en
Feedback
Abu Ahilam Eliyas Nassir

Abu Ahilam Eliyas Nassir

Open in Telegram

በቴሌግራም!!! Abu Ahilam Eliyas Nassir

Show more
2 523
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
record.ogg8.71 KB

107.mp32.35 KB

ወደ ኡማ ግሩፕ።👇👇 https://ummalife.com/umma1697737094

«የእኔን እና የቅን ምትኮቼን ሱና አደራ! በመንጋጋ ጥርሶችችሁ አጥብቃችሁ ያዙ! አዳዲስ ፈጠራዎችን ተጠንቀቁ (ተከልከሉ)፣ በዲን ውስጥ የተጨመረ ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው» ኢማሙ አህመድ ዘግበውታል።

መውሊድ /

ምንድነው የሚለው?

ዐብደላህ ቢን መስዑድ ረዲየላሁ ዐንሁማ ኩፋ መስጂድ ውስጥ ተሰብስበው ዚክርን በቁጥር ገድበው ጠጠሮችን የሚጠቀሙ ሰዎችን በተመለከቱ ግዜ፦"ምናልባት እናንተ ከመሐመድ ሃይማኖት የተሻለና የተመራ ሃይማኖ
ዐብደላህ ቢን መስዑድ ረዲየላሁ ዐንሁማ ኩፋ መስጂድ ውስጥ ተሰብስበው ዚክርን በቁጥር ገድበው ጠጠሮችን የሚጠቀሙ ሰዎችን በተመለከቱ ግዜ፦"ምናልባት እናንተ ከመሐመድ ሃይማኖት የተሻለና የተመራ ሃይማኖትን እየተከተላችሁ ነው! ወይም የጥመት በር በመክፈት ላይ ናችሁ።» ሲሏቸው፦ ‹‹በአላህ እንምላለን አቡ አብዱረህማን ሆይ! እኛ( በዚህ ድርጊታችን) የምንፈልገው በጎ ነገርን ብቻ ነው።›› አሉ። " እሳቸውም፦ "መልካምን የሚፈልግ ሰው ሁሉ መልካምን አይገጠምም።" ብለው አውግዘዋል። “ተክቢር” መቶ ጊዜ፣ “ሱብሃነሁ” መቶ ጊዜ ፣ ይህ የዚክር አደራረግ ከነቢዩ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ተፈፅሞ አልመጣምና። ይህ የኢብኑ መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ ቂሳ ዳረሚይ (204) የተዘገበ ሲሆን ዛሬ በሚንበር ቲቪ አዘጋጅነት ምርኩዝ 26 ዙር ብሎ ባዘጋጁት ፕሮግራም ሰለዋትን በቁጥሮች ገድበው እያንዳንዱ ሰው 200 ሰለዋት ማውረድ አለበት ብለው ሰለዋት ማስደረጋቸው ትክክል አለመሆኑን እና ቢድዓ መሆኑን የሚያሳይ ግልፅ ማስረጃ ነው። የተሳሳቱ ሙስሊሞችን ሁሉ አላህ እንዲመራ ሁሉን ቻይ የሆነውን አምላክ እንለምነዋለን!

“ንግግርህ ካስደነቀህ ዝም በል፣ ዝምታህ ካስደነቀህ ተናገር።”

ሽርክ ከወንጀሎች ሁሉ የከፋ መሆኑ ከዚህ አስከፊ ወንጀል መራቅ እንዳለብን ለወገናችን ይህንን ማስተማር እንዳለብን የተወሳበት ነው አንድ ደርስ ላይ ሊጠቅም ይችል ይሆናል በማለት ለጥፌዋለሁ አሏህ ይጠብቀን

