cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Show more
Advertising posts
34 441
Subscribers
+1224 hours
+1047 days
+65530 days
Posts Archive
የአሏህ ምርጫ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 42፥13 አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል፡፡ የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል፡፡ اللَّهُ يَجْتَبِي إِلَيْهِ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي إِلَيْهِ مَن يُنِيبُ "ኢንቲኻብ" اِنْتِخَاب ማለት "ምርጫ"election" ማለት ነው፥ ኢንቲኻብ እራሱ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ እና "ኢንቲኻብ ገይሪ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب غَيْرِ شُرْطِيّ ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ። ፨ "ሹሩጢይ" شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ"conditional" ማለት ሲሆን በጥቅሉ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ ምርጫ"conditional election" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ አደም በሠራው ኃጢአት "ጌታችን ሆይ! እራሳችችንን በደልን፥ ለእኛ ባትምረን እና ባታዝንልን በእርግጥ ከከሳሪዎቹ እንኾናለን" ብሎ ተጸጸተ፦ 7፥23 «ጌታችን ሆይ! እራሳችችንን በደልን፥ ለእኛ ባትምረን እና ባታዝንልን በእርግጥ ከከሳሪዎቹ እንኾናለን» አሉ፡፡ قَالَا رَبَّنَا ظَلَمْنَا أَنفُسَنَا وَإِن لَّمْ تَغْفِرْ لَنَا وَتَرْحَمْنَا لَنَكُونَنَّ مِنَ الْخَاسِرِينَ አደም ተጸጽቶ በንስሓ ወደ አሏህ ሲመለስ አሏህ ጸጸትን በመቀበል ተመለሰለት፥ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፦ 2፥37 አደምም ከጌታው ቃላትን ተቀበለ፡፡ በእርሱ ላይም ጌታው ጸጸትን በመቀበል ተመለሰለት፥ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፡፡ فَتَلَقَّىٰ آدَمُ مِن رَّبِّهِ كَلِمَاتٍ فَتَابَ عَلَيْهِ ۚ إِنَّهُ هُوَ التَّوَّابُ الرَّحِيمُ አደም ተጸጽቶ ንስሓ ወደ አሏህ በመግባቱ አሏህ ጸጸትን በመቀበል መረጠው፦ 20፥122 ከዚያም "ጌታው መረጠው" ከእርሱም ጸጸቱን ተቀበለው መራውም፡፡ ثُمَّ اجْتَبَاهُ رَبُّهُ فَتَابَ عَلَيْهِ وَهَدَىٰ "ጌታው መረጠው" የሚለው ይሰመርበት! ማንኛውም ሰው ከነበረበት ኩፍር ወይም ሺርክ አሊያም ዘንብ ወደ አሏህ በንስሓ ቢመለስ አሏህ ወደ ራሱ ለጀነት ይመርጠዋል፦ 42፥13 አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል፡፡ የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል፡፡ اللَّهُ يَجْتَبِي إِلَيْهِ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي إِلَيْهِ مَن يُنِيبُ "አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል" የሚለው "ዓም" ሆኖ የመጣ ነው፥ "ዓም" عَامّ ማለት "ጥቅል"general" ማለት ነው። ነገር ግን "አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል" የሚለው ዓም "የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል" በሚል "ኻስ" ሆኖ እዛው ላይ መጥቷል፥ "ኻስ" خَاصّ ማለት "ተናጥል"specifical" ማለት ነው። መመራትን ሰው የሚያገኘው በማመን መሆኑ "ኻስ" ሆኖ የሚመጣ ነው፦ 22፥54 አሏህ እነዚያን ያመኑትን ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ "መሪ" ነው፡፡ وَإِنَّ اللَّهَ لَهَادِ الَّذِينَ آمَنُوا إِلَىٰ صِرَاطٍ مُّسْتَقِيمٍ "እነዚያን ያመኑትን" የሚለው ይሰመርበት! ያላመነው እና ንስሓ ያልገባ ሰው የሸይጧን ተከታይ ነው፥ ሸይጧን የተከተለውን ሰው ወደ ጀሀነም ይመራዋል፦ 22፥4 "እነሆ! የተከተለውን ሰው እርሱ ያጠመዋል፡፡ ወደ ነዳጅ እሳት ስቃይም ይመራዋል" ማለት በእርሱ ላይ ተጽፏል፡፡ كُتِبَ عَلَيْهِ أَنَّهُ مَن تَوَلَّاهُ فَأَنَّهُ يُضِلُّهُ وَيَهْدِيهِ إِلَىٰ عَذَابِ السَّعِيرِ ወደ ጀሀነም የሚገባ ሰው አሏህ ለጀነት ያልመረጠው በገዛ ፈቃዱ ሸይጧንን በመከተሉ ነው፥ ይህ የእኛ ጣልቃ ገብነት እና ድርሻ ያለበት የአሏህ ምርጫ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ ይባላል። ፨ "ገይሪ ሹሩጢይ" غَيْرِ شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ አልባ"unconditional" ማለት ሲሆን በጥቅሉ "ኢንቲኻብ ገይሪ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب غَيْرِ شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ አልባ ምርጫ"unconditional election" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፦ 28፥68 ጌታህም የሚሻውን ይፈጥራል፤ ይመርጣልም፡፡ ለእነርሱ ምርጫ የላቸውም፡፡ አሏህ ከማይግገባው ሁሉ ጠራ፡፡ ከሚያጋሯቸውም ላቀ፡፡ وَرَبُّكَ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ وَيَخْتَارُ ۗ مَا كَانَ لَهُمُ الْخِيَرَةُ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ وَتَعَالَىٰ عَمَّا يُشْرِكُونَ "የሚሻውን ይፈጥራል" በሚል ኃይለ ቃል "ይመርጣል" የሚለው ቃል አሏህ የሚሻውን ሰው፣ የሚሻውን እንስሳ፣ የሚሻውን አታክልት፣ የሚሻውን ማዕድን አርጎ መፍጠሩ የእርሱ ሁኔታዊ አልባ ምርጫ ነው፥ "ለእነርሱ ምርጫ የላቸውም" ማለት ፍጡራን "ይህንን ሆኜ ልፈጠር" የሚል ምርጫ የላቸውም። ወንድነት እና ሴትነት የእኛ ምርጫ ሳይሆን የእርሱ ምርጫ ብቻ ነው፦ 42፥49 የሰማያትና የምድር ንግሥና የአሏህ ነው፡፡ የሚሻውን ይፈጥራል፤ ለሚሻው ሴቶችን ይሰጣል፥ ለሚሻውም ወንዶችን ይሰጣል፡፡ لِّلَّهِ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ يَهَبُ لِمَن يَشَاءُ إِنَاثًا وَيَهَبُ لِمَن يَشَاءُ الذُّكُورَ "የሚሻውን ይፈጥራል" በሚል ኃይለ ቃል "ለሚሻው ሴቶችን ይሰጣል፥ ለሚሻውም ወንዶችን ይሰጣል" የሚለው ቃል ሴት መሆን እና ወንድ መሆን የአሏህ ሁኔታዊ አልባ ምርጫ ነው፥ የእኛ ምርጫ፣ ድርሻ፣ ፈቃድ ስለሌለበት ወንድነት እና ሴትነት ቅጣት እና ሽልማት አሊያም ተጠያቂነት የለበትም። አምላካችን አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፦ 40፥7 እነዚያ "ዙፋኑን የሚሸከሙት" እና እነዚያ በዙሪያው ያሉት በጌታቸው ምስጋና ያወድሳሉ፡፡ በእርሱም ያምናሉ፡፡ الَّذِينَ يَحْمِلُونَ الْعَرْشَ وَمَنْ حَوْلَهُ يُسَبِّحُونَ بِحَمْدِ رَبِّهِمْ وَيُؤْمِنُونَ بِهِ 22፥75 አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፥ ከሰዎችም እንደዚሁ ይመርጣል። አላህ ሰሚ ተመልካች ነው፡፡ اللَّهُ يَصْطَفِي مِنَ الْمَلَائِكَةِ رُسُلًا وَمِنَ النَّاسِ ۚ إِنَّ اللَّهَ سَمِيعٌ بَصِيرٌ "ከሩቢዩን" كَرُوبِيُّون የሚባሉት መላእክት የአሏህን ዐርሽ የሚሸከሙ ሲሆን በዐርሹ ዙሪያ ካሉት መላእክት ወደ ሰዎች የሚልካቸው መላእክት የእርሱ ሁኔታ አልባ ምርጫ ነው። "ከሰዎችም እንደዚሁ ይመርጣል" ስለሚል አሏህ ከሰዎች ለመልእክተኛነት መምረጡ ይህ የእርሱ ሁኔታ አልባ ምርጫ ነው፦ 2፥105 አሏህም በችሮታው (በነቢይነት) የሚሻውን ይመርጣል፡፡ አላህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው፡፡ وَاللَّهُ يَخْتَصُّ بِرَحْمَتِهِ مَن يَشَاءُ ۚ وَاللَّهُ ذُو الْفَضْلِ الْعَظِيمِ 3፥74 በችሮታው (በነቢይነት) የሚሻውን ይመርጣል፡፡ አሏህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው፡፡ يَخْتَصُّ بِرَحْمَتِهِ مَن يَشَاءُ ۗ وَاللَّهُ ذُو الْفَضْلِ الْعَظِيمِ
Show all...
የረመዷን ስጦታ ረመዷን ሙባረክ ያ ሙሥሊሙን ወሙሥሊማት! በ 18 አርስት የተሰደረ መጣጥፍ በረመዷን ወር እንካችሁ ብለናል። ሊንኩን በማስፈንጠር ያግኙት! 1. ሶውም https://t.me/Wahidcom/3136 2. የጦም ትሩፋት https://t.me/Wahidcom/3470 3. ረመዷን https://t.me/Wahidcom/2727 4.. የረመዷን ወር https://t.me/Wahidcom/3107 5. የክርስትና ጦም https://t.me/Wahidcom/3176 6. የጨረቃ አቆጣጠር https://t.me/Wahidcom/2717 7. ጨረቃ እና ኮከብ https://t.me/Wahidcom/2360 8. የሚታሰሩ ሰይጣናት https://t.me/Wahidcom/2724 9. ሡሑር https://t.me/Wahidcom/2726 10. ተራዊህ https://t.me/Wahidcom/833 11. ኢዕቲካፍ https://t.me/Wahidcom/2286 12. ለይለቱል ቀድር https://t.me/Wahidcom/2289 13. መሓላ እና ማካካሻው https://t.me/Wahidcom/2336 14. ጦመኛ https://t.me/Wahidcom/3120 15. የተባረከ ወር https://t.me/Wahidcom/3707 16. ዘካቱል ማል https://t.me/Wahidcom/3126 17. ዘካቱል ፊጥር https://t.me/Wahidcom/3156 18. ተሀጁድ https://t.me/Wahidcom/3152 ሁሉም ቦታ ለሁሉም ሰው እንዲዳረስ አሰራጩ! ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!
Show all...
