Brook Fekadu
Open in Telegram
1 815
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 815
«ቸርነትን አሰብኩት። በአሏህ ላይ መልካም ጥርጣሬ ከማድረግ በስተቀር ግንድም ሆነ ቅርንጫፍ እንደሌለው ተረዳሁኝ። የንፉግነት ግንዱና ቅርንጫፉ ደግሞ በአሏህ ላይ መጥፎ ጥርጣሬን ማሳደር መሆኑን አወቅኩኝ።»
ሐሰን አልበስሪ [ረዐ]
:
አንፊቅ ዩንፈቅ ዐለይክ!
https://t.me/Brookfekaduu
1 815
«ሴት ልጅ የማህበረሰቡ ግማሽ ናት እሷ
ከተስተካከለች ግማሽ ህዝብ ይስተካከላል»
አሽረፈል ኸልቅ የአለሙ እዝነት ሰይዲ ﷺ
ያስተላለፉት ውብ መልዕክት!
https://t.me/Brookfekaduu
1 815
فقلت اسةغفروا ربكم انه كن غفر
አልኳቸዉም፦ ጌታችሁን ምህረትን ለምኑት ፤ እርሱ በጣም መሐሪ ነዉና።
ያ ረብ ምህረትህን አቅርብልን 🙏🙏
https://t.me/Brookfekaduu
1 815
ከቻልክ
መልካም ነገር ሁሉ የሚገባበት በር ሁን፣
ካልሆነ ብርሃን የሚገባበት መስኮት ሁን፣
ካልቻልክ የደከማቸው የሚደገፉበት ግድግዳ ሁን::
ይህንን ሁሉ ካልቻልክ ሰዎችን የሚያስቸግር የመሬት እሾህ አትሁን
❤️❤️❤️اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين ❤️❤️❤️
የአላህ እዝነትና ሰላም መልካም ነገርን ሁሉ ባስተማሩን ነቢይ ላይ ይስፈን።
በሰለዋት፣ በዱዓ፣በካህፍ የተዋበና ሰላም የሆነ ጁምዓ ይሁንልን!
https://t.me/Brookfekaduu
1 815
I'm on Instagram as @fekadubrook. Install the app to follow my photos and videos. https://www.instagram.com/invites/contact/?i=pj1yw87hmhkv&utm_content=1kxexih
1 815
እርግጠኛነትን ማሳካት (የቂን)
ኢብኑ ተይሚያህ “እንዲህ ጽፈዋል
በእምነት ዙርያ (የቂን) እርግጠኝነት በሶስት ጉዳዮች የተገኘ ነው-
1) በአላህ መጽሐፍ ላይ ማሰላሰል
2) በአላህ ፍጥረት ላይ ማሰላሰል ይህም የአላህን ታላቅነት ያስታውሳል
3) እውነት መሆኑን ባወቅነው ጉዳይ ላይ እንቅስቃሴ መጀመር፡፡
ሁላችንም እምነታችን እየከሰመ የሚሄድባቸው የሕይወት ጊዜያት ይኖራሉ፡፡ ኢብኑ ተይሚያህ እምነታችንን ለማጠንከር ሦስቱ ምርጥ መንገዶችን ያስታውሱናል ፡፡
፠የመጀመሪያው ቁርአንን ለማንበብ ፣ ለማዳመጥ እና ለማሰላሰል ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል፤ ምክኒያቱም እንደ ቁርዓን ኢማንን ሚሞላ ስለሌለ ፡፡ *ምንም*.
፠ሁለተኛ የፍጥረታትን ውበት እና ፍጹምነት መገንዘብ ወደ ፈጣሪ ግርማ እና ኃይል የሚወስደን ትልቅ ድልድይ ነው ፡፡ በእርግጥም ሰማያትንና ምድርን በመፍጠር እንዲሁም በሌሊትና በቀን መካከል ያለው መለዋወጥ ለብልህ ሰዎች ተዓምራት ናቸው፡፡ ይህ ፍጥረት በፈጣሪ በኩል ካልሆነ በቀር ሊገለፅ አይችልም፤ የትኛውም እምነት ፈጣሪን እና ስነ መለኮትን እንደ እስልምና እምነት ቀላል እና ቆንጆ አድርጎ የሚያረጋግጥ የለም ፡፡
፠በመጨረሻም በእምነታችን ስንኖር ፣ጌታችንን ስናመልክ በህይወት የመኖር ዓላማንና የሰላም ስሜትን እናጣጥማለን።
፨የሃይማኖታችንን እውነተኝነት ለማረጋገጥ ጽኑ እምነትም ተሰጥቶናል ፡፡
አላህን እርግጠኝነት (የቂን) እና የእምነት ጣፋጭነት እንጠይቃለን!🤲
Dr Yasir Qadih😁😁😁☺️☺️☺️☺️
1 815
ስለ ትህትና
•እናታችን አኢሻህ(ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስታወሱን “ትልቁ የአምልኮ ተግባር የሆነውን ትህትና እና መተናነስን ችላ ትላላቹ” [በኢብኑ አል-ሙባራቅ ኪ. አል-ዙህድ ተዘግቧል]
•ቃታዳህ ደግሞ እንዲህ ብለዋል “ሀብት ፣ ውበት ፣ ጥሩ ልብስ ፣ እውቀት ተችሮት ትሑት ያልሆነ ሰው በፍርድ ቀን በእነዚህ በረከቶች ይጸጸታል” ፡፡
•የአነስ ኢብኑ.ማሊክ(ራ.ዐ)ተማሪ የሆነው ያሂያ ኢብን.አቢ ከቲር ፣ “ሦስቱ የትህትና ምሰሶዎች እኒህ ናቸው ሲሉ መክረዋል:- እርስዎ ከእርስዎ ያነሱ ናቸው ብለው ከሚያስቡዋቸው ሰዎች ጋር ቁጭ ብለዋል ብለው ሰዎች ባሰቡ ጊዜ ያገኙትን ሰው ሁሉ ቅድሚያ ሰላምታ በመስጠት ማንኛውምየተመሰገኑበት ተግባር ላይ ራስን ማውገዝ ፡፡
oአላህን ትህትና መተናነስን እንጠይቃለን ፤ ከእብሪትና ከትምክህትም መጠጊያውን ከአላህ እንሻለን ፡፡
