en
Feedback
Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Open in Telegram

دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol

Show more
1 610
Subscribers
+124 hours
+47 days
-230 days
Posts Archive
photo content
+1

🌙 የጎዳና ኢፍጣር🌙 =============== 🖌 በኢልያስ አሕመድ በቅድሚያ ይህን ፕሮግራም ለማሰናዳት በቅንነት የሚለፉ ግለሰቦችና ድርጅቶችን አላህ የኒያቸውን እንዲሰጣቸው እንለምናለን፤ ከዚህ በታች ያለው አጭር ፅሑፍ የልፋታቸው መሰረት የተስተካከለ እንዲሆን ታስቦ በተቆርቋሪነት የተከተበ ነው።               ››››› ‹‹‹‹‹ በህብረት ማፍጠር ሁለት አይነት አፈፃፀሞች ሊኖሩት ይችላል፦ 1ኛ/ ለማፍጠር መሰባሰቡን ዋና ኢላማ ሳያደርጉ በተወሰኑ አጋጣሚዎች በህብረት ማፍጠር ሲሆን ይህም እንደማይወገዝ ግልፅ ነው። ለምሳሌ፦ ለሰላት ወደ መስጂድ የመጣውን ስብስብ ወይም ድሆችን በአንድ ቦታ ለማስፈጠር የሚኖረው መሰባብሰብ ተቃውሞ ሊነሳበት አይችልም። ዘመድና ጓደኛን ጠርቶ በጋራ ማፍጠርም እንደተራ ግብዣ ሊታይ ይችላል። ፆመኛን ማስፈጠርን አስመልክቶ የተወራውን ምንዳ ለማግኘት ከታሰበ ደግሞ እንደ እሳቤው የተወደደ ሊሆን ይችላል። ብዙ ዑለማዎች የፈቀዱትም በዚህኛው ምድብ የሚካተተውን ነው። 2ኛው/ ለኢፍጣር መሰባሰቡ ራሱ እንደ ዋና ግብ ታልሞና ይህንንም በሚያሳብቁ ተግባራት ታጅቦ በስፋት የሚተገበር አፈፃፀም ሲሆን ይህ የቢድዓ መገለጫን ሊላበስ ይችላል። በሀገራችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለመደው የጎዳና ኢፍጣር ይህንን ይዘት እንደተላበሰ ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል፦ 👉 እንደ በዓላት የሚጠበቅ ህዝባዊ ኩነት መሆኑ፣ (Grand Iftar 1, 2 እየተባለ ዘንድሮ 4ኛው ላይ ደርሰናል!) 👉 ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የበድር ዘመቻ የተካሄደበት የረመዳን 17ኛው እለት ለዚህ አመታዊ መሰባሰቢያ እንዲሆን በተደጋጋሚ መመረጡ፣ 👉 ሰዎች በነቂስ ወጥተው እንዲታደሙ ሰፊ ጥሪ መደረጉ፣ 👉 በታዳሚያን ብዛት ከሌሎች አገራት ጋር ፉክክር ውስጥ የተገባበት መሆኑ፣ እና ሌሎች አባሪ ሂደቶች ሊጠቀሱ ይችላሉ። የነዚህ ሂደቶች ስብስብ ተግባሩን ራሱን የቻለ አዲስ የሙስሊሞች ይፋዊ ምልክት (ሺዓር) እያደረገው ነው። 📌 ታላቁ ኢማም #ኢብኑ_ተይሚያህ በዲን ውስጥ ስለሚጨመሩ የፈጠራ በዓላት በሚያብራሩበት አውድ ስለ በዓላት ምንነት ሲያስረዱ የሚከተለውን ይላሉ፦ «“ዒድ” (በዓል) በተለመደ መልኩ ለሚደጋገም ሁሉን አቀፍ መሰባሰብ የሚሰጥ ስያሜ ሲሆን በየአመቱ፣ በየሳምንቱ፣ በየወሩ ወይም በተመሳሳይ ሁኔታ (በውስን ቀናት) የሚመላለስ ነው። በዓል የተወሰኑ ነገሮችን አቅፎ ይይዛል፤ ከነሱ መካከል፦ እንደ ዒድ አል-ፊጥር እና እንደ ጁሙዓ የሚመላለስ ቀን፣ (በቀኑ) መሰባሰብ፣ ይህን ተከትለው የሚመጡ አምልኳዊ ወይም ልማዳዊ ተግባራት ይገኛሉ። በዓል በውስን ቦታ የተገደበ ሊሆን ይችላል፤ ያልተገደበም ሊሆን ይችላል፤ እነዚህ ነገሮች ሁሉ (በነጠላ) ዒድ ሊሰኙ ይችላሉ.... “ዒድ” የሚለው ቃል ለእለቱና በውስጡ ላለው ተግባር ጥምረት የሚሰጥ ስም ሊሆን ይችላል፤ ይህም አብዛኛው (አጠቃቀሙ) ነው።» [“ኢቅቲዷኡ’ሲራጢ’ል’ሙስተቂም” (1/496 – 497)] 📌 በሌላ ቦታም