የመካህ-የሐጅ ስጦታ 🔅ከሐጅ ሲመለሱ ለቤተሰብ ስጦታ ማምጣት ተወዳጅ እንደሆነ አል-ኢማሙን'ነወዊይ እና ሌሎችም የፊቅህ ሊቃውንት ገልጸዋል። ለዚህ እንደማስረጃ የሚቀርብ ሐዲሥም ዳረቁጥኒይ ኪታቡል-ሐጅ መጨረሻ ላይ ዘግበዋል። የሐዲሡ ሰነድ ደዒፍ ቢሆንም በመሰረቱ ስጦታ መሰጣጠት ውዴታን እንደሚጨምር በትክክለኛ ሐዲስ ስለተነገረና ስጦታ መስጠትም በመሰረቱ ተወዳጅ መሆኑ ላይ ሊቃውንት በመስማማታቸው በዚህ ይጠናከራል። 📚 ሱነን አድዳረቁጥኒይ ሐዲሥ ቁ: 2791፣ ፈታዋ አንነወዊይ ገጽ 156 ፈ ቁ:117። 🔅ለወላጆች፣ ለትዳር አጋር፣ ለልጆች ወዘተ ትንሽም ብትሆን የሚያስደስታቸውን ሀዲያህ ይዞ በመመለስ ውዴታና ክብርን መግለጽና ማደስ ይበረታታል። አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል:- 🔅وَتَزَوَّدُوا فَإِنَّ خَيْرَ الزَّادِ التَّقْوَىٰ ۚ وَاتَّقُونِ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ "ስንቅ ያዙ፤ ከስንቆች ሁሉ በላጩ አላህን መፍራት ነው፤ የአእምሮ/ የልብ ባለቤቶች ሆይ ፍሩኝ" ሱረቱል በቀራ /197 ✍Menqul

በሰራኸው ሾል አትመፃደቅ ሼይኽ ፈውዛን የሆነ ጊዜ ስለእራሳቸው የሂወት ታሪክ ቃለ መጠይቅ እየተደረገላቸው ሾለ ኩቱቦቻቸው ተጠይቀው የመለሱትን ከመለሱ በሗላ ጠያቂው:  ተኪታቦዎ በጣም ጠቃሚ የምትሉትን ኪታብ ብጠቅሱልን? ይለዎታል እርሳቼውም በመቆጣት ስራዬን እንዳመሰግን ነው የምትፈልገው? በማለት ቆጣ ብለው ሲመልሱለት ጠያቂውም በመደንገጥ ወደሌላ ጥያቄ አለፈ __ ልብ በል ሼይኽ ፈውዛ ኪታባቸው እጅግ ተሰራጭቶ ያሉ በጣም ወሳኝና ጠቃሚ ኩቱቦች አሏቸው ቢሆንም ግን እሄን እሄን ኪታብ አንብቡት በጣም ጠቃሚ ነው በማለት አል ዘረዘሩም ይልቁንም ስራዬን እንዳመሰግን ትፈልጋለህን በማት ጠያቂውን ተቆጡት ዛሬ የኛዎቹ ከጎግልና ከመክተበተ ሻሚላ በመሰብሰብ በ ኮፒ ፔስት ያበደ ኪታብ ለመሆን ብዙ የሚጎድለው ትንሽ pdf ያዘጋጁና በመረጃ የተጫቀ + በመረጃ የታጀበ = አንብቡት እያሉ ይመፃደቁብናል። አሏሁል ሙስተዓን

የኔ ጀግና! ~ ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ ኢስላምን ያጠለሹ፣ ሙስሊሞችን በአጉል ኮተቶች ጠፍረው ያሰሩ የሱፊያ ኮተቶችን የበጣጠሰ አንበሳ ነው። በጀሊሉ፣ በወሃቡ ፈቃድ የተሃድሶ ንቅናቄው የቀብር አምልኮትን ግንድ ከምድረ ሰዑዲያ ገንድሶታል። በመላው የሙስሊሙ አለም ያለውን የበሰበሰ የሱፊያ ሸክም አነቃንቆታል። ኧረ ክፉኛ ወዝውዞታል። በዚህ የተነሳ ሱፊዮች ዘንድ እንደሱ የተጠላ ፍጡር የለም። የተፃፈ ኹጥባ ለማንበብ ሚንበር ላይ ወጥቶ የሚንገዳገደው ሁላ እየተነሳ "ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ ጃሂል ነው" ሲል የምንሰማው ያለ ምክንያት አይደለም። ይገባናል፣ የሚያስጮሃችሁ ህመማችሁ ነው። "አሶራኹ ዐላ ቀድሪል አለም" እንዲል ዐረብ። "ጩኸት በህመም ልክ ነው!" ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ እንዳንተ ሶደቃ ሲያባር እድሜውን አልፈጀም። ጋርዶ ጫት የሚቀረጥፍ ቦዘኔ አልነበረም። ሁሉን እንዳመጣጡ ያስተናገደ፣ ለቆመበት አላማ ቆርጦ የተነሳ፣ ከዚያም እስከ ደም ጠብታ የታገለ ቆራጥ ነበር፣ የጀግና ጀግና! የፅናት፣ የትጋት፣ የብቃት ተምሳሌት! ዛሬ ግን ይሄ ነው የሚባል የዒልም ቅሪት የሌለው፣ ኢስላምን የግል ጥቅም መሸመቻ ያደረገ፣ ከሆዱ አሻግሮ መመልከት የማይችል ቦዘኔ ሁላ እየተነሳ "እሱ'ኮ ጃሂል ነበር" ይላል። እርሱ ጃሂል ከነበረ አንተ ጅህልና እራሱ ነህ! • "ወሃብዮች ዑለማእ አያከብሩም" የሚሉ አስመሳዮች ሁላ በሸይኹ ላይ ምላሳቸውን ሲያሾሉ ማየት በስፋት የተለመደ ነው። ግማሹ "ተ'ክ'ፊ'ር ነው" ይላል። ግማሹ "የሁዲ ነው" ይላል። ግማሹ "የእንግሊዝ ቅጥረኛ ነበር" ይላል። ሌላም ሌላም ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ውንጀላዎች አሉ። እናንተ ናችሁ ስለ ዑለማእ ክብር የምታወሩት? በጀግኖቻችን ክብር ላይ እየተረማመዱ ከዚያ የነሱን የጥፋት ሰባኪዎች እንድናከብርላቸው ይፈልጋሉ። በሃገራችን በመውሊድ ሰበብ ስማቸው ገኖ ከሚታወቁ ቦታዎች ጋር ተቆራኝቶ ዝናቸው ከናኘ መሻይኾች ውስጥ #ብዙዎቹ የእውነት እንደሚባለው በዒልም የላቁ እንደነበሩ የሚያሳይ ማስረጃ ብትጠይቁ አስቂኝ ነገር ነው የምትሰሙት። "እስኪ ኪታባቸውን አሳዩን?" ብትሉ "የመውሊድ መንዙማ ፅፈዋል" "ማዲሕ ነበሩ። መድሕ አዘጋጅተዋል" ብለው የግጥም መድብል ይነግሯችኋል። ዒልም ማለት ግጥም መፃፍ ነው እነዚህ የዞረባቸው ዘንድ! በዚህ የግንዛቤ አቅምህ ነው ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብን በጅህልና የምትወርፈው?! አዎ መውሊድ ያገነናቸው ብዙ ስመ ገናናዎች አሉ። ከመውሊድ ጭፈራ ባለፈ ከነ ጭራሹ በቦታው ምንም አይነት የዒልም እንቅስቃሴ የሌለባቸው ብዙ ናቸው። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor

ኢናሊላሂወኢናኢለይሂራጂዑን!! መጨረሻችን የት ነው? ይህ ትውልድ ወዴት እያመራ ነው? ኳስ ዘመናዊ ጣዖት: ኳስ የዘመናችን ወጣት ልብ የተቆጣጠረ: ኳስ ወደ ዲን ቀርቤያለሁ የሚለው ሳይቀር የተፈተነበት በሽታ። እግር ኳስ መመልከት ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ጥፋትና መዓት ብቻ። ነው። ምክንያቱም ይበሳጫል: ይወራጫል: ይናደዳል: ቡድንተኝነት ይዘዋል: ሌላም ሌላም። ተጫዋቾቹ የራሳቸው የሆነ እብደት ያሳያሉ። ወይ በደስታ  ወይ በብስጭት። አስቡት አንዴ ቲሸርት ሲያወልቅ: አንዴ ሲወድቅ: አንዴ መሬት ሲመታ: አንዴ ተመልካች ሲሰድብ: መጮኽ: ጭፈራ: ያለ ቅጥ መደሰትና መማረር:መበሳጨት ያለበት የፈሳድ ሜዳ። ይህ ሁሉ ቆም ብሎ ላሰበውና ትንሽ የዲን እውቀት ለቀሰመ: ጥፋትነቱ አይሰወረውም። ግን ለምን  ጭፍንተኛ ሆንን? ለምን ፈረንጅ በተራገጠበት እኛ ወገንተኝነት ያዘን? ደጋፊዎችና ተመልካቾች ሳይቀሩ: ልብሳቸውን ይቀዳሉ። ቅጥ ያጣ ደስታ ውስጥ ይገባሉ። ቅጥ ያጣ ብስጭት ውስጥ ይገባሉ። ከቤተሰብ ይጣላሉ። እቤታቸው ምግብ አንበላም እስከማለት ይደረሳሉ። ይህ ሁሉ የኳስ በሽታ የያዛቸው ደዩሶች ሾል ነው። እኔ አንዳንድ ሰዎች ይገርሙኛል: ምንም ሳያፍሩ; ወደ ዲን ቀርበው; ሰለፊይ ነን እያሉ: ፂማቸው አሳድገው: ሱሪያቸው ቆርጠው: "እኔ የእገሌ ደጋፊ ነኝ" ይላል። አኡዙቢላህ። ኧረ ልክህን እወቅ?? በኳስ መለከፍ ማለት ሳይታወቅ በኩፍር መለከፍ ነው። ኳስ የዘመናችን ህዝብ በዘመናዊነት የሚያመልከው ጣዖት ነው"  አያፍሩም ደግሞ የተጫዋች ፎቶ ፕሮፋይል አድርገው ዘና ሲሉ። ኳስ ጊዜህ: አቅልህ: እድሜህ: እምሽክ አድርጎ ሚበላ የሰይጣን ጥሪ ነው። የሰው ልጅ አዕምሮ: ጭንቅላቱ ሁለት ተቃራኒ ነገር መያዝ አይችልም። ወይ ቁርአንና ሃዲስ ወይ ፊልም: ሙዚቃ ኳስ: ምርጫው በእጅህ ነው። ተውሒድ የተረዳ ፈፅሞ በእንዲህ አይነት ሰይጣናዊ ሾል አይገባም። እንዴ የተውሒድ ባለቤት አላህን የሚያስቆጣ ሾል ይሰራል? 90 ደቂቃ ነገ አላህ ሲጠይቅህ: ምን አረኩባት ልትለው ነው። መዓት ተጫዋቾች ሃፍዘሃል!! እስቲ ነብይህ ታውቃቸዋለህ? የስንት ሶሐቦች ስም ታውቃለህ? ታቢኢዎችስ: አኢማዎችስ? ይህ የምልበት የራሴ ተሞክሮ ስላለኝ ነው። (ወላሂ) አራቱ ኸሊፋዎች ማናቸው ብትለው- ኧረ ተወው አራቱም ስማቸው ጠቅሰህ ማናቸው እነዚህ ሶሐቦች ብትለው ማያውቅ: ግን እያንዳንዱ አለም ላይ በሰፊው የሚታወቁ ክለቦች ከነ ተጫዋቾቻቸው ያውቃል። የት እንደተሸጠ: ስንት እንደተሸጠ: እንዴት እንደተሸጠ ብቻ ስለእያንዳንዱ ተጫዋች ያውቃል። ግን ሐዋሪያቶች የማያውቁ መዓት የቁም ሙቶች ሞልተዋል: በኳስ ተበልተዋል። ኳስ የሰው ነብስ ያጠፋል: ወንድም ለወንድም ያቀያይማል: እልህ ያሲዛል ብቻ የሙስሊሙ ባህሪ ጭራሽ የራቀ ነው። ሙስሊሞች ከዚህ የሸይጧን በሽታ መራቅ አለባቸው። አሁን ከወንዶች አልፎ ሴት እህቶቻችንም እዚህ ቆሻሻ ውስጥ ተንቦራጭቀዋል።  የዘንድሮው ደግሞ በጣም ሚያሳዝነው: ሚያስለቅሰው የወንጀላችን ጥግ: የአላህ ቤት መስጅድ ውስጥ ኳስ ሲታይ።  TG https://t.me/iliyasNassir/4792 Facebook ላይ የሸይኽ አብዱራዛቅ አል በድር ሃፊዘሁላህ አጭር ምክርም አለበት። ገብታቹ ተመለከቱ። https://fb.watch/h_pddyi4hN/ ይህ ነገር ብዙዎች ቢያስደነግጥም ሃታ!! ኳስ አፍቃሪዎችም ቢደነግጡም: ግን ይህ ነገር የመጣው በኔ ምክንያት ነው ብለው አለመደንገጣቸው ነው። ዝሙት በአንድ ቀን አይፈፀምም: ቀናት: ወራት ሊያስቆጥር ይችላል። ኳስ ወደ ሙስሊሙ ወጣት ልብ ሲገባ ቀስ-በቀስ ነው። ዘንድሮ መስጅድ ውስጥ ሲታይ ብዙዎች ደነገጡ። ቀጣይ ከተደገመ: ይለመዳል።  መደገንጥ ብቻ መፍትሔ አይደለም: በቃ በኔ ሰበብ ነው ይህ ፈሳድ የመጣው ብለህ ኳሱን ተወው። "አንተም-ቤተሰብህም-የዲንህም ክብር አስጠብቅ- "ኳስ እኮ ሙስሊሞችም ያያሉ" ሲባል ወላሂ ያሳፍራል። ምንም ካልተሰማህ: አንተ የገዛ አዕምሮህ ለሰይጣን አስረክበሃል ማለት ነው። በነገራችን ላይ ኳስ መመልከት የልብ በሽታና የተያያዙ ሌላም እስከሞት የሚያስከትል በሽታ ያመጣል። "cardiovascular mortality and proarrhythmic effect" ይጨምራል ይላሉ።(ዶክተሮች) በመጨረሻም ለሌላ ባታስብ ለነፍሲያህ እዘንላት።

👉 ስሜታዊ ስትሆን እንዲህ ንግግርህ እርስ በእርሱ ይጣረሳል 🔹ዳእዋን በትህትና በእዝነት እናድርግ በስድብና በማብጠልጠል ማድረግ የለብንም ይሉና 🔹ደጃል ፣ ከዛብ ፣ ገሻሽ ፣ ሸይጣን ፣ ጠብደል … እያሉ ይሳደባሉ 🔹ሸይጣን ብለን እስካሁን ድረስ ለአህባሽ እንኳን አላልንም ይሉና 🔹 መርቀን ሲሉ ደግሞ ሸይጣን ብለው ሊያውም የሱና ወንድማቸውን ሙልጭ አድርገው ይሳደባሉ 🔹ለድሮ ሙብተዲኦች የተሰጠውን ረድ አሁን ላይ አምጥቶ መጠቀሙ ይከብዳል ይሉና 🔹 የድሮዎቹን ሙብተዲአ ያስባለው ነገር የዛሬዎችንም ሙብተዲእ ያስብላል 👉 ለሀቅ የምትወግንና ከሂዝቢያ አመለካከት የፀዳህ ከሆንክ ይህን ግልፅ ተናቁድ አውግዝ ዝም ብለህ በስሜት አትነዳ منقول (አኡዙቢላህ) ወላሂ በጣም ነው ሚያሳዝነው-ሚያስደነግጠውም

ዘመነኛ የልመና ስልት...!!? በርግጥ የእናንተ አረዳድ ጥሩ ቢሆን ኑሮ ይህ ጉዳይ መልካም ኸይር ስራ ነበርና ምንም የምለው ነገር አልነበረኝም። ነገር ግን እናንተ የዚህን መሰል መልካም ስራ የሚሰሩ
ዘመነኛ የልመና ስልት...!!? በርግጥ የእናንተ አረዳድ ጥሩ ቢሆን ኑሮ ይህ ጉዳይ መልካም ኸይር ሾል ነበርና ምንም የምለው ነገር አልነበረኝም። ነገር ግን እናንተ የዚህን መሰል መልካም ሾል የሚሰሩ ወንድሞቻችሁ ላይ የምትዋሹት የምትቀጥፉት ቅጥፈትና አይን ያወጣ በደል ስመለከት እናንተም ልመናውን በረቀቀ መንገድ ከማፅደቅ በዘለለ የፈጠራችሁት ለውጥ እንደሌለና ከልመና እንዳልተቆጠባችሁ ለመጠቆም እወዳለሁ። በበኩሌ መክተባ መስራታችሁን እደግፋለሁ ነገር ግን አንድ አይነት ሾል እየሰራን እናንተ ስትሰሩት ቅዱስ እኛ ስንሰራው እርኩስ የሚሆነው ነገር ምን እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም። “አንለምንም ግን ከእለታችን ፍጆታ ቀንሰን ኢሄን ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው እስቱድኦችንን  ለማቋቋም.. ሁላችንም ጥረት እናድርግ” ምን ማለት ነው በአሏህ⁉️ ➤የኛ ሀሳብስ ከዚህ የተለዬ ነበርን⁉️ ጀምዕያን በውስጥ አዋቂነት አፀደቃችኋትኮ Mathes መምህራችን በውስጥ ታዋቂነት አንድ አለኝ ይለን ነበር‼️ ለነገሩ ሒሳብ ላይ አክቲቭ ናችሁ። “እስኪ ሐቅን እንመስክር ምን ማለት ነው እኛስ ከዚህ ውጭ ምን አልን በአሏህ˝!? የአረብ ሀገር ዘሙየወች እያላችሁ በእህቶቻችሁ ክብር ላይ የምትረማመዱ እዝነት አልባ አረመኔ ጨካኞች በውስጥ ለውስጥ ግን ወላሒ ቢላሒ ተሏህ የአረብ ሀገር እህቶችን በተለያዬ ነገር የምታምታቷቸው እናንተ ናችሁ። ዘሙየወች ብላችሁ የምትሰድቧቸውን የዋሆች አግብታችሁ ነው ህይወታችሁን እየቀየራችሁ ያላችሁት እናውቃለን። ታዲያ ስድቡ ለምን !? ለልመናውም ይሔው ካለን ቀንሰን እናቋቁም እያላችሁ ነው። ልዩነታችን ምንድን ነው በአሏህ እስኪ በተረጋጋ መንፈስ እንነጋገር!? http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi

ሸይኽ ሙቅቢል አሏህ ይዘንላቸው እንድህ አሉ፦ "ያ ከኢኽዋኖች ጋር የሆነ ሰው አርባ ፊት ሊኖረው (የግድ) የማይቀር ነው።" አል ቡርካን {40}

እንዳንታለል/እንዳንሸወድ ልንቀራ ልንማር ይገባል። ሁሌም አፋችንን ከፍተን መስማትና ማድመጥ ብቻ የለብንም። አይንና ልቦናችንን ገልጠን መቀደምቶች አረዳድ የተፃፉ (የተሸረሁ) ኪታቦች አንብበን ልንረዳ ይገባል።

photo content

عَنْ ابْنِ عَبَّاسٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ: "إنَّ اللَّهَ تَجَاوَزَ لِي عَنْ أُمَّتِي الْخَطَأَ وَالنِّسْيَانَ وَمَا اسْتُكْرِهُوا عَلَيْهِ" . حَدِيثٌ حَسَنٌ، رَوَاهُ ابْنُ مَاجَهْ