማሃል። ይህ የሚሆነው ሁሉንም ነገር የተሟላና ፍጹም የሚያደርገው የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር በመሆኑ ነው። ፈጣሪን ሳይጠጉ ምንም ነገር በቂና አርኪ መሆን አይችልም:: ስለዚህ መመኘትና ለማግኘት መጣር ብቻ ሳይሆን አስቀድመህ ፈጣሪህን መጠጋት ይኖርብሀል።   በወጣትነት የሚከሠት ምኞት አንድ ብቻ አይደለም:: ወጣቶች ሁሉም ያምራቸዋል። ከዚህ የተነሣ በአንድ ነገር ላይ መርጋትና መጽናት አይሆንላቸውም:: ተምሮ በማዕርግ መሠረቅ፣ አጭቶ ማግባት፣ ሀብታም ነጋዴ መሆን፣ ትልቅ ባለሥልጣን መሆን ጊዜ ሰጥተን በተራ ብንኖርባቸው ጊዜ ጠብቀው ይሳካሉ፡፡ እነዚህን ነገሮች በአንድ ጊዜ ለማሳካት ብንጥር ይሳካሉን? አበው <<ሁለት የወደደ አንዱን ሳያገኝ ሄደ።>> እንደሚለት ይሆንና አንዱም ላይሳካልን ይችላል:: ስለዚህ ወጣቶች አንድን ነገር መጀመር ሳይሆን በእርጋታ ሆኖ እስከ መጨረሻ መፈጸም እንደሚኖርባቸው ማወቅ አለባቸው::   ከዚህም ሌላ ወጣቶች ምኞቶቻቸው ብዙ ከመሆናቸው የተነሣ ሁለት የማይጣጣሙ ነገሮችን በአንድ ላይ የሚመኙበት ጊዜ አለ፡፡ ሙሽራ ሲያዩ ማግባትንና መውለድን ይመኙና በዚያው ጊዜ ደግሞ ልቡናቸው በመንፈሳዊ ነገር ተነክቶ መመንኮስና መመነንን የሚመኙበት ጊዜ አለ። ታዲያ እነዚህን ሁለት የሚጻረሩ ፍላጐቶች በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ እንዴት ማስኬድ ይቻላል:: ይህ መታወክ ነው።  እንዲህ ያለ ነገር ሲከሰት ወጣት ከመሆናችን የተነሣ እሳታዊና ነፋሳዊ ባሕሪያችን እየተሟገቱ ፈተና ላይ መውደቃችንን ተረድተን ብንታገሥ እንዲህ ያለ ፈተና ከጊዜ ብዛት ራሱ ይርቃል።   በማቴዎስ ወንጌል <<ዝናብም ወረደ ጐርፍም መጣ ነፋስም ነፈስ ያንንም ቤት ገፋው በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም>> ማቴ 7፥25 ተብሎ የተጻፈው ኃይለ ቃል ሲተረጐም <<ቤት>> የተባለው የወጣት ሕይወት ነው፡፡ <<ነፋስ ነፈሰ>> ማለት የአጋንንት ፈተና በወጣቱ ላይ ተነሣበትና ከሴት ርቆ ንጽሕናውን ጠብቆ እንደ እንጦንስና እንደ መቃርስ ለመኖር እንዲመኝ አደረገው ማለት ነው ይለናል፡፡ <<ዝናብም ወረደ>> ማለት ደግሞ ያንኑ ወጣት እንደ እንጦንስና እንደ መቃርስ መኖር አይቻለኝም ባይሆን እንደ ኢዮብና እንደ አብርሃም አግብቼ ልጆች ወልጄ በሕግ ጸንቼ ልኑር አሰኘው ማለት ሲሆን <<ጎርፍም ጎረፈ>> ማለት ደግሞ በመጨረሻ ተስፋ በመቁረጥ ሁሉንም አልችልም እስኪል ድረስ አደረሰው ማለት ነው፡፡ ለመመነንም ሆነ ለማግባት መመኘት መልካም ነገር ሆኖ ሳለ በማይሆን ጊዜና በስሜታዊነት የሚወሰን ግን አይደለም:: ወጣቶችን እንዲህ ያለ መንፈሳዊ የሚመስል የሰይጣን ፈተና ሊያውካቸው ስለሚችል በግብታዊነት ከመወሰን ይልቅ በምክረ ካህን በፈቃደ ካህን መኖር ይኖርባቸዋል፡፡ ያ ቤት ነፋስ ነፍሶበት ጐርፍ ጐርፎበትና ዝናብ ዘንቦበት አልወደቀም፡፡ ምክንያቱም <<በዓለት ላይ>> ስለ ተመሠረተ ነው። ዝናብ፣
Show all...
👍 12 6
  አረጋዊ ዮሴፍ ሽማግሌ ሲሆን በብዙ ጎዳና መልካምነቱ ተመስክሮለት አማናዊት ታቦት ድንግል ማርያምን ለማገልገል ተመርጧል:: እመቤታችንን በአደራ እንዲጠብቃት ለአረጋዊ ዮሴፍ ተሰጠች። እንደዚሁም ሁሉ ወንጌላዊ ዮሐንስ ምንም ወጣት ቢሆን በቅቶ ስለተገኘ ለአረጋዊ ዮሴፍ የተሰጠችው ድንግል ማርያምን ለማገልገል እንደ ዮሴፍ ሁሉ እርሱም ከመስቀሉ ሥር በመገኘት በአደራ ተቀዘላት፡፡ ይህ ጸጋን ለመቀበል በቅቶ መገኘት እንጂ ዕድሜ ወሳኝ አለመሆኑን ያስረዳል። ዮሐ19፥26-27 ማቴ 1፥18-25   ወንጌላዊ ዮሐንስ ለኛ ለወጣቶች መመኪያችን ነው:: በወጣትነት ድንግል ማርያምን አስተናግዷልና። በክርስትና እምነት ከድንግል ማርያም ጋር የሚመሳሰልና የሚተካከል ሀብትም ጸጋም የለም፡፡ ታዲያ ድንግል ማርያምን ለመቀበል የበቃ ሌሎች ነገሮችን ከመቀበል ምን ያግደዋል፡፡ ይህን ሲባል ግን በቅቶ ከተገኘ እንጂ ካልበቃ ሊሆን አይችልም:: በአረጋዊ ዮሴፍ ዘመን ብዙ አረጋዊያን ነበሩ ነገር ግን በትሮቻቸው ተሰብስቦ ቢጸለይበት የቅዱስ ዮሴፍ በትር እንደ አሮን በትር ለምልማ በመገኘቷና በላይዋም «ኦ! ዮሴፍ ዕቀባ ለማርያም : ዮሴፍ ሆይ ማርያምን ጠብቃት» የሚል ጽሑፍ ተገኝቶ ድንግል ማርያምን ወደ ቤቱ ወስዷታል፡፡ (የሕዝቅኤል ትርጓሜ) በዮሐንስ ወንጌላዊም ዘመን ብዙ ወጣቶች ነበሩ ነገር ግን እመቤችንን እንደ ዮሐንስ በአደራ ለመቀበል አልታደሉም። እንዲሁም በዘመናችን ብዙ ወጣቶች አሉ ሁሉም ለቁርባን፣ ለተክሊልና ለክህነት አይበቁ ይሆናል:: ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ግን የሚበቁ ወጣቶች መኖራቸው መዘንጋት የለበትም፡፡   ጸጋ እግዚአብሔር በዕድሜ የሚሰጥ ቢሆን ኖሮ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም «ከሴቶች መካከል ተለይታ የተባረከች» ለመሆን እንዴት ትችል ነበር? ነገር ግን ጸጋ እግዚአብሔር በዕድሜ ባለመሆኑ ምልዕተ ጸጋ ለመሆን በቃች። ምንም እንኳን በዕድሜ ትንሽ ብላቴና ብትሆን መጽሐፈ መነኮሳት <<ለብፅዕትኒ ማርያም ኢከልዓ ደቂቅናሃ ከመ ትኩን ቡሩክተ እም አንስት>> እንዳለ «ብፅዕት ማርያምን በዕድሜ ትንሽ መሆኗ ከሴቶች መካከል ተለይታ ቡርክት ለመሆን አልከለከላትም» ፊል ክፍል4 ተስ47 በዚህም ምክንያት ድንግል ማርያም «ምክሐ ደናግል» ብቻ ሳይሆን «ኃይለ ወራዙት»ም ትባላለች፡፡ ድንግል ማርያም «ኃይለ ወራዙት» ናት ማለት ለወጣቶችም ሆነ ለአረጋዊያን የወጣትነታቸው ኃይል እርሷ ናት ማለት ነው:: (መልክዐ ቁርባን)   እንዲሁም ወጣቶች በሚገባ ከኖሩ ከአረጋዊያን ተሽለው ሊገኙ ይችላሉ:: ይህም «ወራዙትኒ እመኒ ሕፃናት እሙንቱ ወተጸምዱ ለሥርዓተ ንጽሕ ይኄይሱ ፈድፋደ እም አዕሩግ፤ ወጣቶች ምንም ታዳጊዎች ቢሆኑ ንጽሕናን ጠብቀው ከኖሩ ፈጽመው ከአረጋዊያን ይበልጣሉ» በማለት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በተናገረው ቃል ይታወቃል፡፡ ትንሽ ዘመን ኖሮ በብዙ ዘመን የሚገኝ ዕውቀትን ገንዘብ ያደረገ ብልህ ወጣት ብዙ ዘመን ኖሮ ዕውቀት በማጣት እንደ ሕፃን ከሚኖር ሽማግሌ እንደ ምን አይበልጥ?   