እንዲህ ብለዋል፦ «ከተደነገጉት መሰባሰቦች ውጪ ሳምንታት፣ ወራት፣ ወይም አመታት በተደጋገሙ ቁጥር የሚደጋገም  መሰባብሰብን በቋሚነት መያዝ ለአምስቱ ሰላቶች፣ ለጁሙዓ፣ ለሁለቱ ዒዶችና ለሐጅ ከመሰባብሰብ ጋር ይመሳሰላል፤ ፈጠራና አዲስ ተግባር ማለት ይህ ነው!)) [“ኢቅቲዷኡ’ሲራጢ’ል’ሙስተቂም” (2/140)] 📌 አለፍ ብለውም እንዲህ ይላሉ፦ «ከነዚህ (ከተደነገጉት) መሰባሰቦች ባሻገር የሚለመድ ተጨማሪ መሰባሰብ ከተጀመረ አላህ ከደነገገውና ካፀደቀው ፈለግ ጋር የሚመሳሰል ይሆናል …. - ለብቻው የሆነ ግለሰብ ወይም ውስን ስብስቦች አንዳንዴ ከሚሰሩት በተለየ መልኩ!)) [“ኢቅቲዷኡ’ሲራጢ’ል’ሙስተቂም” (2/144)] ይህ ማብራሪያ ሰዎች በየውስን ጊዜ በታወቀ ቀጠሮ የሚፈፅሙት ህዝባዊ ስብስብ እንደ በዓል ባይታቀድ እንኳ በዓላዊ ይዘትን እንደሚላበስ ያሳያል። አንድ ነገር በጥቅሉ የሚፈቀድ፣ ብሎም የሚደነገግ ከመሆኑ ጋር በአፈፃፀሙ ረገድ የሚኖሩ ተጓዳኝ ነገሮች ብይኑ እንዲቀየር ሊያደርጉ ይችላሉ። 📌 ታዋቂው ዓሊም #ኢብኑ_ደቂቅ_አል_ዒድ አንዳንድ ሸሪዓዊ አፈፃፀሞችን ለመተግበር በደካማ የሐዲሥ ዘገባ ላይ ስለመመርኮዝ የሚነሳውን ውዝግብ አስመልክቶ እንዲህ ይላሉ፦ «የ“መውዱዕ” (የተቀነባበረ የውሸት ሐዲሥ) ክልል ውስጥ ያልገባ ደዒፍ (ደካማ) ከሆነ በዲን ላይ አዲስ ይፋዊ ምልክት “ሺዓር” የሚፈጥር ከሆነ ይከለከላል፤ ካልሆነ ደግሞ ምልከታ የሚቸረው ይሆናል...» [“ኢሕካሙ’ል-አሕካም” (1/501)] 👉 አንድን ተግባር እንደ “ሺዓር” ከሚያስቆጥሩት የአፈፃፀም ሂደቶች መካከል ሰዎች ተጠራርተው የሚሰባሰቡበት ኩነት መሆኑ ነው። ይህን የሚያብራራ አንድ ምሳሌ እንጥቀስ፦ ሰዎች በተሰባሰቡበት አጋጣሚ አንዳንዴ ዱዓ ማድረግ የሚቻል ከመሆኑ ጋር ይህን በህብረት ለመፈፀም መጠራራትን ብዙ የኢስላም ሊቃውንት አይደግፉም። 📌 #አል_ኢማም_አሕመድ እንዲህ ተብለው ተጠየቁ፦ «ሰዎች ተሰባስበው አላህን መለመናቸውና እጃቸውንም ማንሳታቸው ይጠላል?» እርሳቸውም፦ «مَا أَكْرَهُهُ لِلْإِخْوَانِ إذَا لَمْ يَجْتَمِعُوا عَلَى عَمْدٍ إلَّا أَنْ يَكْثُرُوا» = «ሆን ብለው ካልተሰባሰቡ ለ(ዲን) ወንድማማቾች አልጠላውም – ካልበዙ በስተቀር!» 📌 #አል_ኢማም_ኢስሓቅ ኢብኑ ራሀወይህ ሲጠየቁም ተመሳሳይ መልስ ሰጥተዋል። «ካልበዙ በስተቀር» ሲሉ ልማድ በማድረግ እስካልተበራከቱ ድረስ ማለታቸው እንደሆነ ጠያቂው (ኢስሓቅ ኢብኑ መንሱር) ተናግረዋል! [“መሳኢሉ’ል-ኢማሚ አሕመድ ወኢስሓቅ” (9/4879)፣ “ኢቅቲዷኡ’ሲራጢ’ል’ሙስተቂም” (2/140)]፣ “አል-ኣዳብ አሽ-ሸርዒይ-ያህ” ሊ’ብኒ ሙፍሊሕ (2/103)] 👉 ስለሆነም ነገሩ ከዚህ በላይ ሳያድግ መግታቱ አስፈላጊ ነው። ይህ ከዚህ በፊት የተስተዋሉ የአፈፃፀም ግድፈቶችን ከግምት ሳናስገባ የምንደርስበት መደምደሚያ ሲሆን፤ ያለ በቂ ምክንያት መንገድ መዘጋጋት፣ አግባብ ያልሆነ የወንድና የሴት መቀላቀል፣ የሴቶች ምስል በሚዲያ የሚሰራጭበት ቀረፃ፣ ሴቶች በምሽት መንገላታታቸው፣ በሙዚቃ መሳሪያ የታጀበ "ነሺዳ"፣ የምግብ ብክነት እና መሰል ጥፋቶች የሚታከሉበት ከሆነ ደግሞ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ይሆናል። አዎን! ፕሮግራሙ ከዚህ በፊት ሞራላዊ ጥቅምን አስገኝቶ ሊሆን ይችላል፤  ነገር ግን በውስጡ ከላይ የጠቆምነውን አመዛኝ ጉዳት ማካተቱ ለመታቀብ በቂ እንደሆነ አስባለሁ። አላህ ይበልጥ አዋቂ ነው። ረመዳን 15/1445 ____ @ustazilyas

