ትንሳኤ ዘኢትኤል መማሪያ
Open in Telegram
የአባቶቻችን እና የሀገራችን ታሪክና ጥበብ ግዕዝን, ስለጥንት ነገስታት ታሪክ፣ ስለዕፆች፣ መድሀኒቶች፣ መሰውሮች፣ የደመና ጥበብ ፣ቅርሶች፣ጥንታዊ የብራና መፅሐፍት፣ስነ ፈለክ ፣አክሲማሮስ፣ራዕየ ሳቤላ፣መፅሐፈ ጅማትርያ ፣መፅሐፈ ፓዝዮን፣መፅሐፈ ፀሐይ፣መፅሐፈ ልሳን፣መፅሐፈ ጥበብ፣የመላእክት ቋንቋ ወዘተ ... ለጓደኛ ያስተላልፉ ኢትኤልን ስለመረጣቹ አመሰግናለሁ ይቆየን.. 👳♂
Show more6 253
Subscribers
-224 hours
-157 days
+530 days
Posts Archive
6 253
የተመኘኸውን ለማግኘት፡፡
ቢስሚላሂ ፡ ሮሂማን ፡ ሮሂም ፡ አላምዱሊላሂ ፡ ረቢ ፡ ለዓለሚን ፡ አራኂማን ፡ አራኂም ፡ መሊክ ፡
ያውመዲን ፡ ኢያከናብዱ ፡ ወኢያካ ፡ ነስቲን ፡ አዲና ፡ ሲራታል ፡ መስተቂም ፡ ሲራታል ፡ አዚን ፡
አናምታ ፡ አላሂም ፡ ቀሪል ፡ መቅዱቢ ፡ ወለዳዕሌን፡፡ ብለህ ፡ የምትፈልገውን ፡ ጨምረህ ፡ በ.........በቀለመ ፡
ወርቅ ፡ ፅፈህ ፡ ፻ ግዜ ፡ ደግመህ ፡ በግራ ፡ ክንድህ ያዝ፡፡
6 253
በስመ አብ በል ጸሎት በእንተ አይነ ጥላ ወገርጋሪ ፡ ቆጅሽ ፡ ቆጅሽ ፡ ቆጅሽ ፡ ቆርሐሹ ፡ ቆርሐሹ ፡ ቆርሐሹ ፡ ሸርማሹ ፡ ሸርማሹ ፡ ሸርማሹ ፡ ኮርሸሹ ፡ ኮርሸሹ ኮርሸሹ ፡ አክሊስ ፡ መክሊስ ፡ አጥሊስ ፡ ፡ መጥሊስ ፡ አሊስ ፡ መሊስ ፡ ኦ ፡ እግዚእነ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡በኃይለ ፡ ዝንቱ ፡ አስማቲከ ፡ ዘአጠፋህከ ፡ ኃይለ ፡ ፅልመት ፡ ወፈትሐከ ፡ መዋህቅተ ፡ ዲያብሎስ ፡ ከማሁ ፡ ፍታሕ ፡ ማዕሠረ ፡ ሰይጣን ፡ ዘይትሜሰል ፡ አይነ ፡ ጥላ ፡ ወገርጋሪ ፡ አድክም ፡ ኃይሎሙ ፡ ወሠውር ፡ ጥበቦሙ ፡ አድህነኒ ፡ ሊተ ፡ ለገብርከ ፡ እገሌ፡፡ ይዐቅቡኒ ፡ ሚካኤል ፡ ወገብርኤል ፡ ሱራፌል ፡ ወኪሩቤል ፡ ዑራኤል ፡ ወሩፋኤል ፡ አፍኒን ፡ ወራጉኤል ፡ ወሳቁኤል ፡ ብርሃናኤል ፡ አጥልሻሻኤል ፡ ወያኑራኤል ፡ ቅምታኤል ፡ አድህኑኒ ፡ እም ፡ አይነ ፡ ጥላ ፡ ወገርጋሪ ፡ ጨምታፎስ ፡ ጨለምታፎስ፡ ገምታፎስ ፡ ገለምታፎስ ፡ ይትፈታሕ ፡ ማዕሠረ ፡ እኩያን ፡ ቁራኛ ፡ ወተያያዥ ፡ አይነ ጥላ ፡ ወገርጋሪ ፡ እምላዕለ ፡ ገብር፡፡ገቢሩ ፡ ዕፀ ፋርስ ፡ ቅጠል ፡ ላይ ፡ ፵፩ ጊዜ ደግሞ ፡ መታጠን ፡ ነው፡፡ አይነ ጥላ ያባርራል፡፡ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ በቀይ ፡ ፅፈህ ፡ ያዝ ፡ ከአይነ ፡ ጥላ ፡ ይዐቅበከ ፡ይጠብቃል፡፡
6 253
ለስራ ሹመት፡፡