ቅዱሳት መጻሕፍትም በዚህ ሐሳብ ተስማምተዋል። ጠቢቡ ሰሎሞን «ክብረ ርእስ አኮ በብዝኃ መዋዕል ፤ መከበር በዘመን ብዛት አይደለም» በማለት ሲናገር ፤ ሲራክ ደግሞ <<ሲበቱ ለብእሲ አእምሮቱ ይእቲ፣ የሰው ሽበቱ ዕውቀቱ ናት» ብሏል፡፡ ጻድቁ ኢዮብም «አኮ ዘአብዝኃ ክራማተ ዘየአምራ ለጥበብ ፤ ጥበብን የሚያውቃት ዕድሜ የጠገበ አይደለም» በማለት ተናግሯል:: እነዚህ ጥቅሶች ሁሉ መብለጥ በሥራ እንጂ በዕድሜ አለመሆኑን የሚያስረዱ ናቸው።   አንዳንድ ወጣቶች በቤታቸው በዕድሜ ታላቅ ስለሆኑ ብቻ ታናናሾቻቸው እንዲንቀጠቀጡላቸው ይሻሉ፡፡ ይህ እጅግ የሚያስገርም ነው:: መልካም ሽምግልና የሌለው ሰው ስለሸበተ ብቻ ማን ያከብረዋል? ሽበት የክብር ምልክት ብቻ ነው እንጂ በራሱ ማስከበር አይችልም:: ዘውድ መድፋት፣ ዝናር መታጠቅ፣ ቅብዓ መንግሥት መቀባት ብቻ ንጉሥን አያስከብሩትም:: አንተም ብትሆን እንዲህ የተሸለመን ንጉሥ የገዛ ባሪያዎቹ ዘውዱን እንደደፋ ሲያቃልሉትና ሲንቁት፤ እያሸሟጠጡ ሲጎትቱት ብታይ ታዝንለት ይሆናል እንጂ አታከብረውም፡፡ ምክንያቱም መከበር በክብር ምልክት ብቻ አይደለምና፡፡ ታዲያ አንተ የታላቅነትን ምልክት ይዘህ ብትጣላ፣ ብትሳደብ፣ ብትሰክር፣ ብታመነዝር፤ ዲቃላ ብትወልድ፣ ገንዘብ አያያዝና ቤት አስተዳደር ባታውቅ ከዚህም በላይ ሰው ማክበርን ጨምሮ ምንም ዓይነት ፍቅርና ሃይማኖት ሳይኖርህ ክብርን መሻትህ እጅግ ያስገርማል፡፡   ጥሩ ወጣትና ጥሩ ታላቅ መሆን ካልቻልክ የምታጣው ክብርን ብቻ አይደለም:: ማንኛውም ኃላፊነትም አይሰጥህም:: አንተ እንደ ዔሳው ስትሆን እንደ ያዕቆብ ያለ ታናሽ ወንድምህ ብኩርናህን ይወስድና አንተ የሱን እጅ ስታይ ትኖራለህ፡፡ ታናናሾችህን የመቆጣትና የመገሠጽ መብት አይኖርህም። ሴሰኛ ሽማግሌ ወጣቶችን መገሠጽ እንደማያምርበት አንተ ሕገ ወጥ ወጣት ሆነህ ታናናሾቼን ልቅጣ ብትል ማን ይሰማሃል። እንዳንተ ያለውን ሰው መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ሲል ይገሥጻል፦ <<እንተ ግብዝ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፤ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ። ማቴ 7፥5   አላረጀሁም ለማለት ነጭ ጉተናቸውን ቀለም እየቀቡ የሚያጠቁሩ አልያም <<ሽበት የሆነብኝ ማር ነክቶኝ ነው፣ ስብ ነክቶኝ ነው፣ በዘር ነው፣ ኑሮ አጎሳቊሎኝ ነው!>> የሚሉ ተራ ምክንያቶችን በማቅረብ ልጅ ነኝ እንደሚሉ ሽማግሌዎች አንተም ምንም እንኳን የወጣት ቁመና ይዘህ ጎልማሳ ብትሆንም ነገረ ሥራህ ሁሉ የሕፃን ከሆነ «ገርጅፎ ነው እንጂ ገና ሕፃን ነው፣ አልበሰለም>> መባልህ አይቀርምና እንደ አካልህ ሁሉ በሥራህና በዕውቀትህም ማደግ ይኖርብሃል። ከዚህ ወጥተህ ወጣትነትህን አታስንቀው::   አንድ ሽማግሌ ዕድሜ እያገዘውና ሥጋው ደክሞለት ሳለ ገና እንደ ወጣት ዘልዬ አልጠገብኩም ቢል ከቅጣት አያመልጥም:: ስለ ስሕተቱም ምክንያት የለውም ማለትም ባለመብሰሌ ነው ወይም ሰውነቴ እንደ እሳት እየፈጀኝ ንጽሕናን ጠብቆ መኖር አልቻልኩም ለማለት አይችልም።   እንደዚሁም ሁሉ ወጣቶችም ሕግ ሲያፈርሱ የሚነቀፉበት ብዙ ነገር አለ፡፡ ሽማግሌ በፍቅረ ንዋይ ቢጠቃና ስስታም ቢሆን እርጅናው ስላመጣበት ድካም የሚረዳው ይሻልና ገንዘብ ካለኝ በገንዘቤ እጦራለሁ ብሎ ነው ይባላል:: ወጣቶች የሚስገበገቡት ለምን ይሆን? እነርሱ ወጥተው ወርደው ራሳቸውን መርዳት ስለሚችሉ ወጣቶች በፍቅረ ንዋይ ቢያዙ ይነቀፋሉ። በዚህም ብቻ ሳይሆን ንጽሕናቸውን ባለመጠበቃቸው፤ በሰካራምነታችው፣ በስንፍናቸውና በመሳሰሉት መጥፎ ሥራቸው ሁሉ ተጠያቂዎች ናቸው:: ንጽሕናን ጠብቀን ለመኖር አንችልም እንዳይሉ ንጽሕናን ለመጠበቅ ያላቸውን አጋዥ ኃይል መመልከት በተገባቸው ነበር:: ወጣቶች አረጋውያን የሌላቸው ኃይለ ሥጋ ስላላቸው ፍትወትን ለማሸነፍ ሲሉ መጾም፣ መጸለይ፣ መስገድና መጽሐፍ መመልከት ይችላሉ፡፡ ይህ ከፍትወት የሚጠበቁበት መሣሪያ የተሰጠው ለመነኮሳት ብቻ አይደለም:: ፍትወት ወዲህና ወዲያ ለሚያፍገመግማቸው ለወጣቶችም ጭምር ነው:: ስለዚህ ወጣቶች የመጸለይ፣ የመጾም፤ የመስገድና የመሳሰሉትን ክርስቲያናዊ ግዴታዎች የመፈጸም ኃላፊነት አለባቸው::
Show all...
👍 14
Photo unavailableShow in Telegram
.                   ምዕራፍ ሁለት                      የልጅ ዐዋቂ   ወጣቶች በመልካም አኗኗር ከኖሩ የልጅ ዐዋቂ ይባላሉ፡፡ ወጣቶች ከፈቀዱ አረጋዊ መሆንና አረጋዊ ከደረሰበት ጸጋና ክብር መድረስ ይችላሉ:: ወጣት የሽማግሌ ሥራ መሥራት ይቻለዋልን? የሚል ቢኖር ከሽማግሌዎች ወገን የወጣቶችን ሥራ በመሥራት ጸንተው የሚኖሩ ብዙ እንዳሉ ሁሉ <<ከማሁ ይትከሀሎ ለወሬዛ የሀሉ በከዊነ አዕሩግ>>፣ <<እንዲሁ ወጣትም የሽማግሌዎችን ሥራ በመሥራት መኖር ይቻለዋል>> የሚል መልስ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ተግሣጽ ዘዮሐ አፈ 7   ነጭ ጉተና (ፀጉር) ከመኮነን እንደማያድን ሁሉ <<ከማሁኪ ጸሊም ድምድማ ኢይከልዕ ረኪበ ጸጋ : እንደዚሁም ጥቁር ፀጉርም ጸጋ ከማግኘት አያስከለክልም::>> በክርስትና መልካም ሥራን እንጂ ነጭና ጥቁር ፀጉርን ማበላለጥ የለም። አረጋዊም ሆነ ወጣት በቅተው ከተገኙ ለማንኛውም ክብር ይበቃሉ፡፡
Show all...