Tahaak gubal tanih tan linkitte suuratul kahfi aw fantih Alcamduh tafsiiriy Dr. Seqid Qali Haaruun samaral gexsiisak geytimah yanih yanik 1-25 fanah xongoloh siinih xayyowteh tani kinnuuk barril tan qafárah tabaa tabissaanam yallih migaaqal sin esserna. Ossitinah Videoh Taahak gubal yan #you_tube linkil inki aracal gee litoonum sin aytil hayna. Yalli abe mara kee ankacisa marak inkih ikhlaas neh yaceeh kay garil oggol geyte taama neh takkem yallak qaaginna. Xongoloh 👇 https://t.me/drseqidqalihaaruuntafsiir Videoh 👇👇 https://youtube.com/playlist?list=PLL7M5XUj8Q4wh4udnSJTA3zlRWEQlxKdP&si=r8pwuuHVyFy2SU7F

photo content

+3
Soom edde qimbisaanam faxximta qumri.opus1.24 KB

AnimatedSticker.tgs0.24 KB

𝙍𝙪𝙛𝙩𝙤 𝙇𝙚 𝙭𝙖𝙖𝙜𝙪𝙝... Dr. Seqid Qali Haaruun Samarak Kaxxa masjiidil abak sugeh yan tafsiirik kahfi suuray (Fantih Alcamdu)25 exxah qulneh nani you tubuk ossitinah inkih 25 exxa #Xongoloh tahaak gubal yan Dr. Seqid migaaqal yanih yan telegraamal siinih xayyosnem rufto luk sin naysixxige. Alcamdulillaah 👇 https://t.me/drseqidqalihaaruuntafsiir Ní ummattay barril tanih tani xongolo maadissaanam massakaxxa luk yallih migaaqal sin esserna.

+1
የዘካህ ህግጋት አጭር ማብራሪያ ================ 📌 የተሻሻለ አዲስ እትም (ረመዳን 1445 ዓ.ሂ) 📖 የ pdf ፋይል 🖌 በኢልያስ አሕመድ @ustazilyas

دكتور محمد حسين ويعسى

استزادة الخير في رمضان جامع الإحسان بمدينة لوغيا إقليم عفر. لفضيلة الشيخ الدكتور  محمد حسين ويعسى 13 رمضان 1445ه‍ شبكة فجر العفر -Afar Maha Network: خطبة الجمعة في جامع الإحسان بمدينة لوغيا إقليم عفر - إثيوبيا. لفضيلة الشيخ الدكتور  محمد حسين ويعسا 21ربيع الأول 1445ه‍ https://t.me/AfarMahaNetwork/937?single