በስመ ፡ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ አሐዱ ፡ አምላክ ፡ ጸሎት ፡ በእንተ ፡ ሹመት ፡ ....... ለነጊድ ፡ ፈጊድ ፡ ለነጊድ ፡ ፈጊድ ፡ ነጊድ ፡ በቤተ ፡ ሄዋው ፡ ነጊድ ፡ በቤተ ፡ ኤሎሃ ፡ ነጊድ ፡ በቤተ ፡ ሰብእ ፡ ነጊድ በቤተ ፡ ፅዮን ፡ ነጊድ ፡ አኸያ ፡ አኸያ ፡ ሸራኸያ ፡ በራኸያ ፡ አዶናይ ፡ ፀባኦት ፡ ኤልሻዳይ ፡ በኃይለ ፡ ዝንቱ ፡ አስማት ፡ አንግሰኒ ፡ በውስተ ፡ መዋዕልየ ፡ ሊተ ፡ ለገብርከ ፡ እገሌ፡፡ በቅብዓ ፡ ቅዱስ ፡ 99 ጊዜ ፡ ደግመህ ስጥ ፡ ጠዋት ጠዋት ግንባሩን በጥቂቱ እየተቀባ ይውጣ፡፡ በትንሽ ግዜ ውስጥ ይሾማል ይሸላምል ስራም ቢሰራ የሰራውን ሰው ይወድለታል፡፡፡፡
6 253
ሳይነስን ለማከም 5 ቀላል መንገዶች
#Ethiopia | ሳይነስ - በሰውነታችን ውስጥ ያሉ አየር የሚንሸራሸርባቻን ክፍሎች የሚያጠቃ የህመም ዓይነት ነው፡፡ ህመሙ ሶስት ደረጃዎች ያሉት ሲሆን፣ አኪዩት፣ሰብ አኪዩት እና ክሮኒክ ሳይነስ (ሲኖሳይተስ) በመባል ይታወቃሉ፡፡
የህመሙ መነሻዎች የቫይረስና ባክቴርያ ኢንፌክሽን ሲሆን፣አልፎ አልፎ የሰዎች አፈጣጠር ወይም አናቶሚ ለህመሙ መከሰት ሰበብ ይሆናል፡፡ከሁሉም በላይ
ግን ለበሽታው መከሰት ምክንያት እየሆነ ያለው አለርጂ ነው፡፡ይህም አለርጂክ ሳይኖሳይተስ በመባል ይታወቃል፡፡
ይህንን ህመም ለመከላከል የሚጠቅሙ 5 ቀለላልና ተፈጥሮአዊ መንገዶች የሚከተሉት ናቸው፡-
1. ቀይ ጥሬ ሚጥሚጣ
ቃጠሎን መቋቋም እስከቻሉ ድረስ ሳይኖሳይተስን
ለማከም ወደር የማይገኝለት ተፈጥሮአዊ መድሃኒት ነው፡፡አፍንጫን በፍጥነት በማጽዳት ውስጡ ላይ ያለን እብጠት በማጥፋት እፎይታን ይሰጣል፡፡በሚመቾት
መንገድ አዘጋጅተው መጠቀም ይችላሉ፡፡
2. ዕርድ
ዕርድ በውስጡ ከርከሚን የሚባል እብጠትና የመለብለብ ስሜትን ሚከላከል ንጥረነገር አለው፡፡ይህ ንጥረነገር ሳይኖሳይተስን ከመከላከሉም
በተጨማሪ የሰውነትን የበሽታ መከላከል አቅም ከፍ ያደርጋል፡፡ 500mg የእርድ ዱቄትን በውሀ በማዋሀድ ወይም በእንክብል መልክ በቀን ሁለት ጊዜ መውሰድ
ጠቃሚ ነው፡፡
3. ነጭ ሽንኩርት
ነጭሽንኩርትን በብዛት መመገብ እጅግ በርካታ የጤና ትሩፋቶችን ያስገኛል፡፡በውስጡ አሊሲን የተሰኘ ንጥረነገር የያዘ ሲሆን፣ ይህ ንጥረነገር ቫይረስ ፣ባክቴርያና ፈንገስን የሚከላከል በመሆኑ ለሳይኖሳይተስ ኢንፌክሽን ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡በቀን ውስጥ ከሁለት እስከ ሶስት ራስ ፍሬሽ ነጭ ሽንኩርትን በማንኛውም ዓይነት መመገብ ከፍተኛ ውጤት ያስገኛል፡፡
4. ቀረፋ
በውስጡ ጎጂ የሆኑ ሳይኖሳይተስን የሚያስከትሉ ባክቴርያዎችን የሚገድል ኬሚካል ስላለው ከግማሽ የሻይ ማንኪያ እስከ አንድ የሻይ ማንኪያ ድረስ ከወለላ ማር በመቀላቀል በአንድ ብርጭቆ ለብ ያለ ውሀ መጠጣት ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡
5. ዝንጅብል
ዝንጅብል በውስጡ ፀረ-የአፍንጫ ፈሳሽ እና ፀረ-መለብለብና እብጠት ኬሚካሎችን በውስጡ ስለያዘ እንዲሁም የሰውነትን የበሽታ መከላከል አቅም ስለሚጨምር ሳይኖሳይተስን ለመከላከል ይረዳል፡፡ የዝንጅብል ሻይን ከሎሚ ጭማቂ ጋር ቀላቅሎ መጠቀም ለሳይኖሳይተስ ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡
ምንጭ፡- ``ናቹራል ኪዩርስ ኤንድ ናቹራል ሬሜዲስ ዶት ኮም`
=================
6 253
በኩላሊት እጥበት ጊዜ ደም ከሰውነታች በቀዩ ቱቦ ይወጣና በ Dialysis Machine አልፎ በሰማያዊ ቱቦ ተመልሶ ወደ ሰውነታች ይገባል።
እንዲህ እያለ ለ 4 ሰዓታት ይቆያል ይህ Dialysis በሳምንት 3 ጊዜ በወር 12 ጊዜ ይደረጋል። በአጠቃላይ በወር ለ 48 ሰዓታት ታማሚው ሳይንቀሳቀስ Dialysis ያደርጋል።
እኔ እና እናንተ ግን በቀን 36 ጊዜ ኩላሊታችን ራሱን ያጥባል ያውም ያለ ምንም ህመም እና ስቃይ።
እግዚአብሔር የዋለልንን ፀጋ እናስታውስ እናመስግን 🙏🙏
በዚህ ህመም ለሚሰቃዩ እግዚአብሔር ጤናቸውን ይመልስላቸው🙏
..........
6 253
Repost from ፈለገ ጥበባት +++
የሚኒሊክ ጀብድ የአድዋው ድል የፈረሰኛው ጊዮርጊስ እርዳታ እና ያልተነገረለት ታላቅ ሀያል ያለው ሞኦ መንግስት የተሰኘው ሀያል ቅዱስ ንዋይ ...
ለበርካታ ሽ አመታት ተጠብቆ ይኖር የነበረ መግነጢሳዊው ቅዱስ ዕቃ ከገዳማቱ ወጣ።
የዛሬ 127 አመት እለተ ቅዳሜ ማታ በአድዋ አቅራቢያ በሚገኘው እምየ ምኒሊክ ባከበሩት የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ታላቅ ሱባኤ ተይዟል ::
ካህናት በግራና በቀኝ
"ነዓ ነዓ ነዓ ጊዮርጊስ እንዘ ትፄአን በፈርስ እያሉ ይለምናሉ።
ሊቃውንቱ በማህሌት ቀሳውስቱ በማይጠንቱ እግዚአብሔርን ይለምናሉ።
እምየ ሚኒሊክ የንግስና ልብሳቸውን አውልቀዉ ቃልኪዳናቸውን ከጊዮርጊስ ጋር ሊያደርጉ '' ጊዮርጊስ ሆይ ተራዳን'' እያሉ ከቤተመቅደሱ ፊት ለፊት ታጥቀው ይማፀናሉ::
ጀግኒት ጣሂቱ
አቤቱ ከጠላቶቻችን አድነን
በላያችንም ከቆሙት አስጥለን "
እያለች ፈጣሪን ትማፀናለች
፡
በዚያም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኮሳትና ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ወደ ምኒልክ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ ከእነ አቡነ ማቴዎስ ጋር
ተቀላቀሉ፡፡ ከዚያም ሌሊቱን ሙሉ ጸሎተ ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ፡
የንጉሥ ሣህለ ማርያምን ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) ሌሊት በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ሥዕል ፊት በጸሎትና በስግደት እያደረች ሲነጋ ወደ ጦርነቱ ቦታ በመሄድ እጅግ በሚያስደንቅ የአነጋገሯ ኃይለ ቃል በጦርነቱ መካከል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች የሞራልና የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው
ነበር፡፡ በዕውነትም ለተመለከታት ሁሉ እንደኃይለኛ ተጋዳይ አርበኛ ትመስል ነበረ እንጂ የሴቶች የተፈጥሮ ባሕርይ በእርሷ ላይ አይታይባትም ነበር፡፡ የንጉሡም
ወታደሮች የንግሥቲቱን የጀግንነት አነጋገር በሰሙ ጊዜ በእሳት ላይ እንደተጣደ የብረት ምጣድ ልባቸው ጋለ፡፡ ይልቁንም ላም እንዳየ አንበሳና ፍየል እንዳየ ነብር
እየተወረወሩ በጦርነቱ መካከል በመግባት የጠላትን ጦር በሰይፍ ይጨፈጭፉት ነበር፡፡ መጽሐፍ ‹ሹመቱን ሽልማቱን ያየ አርበኛ ከጦርነት ከሰልፍ ወደኋላ
አያፈገፍግም› ብሎ ተናግሯልና፡፡ በዚያንም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ሚኒልክ) በጦርነቱ መካከል ሳለ ሊቀ
ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኮሳት ሌሎቹ ካህናት በሙሉ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኋላ በደጀንነት
ቆመው ጸሎተ ምሕላ ያደርሱ ነበር፡፡ ንግሥቲቱ ወለተ ሚካኤል በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ አትለይም ነበር፡፡ የጽዮን አገልጋዮችም
በእግዚአብሔር በሕጉ ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር፡፡ በዚህም ዕለት ይኸውም የካቲት 23 ቀን በሮማውያንና በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ሆነ፡፡
ከጦርነቱ ቀደም በሎ አንድ ሚስጥራዊ ነገር ተፈጽሞ ነበር ይህ ሚስጥር ከጥቂት ሚስጥር አዋቂ ሰወች በስተቀር በህዝብ ዘንድ አይታወቅም ...ይህ ጦርነት ከመከወኑ በፊት አንቱ የተባሉ የአቡሻህር ሊቃውነት ተሰበሰቡ ።
ንጉሰ ነገስት ሚኒልክ ብልህ አርቆ አሳቢ አስተዋይ ነበሩና የሊቃውንቱን ጥበብ በሚገባ ሸምተዋል።
ንጉሱ በብላቴና ዘመናቸው በ አጼ ቴውድሮስ እስር ላይ ሳሉ ጎንደር አዘዞ ተክልሃይማኖት ከተባለ ጥንታዊ ቤተክርስቲያን ቀለብ ተሰፍሮላቸው ለሊቃውቱ በአደራ ተሰጠው ብዙ የቤተክርስቲኒቱን እውቀት እንዲሸመቱ ሁነዋል።
አጤ ሚኒሊክ ብልህ እና አስተዋይ ስለነበሩ የሊቃውንቱን ጥበብና እውቀት በሚገባ ሲሰሙ ነበር ያደጉ።
በንግስና ዘመናቸውም ካከበሯቸው እና ትኩረት ከሰጧቸው ሊቃውነቶች በዋናነት የአቡሻህር ሊቃውነትን ከመላ ኢትዮጵያ በማሰባሰብ ተገቢውን ክብር በመስጠት ብልሀት ያዧቸው።
ዛሬ ላይ 1 ወይ 2 ብለን በጣት የሚቆጠሩ የአቡሻህር ሊቆች እጂግ በጣም ምጡቆች ፣ሚስጥር ጠንቃቂ ነገር አዋቂ እጂግ መንፈሳዊ ጸጋ የተላበሱ ሰማያትን ተመልክተው ስለ መጭው የሚተነብዩ የቀናትን ሀያልነት የሽንፈትና የድል መገኛ ዕለቶችን ጭምር የሚያውቁ አዝማናትን የሚመረምሩ እጂግ ጠቡብና መንፈሳዊ ሰወች ናቸው።
ታዲያ እኒህ ንጉስ ይህንን እውነት በጉባኤ ቤት ሲሰሙ አደገዋልና የአቡሻህር ሊቃውንትን ሰብስበው መፍትሔ ጠየቁ .....ኢትዮጵያ ጣልያንን በስአታት የአሸነፈችበት ምክኒያት ሶስት ሚስጥሮች ናቸው።
ታድያ ዋናው ሚስጥር የተገለጠው በዚህ እለት ብዙ ሽ አመታትን በሚስጥር የተቀመጠ አንድ ድንቅ እቃ ካለበት በሚስጥር እንዲወጣ ታዘዘ ።
ኢትዮጵያ በቀዳማዊ ሚኒልክ ማለትም ከ 3ሺ አመት በፊት ከ እስራኤል ከሌላውያኑ ጋ በሚስጥር የገቡ ታቦተ ጽዮንን ጨምሮ አምስት ሚስጥራዊ መለኮታዊ ሀብታት አሏት።
ከታቦተ ጽዮን ጋር ከመጣው አንዱ እና ሃያሉ እቃ ሞዐ መንግስት ይባላል።
ሞዐ ማለት አሸናፊ ማለት ነው መንግስት ደግሞ ያው መንግስት ነው። አሸናፊ መንግስት የሚል ትርጉም ያለው ድንቅ ቅዱስ እቃ ነው።
ታዲያ ይህ ሚስጥራዊ እቃ በአገሪቱ መራር አገዛዝ ሲመጣ አስከፊ ንጉስ ሲነግስ አገር በ መከራ እና ችግር ውስጥ ስትሆን ካለበት በክብር ይወጣል ራሱን የቻል መለኮታዊ ሀይል ያለው ጸሎት ይጸለይበታል ነገስታቱን ከ መንበራቸው ሹማምኑትን ከስልጣናቸው ጦርኞችን ከጦራችው ይለያል መንግስት ይወድቃል የሀያላኑን ሀያላቸውን ይነሳል ።
ታዲያ ይህ ድንቅ ዕቃ ነበር በአቡሻህር ሊቃውነቶች እና በቅዱሳነ አባቶች ሃይል ካለበት በክብር ወጥቶ የኢትዮጵያን ህዝብ ሃይልን ያጎናጸፋቸው።
በዚህ ዕለት የታዩት በርካታ አስደናቂ ታምራት ከሰማይ ይወጡ ነበር አካባቢው በቀስተ ደመና ተከቦ የሚያስገመግም ድምጽ ይሰማ ነበር።
ይህ ሞዐ መንግስት የተባለ ቅዱስ እቃ ዛሬ ለይ ከአለም ተሰውሮ በታላቅ ክብር ከሌሎች መግነጢሳዊ ሀይል ካላቸው ቅዱስ እቃወች ጋር አንድ ታላቅ ገዳም በ አናብስትና በአናብርት እየተጠበቀ በሚስጥ ተሸሽጎ ይገኛል ።
ታድያ ሌላው ሚስጥር በዚህ ዕለት ሲጎሰም የነቀረው ከ ጉማሬ ቆዶ የተሰራው ዛሬ ላይ ጣና ቂርቆስ የሚገኘው ነጋሪትም በሚጎሰምበት ዕለት የሚያወጣው ድምጽ ታላቅ ሚስጥራዊ ነገር ይፈጸም ነበር ።
በአድዋ ላይ ድል ስላደረገው የጊዮርግስ መገለጥ ሃይሉ ምንጭ ምክኒያት ከዚህው ሞዓ መንግስት ጋር የሚቀዳ ታሪክ አለው።
ብዙ ጊዜ በአድዋ ታቦት አብሮ መዝመቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም መዋጋቱ ይገለጣል ነገር ግን ዋናው ሚስጥር ሲነገር አይስተዋልም።
በዚህም ምክኒያት ነው አገር ስትታመም እና ልትዋረድ ስትል በእግዚአብሔር ፈቃድ በጠብብት ሊቃውንተ ጥበብ የተቀመረው ይህ ሚስጥር ሲገለጥ
ወዲያውም በሰማይ ታላቅ ተአምር ተደረገ፡፡
ይኸውም የቀስተ ደመና ምልክት ታየ፡፡ ከዚያም ቀስተ ደመና ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የሚመስል ጢስ ይወጣ
ነበር፡፡ ከዚያም ጢስ ውስጥ እንደክረምት ነጎድጓድ ያለ ድምፅ ተሰማ፡፡ ከዚያም የነጎድጓድ ድምፅ የተነሣ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሽብር
ሆነ፡፡ ለመዋጋትም አልቻሉም፡፡ ይልቁንም ኃያሉ ገባሬ ተአምር ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረስ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ እየተፋጠነ በአየር ላይ በተገለጠ