👍 15🥰 5 1
"ቅድስት" በዲያቆን ዘማሪ ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ በኩር ናት የበዓላት ኑ ከፍ ከፍ እናድርጋት በእርሷ ደስ ይበለን በሰንበተ ክርስቲያን አዝ... በዝማሬ እንበርታ በገናውን እንያዝና መልካም ስራ ሚሠራባት ሰንበት ቅድስት ናትና ከጨለማ ብርሀን ከመገዛት ነጻነት እግዚአብሔር ይህን ሰጠን ደስ ይበለን በሰንበት አዝ... ለአብርሃም ተገልጣለች ለሙሴም በደብረ ሲና በነቢያት የታወቀች ሰንበት ደሀራዊት ናትና በሳምንቱ ሠለጠነች ተሰበከች በሀዋሪያት ሀሌሉያ እለተ ሰንበት ተሰጠችን ልናርፍባት አዝ... በእልልታ እንሞላ እንደነቢዩ አሳፍ በከበረች የሰንበት ቀን ኑ ለቅኔ እንሰለፍ በመቅደሱ ናቸውና ቅዱስነት እና ግርማ ቅዳሴአችን ይሰማልን ከምድር እስከ ኢዮር ራማ አዝ... እግዚአብሔር አብ የባረካት እግዚአብሔር ወልድ የቀደሳት ከእለታት ሁሉ መርጦ መንፈስ ቅዱስ ከፍ ያረጋት በእርሧ ሀሴት እናድርግ እናክብራት እንድንከብር ከደጀ ሰላሙ ታዛ ከመቅደሱ እንሰብሰብ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 23🥰 12 4
፣በዕዳ የሚጠየቅም ሆነ የሚጠይቅ ሁለቱም በአንድነት ቅዱስ ቃሉን ሲሰሙ ዋሽቶ የሰው ዕዳ ያልከፈለውም ተጸጽቶ ይክሳል ወራት ብሶበት ቀን ጥሎት መክፈል ላልቻለውም ምህረት ይቅርታ እንዲያገኝ ቅዱስ ቃሉ ጸሎቱ ምክንያት ይሆነዋል ። በዚህም የተነሳ ሁለቱም ወገኖች በክፉ ከመፈላለግ ይልቅ የይቅርታ የምህረት ሰዎች ይሆናሉ። በዚህች በኵረ በዓላት በምትሆን በቅድስት በዕለተ ሰንበት የምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት ይባረካል ይቀደሳል በዚህ ታሳቢነት ዕለቱም ዕለተ ቅድስና መሆኑን ለማጠየቅ ቅድስት ተብሏል ። ቅድስና የተፈቀደልን ብቻ ሳይሆን የታዘዝነውም ጭምር ነው “እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተ ቅዱሳን ሁኑ” (ዘሌ.፲፱፥፪) በዚህ ኃይለ ቃል ውስጥ ቅድስና እንደ ፈቃድም እንደ ትእዛዝም ሆኖ ተሰጥቶናል፤ እግዚአብሔር ያልፈቀደውን ነገር አድርጉ ሁኑ ብሎ አያዝም።የቅድስና ሕይወት መሰረቱ የእግዚአብሔር ፈቃድና ትእዛዝ ሆኖ ሳለ ለመቀደስ የእኛ መሻት መፈለግ ዝንባሌም ወሳኝ ነው። ለዚህም ነው ሐዋርያው እንዲህ ሲል የጻፈልን “ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ፥” (ዕብ. ፲፪፥፲፬) ምንም አንኳን ቅድስና የተፈቀደና የታዘዘ ቢሆንም የውዴታ እና የነጻ ፈቃድ ውጤት እንጂ የምንገደድበት አይደለም፡፡እግዚአብሔር ፍቅሩ ገብቶን ወደን እና ፈቅደን በፈቃዱ እና በትእዛዙ ስንመራ ያስደስተዋል እንጂ ተገደን ፈርተን ተንቀጥቅጠን እንድንገዛለት አይወድም፡፡ ወደ ቀደመ ነገራችን ስንመለስ ዕለተ ሰንበትም ቅድስት መባሏ ከላይ ያብራራነውን መሰረታዊ ሃሳብ በተከተለ መልኩ ነው። ዕለቲቱ ቅድስት መባሏ ዋና ዓላማ በሰዎች እና በእግዚአብሔር መካከል ለቅድስና ሕይወት ምልክት ማስታወሻ እንድትሆን ነው። በባህሪው ቅዱስ የሆነ አምላክ ዓለምን የማዳን ስራውን የጀመረበትን ጽንሰቱን እንዲሁም የማዳን ስራውም አጠናቆ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ዘላለማዊ ሕይወትን ያበሰረበትን ትንሳኤውን የምናስብበት በመሆኑ የዕለቱ ቅድስና የፈጣሪን ቅዱስ ተግባር የምናደንቅበት ከማንኛውም የሥጋ ሥራ ተለይተን የዋለልን ውለታ ከፍ ከፍ እያድረግን እርሱን የምናመሰግንበት ዕለት ነው። ይህም እኛን ወደ በለጠ የቅድስና ሕይወት የሚያሸጋግረን ከመሆኑም በላይ የእግዚአብሔርን ጥልቅ ፍቅር በየጊዜው እንድናስብና በፍቅሩም እንድንኖር ያግዘናል፡፡ ©ተሚማ ምስባኩ፦ መዝ ፺፭፥፭ "እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ" "እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ ምስጋና ውበት በፊቱ ቅዱስነትና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው" በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ መልእክታት፦ -፩ኛ ተሰ ፬፥፩-፲፫ -፩ኛ ጴጥ ፩፥፲፫ እስከ ፍጻሜ -የሐዋ ሥራ ፲፥፲፯-፴ ወንጌሉም፦ ማቴ ፮፥፲፮-፳፭ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 11 4
ቅድስት የዐብይ ጾም ሁለተኛ እሑድ(ሳምንት) ቅድስት የሚለው ቃል ግሱ “ቀደሰ” ሲሆን "ለየ፣ አከበረ፣ መረጠ" የሚል ትርጉም ይይዛል። ቅድስት ማለት የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች ማለት ነው። ቅዱስ የሚለው ቃል እንደየአገባቡ ለፈጣሪም ለፍጡርም ያገለግላል። ለፈጣሪ ሲነገር እንደ ፈጣሪነቱ ትርጉሙ ይሰፋል ይጠልቃል ለፍጡር ሲነገር ደግሞ እንደ ፍጡርነቱ እና እንደ ቅድስናው ደረጃ ትርጉሙ ሊወሰን ይችላል። እግዚአብሔርን ቅዱስ ስንል የባህሪይው የሆነ፣ ኃጢአት የማይስማማው ፣ ለቅድስናው ተወዳዳሪ ተፎካካሪ የሌለው፣ ወደር የማይወጣለት፣ ዘለዓለማዊ የሆነ ማለታችን ሲሆን ፍጡራንን ግን ቅዱሳን ስንል ቅድስናቸው የጸጋ የሆነ፤ ከእግዚአብሔር ያገኙት፤ እንደነጭ ልብስ ጽድቁም ኃጢአቱም እንደ ዝንባሌአቸው የሚስማማቸው፤ ለቅድስናቸው ማዕረግ ደረጃ የሚወጣለት እንደ ገድል ትሩፋታቸው መጠን ሊጨምርም ሊጎድልም የሚችል ማለታችን ነው። ከፍጡራን መካከል ለእግዚአብሔር የተለዩ ሁሉ በጸጋ የቅድስናው ተሳታፊ ሊሆኑ ይችላሉ። መላእክት፣ ሰዎች፣ መካናት፣ ዕለታት፣ አልባሳት፣ ንዋያት ሁሉ ለእግዚአብሔር እስከተለዩ ድረስ ከቅድስናው በረከት ይሳተፋ እንደየደረጃቸው ቅዱሳን ተብለው ይጠራሉ። በዚህ ዕለት ስለ ቅድስና እንዲሁም ዘወትር በዕለተ ሰንበት ከሌሎች ቀናት በተለየ ሁኔታ ለጽድቅ ስራ እንድንበረታ፣ ለቅድስና እራሳችንን እንድንለይ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይሰበካል ይነገራል። የሚዘመረውም መዝሙር “ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙለአሕዛብ ምግባሮ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ጸልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ፤ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ስሙንም ጥሩ፤ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯቸው፤ ለስሙም ምስጋናን አቅርቡ፤ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፤ ብል የማያበላሸው ሌባም የማያገኘው በሰማያት ያለ መዝገብን ለእናንተ ሰብስቡ፤ ተዘጋጅታችሁም ተቀመጡ፤ ክርስቶስ ወዳለበት ወደላይ አስቡ፡፡” በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ እንደ ዘመረልን በተለይ ሰንበት ነገረ እግዚአብሔር በተለየ ሁኔታ የሚዘከርባት፤ ኅሊናችን ከምድራዊው ሃሳብ ወጥቶ ወደ ሰማይያዊው የሚነጠቅባት፤ ለቅድስና የተለየች ቅድስት ዕለት መሆኗን ይጠቁማል። በቅዱስ መጽሐፍም “የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” (ዘፀ. ፳፥፰) ተብሏል፡፡ የሰንበትን ቀን አስቀድሞ የቀደሰ የባረከ እራሱ እግዚአብሔር ነው "እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው ቀደሰውም እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአልና"(ዘፍ.