en
Feedback
Aboker prepartory school official channel

Aboker prepartory school official channel

Open in Telegram
922
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለሁሉም የመንግስት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዩ፦ በ2015 ዓ.ም የሚሰጠውን የRemedia| ፈተናን ይመለከታል። በ2014 ዓ.ም የተሰጠውን የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ዩኒቨርሲቲ መግባት #ያልቻሉ ነገር ግን ሻል ያለ ውጤት የነበራቸው እና በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ሲወስዱ ለቆዩ ተማሪዎች የRemecial ፈተና የሚሰጠው 👉 ከሰኔ 26- 30 ቀን 2015 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል። ስለሆነም ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ፈተናውን ውጤታማ በሆነ ሁኔታ እንድትሰጡ አሳስባለሁ። የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)

#MoE የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል። ሚኒስቴሩ ፤ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ #በመንግስት_ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል ብሏል። ዩኒቨርሲቲዎችም ያላቸውን ሾል በማጠናቀቅ ከሐምሌ15/2015 ዓ.ም  ጀምሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የነጻ ትምህርት ዕድል ! በሰዎች ለሰዎች ድርጅት ወይንም Menschen für Menschen Foundation ስር የሚተዳደረው የሐረር ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በ2015 የትምህርት ዘመን ብቁ የሆኑ የተፈጥሮ
+1
የነጻ ትምህርት ዕድል ! በሰዎች ለሰዎች ድርጅት ወይንም Menschen fĂźr Menschen Foundation ሾር የሚተዳደረው የሐረር ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በ2015 የትምህርት ዘመን ብቁ የሆኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ መርሐግብር ሙሉ ወጪያቸውን ሸፍኖ ማስተማር ይፈልጋል፡፡ የዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ ተማሪዎች ከመጋቢተ 18 - 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ባሉት የስራ ቀናት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን። የመመዝገቢያ መስፈርቶች ፦ ትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም. ያወጣውን የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ መስፈርት የሚያሟሉ ወይንም በአገር አቀፍ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያመጡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች፡፡  የምዝገባ ቦታዎች በአዲስ አበባ ቦሌ ቡልቡላ በሚገኘው የሰዎች ለሰዎች ድርጅት ዋና መ/ቤት፤ áˆáˆ¨áˆ­  በኮሌጁ ቅጥር ግቢ፤ የድርጅቱ ፕሮጄክት ጽ/ቤቶች በሚገኙባችው በተጨማሪም በድረ-ገጻችን http://www.mfmattc.edu.et ላይም መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡ ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0256663738/1139 ወይም 0114714579 ደውሎ ማንጋገር ይቻላል፡፡  (ሰዎች ለሰዎች ድርጅት Menschen fĂźr Menschen Foundation)

History entrance 2002 E.C.docx0.38 KB

Draft_Guidelines_for_Enhancing_English_Learning_through_Digital.pdf4.11 MB

March 8 መሪ á‰ƒáˆ እኔ á‹¨áŠĽáˆ…á‰´ áŒ á‰Łá‰‚ áŠáŠ መልእክቶች Ăź    á‹¨áˆ´á‰śá‰˝ áŒ‰áˆáˆ… áˆšáŠ“ áˆˆáŠ áŒˆáˆŤá‹Š áˆ°áˆ‹áˆ áŒáŠ•á‰Łá‰ł Ăź    áŠ áŒˆáˆ­ á‰ á‰€áˆ á‹¨áˆľáˆŤ áˆáŒ áˆŤ á‹áŒ¤á‰śá‰˝ áˆˆáˆ´á‰śá‰˝ áŠ˘áŠŽáŠ–áˆšá‹Ťá‹Š á‰Ľá‰ƒá‰ľ Ăź    áˆáŒ áˆŤáŠ•áŠ“ á‰´áŠ­áŠ–áˆŽáŒ…áŠ• á‰ áˆ˜áŒ á‰€áˆ á‹¨áˆľáˆ­á‹“ተ  á†á‰ł áŠĽáŠŠáˆáŠá‰ľáŠ• áŠĽáŠ“áˆ¨áŒ‹áŒˆáŒĽ!!!. Ăź    áˆáˆˆáŠ•á‰°áŠ“á‹Š á‹¨áˆ´á‰śá‰˝ á‰°áˆłá‰ľáŽáŠ“ á‰°áŒ á‰ƒáˆšáŠá‰ľ áˆˆáˆ°á‰ĽáŠ á‹Š áˆ˜á‰Ľá‰ľ áˆ˜áŠ¨á‰ áˆ­!!! Ăź    á‹¨áˆ´á‰śá‰˝áŠ• áŠĽáˆá‰… áŠ á‰…áˆ á‰ áˆ˜áŒ á‰€áˆ áˆ€áŒˆáˆ­áŠ• áŠĽáŠ•áŒˆáŠ•á‰Ł