የተባረከ ወር በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥185 የረመዷን ወር በእርሱ ውስጥ ቁርኣን ለሰዎች መሪ፣ የመመሪያ ግልጽ ማስረጃ እና ፉርቃን ሲሆን የተወረደበት ነው። شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ አምላካችን አሏህ በቁርኣን ከተገለጹት ስሞቹ አንዱ "አል-ከሪም" الْكَرِيم ሲሆን ትርጉሙ "ቸሩ" "ለጋሱ" ማለት ነው፦ 82፥6 አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ? يَا أَيُّهَا الْإِنسَانُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ الْكَرِيمِ 27፥40 እርሱ ዘንድ ረግቶ ባየውም ጊዜ «ይህ ከጌታዬ ችሮታ ነው፥ የማመሰግን ወይም የምክድ መኾኔን ሊፈትነኝ ቸረልኝ፡፡ ያመሰገነም ሰው የሚያመሰግነው ለራሱ ነው፥ የካደም ሰው ጌታዬ ከእርሱ ተብቃቂ ቸር ነው» አለ፡፡ فَلَمَّا رَآهُ مُسْتَقِرًّا عِندَهُ قَالَ هَـٰذَا مِن فَضْلِ رَبِّي لِيَبْلُوَنِي أَأَشْكُرُ أَمْ أَكْفُرُ ۖ وَمَن شَكَرَ فَإِنَّمَا يَشْكُرُ لِنَفْسِهِ ۖ وَمَن كَفَرَ فَإِنَّ رَبِّي غَنِيٌّ كَرِيمٌ "ከሪም" كَرِيم የሚለው ቃል እንደየ ዐውዱ ዘርፈ ብዙ እና መጠነ ሰፊ ትርጉም አለው፥ "የተባረከ" "የተከበረ" "ቅዱስ" "ክቡር" "ብፁዕ" "ንኡድ" "ውዱስ" "ስቡህ" "እኩት" "እጹብ" የሚል ፍቺ አለው። ለምሳሌ፦ መልአኩ ጂብሪል "ከሪም" كَرِيم ተብሏል፦  81፥19 እርሱ የ-"ክቡር" መልእክተኛ ቃል ነው፡፡ إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ እዚህ ዐውድ ላይ ጂብሪል "ክቡር" ለተባለበት የገባው ቃል "ከሪም" كَرِيم ሲሆን "ንኡድ"noble" ለማለት እንጂ "ለጋሽ" "ቸር" ለማለት ተፈልጎ አይደለም፥ በተመሳሳይ ነቢያችን"ﷺ" ደግሞ "ከሪም" كَرِيم ተብለዋል፦ 69፥40 እርሱ የ-"ተከበረ" መልእክተኛ ቃል ነው፡፡ إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ እዚህ ዐውድ ላይ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" "ክቡር" ለተባሉበት የገባው ቃል "ከሪም" كَرِيم ሲሆን "ንኡድ"noble" ለማለት እንጂ "ለጋሽ" "ቸር" ለማለት ተፈልጎ አይደለም። ስለዚህ አንድ ምንነት ወይም ማንነት "ከሪም" كَرِيم ስለተባለ አሏህ ከተወሰፈበትን ወስፍ ጋር ማምታታት አግባብ አይደለም። ቁርኣን "ከሪም" كَرِيم ተብሏል፦  56፥77 እርሱ "የከበረ" ቁርኣን ነው። إِنَّهُۥ لَقُرْءَانٌۭ كَرِيمٌۭ እዚህ አንቀጽ ላይ ቁርኣን "የተከበረ" ለተባለበት የገባው ቃል "ከሪም" كَرِيم ሲሆን ሌላ አንቀጽ ላይ በተለዋዋጭ ቃል "ሙባረክ" مُّبَارَك ተብሏል፦ 6፥155 ይህም ያወረድነው የኾነ "የተባረከ" መጽሐፍ ነው፡፡ وَهَـٰذَا كِتَابٌ أَنزَلْنَاهُ مُبَارَكٌ እዚህ አንቀጽ ላይ ቁርኣን "የተባረከ" ለተባለበት የገባው ቃል "ሙባረክ" مُّبَارَك ሲሆን "ሙባረክ" እና "ከሪም" የቃላት ልዩነት እንጂ የአሳብ ልዩነት የላቸውም። አትክልቶችን እና የሚታጨድን አዝመራ ፍሬ የሚበቅልበት ውኃ "ሙባረክ" مُّبَارَك ተብሏል፦ 50፥9 ከሰማይም "ቡሩክን" ውኃ አወረድን፡፡ በእርሱም አትክልቶችን እና የሚታጨድን አዝመራ ፍሬ አበቀልን፡፡ وَنَزَّلْنَا مِنَ السَّمَاءِ مَاءً مُّبَارَكًا فَأَنبَتْنَا بِهِ جَنَّاتٍ وَحَبَّ الْحَصِيدِ እዚህ አንቀጽ ላይ ውኃ "ቡሩክ(የተባረከ) ለተባለበት የገባው ቃል "ሙባረክ" مُّبَارَك ሲሆን ሌላ አንቀጽ ላይ በተለዋዋጭ ቃል "ከሪም" كَرِيم ተብሏል፦ 79፥30 ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡ وَالْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَاهَا 79፥31 ውኃን እና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡ أَخْرَجَ مِنْهَا مَاءَهَا وَمَرْعَاهَا 26፥7 ወደ ምድርም በውስጧ "ከ"መልካም" በቃይ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን?፡፡ أَوَلَمْ يَرَوْا إِلَى الْأَرْضِ كَمْ أَنبَتْنَا فِيهَا مِن كُلِّ زَوْجٍ كَرِيمٍ እዚህ አንቀጽ ላይ "መልካም" ለሚለው የገባው ቃል "ከሪም" كَرِيم እንደሆነ ልብ አድርግ! "ሙባረክ" እና "ከሪም" ተለዋዋጭ ቃላት እንደሆኑ ለመረዳት ከላይ የቀረቡት ናሙናዎች በቂ ማሳያ ናቸው። እዚህ ድረስ ከተግባባን የረመዷን ወር ቁርኣን የወረደበት ወር ነው፦ 2፥185 የረመዷን ወር በእርሱ ውስጥ ቁርኣን ለሰዎች መሪ፣ የመመሪያ ግልጽ ማስረጃ እና ፉርቃን ሲሆን የተወረደበት ነው። شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ "ፉርቃን" فُرْقَان ማለት "እውነት ከሐሰት፣ ትክክሉን ከስህተት፣ መልካሙን ከክፉ የሚለይ ሚዛን" ማለት ነው። "ሸህሩ ረመዷን" شَهْرُ رَمَضَان ማለት "የረመዳን ወር" ማለት ነው፥ "ረመዷን" رَمَضَان ደግሞ የዘጠነኛው ወር ስም ነው። "ረመዷን" የወር ስም እንጂ የጦም ስም አይደለም፥ ነገር ግን ይህ ወር ቁርኣን የተወረደበት ወር በመሆኑ "ሸህሩ ሙባረክ" شَهْرُ مُّبَارَك ማለትም "የተባረከ ወር" ተብሏል፦ ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 22, ሐዲስ 17 አቢ ሁራይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የተባረከው ወር ረመዷን መጣላችሁ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ أَتَاكُمْ رَمَضَانُ شَهْرٌ مُبَارَكٌ ከዚህ አንጻር "ረመዷን ሙባረክ" رَمَضَان مُّبَارَك የሚለውን በቋንቋዬ ተርጉሜ "የተባረከ ረመዷን" ብል የቃላት ልዩነት እንጂ የአሳብ ልዩነት ከሌለው "ረመዷን ከሪም" رَمَضَان كَرِيم ሲባል "መልካም ረመዷን" "የተከበረ ረመዷን" ብል የቃላት እንጂ የአሳብ ልዩነት የለውም። "ኢማን" إِيمَان የሚለውን ቃል ቁርኣን እና ሐዲስ ውስጥ በቁናህ ታገኘዋለህ፥ ቅሉ ግን የኢማን ተለዋዋጭ ቃል "ዐቂዳህ" عَقِيدَة የሚለውን በስም መደብ ቁርኣን ውስጥ አታገኘውም። ነገር ግን ዐቂዳህ እያልን እንማራለን እናስተምራለን፥ "ሙባረክ" እና "ከሪም" የሚለውን በዚህ ስሌት እና ሒሣብ መረዳት ይቻላል። ስለዚህ "ረመዷን ሙባረክ" رَمَضَان مُّبَارَك እና "ረመዷን ከሪም" رَمَضَان كَرِيم ተለዋዋጭ ቃላት እስከሆኑ ድረስ መርጠን መጠቀም እንችላለን። "አሏሁ አዕለም! ይህ ሙግት የቋንቋን ሙግት ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ሙግት ነው። "ረመዷን ከሪም" رَمَضَان كَرِيم ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
"ኤኻድ እና ያኺድ" በሚል ርእስ ዙሪያ ዳሰሳ እና ሐተታ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/t2OwjlluSN0?si=Mm8ABvNu3B3XMXlT ያዳመጣችሁ ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!
Show all...
ሶሉ ዐላ ነቢይና"ﷺ" በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡ 94፥4 መወሳትህንም ለአንተ ከፍ አድርገንልሀል። وَرَفَعْنَا لَكَ ذِكْرَكَ አንድ ሙሥሊም በአዛን፣ በቂያም፣ በሸሀዳህ "ሙሐመድ የአሏህ መልእክተኛ ነው" ብለን እናውጃለን፥ አምላካችን አሏህ መወሳት ለነቢያችን"ﷺ" ከፍ አድርጎላቸዋል። እንዲሁ ስማቸው ሲወሳ "የአሏህ ረድኤት እና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁን" በማለት መወሳትን ከፍ እናደርግላቸዋለን፦ 94፥4 መወሳትህንም ለአንተ ከፍ አድርገንልሀል። وَرَفَعْنَا لَكَ ذِكْرَكَ "አሏሁመ ሶሊ ዐላ ሙሐመድ ወአሊ ሙሐመድ" ٱللّٰهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَآلِ مُحَمَّدٍ "ሶለላሁ ዐለይሂ ወሠለም" صَلَّى ٱللَّٰهُ عَلَيْهِ وَسَلَّم ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
"የአብርሃሙ ሥላሴ" በሚል ርእስ ዙሪያ ዳሰሳ እና ሐተታ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/GMhX99TrVJI?si=eeVZkONW3y3GIzvW ያዳመጣችሁ ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!
Show all...
በስልጥኛ ደርሥ ተለቋል። አንብቡ፦ https://t.me/wahidcomselitiy/26
Show all...
የሃይማኖት ንጽጽር ኮርስ በወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር"Wahid islamic apologetics society" 11ኛ ዙር የሙቃረናህ ደርሥ! "ሙቃረናህ" مُقَارَنَة የሚለው ቃል "ቃረነ" قَارَنَ ማለትም "አነጻጸረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ንጽጽር" ማለት ነው፥ ሙቃረናህ የሃይማኖት ንጽጽር"Comparative Religion" ሲሆን በእሥልምና እና በክርስትና መካከል ያለው የሥነ-መለኮት አንድነት እና ልዩነት እየተነጻጸረ የሚቀርብበት ጥናት ነው። ደርሡ (ትምህርቱ) የሚፈጀው 7 ወር ኢንሻሏህ ሲሆን ሁለት ተርም አለው። ፨ የመጀመሪያው ተርም ዐጽመ አሳብ በፈጣሪ እሳቦት ላይ የሚያውጠነጥነው፦ በሥላሴ"trinity" እሳቤ፣ በነገረ-ክርስቶስ ጥናት"Christology"፣ በነገረ-ማርያም ጥናት"Mariology"፣ በነገረ-መላእክት ጥናት"angelology"፣ በነገረ-ምስል ጥናት"Iconlogy" ላይ ነው። ፨ የሁለተኛው ተርም ዐጽመ-አሳብ በቅዱሳን መጽሐፍት ላይ የሚያውጠነጥነው፦ በአህሉል ኪታብ"People of the Book"፣ በመጽሐፍት"scriptures"፣ በመጽሐፍ አጠባበቅ"preservation"፣ በመጽሐፍት ልኬት"Standardization"፣ በባይብል ግጭት"Contradiction"፣ በኦሪት"Torah"፣ በወንጌል"Gospel" ላይ ነው። አባሪ ኮርሶች፦ 1. ዐቂዳህ"creed" 2. ሥነ ምግባር"ethics" 3. ሥነ አመክንዮ"logic" 4. ሥነ ልቦና"psychology" 5. ሥነ ቋንቋ"linguistics" ናቸው። ለመመዝገብ ከታች የተዘረዘሩት አድሚናት በውስጥ ያናግሩ! ወንድም አቡ ኑዓይም፦https://t.me/arhmanu እኅት ሰላም፦ http://t.me/SeuweSe አኅት ዘሃራ፦ https://t.me/Zhara_mustefa እኅት አበባ፦ http://t.me/selemtewa ቦታ ሳይያዝ ይመዝገቡ! መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንልዎ! ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
Show all...
"ኑ እንውረድ" በሚል ደርሥ ተለቊል፥ በነገረ ሥላሴ"triadology" ከሚጠቀሱ ተወዳጆች ጥቅሳት አንዱ ዘፍጥረት 11፥6-7 ነው። በዚህ ዙሪያ ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/Ihf-WhiGhHk?si=Sko8EK2kj8qupQBd
Show all...
ሐውቀላህ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 11፥73 «ከአሏህ ትዕዛዝ ትደነቂያለሽን የአላህ ችሮታና በረከቶቹ በእናንተ በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ይሁን "እርሱ አሏህ ምስጉን ክቡር ነውና» አሉ፡፡ قَالُوا أَتَعْجَبِينَ مِنْ أَمْرِ اللَّهِ ۖ رَحْمَتُ اللَّهِ وَبَرَكَاتُهُ عَلَيْكُمْ أَهْلَ الْبَيْتِ ۚ إِنَّهُ حَمِيدٌ مَّجِيدٌ "መጅድ" مَجْد የሚለው ቃል "መጀደ" مَجَدَ ማለትም "አከበረ" "ከፍ አረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ክብር" "ከፍታ" ማለት ነው። በቁርኣን ከተጠቀሱ የአሏህ የተዋቡ ስሞች መካከል “አል-መጂድ” الْمَّجِيد ሲሆን “እጅግ በጣም የተከበረ” ማለት ነው፦ 11፥73 «ከአላህ ትዕዛዝ ትደነቂያለሽን የአላህ ችሮታና በረከቶቹ በእናንተ በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ይሁን "እርሱ አሏህ ምስጉን ክቡር ነውና» አሉ፡፡ قَالُوا أَتَعْجَبِينَ مِنْ أَمْرِ اللَّهِ ۖ رَحْمَتُ اللَّهِ وَبَرَكَاتُهُ عَلَيْكُمْ أَهْلَ الْبَيْتِ ۚ إِنَّهُ حَمِيدٌ مَّجِيدٌ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 60, ሐዲስ 48 አቡ ሑመይድ አሥ-ሣዒዲይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ ”ሰዎች፦ “የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ሆይ! በእርሶ ላይ እንዴት ረድኤት እናውርድ? አሉ፤ የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “አሏህ ሆይ! ረድኤትን በኢብራሂም ቤተሰብ ላይ እንዳወረድክ በሙሐመድ፣ በባልተቤቶቹ እና በዝርዮቹ ላይ አውርድ! በረከትን በኢብራሂም ቤተሰብ ላይ እንዳወረድክ በሙሐመድ፣ በባልተቤቶቹ እና በዝርዮቹ ላይ አውርድ! አንተ የተመሰገንክ እና የተከበርክ ነህ" አሉ። أَخْبَرَنِي أَبُو حُمَيْدٍ السَّاعِدِيُّ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّهُمْ قَالُوا يَا رَسُولَ اللَّهِ كَيْفَ نُصَلِّي عَلَيْكَ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ قُولُوا اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَأَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، وَبَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَأَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ ‏”‌‏.‏ ይህ አሏህ በአምልኮ ከፍ ከፍ ማድረግ "ሐውቀላህ" حَوْقَلَة ይባላል። ይህም ተዝኪራ "ላ ሀውለ ወላ ቁውወተ ኢላ ቢላህ" لا حَوْلَ وَلا قُوَّةَ إِلا بالله ነው። "ላ ሀውለ ወላ ቁውወተ ኢላ ቢላህ" ማለት "በአሏህ ቢሆን እንጂ ብልሃት ሆነ ኃይል የለም" ማለት ነው፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 33, ሐዲስ 170 አቢ ዘር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ"፦ "ከጀነት ሃብት አንዱን ሃብት ልጠቁምህን? አሉኝ። እኔም፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! አዎ" አልኩኝ። እርሳቸውም፦ "በአሏህ ቢሆን እንጂ ብልሃት ሆነ ኃይል የለም" ነው፥ አሉ"። عَنْ أَبِي ذَرٍّ، قَالَ قَالَ لِي رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏"‏ أَلاَ أَدُلُّكَ عَلَى كَنْزٍ مِنْ كُنُوزِ الْجَنَّةِ ‏"‏ ‏.‏ قُلْتُ بَلَى يَا رَسُولَ اللَّهِ ‏.‏ قَالَ ‏"‏ لاَ حَوْلَ وَلاَ قُوَّةَ إِلاَّ بِاللَّهِ ‏ "አሏሁመ ሶሊ ዐላ ሙሐመድ ወአሊ ሙሐመድ" ٱللّٰهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَآلِ مُحَمَّدٍ "ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሠለም" صَلَّى ٱللَّٰهُ عَلَيْهِ وَسَلَّم ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
"ከእኛ እንደ አንዱ" በሚል ደርሥ ተለቊል፥ በነገረ ሥላሴ"triadology" ከሚጠቀሱ ተወዳጆች ጥቅሳት አንዱ ዘፍጥረት 3፥22 ነው። በዚህ ዙሪያ ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/t8ZAOLTG-6A?si=OwC0Yl-DKEgRK32D ያዳመጣችሁ ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!
Show all...
"እንፍጠር" በሚል ትምህርት ተለቋል። ፈጣሪ “እንፍጠር” ሲል ምን ማለት ነው? "እንፍጠር" ያለው ማን ነው? "እንፍጠር" ያለው ለእነማን ነው? በዚህ ዙሪያ ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/EJA9f_jrPwE?si=ut1YQ8G7a4DatjVc ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!
Show all...
ሰማይ እና ምድር በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 41፥11 ከዚያም ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ፡፡ ለእርሷም ለምድርም «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው፡፡ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፡፡ ثُمَّ اسْتَوَىٰ إِلَى السَّمَاءِ وَهِيَ دُخَانٌ فَقَالَ لَهَا وَلِلْأَرْضِ ائْتِيَا طَوْعًا أَوْ كَرْهًا قَالَتَا أَتَيْنَا طَائِعِينَ አምላካችን አሏህ ሰማይን ጭስ"gas" አርጎ ከፈጠራት በኃላ በጭስ ደረጃ እያለች ለእርሷ እና ለምድር፦ "ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ" አላቸው፥ እነርሱም፦ "ታዛዦች ኾነን መጣን" አሉ፦ 41፥11 ከዚያም ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ፡፡ ለእርሷም ለምድርም «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው፡፡ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፡፡ ثُمَّ اسْتَوَىٰ إِلَى السَّمَاءِ وَهِيَ دُخَانٌ فَقَالَ لَهَا وَلِلْأَرْضِ ائْتِيَا طَوْعًا أَوْ كَرْهًا قَالَتَا أَتَيْنَا طَائِعِينَ አሏህ ሰማይ እና ምድርን «ኑ» ሲላቸው እነርሱም፦ «ታዛዦች ኾነን መጣን» ማለታቸው የሚያስቅ እና የሚያሳልቅ ከሆነ እንግዲያውስ ያህዌህ በባይብል ምድርን እና ሰማያትን ሲጠራቸው በአንድነት እንደሚቆሙ ይናገራል፦ ኢሳይያስ 48፥13 እጄም ምድርን መሥርታለች ቀኜም ሰማያትን ዘርግታለች፥ በጠራኋቸው ጊዜ በአንድነት ይቆማሉ። אַף־יָדִי֙ יָ֣סְדָה אֶ֔רֶץ וִֽימִינִ֖י טִפְּחָ֣ה שָׁמָ֑יִם קֹרֵ֥א אֲנִ֛י אֲלֵיהֶ֖ם יַעַמְד֥וּ יַחְדָּֽו׃ "በአንድነት" ለሚለው የገባው ቃል "የሕዳው" יַחְדָּֽו ሲሆን "አንድ ላይ"together" ማለት ነው፥ የሚጠራቸው መቼ ነው? በአንድ ላይ ሲቆሙ የሚቆሙት አየር ላይ ነው ወይስ ሥፍራ አላቸው? እንኳን ሰማይ እና ምድር ከዋክብትም ሲጠራቸው፦ "ፈጣሪያችን ወደ አንተ መጣን" ይላሉ፦ መጽሐፈ ባሮክ 3፥29(1980 ዕትም) "ይጠራቸዋል እርሱን የሚመስል ሌላ የለምና "ፈጣሪያችን ወደ አንተ መጣን" ይላሉ። Book of Baruch 3፥35 when he calls them, they answer፦ "Here we are" they shine to delight their Creator" "ወሒድ ይህ እኮ ፈሊጣዊ አገላለጽ"idiomatic expression" ነው" ካላችሁ እንግዲያውስ "ኢስጢላሕ" اِصْطِلَاح ማለት "ፈሊጣዊ አገላለጽ" ማለት ነውና አሏህ ሰማይ እና ምድርን «ኑ» ሲላቸው እነርሱም፦ «ታዛዦች ኾነን መጣን» ማለታቸው የሚያስቅ እና የሚያሳልቅ ነገር ሳይሆን ኢስጢላሕ ነው። ቢያንስ ቢያንስ የራሳችሁ መጽሐፍ አታነቡምን? አለዚያ እንደዚህ በሰፈራችሁት ቁና መሰፈራችሁ አይቀርም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
"ኤሎሂም" በሚል ትምህርት ተለቋል። "ኤሎሂም" ማለት ትርጉሙ "አማልክት" ማለት ሲሆን ፈጣሪ “ኤሎሂም” ሲባል ምን ማለት ነው? "አማልክት" የተባሉት ሥላሴ ከሆኑ ሥላሴ አማልክት ናቸው? እነዚህ የመሳሰሉ እሳቦት ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/DYDqQqemDFk?si=qYY0t9HgIv-F0cvi ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!
Show all...
"እጆች" የሚለው ቃል "እጅ" ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ "ጭቃ" ማለት "የውኃ እና የአፈር ቅልቅል ነው። ፈጣሪ ሰውን ከጭቃ በእጁ ለውሶ ሠራው፦ ኢዮብ 10፥8 እጅህ ለወሰችኝ ሠራችኝም። יָדֶ֣יךָ עִ֭צְּבוּנִי וַֽיַּעֲשׂ֑וּנִי ኢዮብ 33፥6 እኔ ደግሞ ከጭቃ የተፈጠርሁ ነኝ። מֵ֝חֹ֗מֶר קֹרַ֥צְתִּי גַם־אָֽנִי׃ ፈጣሪ ሰውን ከጭቃ በእጆቹ ካበጀ እና ከሠራ እጆቹ ቀኝ እና ግራ ናቸው፥ ምክንያቱም ፈጣሪ ቀኝ እና ግራ ካለው ቀኝ እና ግራ እጆች አሉት፦ 1ኛ ነገሥት 22፥19 ሚክያስም አለ፦ እንግዲህ የያህዌህን ቃል ስማ! ያህዌህ በዙፋኑ ተቀምጦ፥ የሰማይም ሠራዊት ሁሉ "በቀኙ" እና "በግራው" ቆመው አየሁ። וַיֹּ֕אמֶר לָכֵ֖ן שְׁמַ֣ע דְּבַר־יְהוָ֑ה רָאִ֤יתִי אֶת־יְהוָה֙ יֹשֵׁ֣ב עַל־כִּסְאֹ֔ו וְכָל־צְבָ֤א הַשָּׁמַ֙יִם֙ עֹמֵ֣ד עָלָ֔יו מִימִינֹ֖ו וּמִשְּׂמֹאלֹֽו׃ እዚህ አንቀጽ ላይ "ቀኝ" ለሚለው የገባው ቃል "የሚን" יָמִין ሲሆን "ግራ" ለሚለው የገባው ቃል ደግሞ "ሸሙል" שְׂמֹאול ነው። "ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ እነርሱም "ፈጣሪ እጅ አለው" ሲባል የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም" ብለዋል፦ ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30 “ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”። እርማችሁን አውጡ! ሠለስቱ ምዕት ፈጣሪ እጅ እንዳለው እንቅጩን ፍርጥ አርገው ተናግረዋል። ለእግዚአብሔር እጆች እንዳሉት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ተናግሯል፦ መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 1 ቁጥር 62 “እግዚአብሔር እጆች እና ክንድ፣ ጥፍር እንዳለው ዕወቁ”። ስለዚህ "አሏህ እጆች አሉት" ሲባል በደምሳሳው የምትተቹ ሰዎች መጽሐፋችሁ ላይ ያህዌህ እጆች እንዳሉት ስትረዱ ምን ይውጣችሁ ይሆን? የመነቸከ ሙግት ከምትሟገቱ ይልቅ የፋፋና የዳበረ እንዲሁ የላመና የጣመ ሙግት ለማደራጀት እና ለማዋቀር መሞከር አይሻላችሁምን? አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
የአሏህ እጆች በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 38፥75 አሏህም «ኢብሊሥ ሆይ! "በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦ 42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም። እዚሁ አንቀጽ ላይ አሏህ "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ተገልጿል፥ ሰውም "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ሌላ አንቀጽ ላይ ተገልጿል፦ 76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا የአሏህ መስማት እና ማየት ከፍጡራን ጋር እንደማይመሳሰል እና እንደማይነጻጸር ሁሉ የፈጣሪ ባሕርዮት ከፍጡራን ጋር አይመሳሰለም አይነጻጸርም። ይህንን መረዳት ይዘን ቁርኣን ላይ አምላካችን አሏህ እጆች እንዳሉት ይናገራል፦ 38፥75 አሏህም «ኢብሊሥ ሆይ! "በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ "ሁለት እጆች" ለሚለው የገባው "የደይየ" ِيَدَىَّ ሲሆን ሙሰና"dual" እንደሆነ ልብ አድርግ! አምላካችን አሏህ ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰሉ እጆች አሉት፥ የእርሱ እጆች ፍጥረታዊ ሳይሆኑ መለኮታዊ እንዲሁ ሰዋዊ ሳይሆኑ አምላካዊ ናቸው። የአሏህ እጆች ቀኝ ናቸው፦ ሚስካቱል መሷሒብ መጽሐፍ 18, ሐዲስ 30 ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር ኢብኑ አል ዓሲ እንደተረከው፦ "የአሏህም መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ፍትኸኞች አሏህ ዘንድ በብርሃን መንበሮች ላይ ከአር ረሕማን በስ ተቀኝ በኩል ይሆናሉ፥ "ሁለቱም እጆቹ ቀኝ ናቸው"። وَعَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرِو بْنِ الْعَاصِ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: إِنَّ الْمُقْسِطِينَ عِنْدَ اللَّهِ عَلَى مَنَابِرَ مِنْ نُورٍ عَنْ يَمِينِ الرَّحْمَنِ وَكِلْتَا يَدَيْهِ يمينٌ "የሚን" يَمِين ማለት "ጠንካራ" "አውንታዊ" "ሙሉነት" በሚል ትርጉም ይመጣል፥ "ሸማል" شِّمَال ማለት "ደካማ" "አሉታዊ" "ጎዶሎነት" በሚል ትርጉም ይመጣል። በዐማርኛችን "በቀኝ አውለኝ" እና "ግራ ያጋባል" በሚል ዐውድ ቀኝ እና ግራ አውንታዊ እና አሉታዊ ነገር ለማመልከት ይመጣሉ፥ እሩቅ ስንሄድ "left" የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል "ደካማ"weak" ማለት ነው። ስለዚህ "የአሏህ እጆች ቀኝ ናቸው" ማለት "ጠንካራ፣ አውንታዊ፣ ሙሉ ናቸው" ማለት ነው እንጂ አሏህ ቀኝ እና ግራ የሆኑ እጆች አሉት፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 52 ሐዲስ 7 ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህም መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ዐዘ ወጀል በፍርዱ ቀን ሰማያትን ይይዛል፥ ከዚያም በቀኝ እጁ ያረግና፦ "እኔ ንጉሡ ነኝ፥ ትዕቢተኞች የት አሉ? ኩሩዎች የት አሉ?" ይላል፥ ከዚያም ምድርን በግራ እጁ አድርጎ፦ "ትዕቢተኞች የት አሉ? ኩሩዎች የት አሉ?" ይላል። عَبْدُ اللَّهِ بْنُ عُمَرَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ يَطْوِي اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ السَّمَوَاتِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ثُمَّ يَأْخُذُهُنَّ بِيَدِهِ الْيُمْنَى ثُمَّ يَقُولُ أَنَا الْمَلِكُ أَيْنَ الْجَبَّارُونَ أَيْنَ الْمُتَكَبِّرُونَ ثُمَّ يَطْوِي الأَرَضِينَ بِشِمَالِهِ ثُمَّ يَقُولُ أَنَا الْمَلِكُ أَيْنَ الْجَبَّارُونَ أَيْنَ الْمُتَكَبِّرُونَ ‏"‏ ‏.‏ "በቀኝ እጁ" እና "በግራ እጁ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! የእርሱን እጆች ትርጉም በመስጠት ሳናራቁጥ እና ከፍጡራን እጆች ጋር ሳናነጻጽር እርሱ በነገረን መሠረት እንቀበላለን። ወደ ባይብሉ ስንገባ ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር ያበጀው በእጆቹ ነው፦ መዝሙር 119፥73 "እጆችህ" ሠሩኝ አበጃጁኝም። יָדֶ֣יךָ עָ֭שׂוּנִי וַֽיְכֹונְנ֑וּנִי ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር "አበጀው"። וַיִּיצֶר֩ יְהוָ֨ה אֱלֹהִ֜ים אֶת־הָֽאָדָ֗ם עָפָר֙ מִן־הָ֣אֲדָמָ֔ה
Show all...
እርማችሁን አውጡ! ሠለስቱ ምዕት ፈጣሪ እጅ እንዳለው እንቅጩን ፍርጥ አርገው ተናግረዋል። ለእግዚአብሔር እጆች እንዳሉት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ተናግሯል፦ መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 1 ቁጥር 62 “እግዚአብሔር እጆች እና ክንድ፣ ጥፍር እንዳለው ዕወቁ”። ስለዚህ "አሏህ እጆች አሉት" ሲባል በደምሳሳው የምትተቹ ሰዎች መጽሐፋችሁ ላይ ያህዌህ እጆች እንዳሉት ስትረዱ ምን ይውጣችሁ ይሆን? የመነቸከ ሙግት ከምትሟገቱ ይልቅ የፋፋና የዳበረ እንዲሁ የላመና የጣመ ሙግት ለማደራጀት እና ለማዋቀር መሞከር አይሻላችሁምን? አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
የአሏህ እጆች በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 38፥75 አሏህም «ኢብሊሥ ሆይ! "በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦ 42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም። እዚሁ አንቀጽ ላይ አሏህ "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ተገልጿል፥ ሰውም "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ሌላ አንቀጽ ላይ ተገልጿል፦ 76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا የአሏህ መስማት እና ማየት ከፍጡራን ጋር እንደማይመሳሰል እና እንደማይነጻጸር ሁሉ የፈጣሪ ባሕርዮት ከፍጡራን ጋር አይመሳሰለም አይነጻጸርም። ይህንን መረዳት ይዘን ቁርኣን ላይ አምላካችን አሏህ እጆች እንዳሉት ይናገራል፦ 38፥75 አሏህም «ኢብሊሥ ሆይ! "በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ "ሁለት እጆች" ለሚለው የገባው "የደይየ" ِيَدَىَّ ሲሆን ሙሰና"dual" እንደሆነ ልብ አድርግ! አምላካችን አሏህ ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰሉ እጆች አሉት፥ የእርሱ እጆች ፍጥረታዊ ሳይሆኑ መለኮታዊ እንዲሁ ሰዋዊ ሳይሆኑ አምላካዊ ናቸው። የአሏህ እጆች ቀኝ ናቸው፦ ሚስካቱል መሷሒብ መጽሐፍ 18, ሐዲስ 30 ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር ኢብኑ አል ዓሲ እንደተረከው፦ "የአሏህም መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ፍትኸኞች አሏህ ዘንድ በብርሃን መንበሮች ላይ ከአር ረሕማን በስ ተቀኝ በኩል ይሆናሉ፥ "ሁለቱም እጆቹ ቀኝ ናቸው"። وَعَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرِو بْنِ الْعَاصِ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: إِنَّ الْمُقْسِطِينَ عِنْدَ اللَّهِ عَلَى مَنَابِرَ مِنْ نُورٍ عَنْ يَمِينِ الرَّحْمَنِ وَكِلْتَا يَدَيْهِ يمينٌ "የሚን" يَمِين ማለት "ጠንካራ" "አውንታዊ" "ሙሉነት" በሚል ትርጉም ይመጣል፥ "ሸማል" شِّمَال ማለት "ደካማ" "አሉታዊ" "ጎዶሎነት" በሚል ትርጉም ይመጣል። በዐማርኛችን "በቀኝ አውለኝ" እና "ግራ ያጋባል" በሚል ዐውድ ቀኝ እና ግራ አውንታዊ እና አሉታዊ ነገር ለማመልከት ይመጣሉ፥ እሩቅ ስንሄድ "left" የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል "ደካማ"weak" ማለት ነው። ስለዚህ "የአሏህ እጆች ቀኝ ናቸው" ማለት "ጠንካራ፣ አውንታዊ፣ ሙሉ ናቸው" ማለት ነው እንጂ አሏህ ቀኝ እና ግራ የሆኑ እጆች አሉት፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 52 ሐዲስ 7 ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህም መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ዐዘ ወጀል በፍርዱ ቀን ሰማያትን ይይዛል፥ ከዚያም በቀኝ እጁ ያረግና፦ "እኔ ንጉሡ ነኝ፥ ትዕቢተኞች የት አሉ? ኩሩዎች የት አሉ?" ይላል፥ ከዚያም ምድርን በግራ እጁ አድርጎ፦ "ትዕቢተኞች የት አሉ? ኩሩዎች የት አሉ?" ይላል። عَبْدُ اللَّهِ بْنُ عُمَرَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ يَطْوِي اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ السَّمَوَاتِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ثُمَّ يَأْخُذُهُنَّ بِيَدِهِ الْيُمْنَى ثُمَّ يَقُولُ أَنَا الْمَلِكُ أَيْنَ الْجَبَّارُونَ أَيْنَ الْمُتَكَبِّرُونَ ثُمَّ يَطْوِي الأَرَضِينَ بِشِمَالِهِ ثُمَّ يَقُولُ أَنَا الْمَلِكُ أَيْنَ الْجَبَّارُونَ أَيْنَ الْمُتَكَبِّرُونَ ‏"‏ ‏.‏ "በቀኝ እጁ" እና "በግራ እጁ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! የእርሱን እጆች ትርጉም በመስጠት ሳናራቁጥ እና ከፍጡራን እጆች ጋር ሳናነጻጽር እርሱ በነገረን መሠረት እንቀበላለን። ወደ ባይብሉ ስንገባ ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር ያበጀው በእጆቹ ነው፦ መዝሙር 119፥73 "እጆችህ" ሠሩኝ አበጃጁኝም። יָדֶ֣יךָ עָ֭שׂוּנִי וַֽיְכֹונְנ֑וּנִי ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር "አበጀው"። וַיִּיצֶר֩ יְהוָ֨ה אֱלֹהִ֜ים אֶת־הָֽאָדָ֗ם עָפָר֙ מִן־הָ֣אֲדָמָ֔ה "እጆች" የሚለው ቃል "እጅ" ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ "ጭቃ" ማለት "የውኃ እና የአፈር ቅልቅል ነው። ፈጣሪ ሰውን ከጭቃ በእጁ ለውሶ ሠራው፦ ኢዮብ 10፥8 እጅህ ለወሰችኝ ሠራችኝም። יָדֶ֣יךָ עִ֭צְּבוּנִי וַֽיַּעֲשׂ֑וּנִי ኢዮብ 33፥6 እኔ ደግሞ ከጭቃ የተፈጠርሁ ነኝ። מֵ֝חֹ֗מֶר קֹרַ֥צְתִּי גַם־אָֽנִי׃ ፈጣሪ ሰውን ከጭቃ በእጆቹ ካበጀ እና ከሠራ እጆቹ ቀኝ እና ግራ ናቸው፥ ምክንያቱም ፈጣሪ ቀኝ እና ግራ ካለው ቀኝ እና ግራ እጆች አሉት፦ 1ኛ ነገሥት 22፥19 ሚክያስም አለ፦ እንግዲህ የያህዌህን ቃል ስማ! ያህዌህ በዙፋኑ ተቀምጦ፥ የሰማይም ሠራዊት ሁሉ "በቀኙ" እና "በግራው" ቆመው አየሁ። וַיֹּ֕אמֶר לָכֵ֖ן שְׁמַ֣ע דְּבַר־יְהוָ֑ה רָאִ֤יתִי אֶת־יְהוָה֙ יֹשֵׁ֣ב עַל־כִּסְאֹ֔ו וְכָל־צְבָ֤א הַשָּׁמַ֙יִם֙ עֹמֵ֣ד עָלָ֔יו מִימִינֹ֖ו וּמִשְּׂמֹאלֹֽו׃ እዚህ አንቀጽ ላይ "ቀኝ" ለሚለው የገባው ቃል "የሚን" יָמִין ሲሆን "ግራ" ለሚለው የገባው ቃል ደግሞ "ሸሙል" שְׂמֹאול ነው። "ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ እነርሱም "ፈጣሪ እጅ አለው" ሲባል የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም" ብለዋል፦ ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30 “ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”።
Show all...
"ሥሉስ አምላክ" በሚል ትምህርት ተለቋል። “ሥሉስ” ማለት “ሥስት”three" ማለት ሲሆን "ሥሉስ አምላክ" ማለት "ሦስት አምላክ" ማለት ነው። ሥላሴአውያን "አምላክ ሦስት ነው" ብለው በትውፊታቸው ማስቀመጣቸው ዳሰናል። ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/iZuSQVwoI3A?si=8wQKlLznMBEH-fOd ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!
Show all...
ትራይፎም አምላክ እና መልአክ የተለያዩ ምንነቶች እንደሆነ ሲነግረው ዮስጦስም የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል የሚመጣው ሌላው አምላክ ኢየሱስ እንጂ የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የተባለው አንድ አምላክ አብ እንዳይደለ ነግሮታል፦ "አንተ እንዳልከው "ሁለቱ መልአክ እና አምላክ ነበሩ" ቢሆን በጣም ትንሽ ዕውቀት ያለው ሰው ካልሆነ በቀር፦"የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል ላይ ታየ" ብሎ ለማስረገጥ አይደፈርም"። Dialogue with Trypho (Justin Martyr) Chapter 60. ዮስጦስ የጂፒተር ልጆች ለሚባሉት ለግሪካውያን የአምላክ በኵር የሆነው ቃል ያለ ተራክቦ መገኘት "እናንተ የጂፒተር ልጆችን ከምታምኑባቸው ጋር ተመሳሳይን እንጂ የተለያየ ነገር አላመጣንም" በማለት ዓይኑን አፍጦ እና ጥርሱን አግጦ ትምህርቱ ከአማውያን እንደሚመሳሰል ተናግሯል፦ "እንዲሁ የአምላክ በኵር የሆነው ቃል ያለ ተራክቦ መገኘት እና መምህራችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቀለ፣ ሞተ፣ ተነሳ እና ወደ ሰማይ ዐረገ ስንል እናንተ የጂፒተር ልጆችን ከምታምኑባቸው ጋር ተመሳሳይን እንጂ የተለያየ ነገር አላመጣንም"። The Ante-Nicene Fathers: The first Apology of justin chapter 21 እንግዲህ ሐዋርያት "አንድ አምላክ አብ ነው" ብለው ስላስተማሩ "አሐዳውያን"unitarian" የነበሩ ሲሆን ከሐዋርያት ቀጥለው የመጡት አበው የሄሌናዊውን ዐረማዊነት በመቀየጥ ከአንዱ አምላክ ከአብ ሌላ ኢየሱስን ሁለተኛ እና ሌላ አምላክ በማድረጋቸው "ክልዔታውያን"Binitarian" ነበሩ። የክርስትና ታሪክ ምሁር ኤድዋርድ ጊቦን "History of christianity" በተባለው መጽሐፋቸው ላይ ስለ ክርስትና ዐረማዊነት"paganism" እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ "አረማዊነት በክርስትና ድል ቢነሳም ክርስትናም በዚያው መጠን በአረማዊነት ተበክሏል"። History of christianity (Edward Gibbon) page XVI(16) ከዚህ ሁሉ ውዝግብ በኃላ አምላካችን አሏህ ቁርኣንን በነቢያች"ﷺ" ላይ እነዚያን "ፈጣሪ ልጅ ወልዷል" ያሉትን ሊያስጠነቅቅበት አወረደው፦ 18፥4 እነዚያንም «አሏህ ልጅን ወልዷል» ያሉትን ሊያስጠነቅቅበት አወረደው፡፡ وَيُنذِرَ الَّذِينَ قَالُوا اتَّخَذَ اللَّهُ وَلَدًا "ፈጣሪ ልጅ ወልዷል" የሚለው ይህ የዐረማዊ ትምህርት ዓለም ላይ ያለውን ሁለት ቢልዮን ክርስቲያን የሚያወዛግብ ስለሆነ ቁርኣን ይህንን ለማስጠንቀቅ መውረዱ ተገቢ ነው። አሏህ አንድ ነው፥ አሏህ የሁሉ መጠጊያ ነው፦ 114፥1 በል «እርሱ አሏህ አንድ ነው»፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ 112፥2 «አሏህ የሁሉ መጠጊያ ነው»፡፡ اللَّهُ الصَّمَدُ እርሱ የሁሉ መጠጊያ ከሆነ ጊዜን እና ቦታን ያካበበ ፈጣሪ በጊዜ እና በቦታ ውስጥ ገብቶ እና ተወልዶ በአጭር ቁመት እና በጠባብ ደረት አይወሰንም፥ በእርሱ ባሕርይ መውለድ እና መወለድ ስለሌለ አልወለደም አልተወለደምም፦ 112፥3 «አልወለደም አልተወለደምም»፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ 114፥4 «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም»። وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ "ኩፉው" كُفُو ማለት "ወደር" "እኩያ" "አቻ" "ቢጤ" "አምሳያ" "ተፎካካሪ" ማለት ሲሆን እርሱ የሚተካከለው አቻ እና እኩያ እንዲሁ የሚመሳሰለው አምሳያ እና ቢጤ ከሌለው ምንም ልጅን አልወለደም፥ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፦ 23፥91 አሏህ ምንም ልጅን አልወለደም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ ۚ ከእርሱ ጋር ሌላ ወይም ሁለተኛ አምላክ ቢኖር ኖሮ በመካከላቸው መለያየት ኖሮ ከፊሉ በከፊሉ ላይ በላቀ ነበር፥ አሏህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፦ 23፥91 ያን ጊዜ ሌላ አምላክ በነበረ አምላክ ሁሉ በፈጠረው ነገር በተለየ ነበር፡፡ ከፊላቸውም በከፊሉ ላይ በላቀ ነበር፡፡ አሏህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡ إِذًا لَّذَهَبَ كُلُّ إِلَـٰهٍ بِمَا خَلَقَ وَلَعَلَا بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! እኛንም በተውሒድ ጸንተው ከሚሞቱ ሙሥሊም ባሮቹ ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
ሁለተኛ አምላክ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 23፥91 አሏህ ምንም ልጅን አልወለደም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ ۚ "ክርስትና" የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የሰየመው አግናጢዮስ ዘአንጾኪያያ በ 110 ድኅረ-ልደት ነው። ክርስትና በአውሮፓ የተሸመነበት ድርና ማግ እንደሆነ ሁሉ የተዋረደበት ማቅ፣ የተገነዘበት በፍታ፣ የተከፈነበት ግምዣ ነው፥ ክርስትና የየአውሮፓ ግሪክ ወሮም"Graeco-Roman" ፍልስፍና እና የኢየሱስ ትምህርት ቅይጥ ነው። የክርስትና ታሪክ ምሁር አዶልፍ ሃርናክ "Outlines of the History of Dogma" በተባለው መጽሐፋቸው ላይ ክርስትና ሥሩን በሄሌናውነት"hellenism" አፈር ውስጥ እንዴት እንደሰደደ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ "ክርስትና ሥሩን በሄሌናዊነት አፈር ውስጥ ሰደደ፥ በዚህም ምክንያት ለአብዛኞቹ ክርስቲያኖች ምሥጢር ሆነ"። Outlines of the History of Dogma(Adolf Harnack) Page 194 በሄለናዊ ግሪክ ሥነ-ተረት"hellenistic Greek mythology" ስለ አማልክት ያላቸው እሳቦት "ዙስ" Ζεύς የሄርሜስ አባት ሲሆን ማዕረጉ "ሆ ቴዎስ ሆ ፓትሮስ" Ο Θεός ο Πατρὸς ነው፥ "ሆ ቴዎስ ሆ ፓትሮስ" ማለት "አምላክ አባት"God the father" ማለት ነው። "ሄርሜስ" Ἑρμῆς ደግሞ የዙስ ልጅ ሲሆን በሰማይ እና በምድር መካከል ያለ መካከለኛ "መልእክተኛ" ነው። ይህ መልእክተኛው ልጅ ማዕረጉ "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዎስ" Ο Θεός ο γιος ነው፥ "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዎስ" ማለት "አምላክ ልጅ"God the son" ማለት ነው። አረማውያን አምላኪዎች በሊቃኦንያ ከተማ "አማልክት ሰዎችን መስለው ወደ እኛ ወርደዋል" በማለት በርናባስንም "ዙስ" ጳውሎስ "ሄርሜስ" አሉዋቸው፥ የድያ ካህን እና ሕዝቡ መሥዋዕት ሊሠውላቸው ወደዱ፦ የሐዋርያት ሥራ 14፥12 በርናባስንም "ዙስ" አሉት፤ ጳውሎስንም እርሱ በመናገር ዋና ስለ ነበረ "ሄርሜስ" አሉት። ἐκάλουν τε τὸν Βαρνάβαν Δία, τὸν δὲ Παῦλον Ἑρμῆν, ἐπειδὴ αὐτὸς ἦν ὁ ἡγούμενος τοῦ λόγου. ዙስ በንግግር ሳይናገር ከእርሱ ተልእኮ የሚናገር መልእክተኛ ሄርሜስን እንደሚልክ በተመሳሳይ የማይናገረውን በርናባስን "ዙስ" የሚናገረውን ጳውሎስን "ሄርሜስ" የማለታቸው ምክንያት ይህ ነው፥ "ዙስ" Ζεύς በሮማውያን "ጁፒተር" ሲባል "ሄርሜስ" Ἑρμῆς ደግሞ በሮማውያን "ሜርኩርይ" ይባላል። ከ 20 ቅድመ ልደት እስከ 50 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረ ፊሎስ ዘእስክንድርያ የግሪክን ፍልስፍና ከአይሁድ ትምህርት ጋር የሚቀይጥ አይሁዳዊ ፈላስፋ እና መካከለኛ አፍላጦናዊነትን"middle platonism" የሚያቀነቅን የነበረ ሲሆን ስለ ሎጎስ እንዲህ ይላል፦ "ሎጎስ የአምላክ የበኵር ልጅ እና የአምላክ መልአክ ነው"። Frederick Copleston, A History of Philosophy, Volume 1, Continuum, (2003), pp. 458–462. "ዲዩቴሮ ቴዎስ" δεύτερο Θεός ማለት "ሁለተኛ አምላክ" ማለት ሲሆን ይህ ሄለናዊ ፊሎስ ሎጎስን "ሁለተኛ አምላክ ነው" ብሎ ያስተምር ነበር፦ "በአምላክ የተነገረው ይህ የንግግር ዓረፍተ ነገር በጣም ተገቢ እና ምንም ውሸት የሌለበት ነበር፥ ሟች የሆነ ነገር የአጽናፈ ዓለም ታላቁ አባት በሆነው ምሳሌ ሊፈጠር አይችልምና። ነገር ግን(የተፈጠረው) የታላቁ ኑባሬ ቃል በሆነው "በሁለተኛው አምላክ" ምሳሌ በኃላ ነው"። Philo: Questions and Answers on Genesis, Chapter 2 Number 62 "ሁለተኛው አምላክ" የሚለው ይሰመርበት! የእስክንድሪያው አርጌንስ ደግሞ ኢየሱስን "ሁለተኛ አምላክ" ብሎ ያስተምር ነበር፦ "ቢሆንም እኛ "ሁለተኛ አምላክ" ብለን ልንጠራው እንችላለን፥ "ሁለተኛ አምላክ" በሚለው ቃል ስንጠራው ሌሎችን በጎነቶችን የማካተት ችሎታ ካለው በጎነት በቀር ምንም ማለት እንዳልሆነ ይወቁ። Origen Against(Contra) Celsum, Book 5 chapter 39 "ሁለተኛው አምላክ" የሚለው ይሰመርበት! "ሄቴሮ ቴዎስ" ἕτερο Θεός ማለት "ሌላ አምላክ" ማለት ሲሆን ዮስጦስ ሰማዕቱ ትራይፎ ለሚባለው አይሁዳዊ ጓደኛው ኢየሱስን "ሌላ አምላክ" ብሎታል፦ "መጻሕፍትን ስለ ተረዳችሁ ላሳምናችሁ እሞክራለሁ፥ እኔ ከምለው ነገር አለ እና አለ ከተባለው፣ ለሁሉን ነገር ፈጣሪ የሚገዛ "ሌላ አምላክ" እና ጌታ አለ። እርሱም መልአክም ተብሎም ተጠርቷል"። Justin Martyr, Dialogue with Trypho, chapter 56 "ሌላ አምላክ" የተባለው ኢየሱስ "ለሁሉን ነገር ፈጣሪ" ለተባለው ለአብ ይገዛል፥ ዮስጦስ ይህንን ሌላ አምላክ መልአክ ተብሎ የተጠራ እና ለሙሴ የተናገረው አምላክ ብሎ የጠራው ከሁሉ ነገር ፈጣሪ ከሆነው ማንነት ለይቶታል፦ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ እና የያዕቆብም አምላክ የነበረው ለሙሴ የተናገረው አምላክ የሁሉ ነገር ፈጣሪ አይደለም"። Dialogue with Trypho (Justin Martyr) Chapter 60. ትራይፎም አምላክ እና መልአክ የተለያዩ ምንነቶች እንደሆነ ሲነግረው ዮስጦስም የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል የሚመጣው ሌላው አምላክ ኢየሱስ እንጂ የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የተባለው አንድ አምላክ አብ እንዳይደለ ነግሮታል፦ "አንተ እንዳልከው "ሁለቱ መልአክ እና አምላክ ነበሩ" ቢሆን በጣም ትንሽ ዕውቀት ያለው ሰው ካልሆነ በቀር፦"የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል ላይ ታየ" ብሎ ለማስረገጥ አይደፈርም"። Dialogue with Trypho (Justin Martyr) Chapter 60.
Show all...
02:03
Video unavailableShow in Telegram
የውኃ ጥምቀት በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ "ባፕቲዝማ" βάπτισμα የሚለው ቃል "ባፕቲዞ" βᾰπτῐ́ζω ማለትም "ነከረ" "አጠለቀ" "አጠመቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መንክር" "ጥልቀት" "ጥምቀት" ማለት ነው፦ ማርቆስ 1፥4 ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ። ἐγένετο Ἰωάνης ὁ βαπτίζων ἐν τῇ ἐρήμῳ κηρύσσων βάπτισμα μετανοίας εἰς ἄφεσιν ἁμαρτιῶν. ዮሐንስ የሚያጠምቀው ጥምቀት የንስሐ ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት ሲሆን ሰዎች ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር፦ ማርቆስ 1፥5 ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር። ኢየሱስም የንስሐ ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ፥ ሲጠመቅ ጸሎት ይጸልይ ነበር፦ ማርቆስ 1፥9 በዚያ ወራትም ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ። ሉቃስ 3፥21 ሕዝቡም ሁሉ ከተጠመቁ በኋላ ኢየሱስ ደግሞ ተጠመቀ። ሲጸልይም ሰማይ ተከፈተ። የተጠመቀበት ምክንያት ጽድቅን ሁሉ ለመፈጸም ነው፥ ጽድቅ አምላክ ያዘዘው ትእዛዝ መታዘዝ ሲሆን ዓመፃ ደግሞ አምላክ የከለከለውን ማድረግ ነው። ኢየሱስ ጽድቅን በወደድ እና ዓመፃን በመጥላት የአምላኩን ትእዛዝ ለመጠበቅ እና ለማድረግ ተጠመቀ፦ ማቴዎስ 3፥15 "ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና" ዕብራውያን 1፥9 "ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ" ዮሐንስ 14፥31 "አብም እንዳዘዘኝ እንዲሁ አደርጋለሁ" ዮሐንስ 15፥10 "እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ" ኢየሱስ የተጠመቀው የውኃ ጥምቀት ብሉይ ኪዳን ላይ ያመ ጥምቀት ነው። የብሉይ ኪዳን ሰዎች የውኃ ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት ይጠመቁ ነበር፥ ይህንን የውኃ ጥምቀት የዕብራውያን ጸሐፊ ጥምቀት ይለዋል፦ ዘኍልቍ 8፥7 ታነጻቸው ዘንድ እንዲህ ታደርግላቸዋለህ፤ ኃጢአትን የሚያነጻውን ውኃ እርጫቸው። ዕብራውያን 9፥10 እስከ መታደስ ዘመን ድረስ ስለ ምግብ፣ ስለ መጠጥ፣ ስለ ልዩ ልዩ "መታጠብ" የሚሆኑ የሥጋ ሥርዓቶች ብቻ ናቸውና። μόνον ἐπὶ βρώμασιν καὶ πόμασιν καὶ διαφόροις βαπτισμοῖς, δικαιώματα σαρκὸς μέχρι καιροῦ διορθώσεως ἐπικείμενα. እዚህ አንቀጽ ላይ "መታጠብ" ለሚለው የገባው ቃል "ባፕቲዝሞስ" βαπτισμός ሲሆን "ጥምቀት" ማለት ነው፦ ዕብራውያን 6፥2 እርሱም ከሞተ ሥራ ንስሐ፣ በአምላክ እምነት፥ ስለ ጥምቀቶች፣ እጆችንም ስለ መጫን፣ ስለ ሙታንም ትንሣኤ እና ስለ ዘላለም ፍርድም ትምህርት ነው። እዚህ አንቀጽ ላይ "ጥምቀቶች" ለሚለው የገባው ቃል "ባፕቲዝሞን" βαπτισμῶν ሲሆን ይህ የውኃ ጥምቀት እስከ መታደስ ዘመን ድረስ ማለትም ኢየሱስ እስኪመጣ ድረስ የነበረ የብሉይ ሕግ ነው፥ ክርስቶስ ሲመጣ ግን ስለ የውኃ ጥምቀት ምንም አላስተማረም። ቅሉ ግን እንደተናገረ አስመስለው አስዋሽተውታል፦ ማርቆስ 16፥16 ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። የሚገርመው የማርቆስ ወንጌል የጥንት ዐበይት የግሪክ ዕደ ክታባት ኮዴክስ ቫቲካነስ እና ኮዴክስ ሲናቲከስ የሚጨርሰው ማርቆስ 16፥8 ላይ ነው፥ New International Version፦ "ከ 9-20 ያሉትን አናቅጽ ጥንታውያን እደ ክታባት እና ሌሎች የጥንት ምስክሮች የላቸውም"The earliest manuscripts and some other ancient witnesses do not have verses 9–20" በማለት ሐቁን ሳይሸሽግ ተናግሯል። አብዛኞቹ የአዲስ ኪዳን ምሁራን ከ 9-20 ያሉት የማርቆስ የመጀመሪያ ጽሑፎች ክፍል እንዳልነበሩ ነገር ግን በኋላ የተጨመሩ እንደሆነ ይስማማሉ። ኢየሱስ "የውኃ ጥምቀት አጥምቁ" ብሎ አላዘዘም። ቅሉ ግን እንደተናገረ አስመስለው አስዋሽተውታል፦ ማቴዎስ 28፥19 “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው። "በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው" የሚለው በግሪክ ዕደ ክታባት ላይ የተጨመረ ሲሆን ማቴዎስ በጻፈው በመጀመርያው በዕብራይስጥ የተቀመጠው ቃል ግን "አሕዛብን ሁሉ በስሜ ደቀ መዛሙርት አድርጉ" የሚል ነበር፥ ይህንን አሽቀንጥረው ስለጣሉት የሚያሳዝነው ይህ ንግግር ጠፍቷል። በዚህ ዙሪያ ከዚህ ቀደም የጻፍኩት መጣጥፍ ስላለ እንድትመለከቱት በትህትና እጠይቃለው፦ https://t.me/Wahidcom/3585 ስናጠቃልልለው ውስብስብ እና ውዝግብ የሌለበትን የአሏህን የተፈጥሮ ጥምቀት እንድትይዙ ጥሪያችን ነው፦ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! እኛንም በተፈጥሮ ጥምቀት ጸንተው ከሚሞቱ ሙሥሊም ባሮቹ ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
ተዋሕዶ በጉራጊኛ ተለቋል። አንብቡ፦ https://t.me/wahidcomguragiga/34
Show all...
ፍካሬአዊ ጥምቀት በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ "ሙሥተሪዎን" μῠστήρῐον ማለት "ምሥጢር"sacrament" ማለት ሲሆን በካቶሊክ፣ በምሥራቅ ኦርቶዶክስ እና በኦሬንታል ኦርቶዶክስ ሰባቱ ምሥጢራት"seven sacraments" የሚባሉት፦ 1. ንስሓ"penance" 2. ጥምቀት"baptism" 3. ቁርባን"eucharist" 4. ሜሮን"confirmation" 5. ክህነት"priesthood" 6. ተክሊል"matrimony" 7. ቀንዲል"unction" ናቸው። የሕፃናት ጥምቀት"pedobaptism" እና የዐዋቂ ጥምቀት"credobaptism" የሚቀበሉ ካቶሊክ፣ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ፣ የኦሬንታል ኦርቶዶክስ፣ ሉተራን፣ ሜቶዲስት ናቸው። ፨ "ጥምቀት የዐዋቂ ብቻ ወይስ ሕፃናትን ይጨምራል" ፨ "ጥምቀት ከገሃነም ቅጣት ያድናል ወይስ አያድንም" ፨ "ጥምቀት በሥላሴ ስም ወይስ በኢየሱስ ስም" ፨ "ጥምቀት በማስጠም"immersion" ወይስ በመርጨት"aspersion" አሊያም በማፍሰስ"affusion" የሚል ውዝግብ በክርስቲያኖች መካከል አለ። የውኃ ጥምቀት እማሬአዊ ጥምቀት ሲሆን የመከራ፣ የመንፈስ ቅዱስ እና የእሳት ጥምቀት ደግሞ ፍካሬአዊ ጥምቀት ነው፥ "ባፕቲዝማ" βάπτισμα የሚለው ቃል "ባፕቲዞ" βᾰπτῐ́ζω ማለትም "ነከረ" "አጠለቀ" "አጠመቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መንክር" "ጥልቀት" "ጥምቀት" ማለት ነው፥ ፍካሬአዊ ጥምቀት "በሆነ ነገር ተጽዕኖ ሥር መሆን" ለማመልከት ይመጣል፦ ሉቃስ 12፥50 ነገር ግን "የምጠመቃት ጥምቀት" አለችኝ፥ እስክትፈጸምም ድረስ እንዴትት እጨነቃለሁ? βάπτισμα δὲ ἔχω βαπτισθῆναι, καὶ πῶς συνέχομαι ἕως ὅτου τελεσθῇ. ኢየሱስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በውኃ ጥምቀት ከተጠመቀ በኃላ "የምጠመቃት ጥምቀት አለችኝ" ሲል ይህ ይህ ጥምቀት የውኃ ጥምቀት ሳይሆን የመከራ ጥምቀት ነው፥ ስለዚህ ጥምቀት ማለት በውኃ በማስጠም፣ በመርጨት፣ በማፍሰስ ብቻ ሳይሆን በሆነ ነገር ተጽዕኖ ሥር መሆን ለማመልከት መጥቷል፦ ሉቃስ 3፥16 እርሱ በመንፈስ ቅዱስ እና በእሳት ያጠምቃችኋል። αὐτὸς ὑμᾶς βαπτίσει ἐν Πνεύματι Ἁγίῳ καὶ πυρί· የመንፈስ ቅዱስ እና የእሳት ጥምቀት በመንፈስ ቅዱስ እና በመንፈስ ቅዱስ ልምምድ ተጽዕኖ ሥር መሆን የሚያመልከት ከሆነ እንግዲያውስ የአሏህ ጥምቀት ልክ እንደ የመከራ ጥምቀት፣ ልክ እንደ የመንፈስ ቅዱስ እና የእሳት ጥምቀት በተፈጥሮ ተጽዕኖ ሥር መሆን ስለሆነ ፍካሬአዊ እንጂ እንደ ውኃ ጥምቀት እማሬአዊ አይደለም፦ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ "ሲብጋህ" صِبْغَة የሚለው ቃል "ሶበገ" صَبَغَ ማለትም "ነከረ" "አጠመቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መንክር" "ጥምቀት" ማለት ነው፥ የአሏህ ጥምቀት የተፈጥሮ ጥምቀት ነው። "የአሏህ የተፈጥሮ ጥምቀት" ስንል ግራ የገባችሁ ክርስቲያኖች ከላይ ካለው ረገድ ተረዱት! አልምጥ እና አልግጥ ከመሆን ይልቅ ለደርዛዊ ሥነ መለኮት ሙግት ተፍ ተፍ እና ጉድ ጉድ ማለታችሁን ወደነዋልና "ይበል" "ይሁን" የሚያስብል ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! እኛንም በተፈጥሮ ጥምቀት ጸንተው ከሚሞቱ ሙሥሊም ባሮቹ ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
አምላካችን አሏህ በዚህ በተፈጥሮ ጥምቀት ስንፈጠር ያጠምቀናል፥ በማጥመቅም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? ማንም የለም፦ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ "ሲብጋህ" صِبْغَة የሚለው ቃል "ሶበገ" صَبَغَ ማለትም "ነከረ" "አጠመቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መንክር" "ጥምቀት" ማለት ነው፥ "ሶብግ" صَبْغማለት "መንከሪያ" "ማጥመቂያ" ማለት ሲሆን ይህም አሏህ ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣና፦ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» ሲል በራሳቸው ላይ የሚያስመሰክረው ምስክርነት ነው፥ እነርሱም፦ «ጌታችን ነህ መሰከርን» አሉ፦ 7፥172 ጌታህም ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣና፦ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» ሲል በራሳቸው ላይ ባስመሰከራቸው ጊዜ የኾነውን አስታውስ! «ጌታችን ነህ መሰከርን» አሉ፡፡ «በትንሣኤ ቀን ከዚህ ኪዳን ዘንጊዎች ነበርን" እንዳትሉ፡፡» وَإِذْ أَخَذَ رَبُّكَ مِن بَنِي آدَمَ مِن ظُهُورِهِمْ ذُرِّيَّتَهُمْ وَأَشْهَدَهُمْ عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ أَلَسْتُ بِرَبِّكُمْ ۖ قَالُوا بَلَىٰ ۛ شَهِدْنَا ۛ أَن تَقُولُوا يَوْمَ الْقِيَامَةِ إِنَّا كُنَّا عَنْ هَـٰذَا غَافِلِينَ ሰው በተፈጥሮው የአምልኮ ፍላጎት እና ዝንባሌ ያለው ፍጡር የሆነው በዚህ ምክንያት ነው፥ ሰው በፊጥራህ ጊዜ "ጌታችን ነህ መሰከርን" ማለታቸው በታኅታይ ሕሊና"subconscious" የተቀመጠ ሲሆን በትንሳኤ ቀን ይህ ውስጣችን ያለው ምሥጢር ይገለጻል፦ 100፥10 "በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ እንዴት እንደሚኾን፡፡ وَحُصِّلَ مَا فِي الصُّدُورِ 86፥9 "ምሥጢሮች በሚገለጡበት ቀን"፡፡ يَوْمَ تُبْلَى السَّرَائِرُ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 60, ሐዲስ 9 አነሥ እንደተረከው፦ “ነብዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አሏህም በትንሹ ቅጣት ለሚቀበል ለእሳት ሰው፦ "በምድር ላይ ሀሉም ነገር ከነበረክ፥ ራስክን ከዚህ ነጻ ለማውጣት ይቻለሃልን? ይለዋል፥ እርሱም፦ "አዎ" ይላል። ከዚያም አሏህ፦ "ከዚህ ያነሰ ነገር በአደም ጀርባ በነበርክበት ጊዜ በእኔ እንዳታሻርክ ጠይቄህ ነበር፥ ነገር ግን አንተ አሻረክ" ይለዋል። عَنْ أَنَسٍ، يَرْفَعُهُ ‏ “‏ أَنَّ اللَّهَ، يَقُولُ لأَهْوَنِ أَهْلِ النَّارِ عَذَابًا لَوْ أَنَّ لَكَ مَا فِي الأَرْضِ مِنْ شَىْءٍ كُنْتَ تَفْتَدِي بِهِ قَالَ نَعَمْ‏.‏ قَالَ فَقَدْ سَأَلْتُكَ مَا هُوَ أَهْوَنُ مِنْ هَذَا وَأَنْتَ فِي صُلْبِ آدَمَ أَنْ لاَ تُشْرِكَ بِي‏.‏ فَأَبَيْتَ إِلاَّ الشِّرْكَ ‏”‌‏.‏ አምላካችን አሏህ የአሏህን መንክር በጽናት እንድንይዝ ይርዳን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
የአሏህ ጥምቀት በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ላ ኢላሀ" لَا إِلَـٰهَ በመባል ነፍይ ሲሆን በጣዖት መካዳችን ሲሆን "ኢለል ሏህ" إِلَّا اللّٰه ደግሞ ኢስባት ሲሆን በአሏህ ማመናችን ነው፥ ይህ ጠንካራ ገመድ ነው፦ 2፥256 በጣዖትም "የሚክድ" እና በአሏህ "የሚያምን" ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا እዚህ አንቀጽ ላይ "ዘለበት" ለሚለው የገባው ቃል "ዑርዋህ" عُرْوَة ሲሆን "ገመድ" "ዘለበት" ማለት ነው፥ ሁለተናውን ለአሏህ በመታዘዝ እና በመገዛት የሰጠ ሰው "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለውን ጠንካራን ገመድ በእርግጥ ጨበጠ፦ 31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አሏህ የሚሰጥም ሰው ጠንካራን ገመድ በእርግጥ ጨበጠ፡፡ የነገሩም ሁሉ ፍጻሜ ወደ አሏህ ነው፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ ۗ وَإِلَى اللَّهِ عَاقِبَةُ الْأُمُورِ "የሚሰጥ" ለሚለው የገባው ቃል "ዩሥሊም" يُسْلِمْ እንደሆነ ልብ አድርግ! "ኢሥተምሠከ" اسْتَمْسَكَ ማለት "ጨበጠ" "ያዘ" ማለት ሲሆን ይህ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለው ጠንካራ የአሏህ ገመድ ምእመናንን በጸጋ ወንድማማቾች የሚያስተሳስር እና ከእሳት ጉድጓድ አፋፍም የሚያድን ስለሆነ "የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ" ተብለናል፦ 3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡ ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአሏህን ጸጋ አስታውሱ! በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፡፡ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ፡፡ وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا 3፥103 በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አሏህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል፡፡ وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለው ጠንካራ የአሏህ ገመድ አሏህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ኢሥላም ናት፦ 30፥30 ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአሏህን ፍጥረት ያችን አሏህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዟት፡፡ فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًۭا ۚ فِطْرَتَ ٱللَّهِ ٱلَّتِى فَطَرَ ٱلنَّاسَ عَلَيْهَا ۚ لَا تَبْدِيلَ لِخَلْقِ ٱللَّهِ ۚ ذَٰلِكَ ٱلدِّينُ ٱلْقَيِّمُ وَلَٰكِنَّ أَكْثَرَ ٱلنَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ "ያዙ" የሚለው ይሰመርበት! ማንም ተወላጅ የሚወለደው በአል-ፊጥራ በዲኑል ኢሥላም ላይ ሆኖ ነው፦ ኢማም ቡኻርይ መፅሐፍ 23, ሐዲስ 138 ከአቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተላለፈው ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፡- "ማንም ተወላጅ የሚወለደው በአል-ፊጥራ ላይ ሆኖ ነው። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ كُلُّ مَوْلُودٍ يُولَدُ عَلَى الْفِطْرَةِ، ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 46, ሐዲስ 38 አቢ ሙዓዊያህ እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ "ማንም የሚወለድ ሰው በአንደበቱ(የኩፍር ቃል) እስከሚል ድረስ በአል-ፊጥራህ ላይ ሆኖ እንጂ አይወለድም። عَنْ أَبِي مُعَاوِيَةَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ إِلاَّ عَلَى هَذِهِ الْمِلَّةِ حَتَّى يُبَيِّنَ عَنْهُ لِسَانُهُ ‏"‏ ‏. አምላካችን አሏህ በዚህ በተፈጥሮ ጥምቀት ስንፈጠር ያጠምቀናል፥ በማጥመቅም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? ማንም የለም፦ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ
Show all...
86፥9 "ምሥጢሮች በሚገለጡበት ቀን"፡፡ يَوْمَ تُبْلَى السَّرَائِرُ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 60, ሐዲስ 9 አነሥ እንደተረከው፦ “ነብዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አሏህም በትንሹ ቅጣት ለሚቀበል ለእሳት ሰው፦ "በምድር ላይ ሀሉም ነገር ከነበረክ፥ ራስክን ከዚህ ነጻ ለማውጣት ይቻለሃልን? ይለዋል፥ እርሱም፦ "አዎ" ይላል። ከዚያም አሏህ፦ "ከዚህ ያነሰ ነገር በአደም ጀርባ በነበርክበት ጊዜ በእኔ እንዳታሻርክ ጠይቄህ ነበር፥ ነገር ግን አንተ አሻረክ" ይለዋል። عَنْ أَنَسٍ، يَرْفَعُهُ ‏ “‏ أَنَّ اللَّهَ، يَقُولُ لأَهْوَنِ أَهْلِ النَّارِ عَذَابًا لَوْ أَنَّ لَكَ مَا فِي الأَرْضِ مِنْ شَىْءٍ كُنْتَ تَفْتَدِي بِهِ قَالَ نَعَمْ‏.‏ قَالَ فَقَدْ سَأَلْتُكَ مَا هُوَ أَهْوَنُ مِنْ هَذَا وَأَنْتَ فِي صُلْبِ آدَمَ أَنْ لاَ تُشْرِكَ بِي‏.‏ فَأَبَيْتَ إِلاَّ الشِّرْكَ ‏”‌‏.‏ አምላካችን አሏህ የአሏህን መንክር በጽናት እንድንይዝ ይርዳን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
የአሏህ ጥምቀት በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ላ ኢላሀ" لَا إِلَـٰهَ በመባል ነፍይ ሲሆን በጣዖት መካዳችን ሲሆን "ኢለል ሏህ" إِلَّا اللّٰه ደግሞ ኢስባት ሲሆን በአሏህ ማመናችን ነው፥ ይህ ጠንካራ ገመድ ነው፦ 2፥256 በጣዖትም "የሚክድ" እና በአሏህ "የሚያምን" ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا እዚህ አንቀጽ ላይ "ዘለበት" ለሚለው የገባው ቃል "ዑርዋህ" عُرْوَة ሲሆን "ገመድ" "ዘለበት" ማለት ነው፥ ሁለተናውን ለአሏህ በመታዘዝ እና በመገዛት የሰጠ ሰው "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለውን ጠንካራን ገመድ በእርግጥ ጨበጠ፦ 31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አሏህ የሚሰጥም ሰው ጠንካራን ገመድ በእርግጥ ጨበጠ፡፡ የነገሩም ሁሉ ፍጻሜ ወደ አሏህ ነው፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ ۗ وَإِلَى اللَّهِ عَاقِبَةُ الْأُمُورِ "የሚሰጥ" ለሚለው የገባው ቃል "ዩሥሊም" يُسْلِمْ እንደሆነ ልብ አድርግ! "ኢሥተምሠከ" اسْتَمْسَكَ ማለት "ጨበጠ" "ያዘ" ማለት ሲሆን ይህ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለው ጠንካራ የአሏህ ገመድ ምእመናንን በጸጋ ወንድማማቾች የሚያስተሳስር እና ከእሳት ጉድጓድ አፋፍም የሚያድን ስለሆነ "የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ" ተብለናል፦ 3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡ ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአሏህን ጸጋ አስታውሱ! በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፡፡ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ፡፡ وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا 3፥103 በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አሏህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል፡፡ وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለው ጠንካራ የአሏህ ገመድ አሏህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ኢሥላም ናት፦ 30፥30 ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአሏህን ፍጥረት ያችን አሏህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዟት፡፡ فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًۭا ۚ فِطْرَتَ ٱللَّهِ ٱلَّتِى فَطَرَ ٱلنَّاسَ عَلَيْهَا ۚ لَا تَبْدِيلَ لِخَلْقِ ٱللَّهِ ۚ ذَٰلِكَ ٱلدِّينُ ٱلْقَيِّمُ وَلَٰكِنَّ أَكْثَرَ ٱلنَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ "ያዙ" የሚለው ይሰመርበት! ማንም ተወላጅ የሚወለደው በአል-ፊጥራ በዲኑል ኢሥላም ላይ ሆኖ ነው፦ ኢማም ቡኻርይ መፅሐፍ 23, ሐዲስ 138 ከአቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተላለፈው ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፡- "ማንም ተወላጅ የሚወለደው በአል-ፊጥራ ላይ ሆኖ ነው። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ كُلُّ مَوْلُودٍ يُولَدُ عَلَى الْفِطْرَةِ، ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 46, ሐዲስ 38 አቢ ሙዓዊያህ እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ "ማንም የሚወለድ ሰው በአንደበቱ(የኩፍር ቃል) እስከሚል ድረስ በአል-ፊጥራህ ላይ ሆኖ እንጂ አይወለድም። عَنْ أَبِي مُعَاوِيَةَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ إِلاَّ عَلَى هَذِهِ الْمِلَّةِ حَتَّى يُبَيِّنَ عَنْهُ لِسَانُهُ ‏"‏ ‏. አምላካችን አሏህ በዚህ በተፈጥሮ ጥምቀት ስንፈጠር ያጠምቀናል፥ በማጥመቅም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? ማንም የለም፦ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ "ሲብጋህ" صِبْغَة የሚለው ቃል "ሶበገ" صَبَغَ ማለትም "ነከረ" "አጠመቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መንክር" "ጥምቀት" ማለት ነው፥ "ሶብግ" صَبْغማለት "መንከሪያ" "ማጥመቂያ" ማለት ሲሆን ይህም አሏህ ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣና፦ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» ሲል በራሳቸው ላይ የሚያስመሰክረው ምስክርነት ነው፥ እነርሱም፦ «ጌታችን ነህ መሰከርን» አሉ፦ 7፥172 ጌታህም ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣና፦ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» ሲል በራሳቸው ላይ ባስመሰከራቸው ጊዜ የኾነውን አስታውስ! «ጌታችን ነህ መሰከርን» አሉ፡፡ «በትንሣኤ ቀን ከዚህ ኪዳን ዘንጊዎች ነበርን" እንዳትሉ፡፡» وَإِذْ أَخَذَ رَبُّكَ مِن بَنِي آدَمَ مِن ظُهُورِهِمْ ذُرِّيَّتَهُمْ وَأَشْهَدَهُمْ عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ أَلَسْتُ بِرَبِّكُمْ ۖ قَالُوا بَلَىٰ ۛ شَهِدْنَا ۛ أَن تَقُولُوا يَوْمَ الْقِيَامَةِ إِنَّا كُنَّا عَنْ هَـٰذَا غَافِلِينَ ሰው በተፈጥሮው የአምልኮ ፍላጎት እና ዝንባሌ ያለው ፍጡር የሆነው በዚህ ምክንያት ነው፥ ሰው በፊጥራህ ጊዜ "ጌታችን ነህ መሰከርን" ማለታቸው በታኅታይ ሕሊና"subconscious" የተቀመጠ ሲሆን በትንሳኤ ቀን ይህ ውስጣችን ያለው ምሥጢር ይገለጻል፦ 100፥10 "በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ እንዴት እንደሚኾን፡፡ وَحُصِّلَ مَا فِي الصُّدُورِ
Show all...
"አሐዱ አምላክ" በሚል ትምህርት ተለቋል። “አሐዱ” ማለት “አንድ”one" ማለት ሲሆን "አሐዱ አምላክ" ማለት "አንድ አምላክ" ማለት ነው። ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/n_udDT19JKw?si=hcuRn6zz-EtfEOou ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!
Show all...
"እናመልካለን" የሚለው ይሰመርበት! የሚመለከውም ዐውዱ ላይ አብ ብቻ ነው። የእስክንድርያው ቄርሎስ ዮሐንስ 2፥22 በፈሠረው ተፍሢሩ ላይ፦ "ስለዚህም ሰው ሆኖ አምልኳል"therefore He worshippeth as man" በማለት እንቅጩን ፍርጥ አርጎ አምላኪ መሆኑን ተናግሯል። የሚያመልከው ልክ እንደ እኛ ሡጁድ በግባሩ በመደፋት ነው። ማቴዎስ 26፥39 ላይ "በፊቱ ወደቀ" የሚለውን ግዕዙ "ሰገደ በገጹ" ይለዋል፦ ማቴዎስ 26፥39 ወተአተተ ሕቀ እምኔሆሙ ወ-"ሰገደ በገጹ" ወጸለየ ወይቤ፦ “አቡየ፡ እመሰ ይትከሀል ይኅልፍ እምኔየ ዝንቱ ጽዋዕ፡ ወባሕቱ ፈቃደ ዚኣከ ይኩን፡ ወአኮ ፈቃደ ዚኣየ።” "ሰገደ" በግዕዝ አላልታችሁ "ገ" ፊደልን ስታነቡት በዐማርኛ "ሰገደ" አጥብቃችሁ "ገ" ፊደልን ስታነቡት ማለት ነው፥ አንድምታውም፦ "ግንባሩን ምድር አስነክቶ ሰገደ" ይለናል፦ የማቴዎስ ወንጌል 26፥39 አንድምታ "ከዚያ ጥቂት እልፍ ብሎ ግንባሩን ምድር አስነክቶ ሰገደ"። ግንባሩን ምድር አስነክቶ ከሰገደ አምላኪ እንጂ ተመላኪ መሆን የለበትም። በተመሳሳይ ማርቆስ 14፥35 እና ሉቃል 22፥41 ግዕዙን እና አንድምታውን ተመልከት! ከምድር ከሰገደ ሰጋጅ እንጂ ተሰጋጅ መሆን የለበትም። ርኩዕ በማድረግ ሸብረክ እና ብርክክ ብሎ ማጎንበሱ ለአንድ አምላክ የሚቀርብ መጎባደድ፣ ማሸርገድ፣ ማጎብደድ ነው፥ ይህ በውጥን የሚቀርብ አምልኮ ነው። "ተሥቢሕ" تَسْبِيح ማለት "ተስብሖት" ማለት ሲሆን የአምልኮ ክፍል ነው፥ "ስብሐት" ማለት "ምስጋና" "መዝሙር" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ከሐዋርያቱ ጋር ተሰብሖት አቅርቧል፦ ማቴዎስ 26፥30 ወሰቢሖሙ ወፅኡ ውስተ ደብረ ዘይት። ትርጉሙ "መዝሙርም ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ" ሲሆን ይህም ስብሐት አንድምታው፦ "አቡነ ዘበሰማያት" እንደሆነ ይናገራል፥ ኢየሱስ ከሐዋሪያቱ ጋር እንዲህ ሲል ዘምሯል፦ ዕብራውያን 2፥12 አየድዖሙ ስመከ ለአኀውየ ወበማእከለ ማኅበር እሴብሐከ። ትርጉም "ስምህን ለወንድሞቼ እነግራቸዋለሁ በማኅበርም መካከል በዜማ አመሰግንሃለሁ" ሲሆን "በዜማ አመሰግንሃለሁ" ለሚለው የገባው ቃል "እሴብሐከ" ነው፥ ተሥቢሕ አምልኮ ከሆነ እንግዲያውስ ከወንድሞቹ ከሐዋርያት ጋር "አባታችን ሆይ" የሚለውን ጸሎት ጸልየዋል፦ ማቴዎስ 6፥9 እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፦ "በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፥ ስምህ ይቀደስ"። አምላክ ኢየሱስን "ባሪያዬ" ካለው ኢየሱስ አምላክን "ጌታዬ" "አምላኬ" "አምላካችም" እያለ ከጸለየ፣ ከጦመ፣ ከፈራው፣ ከሰገደ ከዚህ በላይ አምልኮ የለም። መጾሙ፣ መጸለዩ፣ መለመኑ፣ አምላክን መፍራቱ፣ መስገዱ በፍጹም ሁለተንተናው አምላኩን እመለከው እንጂ ለማስመሰል ድራማ፣ ቲያትር፣ ተውኔት እየተወነ እና ቁማር እየቆመረ አልነበረም፥ አጠናብረው ለመሸወድ ከመሞከር ይልቅ እውነታውን መቀበል ያሻል። "መክረም እስከ መስከረም" በሚል አገሪኛ ብሒል ከሙግት ለማምለጥ ከሚደረግ ጊዜአዊ ሙግት ይልቅ የዘለቀ እና የላቀ ሙግት መሞገት ይሻላል፥ አዲስ ሙግት ሲመጣ ከማጥናት ይልቅ ሳትበሉ ማግሳታችሁ ሁሌ ይገርመኛል። ለማንኛውም ኢየሱስ አምላኪ ሲሆን ፈጣሪው ደግሞ ተመላኪ ነው። "መዕቡድ" مَعْبُود‎ ማለት "ተመላኪ" ማለት ሲሆን "ዓቢድ" عَابِد‎ ማለት ደግሞ "አምላኪ" ማለት ነው፥ በተመላኪ እና በአምላኪ መካከል ያለው ሥርዓት "ዒባዳህ" عِبَادَة‎ ነው። ለአሏህ አምልኮን የሚያቀርብ "ባሪያ" በቁርኣን "ዐብድ" عَبْد ይባላል፥ ዒሣ አሏህን በብቸኝነት ስለሚያመልክ "ዐብዱሏህ" عَبْدُ اللَّه ማለትም "የአሏህ አምላኪ" "የአሏህ ባሪያ" ተብሏል፦ 4፥172 አልመሢሕ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ ክርስቲያኖች ሆይ! ኢየሱስ የሚያመልከውን አንዱን አምላክ አሏህን እንድትመልኩ ጥሪያችን ነው። የኢየሱስ አምላክ አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
ኢየሱስ አምላኪ ነው! በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 4፥172 አልመሢሕ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ ኢየሱስ በምድር ሲመላለስ በጸሎት ብርቱ ስለነበር ሌሊቱን ሙሉ ወደ አምላክ ሲጸልይ ያድር ነበር፥ “ወደ” የሚለው መስተዋድድ ጸላዩን ኢየሱስ ከሚጸለይለት አምላክ ለይቶ ያስቀምጠዋል፦ ሉቃስ 6፥12 በነዚህም ወራት ይጸልይ ዘንድ ወደ ተራራ ወጣ፥ ሌሊቱንም ሁሉ “ወደ” አምላክ ሲጸልይ አደረ። Ἐγένετο δὲ ἐν ταῖς ἡμέραις ταύταις ἐξελθεῖν αὐτὸν εἰς τὸ ὄρος προσεύξασθαι, καὶ ἦν διανυκτερεύων ἐν τῇ προσευχῇ τοῦ Θεοῦ. ዮሐንስ 11፥22 "አሁንም ከአምላክ የምትለምነውን ሁሉ አምላክ እንዲሰጥህ አውቃለሁ" አለችው። καὶ νῦν οἶδα ὅτι ὅσα ἂν αἰτήσῃ τὸν Θεὸν δώσει σοι ὁ Θεός. "ከአምላክ የምትለምነውን ሁሉ አምላክ እንዲሰጥህ አውቃለሁ" የሚለው ይሰመርበት! ኢየሱስ እራሱ አንዱን አምላክ ጠይቆ መልስ የሚጠብቅ ለማኝ ነበር፥ ወደ አምላኩ የሚጸልየው ጸሎት በኢማን ነውና ሁልጊዜም ጸሎቱ ቅቡል ነው፦ ዮሐንስ 11፥41 ኢየሱስም ዓይኖቹን ወደ ላይ አንሥቶ እንዲህ አለ።፦ “አባት ሆይ፥ "ስለ ሰማኸኝ" አመሰግንሃለሁ። "ሁልጊዜም እንድትሰማኝ አወቅሁ። ὁ δὲ Ἰησοῦς ἦρεν τοὺς ὀφθαλμοὺς ἄνω καὶ εἶπεν Πάτερ, εὐχαριστῶ σοι ὅτι ἤκουσάς μου. ἐγὼ δὲ ᾔδειν ὅτι πάντοτέ μου ἀκούεις· "ስለ ሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ" "ሁልጊዜም እንድትሰማኝ አወቅሁ" የሚለው ኃይለ ቃል ጠይቆ መልስ የሚጠብቅ መሆኑን ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ ኢየሱስ አምላክን ይፈራ ስለነበር ጸሎቱ ምላሽ ያገኛል፦ ዕብራውያን 5፥7 አምላክን ስለ መፍራቱ ተሰማለት። καὶ εἰσακουσθεὶς ἀπὸ τῆς εὐλαβείας, "አምላክን መፍራት" ማለት "አምላክ በልቤ የማስበውን ያውቃል፣ በአንደበቴ የምናገረውን ይሰማል፣ በድርጊቱ የምሠራውን ያያል" ብለህ ክፉ ሥራ ከማሰብ፣ ከመናገር፣ ከመሥራት የምትቆጠበው እና መልካም ሥራ ከማሰብ፣ ከመናገር፣ ከመሥራት አለመቦዘን ነው። ኢየሱስ አምላክን በመፍራቱ ደስተኛ ነበር፦ ኢሳይያስ 11፥3 ያህዌን በመፍራት ደስታውን ያያል። וַהֲרִיחֹ֖ו בְּיִרְאַ֣ת יְהוָ֑ה "ይፈሩኛል" የሚለው "ያምልኩኛል" በሚል ተለዋዋጭ ቃል ከመጣ አምላክን መፍራት አምልኮ ነው። ኢሳይያስ 29፥13 እና ማቴዎስ 15፥9 ተመልከት! ጸሎት እና አምላክን መፍራት አምልኮ መሆኑን ካየን ዘንዳ በተጨማሪ ኢየሱስ ይጦም ነበር፦ ማቴዎስ 4፥2 አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም "ከጦመ በኋላ ተራበ። καὶ νηστεύσας ἡμέρας τεσσεράκοντα καὶ τεσσεράκοντα νύκτας ὕστερον ἐπείνασεν. ጦም ተቅዋእ ለመቀበል የሚደረግ መተናነስ ነው። ኢየሱስ አምላክን በማወቅ እና በመስገድ ያመልከው ነበር፦ ዮሐንስ 4፥22 እናንተስ ማታውቁትን ታመልካላችሁ፥ እኛ መዳን ከአይሁድ ነውና የምናውቀውን "እናመልካለን"። ὑμεῖς προσκυνεῖτε ὃ οὐκ οἴδατε, ἡμεῖς προσκυνοῦμεν ὃ οἴδαμεν, ὅτι ἡ σωτηρία ἐκ τῶν Ἰουδαίων ἐστίν· ዮሐንስ 4፥23 ነገር ግን በእውነት አምላኪዎች አብን በመንፈስ እና በእውነት "የሚያመልኩበት" ጊዜ ይመጣል፥ አሁንም ሆኖአል። "አብ ሊያመልኩት" እንደ እነዚህ ያሉትን ይፈልጋልና። ἀλλὰ ἔρχεται ὥρα καὶ νῦν ἐστιν, ὅτε οἱ ἀληθινοὶ προσκυνηταὶ προσκυνήσουσιν τῷ Πατρὶ ἐν πνεύματι καὶ ἀληθείᾳ· καὶ γὰρ ὁ Πατὴρ τοιούτους ζητεῖ τοὺς προσκυνοῦντας αὐτόν·
Show all...
ተዋሕዶ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 5፥72 እነሆ በአሏህ የሚያጋራው ሰው አሏህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፥ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ አንድ እናት ልጅ ስትወልድ "ምን ወለደች" ብለን ስንጠይቅ "ወንድ" ወይም "ሴት" ስንል ወንድ እና ሴት ምንነት ነው፥ "ፊሲስ" φύσις ማለት "ባሕርይ"nature" ማለት ሲሆን ወንድ ወይም ሴት ምንነት ስለሆነ ባሕርይ ነው፦ ሮሜ 1፥26 ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ። αἵ τε γὰρ θήλειαι αὐτῶν μετήλλαξαν τὴν φυσικὴν χρῆσιν εἰς τὴν παρὰ φύσιν, ሮሜ 1፥27 እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ። ὁμοίως τε καὶ οἱ ἄρσενες ἀφέντες τὴν φυσικὴν χρῆσιν τῆς θηλείας ἐξεκαύθησαν ἐν τῇ ὀρέξει αὐτῶν εἰς ἀλλήλους, እዚህ ጥቅስ ላይ "ባሕርይ" ለሚለው የገባው ቃል "ፊሲከን" φυσικὴν ሲሆን "ፊሲስ" φύσις ለሚለው ገላጭ ቅጽል ነው፥ ወንድነት እና ሴትነት ሁለት የተለያዩ ባሕርዮት ሲሆኑ በመገናዘብ፣ በተዐቅቦ፣ በመጠባበቅ አንድ ይሆናሉ፦ ማቴዎስ 19፥5 አለም፦ "ስለዚህ ሰው አባቱን እና እናቱን ይተዋል፥ ከሚስቱም ጋር ይተባበራል። ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ" የሚለውን ቃል አላነበባችሁምን? καὶ εἶπεν Ἕνεκα τούτου καταλείψει ἄνθρωπος τὸν πατέρα καὶ τὴν μητέρα καὶ κολληθήσεται τῇ γυναικὶ αὐτοῦ, καὶ ἔσονται οἱ δύο εἰς σάρκα μίαν; እዚህ አንቀጽ ላይ "አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "ሚአን" μίαν ሲሆን "ሚአ" μία ለሚለው ገላጭ ቅጽል ነው፥ ባል የወንድነት ባሕርይውን ሳይለቅ እንዲሁ ሚስት የሴትነት ባሕርይዋን ሳትለቅ ያለመቀላቀል እና ያለመደባለቅ አንድ ሥጋ በመሆን ይገናዘባሉ፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 7፥4 ሚስት በገዛ ሥጋዋ ላይ ሥልጣን የላትም፥ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ። እንዲሁም ደግሞ ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም፥ ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ። ἡ γυνὴ τοῦ ἰδίου σώματος οὐκ ἐξουσιάζει ἀλλὰ ὁ ἀνήρ· ὁμοίως δὲ καὶ ὁ ἀνὴρ τοῦ ἰδίου σώματος οὐκ ἐξουσιάζει ἀλλὰ ἡ γυνή. ግን ይህ ለአንድ ባሕርይ ትምህርት ምሳሌ መሆን አይችልም። ምክንያቱም ወንድ ሴት እንዲሁ ሴት ወንድ አይደለም፥ ሴት ወንድ አትሆንም እንዲሁ ወንድ ሴት አይሆንም። ሴት እና ወንድ አንድ ከሆኑ በኃላ ሁለት አካላት"person" እና ሁለት ባሕርያት እንጂ አንድ አካል አንድ ባሕርይ አይደሉም፥ ስለዚህ ባይብል ላይ ያለው "ሚአ ፊሲስ" μία φύσις ለተዋሕዶ እሳቤ ናሙና መሆን አይችልም። በ451 ድኅረ ልደት በኬልቄዶን የተወገዘው የእስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ የዲዮስቆርዮስ እሳቤ "ሚአ ፊሲስ" μία φύσις ሲባል ትርጉሙ "አንድ ባሕርይ" ማለት ነው፥ "ተዋሕዶ" የሚለው የግዕዝ ቃል "አንድ" ማለት እንጂ "ቱሳሔ" ማለትም "ቅልቅል" "ድብልቅ" "ውሕደት" ማለት አይደለም። ትስብእት እና መለኮት በመገናዘብ፣ በተዐቅቦ፣ በመጠባበቅ አንድ ባሕርይ የሚባለው ትምህርት "ተዋሕዶ" ይባላል። ፨ "ትስብእት" የሚለው የግዕዝ ቃል "ተሰብአ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሰውነት" ማለት ነው፥ የስም መደቡ ደግሞ "ሰብእ" ማለትም "ሰው" ነው። ፨ "መለኮት" የሚለው የግዕዝ ቃል "መለከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አምላክነት" ማለት ነው፥ የስም መደቡ ደግሞ "አምላክ" ነው። ተዋሕዶ አሳቡ "መለኮት በትስብእት ፍጡር፣ ሰው፣ አምላኪ ሆነ፥ ትስብእት በመለኮት ፈጣሪ፣ አምላክ፣ ተመላኪ ሆነ" የሚል ነው፦ ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 78 ቁጥር 31 "ዳግመኛ የጌታችን የክርስቶስ "ሥጋ አምላክ እንደሆነ" እንናገራለን"። ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 112 ቁጥር 31 "ፈጣሪ ከእኛ ባሕረይ ከተገኘች በእውነት ድንግል ከምትሆን ከማርያም ፍጡር ሆነ" ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 61 ቁጥር 23 "ሰው አምላክ ሆነ" ዮሐንስ 2፥14 አንድምታ፦ "አምላክ ሰው ሆነ፥ ሰው አምላክ ሆነ" እያሉ ርደቱን እና ዕርገቱን ለመንገር። "ሥጋ አምላክ እንደሆነ" "ፈጣሪ ፍጡር ሆነ" "አምላክ ሰው ሆነ" "ሰው አምላክ ሆነ" የተባሉት ቃላት ይሰመርበት! የመለኮት ገንዘብ ለትስብእት የትስብእት ገንዘብ ለመለኮት ስለሚነገር በሚል ፈሊጥ "መለኮት በትስብእት ፍጡር፣ ሰው፣ አምላኪ ነው፥ ትስብእት በመለኮት ፈጣሪ፣ አምላክ፣ ተመላኪ ነው" የሚል ይህን የዲዮስቆርዮስ ስብጥር ትምህርት የሚያራምዱ ጽብሓውያን ክርስቲያን"oriental Christian" የግብፅ፣ የአርመንያ፣ የሕንድ፣ የኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። ፨ ፈጣሪ ለፍጡር አምላክነቱን እና አምልኮቱን ካጋራ ትልቁ ሺርክ ነውና እራሱ አሻራኪ ይሆናል፣ ፨"ፈጣሪ ከፍጡር ጋር አንድ ነው እና አንድ ሆነ፥ ፍጡር ከፈጣሪ ጋር አንድ ነው እና አንድ ሆነ" ማለት ትልቁ ሺርክ ነው፣ ፨ "ፍጡር ከፈጣሪ ጋር ተስተካከ እና ተቆራኘ፥ ፈጣሪ ከፍጡር ጋር ጋር ተስተካከ እና ተቆራኘ" ማለት ትልቁ ሺርክ ነው። እውነት ነው! "ፈጣሪን ፍጡር ነው፥ ፍጡር ፈጣሪ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፥ መሢሑ ኢየሱስ ያስተማረው፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ» የሚል ነው። እነሆ! በአሏህ የሚያጋራ ሰው አሏህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፦ 5፥72 እነዚያ «አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አል መሢሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ አል መሢሕም አለ፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ፡፡» እነሆ! በአሏህ የሚያጋራ ሰው አሏህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡ لَقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ ۖ وَقَالَ الْمَسِيحُ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ ۖ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ ሙሽሪክ መኖሪያውም እሳት ናት፥ የአሏህ የአምልኮ ገንዘብ ለፍጡር ማጋራት በአሏህ ሐቅ ላይ የሚፈጸም ትልቁ ሺርክ ነውና ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡ አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
በአፈሪኛ ደርሥ ተለቋል። ፦ https://t.me/wahidcomafarega/15
Show all...
...
Show all...
"የሥላሴ ትምህርት መግቢያ" በሚል ትምህርት ተለቋል። "ሥላሴ" የሚለው ቃል “ሠለሰ” ከሚል ሥርወ ቃል የተገኘ ሲሆን "ሦስትነት"threeness" ማለት ነው፥ “ሥሉስ” ማለትም “ሥስት”three" ማለት ሲሆን ሥላሴ ደግሞ የሥሉስ ግሣዊ ስም ነው። "አምላክ በስም፣ በአካል፣ በግብር ሥስት ነው"Triune God" የሚል ትምህርት "ነገረ ሥላሴ"triadology" ይባላል። ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/jTGV0vTyhhE?si=q67nge-dteIAAUcr ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!
Show all...
ምንታዌ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 5፥17 እነዚያ አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሢሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ "ምንታዌ" ማለት "ሁለት" "ሁለትነት" ማለት ሲሆን በ451 ድኅረ ልደት በኬልቄዶን የጸደቀው "ዲያ ፊሲስ" δυο φύσις ትምህርት ነው፥ "ዲያ" δυο ማለት "ምንታዌ" "ሁለት" ማለት ሲሆን "ፊሲስ" φύσις ማለት ደግሞ "ባሕርይ"nature" ማለት ነው። በጥቅሉ "ዲያ ፊሲስ" δυο φύσις ማለት "ሁለት ባሕርይ" ማለት ሲሆን የኬልቄዶን ጉባኤ የአውጣኬን ትምህርት በማውገዝ፦ "ኢየሱስ ከሰው ጋር እና ከአብ ጋር "በባሕርይ የተስተካከለ"consubstantial" በአንድ አካል ያለ ውላጤ፣ ያለ ሚጠት፣ ያለ ትድምት፣ ያለ ቱሳሔ፣ ያለ ቡዓዴ ሁለት ባሕርይ አለው" የሚል እሳቤ ነበር። ፨ "ውላጤ" ማለት "መለወጥ" ማለት ሲሆን "ሥጋ ወደ መለኮት ተለወጠ" ወይም "መለኮት ወደ ሰውነት ተለወጠ" የሚል እሳቤ ነው። ፨ "ሚጠት" ማለት "መመለስ" ሲሆን "ሥጋ ከትንሳኤ ወይም ወደ ከእርገት በኃላ ወደ መለኮት ተመለሰ" የሚል እሳቤ ነው። ፨ "ቱሳሔ" ማለት "ቅልቅል" ማለት ሲሆን "ልክ እንደ ውኃ እና ማር ብርዝ አሊያም እንደ ወተት እና ቡና ማኪያቶ ጣዕም እና መልክ በመቀላቀል ተዋሐደ" የሚል እሳቤ ነው። ፨ "ትድምት" ማለት "መደመር" ወይም "መደረብ" ማለት ሲሆን "ልክ ልብስ በአካል እንደሚደረብ እና እንደሚለበስ መለኮት መለኮትን ሳይለቅ ሥጋ ጨመረ፣ ደረበ፣ ለበሰ" "ደመረ" የሚል እሳቤ ነው። ፨ "ኅድረድ" ማለት "ማደር" ማለት ማለት ሲሆን "ልክ ቤተመቅደስ አምላክ እንደሚያድር መለኮት ሥጋ ላይ አደረበት ወይም ልክ ውኃ በማድጋ፣ ሰይፍ በሰገባ፣ መጽሐፍ በተደጎሰ ማኅደር፣ ጽላት በታቦት እንደሚያድሩ መለኮት ሥጋ ላይ አደረበት የሚል እሳቤ ነው። ፨ "ቡዓዴ" ማለት "መለየት" ማለት ሲሆን "ልክ ብረት ብረትትነቱን ሳይለቅ ከእንጨት ጋር በብሎን ተለያይቶ እንደሚተሳሰር መለኮት ከሥጋ ጋር ተለያይቶ በአንድ አካል ተሳሰረ" የሚል እሳቤ ነው። ይህንን የሁለት ባሕርይ እሳቤ የሚያራምዱት ካቶሊክ፣ የምሥራቅ ኦርቶዶክ እና ፕሮቴስንታንት ናቸው፥ ይህ ሁሉ ውዝግብ ግን በባይብል ላይ የለም። ከዚያ ይልቅ አምላክ እና ሰው ሁለት ለየቅል ባሕርዮት ሲሆኑ በአንድ ማንነት"person" አይኖሩም፥ ባሕርይ አንድ ሳይሆን አካል"person" አንድ አይሆንም፦ ኢሳይያስ 31፥3 ግብጻውያን ሰዎች እንጂ አምላክ አይደሉም። וּמִצְרַ֤יִם אָדָם֙ וְֽלֹא־אֵ֔ל ሕዝቅኤል 28፥2 ነገር ግን ልብህን እንደ አምላክ ልብ ብታደርግም አንተ ሰው ነህ እንጂ አምላክ አይደለህም። וְאַתָּ֤ה אָדָם֙ וְֽלֹא־אֵ֔ל וַתִּתֵּ֥ן לִבְּךָ֖ כְּלֵ֥ב אֱלֹהִֽים׃ "አምላክ" መለኮታዊ ኑባሬ ከሆነ "ሰው" ሰዋዊ ኑባሬ ከሆነ ሰው እና አምላክ ሁለት ለየቅል ማንነት እና ምንነት ናቸው፦ ሆሴዕ 11፥9 እኔ አምላክ ነኝ እንጂ ሰው አይደለሁምና። כִּ֣י אֵ֤ל אָֽנֹכִי֙ וְלֹא־אִ֔ישׁ "እኔ" እያለ የሚናገር አንድ ነጠላ ማንነት በምንነቱ ሰውነት ስለሌለበት "እኔ አምላክ ነኝ እንጂ ሰው አይደለሁምና" በማለት እንቅጩን ፍርጥ አርጎ ይናገራል። አምላክ በማንነት አንድ ስለሆነ አንድ አምላክ አለ፥ ሰው ግን በማንነት ብዙ ስለሆነ ብዙ ሰዎች አሉ፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 8፥4 ከአንዱም በቀር ማንም አምላክ እንደሌለ እናውቃለን። καὶ ὅτι οὐδεὶς Θεὸς εἰ μὴ εἷς. 1 ጢሞቴዎስ 2፥5 አንድ አምላክ አለና፥ በአምላክ እና በሰዎች መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። εἷς γὰρ Θεός, εἷς καὶ μεσίτης Θεοῦ καὶ ἀνθρώπων, ἄνθρωπος Χριστὸς Ἰησοῦς, በአንድ አምላክ እና በሰዎች መካከል ያለው መካከለኛ ከአንዱ አምላክ እየሰማ የሚያስተላልፍ ሰው ነበር፦ የሐዋርያት ሥራ 2፥22 ከአምላክ ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ። ἄνδρα ἀποδεδειγμένον ἀπὸ τοῦ Θεοῦ εἰς ὑμᾶς. ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከአምላክ የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ። νῦν δὲ ζητεῖτέ με ἀποκτεῖναι, ἄνθρωπον ὃς τὴν ἀλήθειαν ὑμῖν λελάληκα, ἣν ἤκουσα παρὰ τοῦ Θεοῦ· እዚህ አንቀጽ ላይ ላኪ "አምላክ" ባለቤት ተላኪ "ሰው" ተሳቢ መሆኑ እና በባለቤት እና በተሳቢ መካከል "የሰማሁት" የሚል ተሻጋሪ ግሥ መሆኑ በራሱ አምላክ እና ሰው ሁለት የተለያዩ ማንነቶች መሆናቸውን ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ ከዚያም ባሻገር አምላክ በኑባሬ ከሰው በምንነት ስለሚለያይ አምላክ የተባለው ላኪ እና ሰው የተባለው ተላኪ ሁለት የተለያዩ ምንነቶች መሆናቸውን ፍንትው አርጎ ያሳያል። ስለዚህ መሢሑ ሰው፣ ነቢይ፣ መልእክተኛ ሆኖ ሳለ አምላክ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ፦ 5፥17 እነዚያ አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሢሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
እዚህም አንቀጽ ላይ "ሆነ" ለሚለው የግስ መደብ የተጠቀመት ቃል "ኤጌኔቶ" ἐγένετο ሲሆን "ሆነ" ያልሆነበትን ወደ መሆን ስለሆነ "ተለወጠ" የሚል እምነት አላቸው፦ ዘጸአት 4፥2 ጌታም፦ “ይህች በእጅህ ያለችው ምንድር ናት?” አለው። እርሱም፦ “በትር ናት፡” አለ። εἶπε δὲ αὐτῷ Κύριος· τί τοῦτό ἐστι τὸ ἐν τῇ χειρί σου; ὁ δὲ εἶπε· ῥάβδος. ዘጸአት 4፥3 “ወደ መሬት ጣላት፡” አለው፤ እርሱም በመሬት ጣላት፥ እባብም ሆነች፤ ሙሴም ከእርሷ ሸሸ። καὶ εἶπε· ρίψον αὐτὴν ἐπὶ τὴν γῆν. καὶ ἔρριψεν αὐτὴν ἐπὶ τὴν γῆν, καὶ ἐγένετο ὄφις· καὶ ἔφυγε Μωυσῆς ἀπ᾿ αὐτοῦ. "ካይ ኤግኔቶ ኦፊስ" καὶ ἐγένετο ὄφις·ማለት "እባብም ሆነች" ማለት ሲሆን "ሆነ" ማለት "ተለወጠ" በሚል ተለዋዋጭ ቃል መጥቷል፦ ዘጸአት 7፥15 እባብም ሆና "የተለወጠችውን" በትር በእጅህ ትወስዳለህ። καὶ τὴν ράβδον τὴν στραφεῖσαν εἰς ὄφιν λήψῃ ἐν τῇ χειρί σου. "የተለወጠችውን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! "ይህ ወደ ሥጋ የተለወጠው ቃል ወደ አምላክነት ከትንሳኤ በኃላ ወይም ከዕርገት ተመልሷል" የሚል ትምህርታቸው "ሚጠት" ይባላል፥ "ሚጠት" ማለት "መመለስ" ማለት ነው። "ቃል ሥጋ ሆነ" ማለት "ቃል ሥጋ ለበሰ" ማለት ቢሆን ኖሮ "በትር እባብ ሆነ" ማለት "በትር እባብ ለበሰ" ማለት ይሆን ነበር፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን "ቃል ሥጋ ሆነ" ማለት "ከጥንት ሲነገር የነበረው ቃል ሰው በመሆን ተፈጸመ" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ ለኢዩ፦ "ልጆችህ እስከ አራት ትውልድ ድረስ በእስራኤል ዙፋን ላይ ይቀመጣሉ" ተብሎ የተነገረው የአምላክ ቃል ጊዜው ሲደርስ ሆኗል፦ 2ኛ ነገሥት 15፥12 ለኢዩ፦ "ልጆችህ እስከ አራት ትውልድ ድረስ በእስራኤል ዙፋን ላይ ይቀመጣሉ" ተብሎ የተነገረው የጌታ ቃል ይህ ነበረ፥ እርሱም "ሆነ"። ὁ λόγος Κυρίου, ὃν ἐλάλησε πρὸς ᾿Ιοὺ λέγων· υἱοὶ τέταρτοι καθήσονταί σοι ἐπὶ θρόνου ᾿Ισραήλ· καὶ ἐγένετο οὕτως. በግሪክ ሰፕቱአጀንት ላይ "ካይ ኤጌኔቶ አውቶስ" καὶ ἐγένετο οὕτως ማለትም "እርሱም ሆነ" ተብሎ ተቀምጧል፥ "እርሱ" ተብሎ የተቀመጠው ተውላጠ ስም "የጌታ ቃል" የሚለውን ባለቤት ተክቶ የመጣ ነው። "ልጆችህ እስከ አራት ትውልድ ድረስ በእስራኤል ዙፋን ላይ ይቀመጣሉ" የሚለው የአምላክ ቃል ጊዜው ሲደርስ "ሆነ" እንደተባለው ሁሉ "የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ" ተብሎ የተነገረው ቃል ጊዜው ሲደርስ ሥጋ ማለትም ሰው "ሆነ" ማለት ነው፦ ሕዝቅኤል 12፥28 ስለዚህ በላቸው፦ አዶናይ ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ "የምናገረው ቃል ይፈጸማል" እንጂ ከቃሌ ሁሉ ደግሞ የሚዘገይ የለም፥ ይላል አዶናይ ያህዌህ። לָכֵ֞ן אֱמֹ֣ר אֲלֵיהֶ֗ם כֹּ֤ה אָמַר֙ אֲדֹנָ֣י יְהוִ֔ה לֹא־תִמָּשֵׁ֥ךְ עֹ֖וד כָּל־דְּבָרָ֑י אֲשֶׁ֨ר אֲדַבֵּ֤ר דָּבָר֙ וְיֵ֣עָשֶׂ֔ה נְאֻ֖ם אֲדֹנָ֥י יְהוִֽה׃ ס እዚህ አንቀጽ ላይ "ቃል" ለሚለው የገባው ቃል "ደበር" דָבָר ሲሆን ግሪክ ሰፕቱአጀንት ላይ "ሎጎስ" λόγος ይለዋል። ይህም "የምናገረው ቃል" ስለሚል የሚናገረው ቃል ፍጻሜውን በማግኘት ሥጋ ሆነ፥ "ቃል ሥጋ ሆነ" ማለት ምን ማለት እንደሆነ በዚህ መልክ እና ልክ ተረድተነዋል። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...