፪፥፫) እንግዲህ “የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” የተባለው እግዚአብሔር አስቀድሞ የባረከውን የቀደሰውን እኛ ድጋሚ የምንቀድስ የምንባርክ ሆነን ሳይሆን በዕለተ ሰንበት እራሳችንን በተለየ ሁኔታ ለቅዱስ ተግባር እንድንለይ ለሥጋችን ከምንፈጽማቸው ተግባራት ይልቅ ለተግባረ ነፍስ እንድናደላ ያስረዳናል። ምንም እንኳን ለስጋችን ስንባክን ጊዜ ቢያጥረን በዕለተ ሰንበት ግን ቅዳሴ ከማስቀድስ ቅዱስ ቃሉን ከመስማት ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ከመቀበል እንዳናስታጉል በሥርዓት ቤተ ክርስቲያን ታዝዘናል፡፡ ሊቃውንቱ በፍትሐ ነገሥት "ተጋብኡ ኩሎ ዕለት ኀበ ቤተ ክርስቲያን ወፈድፋደሰ በዕለተ ሰንበት ወበበዓላት ወበዕለተ ትንሣኤ ዘውእቱ ዕለተ እሑድ፤ ሁልጊዜ በቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ፤ ይልቁንም በዕለተ እሑድ፣ በዕለተ ቀዳሚት፣ በጌታ በዓላት ወደ ቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ፡፡” (ፍትሐ ነገሥት ገጽ ፪፻፶፬) ብለው ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ከሌሎች ቀናት በተለየ ሁኔታ ትኩረት የምንሰጥበት የምንቀደስበት ዕለት ቅድስት ሰንበት እንደሆነች ተናግረዋል። ሐዋርያዊው ቅዱስ አትናቴዎስም በቅዳሴው ላይ ሰንበት የተቀደስች እና ሕይወታችን እንዲቀደስባት የተለየች ቀን መሆኗን ሲያስረዳ እንዲህ ይላል፡፡ “ወንበል ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር ንትፈሣሕ ወንትሐሰይ ባቲ፤ ይህች ዕለት እግዚአብሔር የሠራት ያከበራት ዕለት ናትና በእርሷ ፈጽሞ ደስ ይበለን” ሰንበት ለክርስትያኖች ለመንፈሳዊ ደስታ የተለየች ቀን ናት። የመንፈሳዊ ደስታ ምንጩ በነፍስ የሚገኝ መንፈሳዊ በረከት ነው። ሰው የኃጢአትን ሸክም በንስሃ ሲያራግፍ፤ ነፍሱ በጸጋ እግዚአብሔር ስትቃኝ የሚሰማውን ደስታ በሌላ በምንም መንገድ ሊያገኘው አይችልም። ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ሰንበት ቅድስትና ለቅድስና የተለየች ቀን መሆኗን ያስተማረን አስቀድሞ በነብያት ትንቢት ያናግር የነበረ መንፈስ ቅዱስ አነሳስቶት ነው። ስለ ሰንበት መለየትና መቀደስ እንዲሁም የመንፈሳዊ ሐሴት ቀን ለመሆኗ ነቢዩ ቅዱስ ዳዊት መዝሙሩ እንዲህ ብሎ ነበር “እግዚአብሔር የሠራትቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።” (መዝ. ፻፲፯፥፳፬) ቅዱስ ዮሐንስም ራእዩ ሰንበት የጌታ ቀን ስለመሆኗ እንዲህ ይላል “በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ” (ራእ. ፩፥፲) ሰንበት የእኛ ቀን ሳትሆን ለጌታችን የምንሰራባት የምንለይባት ፣ የምንቀደስባት፣ ነገረ እግዚአብሔርን የምንዘከርባት የጌታ ቀን ናት። ለቅድስና የተለየች ቅድስት ቀን ናት ። በተለይ የክርስቲያን ሰንበት እሑድ “በኵረ በዓላት” ትባላለች በኵር ታላቅ እና መጀመርያ ማለት ነው፤ የመዳናችን መሰረት የተወጠነባት የጌታ የጽንሰቱ ቀን ዕለተ ሰንበት ናት፤ የመዳናችን ማረጋገጫ፣ የእምነታችን መሰረት ፣ የበዓላት ሁሉ ዓቢይ ትንሳኤው የተፈጸመው በዕለተ ሰንበት ነው። እንግዲህ በዚች ቅድስት ዕለት፥ ለቅድስና በተለየች ዕለትስ ሥጋውንም ነፍሱንም በሚያርያረክስ ተግባር የተሰማራስ ለነፍሱ ምን ዋስትና ይኖረዋል? ቅድስት በተባለች በሰንበት እሑድ ማንም በምንም ምክንያት ወደ ቤተ እግዚአብሔር ከመሄድ እንዳያስታጉል በስርአተ ቤተክርስትያን ተቀምጦልናል። ሌላው ቀርቶ በዕዳ በብድር በቀረጥ በግብር በአስራት በበኩራት ይሉኝታ ፈርቶ ማንም ቅድስት በምትባል በእሑድ ሰንበት ቅዳሴ እንዳያስታጉል ማንም ማንንም በዚህች ቅድስት ዕለት ምንም አይነት እዳ እንዳይጠይቅ ታዟል። “ወኢይኅሥሥ መኑሂ በይእቲ ዕለት ንዋዮ እምካልኡ ወኢይጽሐቅ አሐዱሂ እምእመናን በእንተ ኃሥሠ ዕዳ ። አው ተጻልኦ አው በዘይመስሎ ለዝንቱ። ወይሑሩ ቦቱ ኩሉሙ ሰብእ ኀበ ቤተ ክርስቲያን ወይምጽኡ ኲሉ ለለ ፩ ፩ እምእመናን ኅቤሃ በንጽሕ ወበትህትና ዘእንበለ ፍርሃት እምነ መኮንን ወእም በዓለ ዕዳ አው እምፈታሒ አው ዘይመስሎ። ወእመሰ ተሀበለ ፩ሂ ክርስቲያን ምክዕቢተ ይፍዲ፤ ከምእመናን ወገን አንድስ እንኳ በእሑድ ቀን ለገንዘብ መትጋት፤ገንዘቤን አምጣ ብሎ መጣላት፣ ዋስ መያዝ አይገባውም ። ሁሉም ምእመናን ወደ ቤተክርስቲያን በንጽሕና በትሕትና ሆነው ይምጡ እንጂ ። ዳኛ ግብሬን፣ አበዳሪ ብድሬን ፣ኤጲስቆጶስ ዐሥራት በኵራት ፣ ነጋ ድራስ ቀረጥ አምጡ ይሉናል ብለው ሳይፈሩ ይምጡ። ከነጋድራሶች አንዱ እንኳ ወደ ቤተክርስትያን ከሚሄዱ ሰዎች ቀረጥ ይቀበል ዘንድ የድፍረት ሥራ የሠራ ቢሆን እጽፍ አድርጎ ይክፈል።” (ፍትሐ ነገሥት ገጽ ፪፻፶፰-፪፻፶፱) ቅድስት ቤተክርስቲያን ይህን ያህል ጥንቃቄ የምታደርገው ሰዎች በተለያየ ምክንያት ከቤተ እግዚአብሔር እንዳይርቁ ከዛም አልፎ ተበዳይም ሆነ በዳይ
Show all...
👍 20 11
ይትበሃሉንና ቃሉን አነበብነው: ሐተታውንና ምሥጢሩን ተማርነው: በቅዱሳን ህይወት ወንጌሉን አየነው።[፪] @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
🥰 14👍 8 1👏 1
መላእክትም በእሳት ሰይፍ መተሩአቸው በመብረቅም አጨዱ አቸው አመድም ሆነው በነፋስ በተኑአቸው። የእነዚያም አጋንንት ቁጥራቸው ሰባት መቶ ሺህ እልፍ ከአንዱ ሺህ ነበር። ከዚህም በኃላ ጌታ ክርስቶስን የካዱ ወዳሉበት ወደ ምእራብ ሀገር ወሰደው። ነገስታቱና መሳፍንቱ መኳንንቱም በሚወ ጡበትና በሚገቡበት ጉዳና ላይ አቆመው ጌታችንም በዚች ጉዳና ብዙ መከራ ያገኝሀል ግን በርታ ታገስ ብሎት በዚያ ተወው። በዚያን ጊዜም የአርብ ንጉስ ጣዖታቱን አስይዞ መኳንንቱን ሰራዊቱን አስከትሎ በዚያች ጎዳና መጣ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስን በጎዳና ውስጥ በተገናኙት ጊዜ ጣኦታቱ ወድቀው ተሰባበሩ። ንጉሱም አባታችንን በአየው ጊዜ አንተ ጠጉር ለባሽ ምንድነህ ሰው ነህን አለው።አባታችንም አዎን ክብር ያለው የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያው የሆንኩ ሰው ነኝ ብሎ ለከሀዲው ንጉስ መለሰለት። ንጉሱም ዳግመኛ አባታችንን በዚያ አይሁድ በሰቀሉት ታምናለህን አለው አባታችንም በሰው ፊት አምንበታለሁ።ስለ እኔ በተሰቀለው አላፍርበትም ስለ እኔ ብቻ የተሰቀለ አይደለም ስለ አንተና ከአንተ ጋራ ስለ አሉትም ነው እንጂ ንጉስ ሆይ የዘላለም ህይወትን ታገኛላችሁ እመኑበት አለው። ንጉሱም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ተቆጣ ሰራዊቱንም ጠርቶ በፍጥረት እሳትን አንድዱ ለተሰቀለው ለናዝሬቱ ሰው ባሪያው ነኝ የሚለውን ጠጉር ለባሽ ወስዳችሁ ጨምሩት አላቸው። የእሳቱም ነበልባል በረጅም ዛፍ መጠን ከፍ ከፍ እስከሚል አነደዱ። አባታችን ግን ንጉሱና ሰራዊቱ ሁሉ እያዩት አልፎ በፈቃዱ ወደ እሳቱ ገባ። እሳቱም እንደወንዝ ውኃ ሆነ ሰረዊቱም እጅግ አደነቁ እኩሌቶቹም የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ንጉሱም ሲያደንቁ በአየ ጊዜ ፈፅሞ ተቆጣ ከሰባ ሰባት አርበኞቹ ጋራ በቁጣ ተነስቶ ያደነቁትንና ያመኑትን አንገታቸውን ቆረጠ ። በዚያችም ቀን የተቆረጡ አርባ መቶ ሺህ ሆነው ተቆጠሩ።ንጉሱም የአባታችንን አንገት ሊቆርጥ ሰይፉን መዞ ተወርውሮ ሄደ። ያን ጊዜም ከመብረቅና ከነጎድጓድ ጋራ ታላቅ ንውፅውፅታ ሆነ ንጉሱንም ከሰራዊቱ ጋራ አጠፋው ከከሀዲው ንጉስ ጋራ የሞቱት ቁጥራቸው አራት ሺህ እልፍ ሆነ። ጌታችንም አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስን ጠላቶችህንና የኔንም ጠላቶች አጠፋሁልህ አለው።አባተችን ግን በመብረቅ የሞቱትን ሬሳቸውን ነፍሳቸውንም መላእክተ ፅልመት ወደ ስቃይ ሲወስዱአቸው በአየ ጊዜ መድኃኒታችንን እሊህን ስሁታን ማርልኝ ሰው ስሁትና ከዳተኛ ነውና አቤቱ አንተ ግን መሀሪ ይቅር ባይ ታጋሽም ነህ አለው።አባታችንም ይህን ሲናገር ጌታችን ተሰወረ። አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም ከዚያ ሄደ ታላቅ ገደልም አገኘ እግሮቹንም በገመድ አስሮ በገደሉ ውስጥ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ።ሰይጣንም መጥቶ ያቺን ገመድ ቆረጣት ወደ ታችም ተወርውሮ ወረደ።ቅዱስ ሚካኤልም ቀድሞ አባታችንን ያዘው በእግርህ ላቁምህ ወይም በራስህ አለው በራሴ እቆም ዘንድ ተወኝ አለው ትቶት ሄደ። በዚያም በራሱ ቁሞ በጥርሶቹም ደንጊያ ነክሶ እስከ ሰላሳ አመት ኖረ አንጀቱና ናላው ሁሉ እየፈሰሰ አልቆ መላ አካሉ እንደእንጨት ቅርፊት ሆነ። ከሰላሳ አመትም በኃላ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አባታችንን ገብረ መንፈስ ቅዱስ እያለ ሶስት ጊዜ ጠራው። እርሱም እነሆኝ ጌታዬ አለ ጌታችንም እነዚያን ከሀዱዎች ምሬልሀለሁ ከዚህ ተነሳ አለው።ያን ጊዜ የነከሰውን ደንጊያ ትቶ ተነሳ።ጥርሱም ተነቅሎ በድንጊያ ተተክሎ ቀረ። ክንፎችም ተሰጥተውት እየበረረ ከእግዚአብሔር ፊት ደረሰ ጌታውንም ከማርክልኝ ከስጋቸው ጋራ ተነስተው በመጠመቅ ክርስቲያኖች ይሁኑ ብሎ ለመነው። መድኃኒታችንም በሽተኞችን ልትፈውስ ሙታንን ልታስነሳ ስልጣን ሰጥቼሀለሁ አሁንም ወደተገደሉት ሄደህ በመስቀል ምልክት በላያቸው አማትብ ህይወት መድኃኒት በሆነ ስሜም አስነሳቸው አለው።ያን ጊዜም በድኖቻቸው ወዳሉበት ሂዶ አስነሳቸው አጥምቆም ክርስቲያኖች አደረጋቸው ከእርሳቸውም ሄደ። ከዚህ ዓለም የሚለይበት በቀረበ ጊዜ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነሆ ተገለጠለት። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ እስከ አስራ አምስት ትውልድ የምህረት ቃል ኪዳን ሰጠው።የእድሜውም ዘመናት አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ሲሆን በሰላም በፍቅር አረፈ። ጌታችንም ነፍሱን ተቀበለ አቅፎም ሳማት በመላእክትና በቅዱሳን ሁሉ ምስጋና አሳረጋት። በጸሎቱ ያስምረን:ሀገራችንን ኢትዮጵያን ከገባችበት ፈተና በጸሎቱና በተሰጠው ቃልኪዳን ያድናት: አሜን! @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
16👍 10
መጋቢት ፭ እረፍቱ ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ መጋቢት አምስት በዚህች ቀን ተአምራቱና ትሩፋቱ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነ ቅዱስ አባት ተጋዳይ አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የእረፍቱ ቀን መታሰቢያ ሆነ፡፡ ይህም ቅዱስ አባት በተወለደባት ቀን ድንቅ የሆነ ስራን ሰራ ተነስቶ ከእናቱ እቅፍ ወርዶ ከጨለማ ወደ ብርሀን ላወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን እያለ ለስላሴ ሰግዷልና ምስጋናም አቅርቧልና። ህፃኑም ሶስት አመት በሆነው ጊዜ የእግዚአብሔር መልክተኛ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ህፃኑን ከእናቱ እቅፍ አንስቶ ብዙ ባህታውያን ወዳሉበት ገዳም ወስዶ በደጅ አኖረው ወደ አበምኔቱ ወደ አባ ዘመደ ብርሀንም ገብቶ ስለ ህፃኑ እግዚአብሔር ያዘዘውን ሁሉ ነገረው። በዚያን ጊዜም ነገሩ እውነት እንደሆነ ይረዳ ዘንድ አባ ዘመደ ብርሀን ተነስቶ ወደ ደጅ ወጣ። መልአኩም እንደ ነገረው ህፃኑ ከበር ተቀምጦ ፈገግታን ተሞልቶ አገኘው። እጅግም ደስ ብሎት ለእግዚአብሄር ሰገደ ህፃኑንም አንስቶ ሳመው ታቅፎም ወደ በአቱ አስገባው። በፍቅር በስነስርአት አሳደገው። የዳዊትን መዝሙርና ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸውን መፃህፍት ሁሉ ብሉይንና ሀዲስን አስተማረው። ከዚያም በኃላም ክህነት ይሰጠው ዘንድ ስሙ አብርሀም ወደሚባል ጳጳስ ወሰደው ጳጳሱም በአየው ጊዜ ደስ አለው።የዲቁና ማእረግንም ሾመው እንደ ቀዳሜ ሰማእት እስጢፋኖስም ፀጋንና ሞገስን የተመላ ሆነ። ከጥቂት ቀኖች በኃላም በጌታችን ትእዛዝ ቅስና ተቀበለ። በፆም በፀሎት በስግደት በብዙ ትጋትም እየተጋደለ በበረሀ ውስጥ ብቻውን ኖረ። በበረሀም ብዙ ዘመናትን ሲኖር ነፍሱን "ነፍሴ ሆይ እወቂ በእግዚአብሔር ፊት ራቁትሽን ትቆሚ ዘንድ እንዳለሽ እንግዲህስ ፅኚ በርቺ ታገሺ!" ይለት ነበር። ቆዳው ከዐጥንቱ እስቲጣበቅ ያለ መብልና ያለ መጠጥ በእንዲህ ያለ ግብር በገድል ተጠምዶ ኖረ።ከእፅዋት ፍሬዎች ወይም ከእንጨት ስሮች አልተመገበምና ለስጋውም የሚጠቅም ምንም ምን ምክንያት አልፈለገም። ለገብረ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር እንዲህ አለው ከእንግዲህ በአለም ካሉ ሰዎች ከካህናት ከመነኮሳት ወይም ከምእመናን ህዝባውያን እንዳያውቁህ አደርግልሀለሁ። እንዳንተ ካሉ በቀር አንተ ራስህ ብትፈቅድ እንጂ መላእክትም ይጎበኙሀል። የብርሀን ሰረገላም ይሁንልህ መድረስ ወደምትሻበት ሁሉ ብረር እኔንም ማየትና በፈለግህ ጊዜ ከአባቴና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በሶስትነቴ ታየኛለህ። አሁንም ወደ ኢትዮጵያ ምድር ሂድ በዚያም ከደይን የምታወጥቸው ነፍሳት አሉህ አለው። ከዚህም በኃላ ስልሳ አንበሶች ስልሳ ነብሮች በፊት በኃላ አጅበውት ወደ ኢትዮጵያ ምድር ተጓዙ። የእግዚአብሔር መልእክተኛ ቅዱስ ገብርኤልም ከአንበሶችና ከነብሮች ጋር በነፋስ ሰረገላ አሳፍሮ ይመራው ነበር። ወደ ምደረ ከብድም አደረሰው ከዚያም ወደ ልዩ ተራራ ወደ ደብረ ዝቋላ ወሰደው። አባታችንም በባህሩ ቁሞ ምስራቁን ምዕራቡን ሰሜኑን ደቡቡን አራቱን ማእዘን ተመለከተ።የኢትዮጵያ ሰዎች የሚሰሩትን ኃጢአታቸውን በአይኖቹ ፊት የተገለጠ ሆኖ አየ። በራሱም ተዘቅዝቆ ተወርውሮ ወደ ባህሩ ውስጥ ገባ እሊህን የእጅህ ፍጥረቶች የሆኑትን ካልማርካቸው ከእዚህ ባህር እንዳልወጣ በእግሮቼም እንዳልቆም በህያው ስምህ እምላለሁ እያለ ማለ እንዲሁም ሆኖ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ኖረ። ስምህን የጠራውን መታሰቢያህን ያደረገውን እምርልሀለሁ የሚል ቃል በመልአክ አማካይነት ወደ አባታችን መጣ። አባታችንም መልአኩን መላውን የኢትዮጵያን ሰው ካልማረልኝ ከዚህ ባህር አልወጣም አለው መልአኩም ከአጠገቡ ሄደ። አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም በዚያ ባህር ውስጥ መቶ ዓመት ኖረ ስጋው ሁሉ አለቀ ደሙም በባህሩ ውስጥ ፈሰሰ አጥንቶቹም እንደበረዶ ነጭ ሆነው ታዩ። አጋንንትም ከአራቱ ማእዘን በየቀኑ ሰባት መቶ ሽህ ሶስት መቶ ሽህ እየሆኑ በመምጣት በቀስታቸው ይነድፉታል እስከ መቶ አመትም አጥንቶቹን በሻፎ ድንጋይ ይፍቁታል ይህን ሁሉ መከራ በትእግስት ሲቀበል ኖረ። ከዚህም በኃላ ጌታችን ወደርሱ መጥቶ ከባህሩ ዳር ቆመ። አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስንም መላውን የኢትዮጵያ ሰው ምሬልሀለሁና ተነስተህ ውጣ አለው ያንጊዜም ወጣ አጥንቶቹም እንደ ወንፊት ቀዳደሰ የተበሳሱ ሆነው ተገኙ ጌታም ዳሰሰውና ጤነኛ አደረገው ወደ ምድር ከብድም ሰደደው። ከዚያም ወደ ላይ ወጥቶ ከፀሀ ከሰማይ በታች እስከ ሰባት አመት ኖረ። ዳግመኛም ወደ ምድረ ከብድ ተልኮ እንደ አምድም የተተከለ ሆኖ ሰባተረ አመት ቆሞ ኖረ። ወደ ሰማይም ሲመለከት ቅንድቦቹን አልከደነም ራሱንም ወደ መሬት ዝቅ አላደረገም ነበር እጆቹም ወደ ሰማይ ተዘርግተዋል። እነሆ ሰይጣንም በቁራ ተመስሎ መጣ አይኖቹንም ወደ ሰማይ ያንጋጠጡ ሁለቱን አይኖቹን አንቁሮ አሳወረው። እርሱ ግን ምንም ሳያጓድል እስከ ሁለት ሳምንት ድረስ እንደ ቀድሞው በመትጋት ሲፀልይ ኖረ። ከዚህም በኃላ ሚካኤልና ገብርኤል መጥተው በፊቱ ቆሙ በሁለቱ አይኖቹ ላይም እፍ አሉበት ብርሀንም ተሰጥቷቸው እንደ ቀድሞው አዩ። ከሰማይ ታላቅ ኃይል ተሰጥቶሀልና ጠላቶችህን ትበቀላቸው ዘንድ ወደ ዝቋላ ሂድ አሉት ከዚያም መላእክት ከአጠገቡ ሄዱ። እርሱም ተነስቶ ወደ ዝቋላ ተጓዘ በጎዳናም ሲጓዝ ሶስት ሽማግሌዎች ከእንጨት ጥላ በታች ተቀምጠው አየ አባታችንም በአያቸው ጊዜ ልሰውራቸው ብሎ በልቡ አሰበ። እንርሱም ፈጥነው በእግዚአብሔር ዙፋን ተማጥነናልና ሶስታችንንም በጀርባህ እያዘልክ አንዳንድ ምእራፍ ሸኘን እንጂ አትተውን ብለው ተጣሩ። በመጣም ጊዜ ሁለመናቸውን ሽበት የከበባቸው የደከሙ ሽማግሎች ሁነው አገኛቸው አንደኛውንም አንስቶ በጀርባው አዘለው ወደ አንድ ምእራፍም አደረሰው ሽማግሌውም ከዚህ አሳርፈኝ አንተ ደክመሀል የማትበላ የማትጠጣ ስለሆንክ አለው አባታችንም ሽማግሌ ሆይ በምን አወቅከኝ አለ። ሽማግሌውም ሂደህ ባልንጀሮቼን አምጣልኝ አለው ተመልሶ ሁለቱ ወደአሉበትም ደርሶ ሁለተኛውን ሽማግሌ በጀርባው አዝሎ ወደ ቀደመው ሽማግሌ አድርሶ አብሮ አስቀመጠው ሶስተኛም ተመልሶ ሶስተኛውን ሽማግሌ አዝሎ ሁለቱ ወዳሉበት አድርሶ በአንድነት አኖረው፡፡ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም እነዚያን አረጋውያን እናነተ ከወዴትናችሁ መአዛችሁ ልብ ይመስጣል እጅግም ደስ ያሰኛል አላቸው።እነርሱ ግን ተነስተው ቆሙ አንድ ሲሆኑ ሶስት ሶስት ሲሆኑ አንድ መሆናቸውን ገለጡለት የአባቶች አለቃ አብርሀም እንደ አየ። ያንጊዜም የእግዚአብሔርን የጌትነቱን ክብር አየ የእሊያ አረጋውያንም ፊታቸው ተንቦገቦገ ከፀሀይና ከመብረቅ ብልጭታም ሰባት እጅ በራ አባታችንም በምስጢራት ጎርፍ የተዋጠ ሆኖ ፈራ ተንቀጠቀጠ በምድር ላይም ወደቀ። ህልምን የሚአልምም መሰለው ከዚያም ጌታችን አባታችንን አነቃውና መቶ አመት ያህል ስጋህን ሲነዱፉህ አጥንቶችህን ሲፍቁህ የኖሩ አጋንንትን ታጠፋቸው ዘንድ ወደ ዝቋላ ተራራ ውጣ አለው። እኔ እንደ ወሰድኩህ ባለማወቃቸው በባህር ውስጥ አለ በማለት በትእቢት ላይ ናቸው ሰባቱ ሊቃነ መላእክትም ይረዱሀል መባርቅትም በፊት በኃላ ሆነው ይከተሉሀል አለው። ያን ጊዜ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ በመብረቅ ላይ ተጭኖ በረረ እነዚያ አጋንንት ወደአሉበትም ወረደ። ደመናትም ከበቡአቸው
Show all...
👍 20 11🥰 1👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
«ጾም እስከ ስንት ሰዓት ነው?» የቅድስቲቱ ቤተክርስቲያን ሥርዓቱ በልኬት እና በምክንያት የታጀበ ነው። ጾምን ስንመለከት አብዛኞቻችን በተለምዶ ሰዓት ሳንጠብቅ (እስከ 3፣ 6፣ 7፣ 9፣ 11 ሰዓታት እያልን) እንጾማለን እንጂ የአዋጅ አጽዋማት የተወሰነ የተገደበ ሰዓት አላቸው። ፍትሐ ነገሥታችን “ሕማማት እስከ 12 ሰዓት ይጹሟቸው፥ ሌሎቹን አጽዋማት በዓለ ልደት እና ጥምቀት ረቡዕ እና ዐርብ የሚውሉባቸው ካልሆኑ በቀር እስከ 9 ሰዓት ይጹሙ” (ፍት.ነገ አን 15፥565-566) ብሏል። የአጽዋማትን ዝርዝር ካስቀመጠ በኋላም በዚሁ አንቀጽ ቁጥር 572 ላይ ደግሞ “በእነዚህ በታዘዙት ጾሞች ከቀኑ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ይጹሙ፣ ... ከዚህ አብልጦ የጾመ ግን ዋጋው ይበዛለታል፣ ከጥሉላት ምግቦች መታቀብ ካልሆነ በቀር እሑድና ቅዳሜ ግን አይጹሙ” ብሎ ወስኗል። ዐቢይ ጾም/ጾመ ሁዳዴ/ጾመ ዐርብዓ ግን ይለያል። “በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ሱባኤ(ዘወረደ) ፀሐይ እስኪገባ ይጹሙ፣ ሌሎቹን ሳምንታት(ከቅድስት እስከ ሆሣዕና) እስከ 11 ሰዓት ይጹሙ፥ በሰሙነ ሕማማት ግን ኮከብ እስኪወጣ ይጹሙ” ብለዋል (ፍት.ነገ.አን 15፥595) ፍትሐ ነገሥት ቁጥር 578 ላይ ደግሞ “(የሰሙነ ሕማማትን) ዓርብንና ቅዳሜን(አክፍሎት) ግን ሁለቱንም በአንድነት ይጹሟቸው፣ የሚችል እስከ ሌሊት ዶሮ ጩኸት ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው፣ ሁለቱን በአንድነት መጾም የማይቻለው ግን ቅዳሜን ይጹም” ተብሎ ህግ ተሠርቷል። የበረከት ጾም ያድርግልን! @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 109 42🥰 13👏 13🙏 10🔥 3😢 3😱 1
"ዘወረደ" በዲያቆን ዘማሪ ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ በእርሱ ፍቃድ በአባቱ ፍቃድ በመንፈስ ቅዱስ ፍቃድ ከሰማያት ወረደ ከድንግል ማርያም ተወለደ። ዓለሙን እንዲሁ ወደደና ከሰማያት በላይ ወረደና በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወሰነ አምላከ አማልክት   ከሰማያት የወረደው ፍቅር ስቦት የመጣዉ   ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ፈራጅ ነዉ          አዝ።።።።።።።።።።። ቅድመ አለም ተወልዶ ያለ እናት ድህረ አለምም ያለ አባት የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥም ሰው ሆነ ሁሉ በእርሱ ይኸው ተከናወነ   ከሰማያት የወረደው ፍቅር ስቦት የመጣዉ  ወልደ አብ ወልደ ማርያም ክርስቶስ አምላክ ነዉ          አዝ።።።።።።።።።።። የማይታይ ታየ በምድር ረቂቁ ገዘፈ ስለፍቅር ሥጋን ተዋሕዶ ሆነልን ፈውሥ አማኑኤል የነገስታት ንጉሥ  ከሰማያት የወረደው ፍቅር ስቦት የመጣዉ    ወልደ አብ ወልደ ማርያም እግዚአብሔር እርሱ ነዉ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 21🥰 20 8😱 4🔥 1
ዘወረደ የዐብይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት የመጀመሪያ የዐብይ ጾም መግቢያ እሁድ ዘወረደ ይባላል። በዚህ ቀን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ ወደ ምድር መውረድ ይሰበካል ይዘመራል። ሰውም በታላቅ ፍርሃት ወደ አምላክ መቅረብ እንዳለበት ይነገርበታል። ደግሞም ጾመ ሕርቃል ይባላል። ስያሜውም በ614 ዓ.