Soom esserooral yekke Gacsa Dr. Mucammad Cuseen weeqisa شبكة فجر العفر -Afar Maha Network: https://t.me/AfarMahaNetwork/937?single

photo content

soom essero.mp330.72 MB

استزادة الخير في رمضان د محمد.m4a8.05 MB

خطبة الجمعة عن أحوال الناس في رمضان #Ramadhaan addat #sinam kah tan #qaynoota wagsissa Khutba 🎙Sheekh Cuseen Acmad Cafizahullaah 👇👇👇 https://t.me/Kassisfaage

የንግድ ሸቀጦች ዘካ እና ተያያዥ ነጥቦች ~ የንግድ ሸቀጦች ሲባል ለሽያጭ የታሰቡ ሸቀጣ ሸቀጦች፣ እንስሳቶች፣ ወዘተ ናቸው። የነዚህ ለሽያጭ የሚቀርቡ ገንዘቦች ለዘካ የሚደርሱበት መነሻ መጠን (ኒሷብ) ከወረቀት የብር ኖት ጋር ተመሳሳይ ነው። ቀደም ብየ የለጠፍኩትን በዚህ ሊንክ መመልከት ይችላሉ:- https://www.facebook.com/share/p/EJW2reDF5NJePq3j/?mibextid=oFDknk ስለዚህ ለዘካ መጠን የደረሰ ገንዘብ እጁ ከገባ ጊዜ ጀምሮ አንድ አመት ከሞላው አጠቃላይ የንግድ እቃውን ዋጋ ካሰላ በኋላ የጠቅላላውን 2•5% ያወጣል። ልብ በሉ! ከሽያጭ እቃዎቹ ውጭ ያለ ተቀማጭ ገንዘብ ከኖረ አንድ ላይ ተደምሮ ነው ዘካው የሚወጣው። * ጊዜው የሚታሰበው ንግዱን ከጀመረበት ሳይሆን ለዘካ የደረሰ ገንዘብ ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው ረመዳን ላይ ለዘካ የደረሰ ገንዘብ ኖሮት ነገር ግን ስራ የጀመረው ከአምስት ወር በኋላ ቢሆን መታሰብ ያለበት ከረመዳን ጀምሮ ነው። ስለዚህ በቀጣዩ አመት ረመዳን አንድ አመት ሲሞላው ዘካውን ያወጣል። * ከንግድ ስራው በቀጥታ ተያያዥ የሆኑ ማለትም #ለሽያጭ_የታሰቡ ንብረቶች (መኪናዎች፣ ማሽኖች፣ ቤቶች፣ መሬቶች፣…) ካሉ አብረው ተደምረው ይሰላሉ። * ነገር ግን በራሳቸው የግብይቱ አካል ያልሆኑ እንደ የቤት መኪና፣ ማሽኖች፣ ፋብሪካዎች፣ ቤቶች፣ መጋዘኖች፣ … ያሉ ቋሚ ንብረቶች የንግድ ስራውን ለማቀላጠፍ ቢያግዙ እንኳ ዘካ አይመለከታቸውም። * ታሳቢ የሚደረገው የሸቀጦቹ ዋጋ የተገዙበት ሳይሆን ጨመረም ቀነሰ ወቅታዊ ዋጋቸው ነው። * ለንግድ የሚውሉትን ሸቀጦች ወይም እቃዎች ዝርዝር ሂሳባቸውን ለመስራት የሚያስቸግር ከሆነ ነፍሲያ ሳይጎትተው ጤነኛ የሆነ ግምት ይሰራል። * መዘንጋት የሌለበት ተቀማጭ ገንዘብም ሆነ የንግድ እቃዎች ዘካ የሚወጅብባቸው ለዘካ መጠን ከደረሱ በኋላ አመት ከሞላቸው ነው። አመት ካልሞላቸው ዘካ አይመለከታቸውም። * ዘካውን በአይነት መስጠት ይቻላል። ለምሳሌ በእህል የሚነግድ ከሆነ ቀጥታ እህሉን፣ በልብስ የሚነግድ ከሆነ በልብስ፣ ባለ ሱቅ ከሆነ ሱቅ ውስጥ ባለው እቃ የዘካውን መጠን መስጠት ይችላል። ባይሆን እቃው ተቀባዩ የሚጠቀምበት አይነት መሆን አለበት። እንዳስፈላጊነቱ በጥሬ ብር መስጠትም ይቻላል። = (ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 21/2013) የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor