en
Feedback
Live your life ሕይወትህን ኑራት

Live your life ሕይወትህን ኑራት

Open in Telegram

የነፃነት መድረክ ለማስታወስ ያህል ሁላችንም በምክንያት ነው የተፈጠርነው:: ምክንያቱን መርምሮ ማወቅ እና የኛ ድርሻ ነው:: ሕይወትን እስከ ጥግ ኑራት @livurlif @livurlif @livurlif

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Live your life ሕይወትህን ኑራት

Channel Live your life ሕይወትህን ኑራት (@livurlif) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 11 238 subscribers, ranking 3 071 in the Motivation & Quotes category and 2 532 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 238 subscribers.

According to the latest data from 03 December, 2024, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 0 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የነፃነት መድረክ ለማስታወስ ያህል ሁላችንም በምክንያት ነው የተፈጠርነው:: ምክንያቱን መርምሮ ማወቅ እና የኛ ድርሻ ነው:: ሕይወትን እስከ ጥግ ኑራት @livurlif @livurlif @livurlif

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 December, 2024), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Motivation & Quotes category.

11 238
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
መጠበቅ በጣም ከባድ ነገር ነው... ⭐️ባል እና ሚስት ልጅ ለመውለድ አስበው:: ፈጣሪያቸውን ለምነው ከብዙ ጥረት በኃላ ሚስት ማርገዝዋ ሲታወቅ ትልቅ ደስታን ይጭራል:: ግን ሁሉም ገና መጀመሩ ነው ረጅም ጉዞ አለ... 9 ወራትን መጠበቅ አለባቸው ሁለቱም:: ምንም ያህል ቢጓጉም ያልጊዜው ሆዷን ቀደው ልጁን ሊያወጡት አይሞክሩም አይችሉምም:: እና ለስኬት የሚያስፈልጉ እንደ ማንኛውም ባህሪዎች ወይም ልማዶች መጠበቅ አንዱ ነው:: ለዛም መጠበቅን መለማመድ በጣም አስፈላጊ ነው :: ቀላል ነገር አይደልም አንዳንዴ ራስን ማሞኘት ይመስላል ምንም በሌለበት ትልቅ ነገር ተመኝቶ እየሰሩ መጠበቅ:: መጠበቅ ወስጥ ያለው ትልቅ ነገር እምነት ነው:: እምነት ደሞ ማረጋገጥን አይፍልግም:: ካረጋገጥን በኃላ የሚመጣ እምነት እምነት አይባልም:: እምነት ያለምንም ማረጋገጫ ይሚቀድም ነገር ነው:: አምኖ ወጤት እስኪመጣ ጠብቆ ለመቆየት ደሞ ፅናት ይጠይቃል:: አንዳንዴ ምንም ተስፋ ሰጪ ነገር እናጣለን እና የእውነት ፅናታችን እና እምነታችን ሚፈተነው ያኔ ነው:: ምን ያህል ነው መጓዝ የምንችለው?  ምን ያህል ነው መጠበቅ ምንችለው? አንድ ተረት ልንገራቹ.... 👵ተረት ተረት👴 .......... ⭐️ ሁለት ዋሽንት🪈🪈 ሚጫወቱ ልጆች ነበሩ:: እና ሁለቱም በጣም የሚያምር እና መሳጭ ሙዚቃዎችን 🎶🎶🎵ይጫወቱ ነበር... ነገር ግን በተለየ መልኩ አንደኛው ልጅ ዋሽንቱን በሚጫወትበት ሰዓት ሁሌም 🌧🌧ዝናብ🌧🌧 ይዘንብ ነበር እና ሰዉ ይህ ነገር በጣም ስለሚያስደምመው እና ስለሚደንቀው እሱን ልጅ አብልጠው ይወዱት ነበር :: ግን ሁሌም ጥያቄ🤔 ይሆንባቸዋል እንዴት ተምሳሳይ ነገር እየተጫወቱ የሁለቱም ሙዚቃ እያማረ ለአንዱ እየዘነበ ለአንዱ አይዘንብም?  እና የሆነ እለት ዋሽንት ሲጫወት የሚዘንብለትን ልጅ ለመጠየቅ ወሰኑ የተለየ የሚያረገው ነገር ካለ ለማወቅ... እናም ጠየቁት... የልጁ መልስ በጣም አስገራሚ ነበር:: እኔኮ የተለየ ነገር ስለማረግ አይደለም የሚዘንበው: ዋሽንቴን የምጫወተው እስኪዘንብ ድረስ ስልሆነ ነው:: አላቸው ይባላል... በዚህ ልጅ እና በዛኛው ያለው ልዩነት በፅናት የመጠበቅ እና ያለመጠበቅ ነው:: 💡@livurlif 💡@livurlif 💡@livurlif ሼር ማረግ መብታቹ ነው 😊

ልዩነት ትልቁ ውበታችን ልዩነታችን ነው ባይ ነኝ:: በጣም ሰፊ ቃል ነው:: ጥቂቱን ብቻ እናንሳ እና አንተን የመሰለ አንድም ሰው እንደሌለ አስበህ ታቃለህ አንቺስ ውዴ..? አስባቹ ሊሆን ይችላል ግን ደግማቹ አስቡት እስኪ አንድም አንተን ወይም አንቺን የሚመስል የለም ልዩ ነህ /ልዩ ነሽ :: አሁን ላይ ትልቁ ወረርሽኝ ሌላውን ለመምሰል የሚደረግ ጥረት ነው :: መቼም የማይሳካ እያደር ህመም የሚፈጥር በሽታ:: ዓለም(አለምን እየወከሉ ያሉ የሆኑ ህዝቦች) ለብዙ ነገር ያስቀመጡት መስፈርት አለ:: እና አብዛኛው ሰው እሱን መስፈርት ለማሟላት እና ሙሉ ለመሆን እየሞኮረ ያለ ይመስለኛል:: እስኪ እኔ ማነኝ ምንድን ነውስ ሚያስደስተኝ ፍላጎቴስ ምንድነው...? እኔ እኔን የተቀበልኩ ቀን ነው ቀኑ ያበራልኝ መልኬን ቀለሜን ፅጉሬን አቋሜን ድምፄን መላው አካላቴን ማንነቴን... :: ሌላውን በመምሰል ወይም ለምን ይሄ እንድዛ አልሆነም ብሎ በማሰብ ብዙ ጊዜዬን የማባክን ሰው ነበርኩ:: ዓለሙም ባስቀመጠው መስፈርት ይሄ ይጎልሻል ይሄ ይቀራል ሊል ይሞክራል... Really ማነው ያለህ ቆይ ያልኩት ጊዜ ነው ነገር አለሙ የተቀየረው:: በራስ መተማመን ቀና ማለት መጣ አረ ልታይ ልታይ እራሱ ሳልል እቀራለው... አምላካችን የሰውን ልጅ አሳምረን ፈጠርነው ብሎ ሲያበቃ ማን ወንድ ነው ከሰው ላይ አቃቂር ሊያወጣ ሚነሳ...? ሁላችንም በልዩነታችን ውብ ነን:: ሌላን ለመምሰል በሞከርን ሰዓት ወረርሽኙ ያገኘናል::  ልዩ መሆን እንዴት ደስ ይላል በማንኛውም መንገድ በማንነት በሃሳብ በአመለካከት ባካሄድ በባህል በብሄር በዘር በሃይማኖት በቀለም...  በሁሉም ነገር 💡@livurlif 💡@livurlif 💡@livurlif ሼር የማረግ መብታቹ በህግ የተጠበቀ ነው 😊

ሰህተት አንድን ከዚህ በፊት አድርገነው የማናውቀውን(እንዴት እንደሚደረግ የማናውቀውን) ነገር ለማድረግ በምንሞክርበት ሰዓት የሚፈጠር እክል ሲሆን ጥፋት ደሞ አንድ ሰው እያወቀ ትክክል ያልሆነ ነገር ሲሰራ የሚፈጠር ክስተት ነው:: የሰው ልጅ ባህሪዎች ብዙ ናቸው::ተሳሳችነቱ እና አጥፊነቱ ከነሱ መሃል ናቸው:: ሁለቱም ትክክል ያለመሆንን ሁኔታ ሲያሳዩ የመጀመሪያው አብዛኛው ሰው ላይ የሚታይ ነገር አይደለም ምክንያቱም አዲስ ነገር ለመሞከርብዙ ሰው ስለሚፈራ አርፎ ጎመን በጤና ብሎ ካለማወቁ ጋር መቀመጥን ይመርጣል ወይም የማውቀው በቂዬ ነው ባይ ነው:: ሁለተኛው በብዛት በተደጋጋሚ ሰዎች ላይ የሚታይ ባህሪ ነው:: ራሳችንን እንፈትሽ እስኪ ሕይወታችን ላይ ትክክል እንዳልሆነ ውስጣችን እያወቀ (እየነገረን) ግን ማድረጋችንን የምንቀጥለው ምን ያህል ነገር አለ?? ራሳችንን ሳንዋሽ ከፈተሽን የምናረገ አብዛኛው ነገር እንደዛ እንደሆነ እንረዳለን:: ለምን ግን ያንን ነገር እኮ ማድረግ አንፈልግም በማረጋችንም ደስተኛ አይደለንም ካለፈ በኃላ ብዙ ጊዜ ራሳችንን ስንወቅስ እንገኛለን:: ታዲያ ለምንድነው የምናረገው?? ሕይወታችን ላይ የምናከናውነው ተግባራችን አብዛኛው የፈለግነው ሳይሆን ያመንበት ነው የሚሆነው:: እዚህጋ እንዴ እኔ እኮ ያኛው ነገር ትክክል እንዳልሆነ አምኛለሁ ልንል እንችላለን:: ነገር ግን ትክክል እንዳልሆንን አውቀናል እንጂ አላመንም:: ምንድነው ልዩነታቸው...? በኑሮአችን ከ75% በላይ የሚሆነው ተግባራችን የሚሆነው አስበን በምናረገው ሳይሆን ባመነበት እና ወስጣችን በሰረፀው (program) በተደርገው መልኩ ነው ይለናል ቤተሰብ ሳይንስ:: ማለት...? ሰፊ ነው ታሪኩ ከጀመርነው ማለቂያ የለውም ለናንተ ልተወው እና እንድትጎግሉት... አብዛኛው ተግባራችን አስበን በምናረገው ካልሆነ የሚወሰነው⭐️ ልብ ⭐️ ሊባል የሚገባ ነገር ነው ማለት ነው:: ያመንበትን ነገር ውስጣችን የሰረፀውን ራሳችንን ወደሁዋላ አርገን ልናጤነው ይገባል ማለት ነው :: ምን አይነት ሃሳቦች እምነቶች አመለካከቶች ናቸው ውስጣችን ያሉት...? ስለምናረገው ነገር ያለን ሃሳብ እምነት አመለካከት ላይ ይወስናል ድርጊታችን ወይም የሚመጣው ውጤት ወደ ውስጥ ጠልቆ ማየትን ይጠይቃል:: ቆም ብሎ ምንድነው እየተካሄደ ያለው🤔🤔 ራስን መፈተሽ🙇🙇‍♀... ዝም ብለን ራሳችንን እናጥናው ምን ያህሉ የምንፈልገው ነው ምን ያህሉ የማንፈልገው? በዛን ሰዓት ያለንን ስሜት አመለካከት እንቃኘው ራሳችንን jugde ሳናረግ ጥፋቶቻችንን መቃኘት ልማድ ይኑረን እና ቀስ🚶‍♀🚶‍♀🚶🚶 በቀስ ደሞ ትክክል እንዳልሆነ እና ምን ያህል አፀያፊ ተግባር እንደሆነ ለራስ መንገር በተደጋጋሚ... በተደጋጋሚ ... "እዚህ ጋር ወቀሳ ሳይሆን እንደ ምክር ቢጤ ብናረገው"........በመቀጠል እንዴት መቀየር እንደሚቻል መፍትሄ ወይም መፍቻ ቁልፎችን🔑🔑🗝🗝🔑🗝 ማስቀመጥ:: በሚቀጥለው ተመሳሳይ ነገር ሲፈፀም ትኩረት በመስጠት ነገሩን ረጋ ብሎ ማየት እና ከመክፈቻ ቁልፎቹ መሃል አንዱን🗝 በማንሳት ቀሎ የታየንን መክፈት:: ሙሉ በሙሉ በአንድ ሙከራ ከጥፋት መፃዳት የማይታሰብ ነው ነገር እንደሆነ ግልፅ ነው...ግን በሆነ መንገድ ጥፋቱን መቀነስ:: ይህን ሂደት እየደጋገምን በሁሉም ቁልፎች ሁሉንም ጉድለት ከፍተን ማረም እስክንችል ድረስ መቀጠል ከዛም አዲስ እምነቶች እና አመለካከቶችን መገንባት:: ባለፍነው መንገድ ተንተርሰን አዲሱ እምነት ሕይወት እስኪዘራ ድረስ በሁኔታዎች ሁሉ ለራስ እየደጋገሙ መንገር በመጨረሻም ሳናውቀው ራሳችንን ከጥፋት ርቀን ወይም የምንፈልገውን ነገር በመተግበር ላይ እናገኘዋለን:: ቀላል አይደለም .....................................ሒደት ነው ተስፋ ባለመቁረጥ የሚያረጉት የፅናት ጉዞ... እያንዳንዱ ለውጥ ይህንን ሒደት ያስተናግዳል በጣም ባጭሩ... በመሃል አቋርጠን አይሆንም ብንል አዎ አይሆንም ምክንያቱም አልጨረስነውማ:: አንድ ሰው መድረሻውን የሆነ ቦታ አርጎ መንገድ ጀምሮ ሲጓዝ ከርሞ ደክሞት ወይ በሆነ ምክንያት አቋርጦ ቢመለስ እዛ ቦታ መድረስ አይቻልም ማለት ይቻላል? ይህ ነው በአብዛኛው እየተፈጠረ ያለው እና መልካም ጉዞ ከፅናት ጋር ... ፅናት ጎረቤታቹን አይደለም 😊❤️ 💡@livurlif 💡@livurlif 💡@livurlif ሼር ማረግ መብታቹ ነው 😊

አንዳንድ ጊዜ ሁሉም አንድ ሆነው እኛ በምንለይበት ሰዓት የተሳሳት ነው እኛ እንደሆንን ይሰማናል:: ዞር ብለን ስናየው ደሞ የአላማችን ጥንካሬ እና ትልቅነት አስፈላጊነት ሁሉንም ነገር ሲሸፍን እናያለ
አንዳንድ ጊዜ ሁሉም አንድ ሆነው እኛ በምንለይበት ሰዓት የተሳሳት ነው እኛ እንደሆንን ይሰማናል:: ዞር ብለን ስናየው ደሞ የአላማችን ጥንካሬ እና ትልቅነት አስፈላጊነት ሁሉንም ነገር ሲሸፍን እናያለን:: አላማችን ብለን በያዝነው ጉዞ ላይ ተቃዋሚው ሲበዛ ይታያል:: እርግጠኛ መሆን ያለብህ ነገር አላማህ ከፈጣሪ ጋር የማያጋጭህ መሆኑን ብቻ ነው:: ሃሳብህ ከራስህ አልፎ ሌላውን ለመጥቀም ከሆነ በዓላማህ ፅና:: አንተ ብቻ ነህ ውስጥህ ያለውን የምታቀው እና ውጤቱም የሚታይህ:: ለምን ወይም እንዴት ማየት ተሳናቸው ብለህ ለማስረዳት አትሞክር:: ጉልበትህን መጨረስ ነው ትርፉ አንተ ካየከው ይበቃል:: የሚያስፈልገውም እሱ ነው ሁሉም ነገር ፈተና ነው:: አላማ ከፈጣሪ እስከሆነ ድረስ ምን ያህል ብቁ ነው ይህ ሰው ምን ያህልስ መሄድ ይችላል የእውነት ይፈልገዋል እየጠየቀ ያለውን የሚሉ እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ናቸው እየመጡ ያሉት በነዛ ተቃዋሚዎች ምክንያት:: አሁን ላይ ቢቃወሙህም ግን ወደመድረሻህ እያደረሱህ ነው በፅናት ከቀጠልክ:: አንድ አባባል አለ ሁሉንም ማስደሰት ከፈለክ መሪ ሳይሆን ice cream ሻጭ ሁን ይላል:: 😊አመሰግናለሁ መልካም ጊዜ ❤️ 💡 @livurlif 💡 @livurlif 💡 @livurlif

📍የተሻለ አለህ በአውሎ ንፋስ ውስጥ ብትሆን፣ ዶፍ ዝናብ ቢወርድብህ፣ ዋጋህ ያነሰበት፣ መኖርህ የማይቆጠርበት፣ አበርክቶትህ የማይታይበት፣ ስራህ የማያፈራበት፣ ማንነትህ የማይመረጥበት ስፍራ ብትኖር እንኳን ፈጣሪ አብሮህ ካለ ሁሌም የተሻለ ከፍ ያለ ነገር አለህ። 🔷ምንም እንኳን እምነታችን ቢጎድል፣ ክፋታችን ቢበዛ፣ ሃሳባችን ቢያንስ፣ ምግባራችን የወረደ፣ ስራችንም አሳዛኝ ቢሆንም ፈጣሪ ግን ጥሎ አይጥለንም።፣ ትቶ አይተወንም ሁሌም ይመለከተናልና መቼም ችላ አይለንም። የተውን ሰዎች ይኖራሉ፣ ያገለሉን፣ የተጠየፉን እንዲሁ እንደዋዛም የናቁን ሰዎች ይኖራሉ ዋናው ነገር ግን በፈጠረን አለመገፋታችን አለመረሳታችን ነው። ♦️የተሻለ አለህ! ከዛሬው የላቀ፣ ከትናንት የገዘፈ፣ ከአሁንህ ያየለና ከፍ ያለ ስፍራ ይኖርሃል። የማይቀየሩ የሚመስሉ ከባድ ሁኔታዎች ይቀየራሉ፤ ይወርዱ የማይመስሉ ሸክሞች፣ ይፈቱ ያልመሰሉ ችግሮች፣ ይስተካከሉ ያልመሰሉ ውጥንቅጦች ይወርዳሉ፣ ይፈታሉ፣ ይስተካከሉ። እምነትህ ቢፈተን ግራ አትጋባ ይልቅ ለተሻለ ክብር እንደታጨህ አስተውል፤ በፈተናህ ብዛት አትደናገር ይልቅ የድልህ ቀን ቅርብ እንደሆነ አስተውል። በጫናዎች ብዛት የማትሸበር፣ ለምድራዊ ፈተና የማትበገር፣ ከፈጣሪህ ውጪ እንዳልሆንክ አስተውል። 🔷አንዳንዴ ማሳለፍ እየቻልን አቅፈናቸው የምንቀጥላቸው ብዙ ኮተቶቻችን ጣእሙን ማየት እንዳንችል ሁሉ ነገራችንን ዘግተንባቸዋል። ለማማረር እንጂ ለማመስገን ስንፈናል ለማዘን እንጂ ለመደሰት ጉልበት አጠተናል። መቆየት በማይገባን ቦታ ላይ በመቆማችን ማሳለፍ የሚገባንን አላፊ ሃሳቦችን እንዳያልፋ መንገድ ዘግተንባቸዋል እሰኪ ነቅነቅ እንበል እናሳልፋቸው የሚመጡት ሁሉ እንደአመጣጣቸው እንሸኛቸው አኛም ከቆምንበት አስተሳሰብ ስናልፍ ሁሉም ጊዜያዊ መሆኑን እናውቃለን። ሁሉም ያልፍ የለ ትላንትናም አልፏል ዘሬም ታልፋለች ነገም ትቀጥላለች እኔም አንተም እናልፋለን ምክንያቱም ሁሉም ያልፋል።ሁሉን የፈጠረ፣ ሁሉን የያዘ፣ በሁሉ ውስጥ ያለው አምላክህ ባንተ ውስጥ ስለመኖሩ አትጠራጠር፤ ለተሻለው ስፍራ እንደሚያበቃህ እምነት ይኑርህ። 🔑ማሰብ ላይ በርታ፤ መስራት ላይ ጠንክር፣ አምላክህን ይዘህ ፈተናህን ተጋፈጥ፣ በፀሎትህ ፅና፣ ምስጋናህን ደጋግመህ አቅርብ፣ ካንተ በላይ የሚሰራብህ፣ ተአምር የሚያደርግብህ ፈጣሪህ አብሮህ እንደሆነ አስብ። ብቻህን የሆንክ ቢመስልህ እርሱ ከጎንህ አለ፤ የተገፋህ ቢመስልህ በእርሱ እቅፍ ውስጥ ነህ፤ የወደክ ቢመስልህ እርሱ ያነሳሃል፤ በሚገባህ ስፍራም በክብር ያቆምሃል። ውብ አሁን ❤️ @EthioHumanity @EthioHumanity@EthioHumanitybot

✨የውስጥህን ስሜት የምታቀው አንተ እና ፈጣሪህ ብቻ ናቹ አካባቢህ ላይ ያለው ሰው መረዳት ባለመቻሉ ብዙ አትዘንበት ከስንት አንድ በተመሳሳይ ሁኔታ ላይ ያለፈ ሰው ካገኘህ ልትረዳዱ ትችላላቹ እሱም ግ
✨የውስጥህን ስሜት የምታቀው አንተ እና ፈጣሪህ ብቻ ናቹ አካባቢህ ላይ ያለው ሰው መረዳት ባለመቻሉ ብዙ አትዘንበት ከስንት አንድ በተመሳሳይ ሁኔታ ላይ ያለፈ ሰው ካገኘህ ልትረዳዱ ትችላላቹ እሱም ግን ደረጃ አለው ⚡️ሁላችንም በተለያየ ሁኔታ ላይ ማለፋችን አንዳንችን ከአንዳችን እንድንማር የተደረገ የፈጣሪ ስራ ይመስለኛል:: 🔘 እኔ እንደተረዳሁት... እውነታውም ይመስለኛል... ✨ችግር ብለን በጠራነው ሁኔታ ውስጥ ማለፋችን እና ያለንበትን ሁኔታ ሚረዳ ሰው አለመኖሩም የፈጣሪ ስራ ይመስለኛል:: ⚡️ወደሱ ፊታችንን አዙረን መፍትሄያችንን የምፍትሄዎች ሁሉ ባለቤት ከሆነው ከሱ እንድንጠይቅ በዛውም ዝምድናችንን እንድናጠነክር ፈልጎ ሳይሆን አይቀርም:: ምን ትላላችሁ...? @livurlif @livurlif @livurlif

🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧 አንዳዴ በእምነት ፅንቶ እንደመቆየት ሚከብድ ነገር የለም ጭንቅላት ሚሰብከውን አሉታዊ ስብከት አለማዳምጥ እና ወድፊት መጓዝ....😑 🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳 ምንም እንኳን ነገሮች ቢከብዱ ብታጣ እጅህ ባዶ ቢሆንም ወደ ህልሜ እየትቃረብኩ ነው ብሎ ማመን? Wooow በጣም ትልቅ ፅናትን ይጠይቃል። 🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳🕳 ግን የሚገርመው ወሳኙ እና አስፈላጊው እምነት ነገሮች አልጋ ባልጋ በሆኑበት ጊዜ ያለን ሳይሆን ጭንቅላታችን ህልማችን ሊሳካ የማይችልበትን የሚታይ የሆኑ በጣም ብዙ ምክኒያቶች በሚያሳየን ሰአት ይቻላል ብለን የማይታዩትን ምክንያቶች በማየት ትንሿን ብርሃን አይተን በኣላማችን መፅናት ስንችል ነው ከምንፈልገው እና ከሚገባን ስኬት የምንደርሰው። @livurlif @livurlif @livurlif

📍ወዳጄ ሆይ ሥር የሰደዱ ዛፎች ነፋስን ይቋቋማሉ ፣ ወደ ታች የጠለቁ መሠረቶች ብዙ ፎቅ ይሸከማሉ ። ሰውም በሳል ሲሆን በፈተና ይጸናል ፣ ፈተናና ነፋስ ያልፋሉና ። ነፋሱ ዘንበል ቢያደርግህም እንዲሰብርህ መፍቀድ የለብህም ። ብዙ ጫናዎችን ለመሸከም እውቀትና ማስተዋልን ገንዘብ አድርግ ። አንተም እንደዛፉ ስር ስደድ ጠንካራነት እውቀት አለው ፣ በጥበብ ይናገራል ፤ ተግባር አለው ። ጠንካራነት ስሜት ሳይሆን ተግባር ፣ ፉከራ ሳይሆን ድርጊት ነው ። ጠንካራነት ሞራልም ምግባርም ነው። 📍ወዳጄ ሆይ ፊት የልብ አደባባይነውና ሁሉን ቅሬታህን ፊትህ ላይ አታስነብብ፡፡ ጠላቶችህ ፊትህን እንጂ ልብህን እንዲያዩ አትፍቀድ፡፡ ለስድባቸው ስድብን አትመልስ ጆሮ ሰጥቼ ሰምቻችኀለሁ ማለት ነውና፡፡ ለአሳማሚዎችህ በቸኛው ማለፊያ ታምሞ አለመጠበቅ ነው ። ታመህ ካልጠበቀቻው ፣ ጆሮ ሰትጠህ ዝቅ ካላልክላቸው የሚያሳምምህ የለምና፡፡ ከራስህ ጋር ሳትመክር ከሰው ጋር አትመካከር፡፡ ለአንድ ሀሳብ የሶስት ቀን እድሜ ስጠው፡፡ ባዕድ ባለበት ስለቤትህ አታውራ፡፡  ለግቢህ አጥር ፣ለቤትህ በር፣ለህይወትህ ሚስጥር ይኑርህ፡፡ የተሻልክ ሳይሆን የበለጥክ ሁን፡፡ 📍ወዳጄ ሆይ መሬትህ በሚሸከመው መጠን ቤትህን ሥራ ፣ ወዳጅህ በሚችለው መጠን ምሥጢር ንገረው ፣ ተማሪህ ባደገበት መጠን መግበው ። የሌላው የሆነችውን ሴት ላንተ አትመኝ ። ያንን ጥላ ስትመጣ አንተን ጥላህ መሄድ እንደምትችል እያስተማርሃት ነው ። አንቺም የሌላውን ባለትዳር አትመኚ ። 📍ወዳጄ ሆይ ብትታመም በአገርህ ትታመማለህ ። አገርህ የታመመች ከሆነች ግን ዓለም ዝግ ይሆንብሃል ። ተሰደህም ለመከበር አገር ያስፈልግሃል ። ከሰላም የበለጠ ሀብት ፣ ከማስተዋል የበለጠ ሥልጣኔ ፣ ከፍቅር የበለጠ ደስታ የለም ። ያለ ፈጣሪ እየተስፋፉ ያሉ ሰዎች እየጠበቡ ነው ። ልብስ ጸድቶ ልብ ከቆሸሸ የመንፈስ ነጻነት ገና አልመጣም ። የድሮ ሰው ልቡ ንጹሕ ፣ ልብሱ አዳፋ ነበር ። የዛሬ ልጅ ልብሱ ንጹሕ ፣ ልቡ ሸርታታ ነው 📍ወዳጄ ሆይ የሰብዊነት ሥራ ለሰው ሁሉ የሚደረግ የደግነት ስራ ነው፣ ደግ ለመሆን ጥግ አትያዝ ። ከሥርህ ያለው አንተ የማትችለውን የሚችልልህ ነውና አክብረው ። ቆጥረህ ከሰጠህ ስጦታህ ይረክሳል ። ደብቀህ ከሰጠህ ስጦታህ ሲወራ ይኖራል ። ከፍ ስትል ልታይ ካልክ ሁሉም ሰው ስትወድቅ ያይሃል ። በከፈትክለት መጠን ጠላት ይገባል ። ሰይጣን አስገድዶ ሳይሆን አዘናግቶ የሚገድል ጠላት ነው ። 💡እናም ወዳጄ የታወከ ሌሊት ሲገጥምህ በሰላም ስላደርክባቸው ሌሊቶች አለማመስገንህን አስብ ። ቀኑ መብትህ ሳይሆን ስጦታህ ነውና አመስግንበት ። እሰይ ነጋ ማለት ሲገባህ ደሞ ነጋ አትበል ።ሲያነጋልህ ምንም ክፈያ ላላስከፈለህ ጌታ የማለዳ ምስጋና ለማቅረብ አትዘግይ ። ወጥቶ የመግባት ዋጋው ትልቅ ነውና የምሽት ጸሎትህንም አታስታጉል ። እያጣጣርክ ስለ ጤና ከመጸለይ በጤናህ ፈጣሪህን አመስግን ። ውብ ጊዜ❤️ @Ethiohumanity @Ethiohumanity@EthiohumanityBot