#ማስታወቂያ የRemedial ፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆኗል። በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባችሁን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑንና በተመደባችሁበት የትምህርት ተቋሞች በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን እንድትከታተሉ  እንገልፃለን ። ማሳሰቢያ :- የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ ለመግለጽ እንወዳለን። የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች Website: https://placement.ethernet.edu.et SMS: 9444 ትምህርት ሚኒስቴር

#ArbaMinchUniversity በ2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የመግቢያ ቀን á‹¨áŠŤá‰˛á‰ľ 22/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። የምዝገባ ጊዜ ➧ á‹¨áŠŤá‰˛á‰ľ 23 እና 24/2015 ዓ.ም ትምህርት የሚጀምረው ➧ á‹¨áŠŤá‰˛á‰ľ 27/2015 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➧የ8ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣ ➧ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና 2 ኮፒ፣ ➧ የ10 እና 12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና 2 ኮፒ፣ ➧ ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ (4)፣ ➧ የሌሊት አልባሳትና የስፖርት ትጥቅ። የመመዝገቢያ ቦታ ➧የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ፤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በጫሞ ካምፓስ ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኋላ የሚመጣ ተማሪን እንደማያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡ @brilliantsAcademy

#MoE 106 ሺህ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሰጠው የአቅም ማሻሻያ የትምህርት ፕሮግራም ተካተዋል፡፡ በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ወስደው ከ50 በመቶ በታች ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ለአራት ወራት ያህል በሀገሪቱ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በሚሰጠው የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ይሳተፋሉ፡፡ የ Remedial ፕሮግራሙ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ውጪ ባሉ ሁሉም የመንግስት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ባለሙያዎች እና ፕሮፌሰሮች ኮሚቴ በማዋቀር ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉት የትምህርት አይነት ይዘቶችን መለየቱን በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡ በአቅም ማሻሻያ ፕሮግራሙ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፊዚክስ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ እንግሊዘኛ፣ የተፈጥሮ ሳይንስና ሂሳብ የትምህርት አይነቶችን የሚወስዱ ሲሆን፤ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ እንግሊዘኛ፣ ማህበራዊ ሳይንስና ሂሳብ ትምህርት አይነቶችን እንደሚወስዱ መሪ ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡ የትምህርት ይዘቶቹን መሰረት አድርጎ በተቋማት የሚዘጋጅ (ከ30 በመቶ) እና በማዕከል የሚዘጋጅ (ከ70 በመቶ) የሚያዝ ፈተና በመፈተን በድምሩ 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ የሚያገኙ ተማሪዎች መደበኛ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በመንግስት እና በግል ዩኒቨርሲቲዎች መቀጠል ይችላሉ ብለዋል፡፡ @BrilliantsAcademy

የጥሪ ማስታወቂያ በ2014 ዓ.ም. ትምህርት ዘመን የ2ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶ እና በላይ አምጥታችሁ በ2015ዓ.ም. ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርታችሁን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እንድትከታተሉ የተመደባችሁ አዲስ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች በየካቲት 24, 25 እና 26፣ 2015ዓ.ም. ሐረማያ በሚገኘው በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ በአካል ተገኝታችሁ ሪፖርት አንድታደርጉ እናስታውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ፦ 1ኛ. ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ የ8ኛ ክፍል ካርድ ፤ ከ9ኛ አስከ 12ኛ ትምህርት ያጠናቀቃችሁበትን ትራንስክሪፕት እና የ2ኛ ክፍል ሰርትፍኬት ዋናውን እና ፎቶ ኮፒ ፤ 6 ፓስፖርት መጠን ያላቸው ጉርድ ፎቶግራፎችን እንዲሁም በግል የምትጠቀሙባቸውን ብርድልብስ ፣ አንሶላ ፣ የትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ እንድትመጡ፡፡ 2ኛ.ተማሪዎች የመኝታ ክፍል ድልድላችሁን የ2ኛ ክፍል መለያ ቁጥራችሁን በመጠቀም በዩኒቨርሲቲው ድረ-ገጽ (www.haramaya.edu.et) በመግባት ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ 3ኛ. ዩኒቨርሲቲው ጥሪ ካደረገባቸው ቀናት በፊትም ሆነ ዘግይቶ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ከምደባ ጋር ተያይዞ መረጃ ለማግኘት 👇 https://t.me/Freshman_info https://t.me/Freshman_info

#የ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ውጤትን መሠረት ያደረጉ መረጃዎች ፨ 50 ከመቶ እና በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች በወጪ መጋርት (ስኮላርሺፕ) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ወይም በተለያዩ አማራጮች በቅድመ ምረቃ መደበኛ መረሀ ግብር  ትምህርታቸውን መከተታተል ይችላሉ፡፡ ፨ እንደተፈተኑት የትምህርት ዓይነት ብዛት 30 ከመቶ (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ 500) እና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎች በአቅም ማሻሻያ ወይም  Remedial ፕሮግራም በሁሉም አማራጮች በመንግስትና በግል  የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን መከተታተል ይችላሉ፡፡ ፨ የአቅም ማሻሻያ  ወይም  Remedial ፕሮግራም የሚቆየው ከየካቲት 15 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ.ም ነው፡፡ ፨ የአቅም ማሻሻያ ወይም  Remedial ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች ምዘና በተቋማት 30 ከመቶ እና በማዕከል 70 ከመቶ ተመዝነው በአማካይ 50 ከመቶ ውጤት ካመጡ እየተማሩ ባሉበት ተቋም መቀጠል የሚችሉ ይሆናል፡፡ ፨ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአቅም ማሻሻያ ወይም Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የተመዘገቡ ተማሪዎችን ስም፣የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስም ፣አድሚሽን ቁጥር ፣የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት እና ወዘተ… በአስር ቀናት ውስጥ ለኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ማሳወቅ አለባቸው ፡፡ ፨ የአቅም ማሻሻያ ወይም  Remedial ፕሮግራም በተፈጥሮ ሳይንስ  እና  በማህበራዊ ሳይንስ በሁለት መስክ ተከፍሎ ከማዕከል በተዘጋጀ ይዘት መሠረት ዩኒቨርስቲዎች ተጨማሪ የሚያክሉትን በማካተት በተዘጋጀው መነሻ መሠረት ፕሮግራሙ ይከናወናል፡፡ ፨ የአቅም ማሻሻያ ወይም  Remedial ፕሮግራም የሚደረገው ለአንድ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ በኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጣና ባለሥልጣን https://t.me/brilliantsAcademy

የጥሪ ማስታወቂያ በ2015 ዓ/ም በመደበኛ መርሃ ግብር የመጀመሪያ ዲግሪ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች በሙሉ ፨ሁሉም የማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) ተማሪዎቹ እና ስማችሁ ከ ̈ የሚጀምር የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) ተማሪዎች በግሸ አባይ (ይባብ ካምፓስ፣ 👉ከየካቲት 20/2015 እስከ 22/2015 ዓ/ም ሪፖርት እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ከምደባ ጋር ተያይዞ መረጃ ለማግኘት 👇 https://t.me/Freshman_info https://t.me/Freshman_info

ማስታወቂያ ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች **** በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶና ከዚያም በላይ አምጥታችሁ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች:- ምዝገባ  በበየነ መረብ ”Online”  ከየካቲት  20-26/2015 ዓ.ም ድረስ የሚከናወን ሲሆን  የተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ  የመግቢያ እና ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ የካቲት 27-28/2015 ዓ.ም በዋናው ግቢ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ማሳሰቢያ፤ ስለምዝገባ ሂደቱ ዝርዝር መረጃዎችን በዩኒቨርስቲዉ ድህረ-ገጽ https://hu.edu.et እና በዩኒቨርስቲው የማህበራዊ ገጾች የሚገለጹ መሆኑን እንድታውቁ፡፡ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲመጡ የሚከተሉትን ይዘው መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡ 1ኛ.  የ12ኛ  ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዋናውና ቅጂው 2ኛ.  ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ቅጂው 3ኛ.  የሌሊት አልባሳት 4ኛ.  4 ጉርድ ፎቶ ግራፍ 5ኛ. የስፖርት ትጥቅ በተለያየ ምክንያት ትምህርት አቋርጣችሁ ለመልሶ ቅበላ ውጤታችሁ የሚያበቃችሁ ተማሪዎች አዲስ ከተመደቡ የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች ጋር በመቅረብ በ2015 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ የካቲት  29 እና 30 2015 ዓ.ም እንድታመለክቱ እናሳውቃለን፡፡ ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኃላ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡       የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ  ሬጅስትራር እና አልሙኒ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ከምደባ ጋር ተያይዞ መረጃ ለማግኘት 👇 https://t.me/Freshman_info https://t.me/Freshman_info

የካቲት 11 ቀን 2015   ማስታወቂያ   በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2015 የትምህርት ዘመን በመደበኛ መርሃ-ግብር ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት አዲስ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ   በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2015  á‹¨á‰ľáˆáˆ…áˆ­á‰ľ ዘመን በመደበኛ የዲግሪ ትምህርት መርሃ-ግብር በትምህርት ሚ/ር መስፈርት መሠረት አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡ የካቲት 15 ቀን እና የካቲት 16 ቀን 2015 ዓ.ም በየተመደባችሁበት የዩኒቨርስቲው ካምፓሶች በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ያሳውቃል፡፡ በተጨማሪም ተማሪዎችም ለምዝገባ ስትመጡ 1ኛ - የአስራ ሁለተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውንና ፎቶ   ኮፒ፣ 2ኛ - ስምንት ጉርድ ፎቶግራፍ፣ 3ኛ - ብርድልብስና አንሶላ እንዲሁም የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ መምጣት እንዳለባችሁ ያስታውቃል፡፡ ➢ በተጠቀሱት ቀናት ከአዲስ አበባ ውጪ ለሚመጡት ተማሪዎች በመርካቶ አውቶብስ ተራ፣ በላም በረት፣ በአቃቂ እና በአስኮ የመኪና መናኸሪያዎች በመገኘት ዩኒቨርስቲው የትራንስፖርት አገልግሎት ያቀርባል፡፡ ፡ ➢ ከተገለጸው ቀን በፊት ለሚመጡ ተማሪዎች ምንም ዓይነት አገልግሎት ዩኒቨርስቲው አይሰጥም፡፡ ➢ ለተጨማሪ መረጃ የዩኒቨርስቲውን ድረገጽ https://portal.aau.edu.et/ ወይም www.aau.edu.et ማየት የሚቻል ሲሆን ➢ ነዋሪነታችሁ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሆኖ ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ሪፖርት የምታደርጉትና ሾለ ዩኒቨርስቲው ገለጻ የምታገኙት የካቲት 17 ቀን 2015 ዓ.ም መሆኑን ያሳውቃል፡፡ ➢ ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ውስጥ የመኝታ አገልግሎት ለማግኘት የተመደበላችሁን የመኝታ ክፍል 12ኛ ክፍል በተፈተናችሁበት ቁጥር በመጠቀም ከ https://portal.aau.edu.et ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡ ➢ በተለያየ ምክንያት ትምህርት አቋርጣችሁ ለመልሶ ቅበላ ውጤታችሁ የሚያበቃችሁ ተማሪዎች አዲስ ከተመደቡ 1ኛ ዓመት ተማሪዎች ጋር በመቅረብ በ2015 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ ከየካቲት 15 እስከ የካቲት 17 2015 ዓ.ም እንድታመለክቱ እናሳውቃለን፡፡   አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ                                                             ሬጅስትራር ከምደባ ጋር ተያይዞ መረጃ ለማግኘት 👇 https://t.me/Freshman_info https://t.me/Freshman_info

#ማስታወቂያ በ2014 ዓ.ም ተፈትናችሁ ማለፊያ ዉጤት ላመጣችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን  የሥነ-ትምህርት ባለሙያዎችን የማፍራት ተልዕኮ ተሰጥቶት በአዲስ መልኩ የተቋቋመው አንጋፋው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው የማለፊያ ነጥብ ካስመዘገቡት ተማሪዎች መካከል አወዳድሮ በቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራሞች እንዲቀበል በትምህርት ሚኒስቴር በተፈቀደለት መሰረት ለ2015 የትምህርት ዘመን ለመቀበል ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡  ስለሆነም በመምህርነት፣  በኮምፒዩተር ሳይንስ ኤዱከሽን፤ በሄልዝ ሳይንስ ኤዱከሽን፤ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ትምህርት፤ በቢዝነስ ኤዱኬሽን፤ በኬርዬር እና ቴክኒካል ኤዱኬሽን፤ በፊዚካል ኤዱኬሽንና ስፖርት፤ በትምህርት አመራር እና አስተዳደር፣ በክወናና እይታ ጥበባት ትምህርት፤ በቀዳማይ ልጅነት እድገትና ትምህርት፤ በትምህርት ሳይኮሎጅ፣ በልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት እና ተያያዥ የስነ ትምህርት ዘርፎች በመደበኛ መርሀግብር ለመሰልጠን ፍላጎት ያላችሁ እና ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣዉን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ብቻ ከየካቲት 13-17/2015 ዓ.ም ድረስ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁንና ተያያዥ ሰነዶችን በመያዝ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ➽ከምደባ ጋር ተያይዞ መረጃ ለማግኘት  ይህን ቻናል ይጎብኙ👇 https://t.me/Freshman_info

#MoE በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን አማካይነት ማስተካከል ይችላሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አሳስውቋል። ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ማስተካከል የሚችሉት እስከ የካቲት 10/2015 ዓ.ም ድረስ መሆኑ ተመላክቷል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በዚህ ፕሮግራም የማይካተቱ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ More : @tikvahuniversity @tikvahethiopia