ም ኪርዮስ የተባለ የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር ጥቃት አደረሰ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው ቤተ መቅደስ ውስጥ ሲገባ ንግሥቷ በክብር አስቀምጣው የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው ቢነካው አቃጠለው ዲያቆናቱንም አሸክሞ ሌላውን ንዋየ ቅዱሳን ዘረፈ: 60 ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ 3 ሺ የሚሆኑትን ማርኮ ከተማውንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን ይመለሳል። በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ ገብተው የተሸሸጉ ተስብሰበው ከ14 ዓመት በኃላ በ628 ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲያኑ የሮም ንጉስ ሕርቃል ይነግሩታል። እርሱም "ሐዋሪያት ሰው የገደለ እድሜውን በሙሉ ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርገው?" አላቸው "እኛ የአንተን እድሜ ተከፋፍለን እንጾማን" ብለን አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው ጾሙን በሚገባ ጾመውታል። ምስባኩም:- መዝ ፪፥፲፩ "ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ወተሐሰዩ ሎቱ በረዓድ አፅንእዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐፅ" "ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ በርአድም ደስ ይበላችሁ ተግሣጹን ተቀበሉ ጌታ እንዳይቆጡ" በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡት ጥቅሶች: -ዕብ ፲፫፥፯-፲፯ -ያዕቆብ ፬፥፮ እስከ ፍጻሜ -የሐዋ ሥራ ፳፭፥፲፫ እስከ ፍጻሜ ወንጌሉም:- ዮሐ ፫፥፲-፳፭ "¹⁰ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን? ¹¹ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ምስክራችንንም አትቀበሉትም። ¹² ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ? ¹³ ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው። ¹⁴-¹⁵ ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል። ¹⁶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ¹⁷ ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና። ¹⁸ በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል። ¹⁹ ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው። ²⁰ ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤ ²¹ እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደ ሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል። ²² ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ይሁዳ አገር መጣ፥ በዚያም ከእነርሱ ጋር ተቀምጦ ያጠምቅ ነበር። ²³ ዮሐንስም ደግሞ በሳሌም አቅራቢያ በሄኖን በዚያ ብዙ ውኃ ነበርና ያጠምቅ ነበር፥ ²⁴ እየመጡም ይጠመቁ ነበር ዮሐንስ ገና ወደ ወኅኒ አልተጨመረም ነበርና። ²⁵ ስለዚህም በዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና በአይሁድ መካከል ስለ ማንጻት ክርክር ሆነ።" @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 15 10😢 1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ዐብይ ጾም ------------------------------- @Ethiopian_Orthodox ------------------------------- ጾም ማለት "ተወ"፣ "ታቀበ" ፣"ታረመ" ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ነው። ፍቺውም ምግብ መተው ፤መከልከል፤ መጠበቅ ማለት ነው። ጾም ማለት ሰውነት ከሚያስፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል፤ መወ'ሰን ማለት ነው። ወይም ሰውነት የሚያምረውን የሚያስጎመጀውን ነገር መተው ማለት ነው። ጾም ከሃይማኖት ጋር ዝምድና ስላለው ሃይማኖት ባለበት ሁሉ ጾም አለ። ✳️ ጾም በብሉይ ኪዳን ከፍተኛ ቦታ አለው። ነብያት ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ወራት እህል ውሃ በአፋቸው አይገባም ነበር። (ዘፀ 30÷34-28) ✳️ በኃጢአት ብዛት የታዘዘውን የእግዚአብሔርን መዓት የሚመልሰው ሕዝቡ በጾም ሲለምኑት ሲማልዱት ነበር። (ዮሐ 2÷7-10) ✳️ በሐዲስ ኪዳንም ጾም ሰው ሰራሽ ህግ ሳይሆን እራሱ መድኃኒታችን በመዋዕለ ሥጋዌው የሥራ መጀመሪያ አድርጎ የሰራው ህግ ነው። ✳️ ይህ ብቻ ሳይሆን በቁራኝነት አብሮ የሚኖር መንፈስ እርኩስ ሰይጣን እንኳን በጾም የሚወገድ መሆኑን መድኃኒታችን ተናግራል።(ማቴ 17÷21) ✳️ ቤተክርስቲያንን እንዲያገለግሉ የታዘዙት ሐዋርያትም ከመንፈስ ቅዱስ በየጊዜው ትዕዛዝ የሚቀበሉበት በጾም እና በጸሎት ላይ እንዳሉ ነበር።(ሐዋ 13÷2) ✳️ ለስብከተ ወንጌል የሚያገለግሉ ዲያቆናት ቀሳውስት የሚሾሙት በጾምና በጸሎት ነበር። (ሐዋ 13÷3) ጾምስ በታወቀው እለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ መከልከል ነው። ጾም ማለት ጥሉላት ማባልዕት ፈፅሞ መተው ሰውነትንም ከመብልና ከመጠጥ ከሌላውም ክፉ ነገር ሁሉ መጠበቅ፣ መግዛት፣ መቆጣጠር፣ በንስሐ ታጥቦ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ "ይቅር በለኝ" በማለት ቅድመ እግዚአብሔር በመንበረከክ ምሕረት ለአምላክ ለመቀበል መዘጋጀት ነው። ፆም ነፍስን ቁስልን የምትፈውስ፣ ሀይለ ፍትወትን የምታደክም የበጎ ምግባር ሁሉ መጀመሪያ ከእግዚአብሔር ጸጋን የምታሰጥ የወንጌል ስራ መጀመሪያ ፣ የፅሙዳን ክብራቸው፣ የደናግል የንፅህና ጌጣቸው ፤የንፅህና መገለጫ ፣ የጸሎት ምክንያት እናት፤ የእንባ መናኛ መፍለቂያ አርምሞን የምታስተምር፣ ለበጎ ስራ ሁሉ የምታነቃቃ፣ ሰውነትን በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ትህትናን ገንዘብ ለማድረግ የምትረዳ መድኃኒተ ነፍስ ናት። ከህገ ልቦና ከነበሩ አበው አንስቶ በዘመነ ኦሪት እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ በተለያዩ ጊዜያት የነበሩ ቀደምት አበው ነቢያት፣ ነገሥታት፣ ካህናት በፆምና በጸሎት ፅመድ ሆነው እግዚአብሔር አምላካቸው ከክፉ ነገር እንዲሰውራቸው በይቅርታ እንዲጎበኛቸው ሀይልም እንዲጎናፅፋቸው ተማፅነው ሀሳባቸውን ፈፅሞላቸዋል። በሀዲስ ኪዳን ጾም ስለ ፅድቅ ተብሎ መከናወን ያለበት አብይ ተግባር ነው።// ማቴ 5÷6// ስጋዊ ጥቅምን ለማግኘት ተድላ ሰጋን በመሻት ሳይሆን ዘላለማዊ መንግስት ለመውረስ ስለ ፅድቅ ተብሎ የሚፈፀም ነው። ጾም እንደምን ነው ቢሉ የስጋ ምግባር ነው። ምፅዋት የገንዘብ ግብር እንደሆነች አንድም ምፅዋት ስጋን መገበር ነው። ምፅዋት ገንዘብ መገበር እንደሆነች ~~~ ስለዚህም የሚፆም ሰው በፈቃደ ስጋው ላይ ድልን ይቀዳጃል። በእምነት ሆኖ የለመነውን እግዚአብሔር ይሰጠዋል። ሰማያዊ የሆነውን ምስጢር ለማየት ከዓለማዊነት ነገሮች ተለይቶ ይነጠቃል። በዓለም እየኖረ ከዓለሙ ይለያል። ከዓለም አይደለምና //ዮሐ 15÷19// 🔰ዐብይ ጾምም ቤተክርስቲያናችን እንድንጾም ካወጀችልን ጾም አንዱ ነው። አብይ ጾም የተለያዩ ስሞች አሉት: ፩. ዐብይ ጾም: ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም በመሆኑ እንዲሁም ዐብይ እግዚአብሔር ወዓቢይ ኀይሉ ዓቢይ እግዚአብሔር ወብዙኃ አኰቴቱ የተባለ ጌታ የጾመው ስለሆነ፣ //መዝ 47÷1 መዝ 146÷5// ዐብይ ጾም መባሉ ትልቅና ታላቅ ጾም መሆን ለማሳወቅ ነው። ይህ ጾም ታላቅ መባሉም ለ55 ቀናት ያህል መጾሙና ከሌሎች አፅዋማት ጋር ሲነጻጸር በቁጥር መብለጡ ብቻ ሳይሆን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንጦስ መጾም ሳይገባው ለእኛ አርአያና ትልቅ ምሳሌ ለመሆን የጾመው ጾምም በመሆኑ ነው። ፪. ሁዳዴ ጾም: ይህም የመንግሥት እርሻ ወይም ማንኛውም የሕዝብ ብዛት ያለበት ሥራ ሁዳድ ስለሚባል ሲሆን ከአጽዋማት ሁሉ ብዙ ቀናት ስለሚጾምና ኃያሉ አምላካችን ስለጾመው ነው።፣ /አሞ 7÷1 // ፫. በዓተ ጾም : ፆም መግቢያ፣ መባቻ ወይም ጾሙ የሚሰፍርበት በዓል ማለት ነው ፬. ጾመ አርቦ: ጌታችነ ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመዉ 40// አርባ ቀን ስለሆነ ነው //ማቴ 4÷1 ፭. ጾመ ኢየሱስ : ጾሞ ፣ ጹሙ ብሎ ስላዘዘን፣ ፮. ጾመ ሙሴ : ቅዱስ ያሬድ በዘወረደ ሰኞ "ዕዝል ከመዝ ይቤ ሙሴ እስመ ለዓለም ፣ ሙሴኒ ይቤ በውስተ ኦሪት" እያለ በጾመ ድጓ ስለ ዘመረ ነው። 🌿ዐብይ ጾም ጌታ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም ነው። //ማቴ 4÷1 ምእመናንም ጌታቸው ያደረገውን ምሳሌ ተከትለው ይጾሙታል። 🌿ዐብይ ጾም ስምንት ሳምንታት //55 ቀኖች // አሉት። 7//ሰባት ቅዳሜ 8//ስምንት እሁድ ይገኛሉ። አስራ አምስት ቀን 55//ማለት ነው። ከጥሉላት እንጂ ከእህል ወኃ ስለማይጾሙ የጾሙ ወራት አርባ ቀን ብቻ ይሆናል። የዐብይ ጾም ሶስት ክፍሎች ፩. ዘወረደ ( ጾመ ሕርቃል)፦ ይህም ጾሙ ከሚገባበት ሰኞ ጀምሮ እስከ እሁድ ያረሰ ያለው 7 ቀን ነው። ፪. የጌታ ጾም፦ ይህም ከቅድስት ሰኞ እስከ ሆሣዕና ዋዜማ ዓርብ ድረስ ያለው አርባ ቀን ነው። ፫. ሕማማት፦ ይህ ጌታችን በአልዓዛር ቤት ለማዕድ ከተቀመጡበት የሆሳዕና ቅዳሜ ጀምሮ እስከ ሥዑር ቅዳሜ ያለው መከራን የተቀበለበት 8 ቀን ሕማማት ነው። ይህም ፯+፵+፰=፶፭(7+40+8=55)ቀን ይሆናል። የዐብይ ጾም ሳምንታት 8 ሲሆኑ: ፩. ዘወረደ ፪. ቅድስት ፫. ምኲራብ ፬. መጻጉዕ ፭. ደብረ ዘይት ፮. ገብርሔር ፯. ኒቆዲሞስ እና ፰. ሆሣዕና ናቸው። ጾሙን ጾመን ድኅነት የምናገኝበት የበረከት እንዲሁም ቤተክርሰቲያናችንን ከመዓት የምንታደግበት ያድርግልን! አሜን! @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 49 13🔥 2😢 2
አበው ከአፋፍ ላይ ነፋስ ከአፍ ላይ አስትንፋስ፡፡ እንዲሉ የሰው ልጅ በዘመኑ ሁሉ ሲተነፍስ ይኖራል፡፡ ይህም በተፈጥሮው ባሕርየ ነፋስ ለመኖሩ ምልክት ነው:: በጤናማ ሕይወት የሚታየው ቋሚ የሰውነት ሙቀቱ፤ በተለያዩ እንቅስቃሴዎችና በጤና መታወክ ጊዜ የሚያስመዘግዘበው ከፍና ዝቅ ያለ የሰውነት ሙቀት በሰውነቱ ባሕርየ እሳት ለመኖሩ በቂ ማስረጃ ነው፡፡ ምክንያቱም ዋዕይ ባሕርየ እሳት ነውና። ከሰው ሰውነት ብዙው እጅ ውኃ መሆኑ ደግሞ ከውኃ መገንባቱን ያሳያል፡፡ በተጨማሪም የሰው ልጅ በሚሞትበት ጊዜ አፈር ይሆናል፡፡ «አፈር ነህና ወደ አፈርም ትመለሳለህ>> ተብሏልና፡፡ ዘፍ. 3፥19 በሌላ አቅጣጫም ብንመለከት ሰው ሁሉ ግዙፍ ነገር ተመግቦ ግዙፍ ነገር ማስወገዱ የአፈርነት ባሕርይ አለው ያሰኛል:: ምክንያቱም የምንመገበው ማንኛውም ነገር ምንጩ አፈር ፍጻሜውም አፈር ነውና። የማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ <<በዪውም አፈር ተብዪውም አፈር ነውና።>> በማለት ምግቡ ብቻ ሳይሆን ተመጋቢው የሰው ልጅም አፈር መሆኑን ይገልጻል:: ማቴ. 15፥20   ቅዱስ ዳዊት << የዘመኖቻችንም ዕድሜ ሰባ ዓመት ቢበረታም ሰማንያ ዓመት ነው።>> ይላል፡፡ መዝ 89፥10 ይህን የሰው ልጃ ዕድሜ አራቱ ባሕርያተ ሥጋ በእኩል ይካፈሉታል፡፡ ይህም ማለት ምንም እንኳን አራቱም በሰው ልጅ የሕይወት ዘመን ሙሉ በአንድነት ቢዘልቁም በተለየ መልኩ ጐልተው የሚታዩበት ሃያ ሃያ ዘመን አላቸው ማለት ነው።   ከአንድ አመት እስከ ሃያ ዓመት ያለው ዕድሜ የነፋስ ባሕርይ ጉልቶ የሚታይበት በመሆኑ ይህ ዘመን <<ዘመነ ነፋስ>> ወይም «ምግበ ነፋስ» ይባላል፡፡ በዚህ ወቅት ነፋስ ወደ ወደደው ይነፍሳል» እንደተባለው ሕፃናት እንደመሰላቸው ሽው ሽው ይላሉ፡፡ ዮሐ 3፥8 ነገር ግን ነፋስ ምንም እንደማያሳይ ሁሉ በምግበ ነፋስ ያሉ ሕፃናትም ብዙ የሚያስተውሉት ነገር የለም፡   ሕፃናት በዘመነ ነፋስ ስለሚገኙ ዐላዋቂነት ያጠቃቸዋል፡፡ የያዙትን ውድ ነገር ዋጋ ለሌለው ብልጭልጭ ነገር ለመለወጥ በቀላሉ ይታለላሉ፡፡ ይህን በማነጻጸር እኛም በምግበ ነፋስ እንደሚገኝ ብላቴና ሆነን ሰማያዊውን ዓለም በኃላፊውና በብልጭልጩ ዓለም እንዳንለውጥ፤ ከሃይማኖትም ወደ ጥርጥርና ወደ ክህደት እንዳንመለስና በአእምሮ ሕፃናት መሆን እንደማይገባን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ሲል ይመክረናል፡፡ <<እንደ ስሕተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደፊት አይገባንም::>> ኤፌ 4፥14   ከሃያ እስከ አርባ ያለው ዕድሜ ደግሞ የእሳት ባሕርይ ጎልቶ የሚታይበት ነውና <<ዘመነ እሳት>> ወይም <<ምግበ እሳት>> ይባላል፡፡ ይህ ሰውን ወጣት የሚያሰኘው ዘመን ነው:: ከዚህም ምስጢራዊና ምሳሌያዊ ትምህርት በመነሣት ወጣትነትን «የእሳት ዘመን>> ወይም <<ፋየር ኤጅ>> ማለት ከቤተክርስቲያን የተገኘ እንጂ ከፈረንጅ (ከአውሮፖና ከአሜሪካ) የተወረሰ አለመሆኑን ልብ ይሏል፡፡ እሳት ብሩህ እንደሆነ ወጣቶችም ክፉና ደግን የሚያስለይ የዕውቀት ብርሃን አላቸው፡፡ ሆኖም እሳት ያገኘውን ልብላ (ላቃጥል) እንደሚል ሁሉ እንደዚሁም ወጣቶች ሁሉ የሚያምራቸውና ትምክህተኞች ናቸው። ከአርባ እስከ ስድሳ ያለው ዘመን <<ዘመነ ማይ>> ወይም <<ምግበ ማይ>> ሲባል ከስድሳ እስከ ሰማንያ ያለው ደግሞ <<ዘመነ መሬት>> ወይም <<ምግበ መሬት (አፈር)>> ይባላል::   ከሃያ እስከ አርባ ዘመን ያለው ዕድሜ ምግበ እሳት ቢባልም አንድ ወጣት ልክ ሃያኛ ዓመቱን ሲይዝ እሳታዊ ባሕርይ መጋቢነቱን ክነፋሳዊ ባሕርይ ይቀበላል ማለት አይደለም፡፡ ከአሥራዎቹ ዓመታት ጀምሮ እሳታዊ ባሕርይ መጋቢነቱን በእጁ ለማድረግ ሲጥር ነፋሳዊ ባሕርይም በበኩሉ ይዞታውን ለማስከበር እየታገለ እስከ ሃያዎቹ አጋማሽ ሊዘልቅ ይችላል:: በዚህ ትግል ምክንያት እሳታዊ ባሕርይ የበረታ እንደሆነ የወጣትነት መገለጫ ምልክቶች በአሥራ ሁለትና ከዚያም በታች በሆነ ዕድሜ ይከሠታሉ፡፡ ምግበ ነፋስ ከበረታ ደግሞ በሃያዎቹ ዕድሜ ውስጥ ያሉ ወጣቶች ከጎረምሳነት ይልቅ ልጅነት ማሳየት የሚጀምሩት ዘግየት ብለው ይሆናል፡፡ ወጣትነትን በዘመን ሰፍሮ በዚህ ጊዜ ይከሠታል በዚህ ጊዜ ደግሞ ያክትማል» ብሎ የተወሰነ እኃዛዊ መረጃ ለመስጠት አስቸጋሪ ያደረገው ይህ መዋዠቅ ነው።   የእሳትነት ዘመን (ጕልማስነት) ከሃያ ዓመት በታች ሊጀምር እንደሚችል መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ዖዝያን <<የዐሥራ ስድስት ዓመት ጎልማሳ የነበረውን>> በማለት የሰጠው ገለጻ ያስረዳል፡፡ ዖዝያንን በዐሥራ ስድስት ዓመቱ ጎልማሳ ብሎታልና፡፡ 2ዜና 26፥1   ጎልማስነት ያለጥርጥር እስከ አርባና እስከ ሠላሳዎቹ መገባደጃ ድረስ ወይም ከዚያም በላይ ሊቆይ እንደሚችል ደግሞ «ኢዮሣፍጥም መንገሥ በጀመረ ጊዜ የሠላሳ አምስት ዓመት ጎልማሳ ነበር።>> ከሚለው የእግዚአብሔር ቃል መረዳት ይቻላል:: 2ዜና 20፥ 31 ምዕራፍ ሁለት ይቀጥላል...... @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 23 10